uz
Feedback
Halal Fkr

Halal Fkr

Kanalga Telegram’da o‘tish

Elegant. Faithful. Halal. Tiktok: http://tiktok.com/@halal_discuss

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Halal Fkr analitikasi

Halal Fkr (@halalfkr) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 374 obunachidan iborat bo'lib, Din & MaĘźnaviyat toifasida 6 625-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 529-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 374 obunachiga ega bo‘ldi.

26 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -41 ga, so‘nggi 24 soatda esa -4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 20.77% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.44% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 779 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 129 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 51 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“Elegant. Faithful. Halal. Tiktok: http://tiktok.com/@halal_discuss”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 27 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

13 374
Obunachilar
-424 soatlar
-147 kunlar
-4130 kunlar
Postlar arxiv
Halal Fkr
13 374
ዓይንም የአለቃውን ትእዛዝ ተቀብሎ አፈጠጠ። ነገር ግን አቅራቢያዋ በደረሰች ቁጥር የለበሰችው ሜካፕ እየተገለጠ ይመጣና፣ ሜካፑ ተንሳፎ ከስር የሚቀረውን እውነተኛ ማንነቷን ሲያይ ዓይኔ ይጨነቃል። "አሁን ምን ብዬ ነው ለአለቃዬ የምነግረው?" ብሎ ያስባል፣ ያሰላስላል። በመጨረሻም፦ "ይቅርታ አለቃ… የቅድሟ እቃ እንደጠበቅናት አይደለችም (ፌክ ነች)፤ከላይ በባዕድ ነገር ተሸፋፍና አታላናለች። ግድ የለም ሌላ እንሞክራለን" ብሎ ሪፖርት ይልካል። አለቃ ልብም በዓይን መታለል ተናዶ፣ የፍለጋ ስራው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን ትእዛዝ ሳይሆን ጠንካራ ግሳጼ ያስተላልፋል። ዓይን አሁንም የአለቃውን ትእዛዝ በመቀበል መነፅሩን «ገጭ» አድርጎ ወደ ስምሪቱ ተመልሷል። ይሁን እንጂ በተደጋጋሚ ቢሞክርም ውጤቱ ያው ነው። ተስፋ ቆርጦ ወደ ሌላ ስራ መለስ ካለ ከደቂቃዎች በኋላ ቀና ሲል ግን… ያየውን ማመን አቅቶት ፈዘዘ፣ ደነዘዘ፣ ቀረዘዘ! ለማጣራት ያደረገው የላቦራቶሪ ምርመራ ውጤት «75% Original» በመሆኑ ተደስቶ ለአለቃው የ«እንኳን ደስ አለዎት» መልእክት አቀበለ። … ግን ምን ያደርጋል! ያቺ ቆንጆ የልቤን ጥሪ ሳታስተውል እርሷ በሌላ መስመር አልፋ ሄደች። ምስኪኑ ልቤ… የሚፈልገውን በማጣቱ የተፈጠረው ጉድለት ወደ ዘላቂ ደስታ ሊቀየር አይችልም። ምክንያቱም በየመንገዱ የሚያገኛቸውን 100% ኦሪጅናል ቆንጆዎች ሁሉ የራሱ ማድረግ አይችልምና! ታድያ ከዚህ ሁሉ «ጥናትና ምርምር» ምስኪኑ ልቤ የሚተርፈው ዓይን አንስቶ የላከለት «ፎቶዎች» ብቻ ናቸው። እነዚያን ምስሎች እያጠነጠነ… "ብያገኛት ኖሮ አካላቴን ተጠቅሜ እንዴት እንደማማልላት፣ ከአንደበቴ በሚወጡ በጣፋጭ ቃላት እንዴት እንደምይዛት፣ ከዛም እንዴት አብረን ያማረ ጊዜ እንደምናሳልፍ…" እያለ ያመሰጥራል። ስራ ፈትቶ ተመስጧል! ስንት ሀላፊነት፣ ስንት ሸክም ያለበት ትልቁ ልቤ በስሜቱ ተሸንፎ ይንደፋደፋል፣ ይንከራተታል። አንድ ቀን ግን… መጨረሻዬን፣ የነፍሴን ውድቀት አሰብኩ። ልቤን ከዚህ መከራ የማዳን ሀላፊነት አለብኝና በከፍተኛ ፀፀት ሆኜ «No More! ከእንግዲህ ይበቃል!» ብዬ ወሰንኩ። ነገር ግን ፈተናዬ በዚህ አላበቃም! «በቃኝ» ብዬ መንገዴን ስቀጥል፣ አንዷ ድንገት ፊትለፊቴ ትሰየምና «ፋሽን ሾው» ትጀምራለች። (ውዝዋዜና መወረግረግስ አይቀራት!) አቤት ተንኮላቸው… ጌታዬ አላህ (ሱ.ወ) በቅዱስ ቁርኣኑ እንዲህ ይላል፦فَلَمَّا رَأَىٰ قَمِيصَهُ قُدَّ مِن دُبُرٍ قَالَ إِنَّهُ مِن كَيْدِكُنَّ ۖ إِنَّ كَيْدَكُنَّ عَظِيمٌ "ቀሚሱንም ከበስተኋላ ተቀድዶ ባየ ጊዜ «እርሱ (የተናገርሺው) ከተንኮላችሁ ነው፤ (ሴቶች) ተንኮላችሁ በእርግጥ ብርቱ ነውና» አላት።" (ሱረቱ ዩሱፍ፡ 28) ታዲያ ምን ይሻለኛል? እርሷን ላለማየት ስሞክር ወደ ላይ ካየሁ እንቅፋት ሊመታኝ ነው፤ ወደ ቀኝ ወይ ወደ ግራ ከዞርኩ ደግሞ ከሰው ወይም ከግድግዳ ልጋጭ ነው። ስለዚህ ያለኝ ብቸኛ አማራጭ አንገቴን ሳይሆን እይታዬን ወደ ታች ሰበር ማድረግ ብቻ ሆነ! እንደምንም ብዬ ዓይኔን ቀለበስኩት። (ፌሮ ማጠፍ እንኳ እንዲህ አይከብድም!).....ግን ይህን በተጋደሎ ባደረግኩበት ቅፅበት በውስጤ የተሰማኝ ደስታና የኢማን ጥፍጥና… ከከፈልኩት ልፋት በላይ እጅግ የላቀ ነበር! አላህም እውነትን ተናገረ፦
قُل لِّلْمُؤْمِنِينَ يَغُضُّوا مِنْ أَبْصَارِهِمْ وَيَحْفَظُوا فُرُوجَهُمْ ۚ ذَٰلِكَ أَزْكَىٰ لَهُمْ ۗ إِنَّ اللَّهَ خَبِيرٌ بِمَا يَصْنَعُونَ
"ለምእመናን ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን (ያልተፈቀደን ከማየት) ይከልክሉ፤ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፤ ይህ ለነሱ የተሻለ (የጠራ) ነው፤ አላህ በሚሠሩት ሁሉ ውስጥ ዐዋቂ ነው ።" (ሱረቱ አን-ኑር፡ 30)
በሉ ወንድሞች/ምእመናን… የልባችንን ሰላም፣ የነፍሳችንን ጥራት ከፈለግን — ዓይናችንን ሰበር እናድርግ! እንደሱ እንደሆነ... JOIN US: ❯❯ 𝓗𝓪𝓵𝓪𝓵 𝓕𝓴𝓻 ™

Halal Fkr
13 374
«ዓይኔ አያርፍም ፤ ልቤም አያተርፍም» ልቤ ቆንጆ ይወዳል ፤ ዓይኔ ደግሞ ተላላኪ አፈላላጊው ነው። ቺኮቹም በዓይኔ ተመልምለው በልቤ ለመመረጥ ቀንም ማታም የሚፎካከሩ ይመስላሉ። ታድያላችሁ… በአንድ ወቅት በመንገድ ላይ ሆኜ ዓይኔ በለመደው የፍለጋ ስራው ላይ ሳለ፣ ድንገት ከፊቴ በአለባበሷ የዘነጠችና በሜካፕ ፊቷን የተሸፈነች ሴት ያኝና በፍጥነት ወደ አለቃው ልቤ) «Text» ይልካል። ልቤም ደንገጥ ብሎ፣ «እስኪ በደንብ አጣራ!» በማለት ለዓይን መመሪያ ያስተላልፋል። እውነቱን ለመናገር… ልቤ ጨዋ ነበር፤ ዓይኔ ነው እንዲህ እየለቃቀመ ያበላሸው! የሌለበትን መጥፎ አመል አስለመደው። 2022 የተፃፈ አንባቢያን ካሉ ይቀጥላል አላለቀም .... JOIN US: ❯❯ 𝓗𝓪𝓵𝓪𝓵 𝓕𝓴𝓻 ™

Halal Fkr
13 374
በአንድ ወቅት ሰዎች ተሰብስበው ስለ ሌሊት (ተሀጁድ) ሶላት ትሩፋት እያወሩ ነበር። ከነርሱም መሃል አንድ የዋህ የገጠር ሰው አብሮ ተቀምጦ ያዳምጥ ነበር። ሰዎቹም ወደ ሰውዬው ዘወር ብለው፦ "አንተስ ለለይል ትነሳለህን?" ሲሉ ጠየቁት። እርሱም በልበ ሙሉነት፦ "ወሏሂ! አዎ እንጂ!" በማለት መለሰ። ሰዎቹም በሰውዬው ጠንካራ ኢማን ተገርመው እና ተደስተው፦ "ማሻአላህ! ታዲያ ስትነሳ ምንድን ነው የምታደርገው?" አሉት። ሰውዬውም በእርጋታ፦
"ተነስቼ ሽንቴን እሸናና ተመልሼ እተኛለሁ!" አላቸው።
ምንጭ ፡- አኽባሩል ሀምቃ ወልሙገፈሊን (የሞኞች እና የዋሆች ዜናሀ ።

Halal Fkr
13 374
የ Double Standard ጉዳይ... (Let’s be real!) አንዳንድ ጊዜ ሰፈር ውስጥም ሆነ ሶሻል ሚዲያ ላይ የምናየው ፍርድ በጣም ይገርማል። ሼካ ሙድ ስናራምድ... The Hypocrisy: አንዱ ሼካ አንዲትን  ጎረምሳ ሹሪ ያደረገች እህቱን ሲያይ "ሃያ ቢስ! ዱርዬ! ቀበጥ !አሁን አንቺ ሙስሊም ነሽ? ሂጃቡን ብታወልቂው አይሻልም?" ብሎ በ judgmental ቃላት ሙልጭ አድርጎ ይሳደባል። The Excuse: ግን ደግሞ ያቺው "የኛ ጀመዓ" የሚላት ወይም ኒቃቢስት የሆነች ልጅ ስህተት ስትሰራ ሲያይ ጠበቆ ጅልባብ ለብሳ ስትታይ "ኧረ ተዉ እሷም እኮ ሰው ነች፣ ነፍስያ አሸንፏት ነው፣ ሸይጣን አሳስቷት ነው..." እያለ ሺህ cover-up ወሽካታ ምክንያት ይደረድርላታል።😭 Facts Onlyš⁰⁰ የኛ ጀመዓ ስለሆነች ብቻ bias መሆን እና ምክንያት መፈለግ ፌር አይደለም። እህቶቻችንን እኩል እንመልከት! አለባበስ እና Modesty: በሱሪም ሆነ በቀሚስ (ወይም ጅልባብ) የሰውነትን ቅርፅ አጥብቆ ማሳየት አግባብ አይደለም። The Vibe እይታ ውስጥ የሚጥል ሹሪ ልክ እንዳልሆነው ሁሉ፣ አላስፈላጊ ትኩረት የሚስብ ኒቃብም አይፈቀድም። ዋናው ሀሳቡ ራስን ከእይታ መደበቅ እንጂ በልብስ መፎካከር አይደለም! ለእኛ ወንዶች ደግሞ ሴቶቹን "ከላይ ማሻአላህ፣ ከስር ኢንሻአላህ" እያላችሁ ትችት ከመደርደር፣ ወንዶችም እኮ የራሳችን የቤት ሾል አለብን። እኛም ደዕዋችን "ማሻአላህ" እንደሆነው ሁሉ... አይናችንን በመስበሩ በኩል "ኢንሻአላህ" ብለን ራሳችንን መቆጣጠር እንዳለብን አንርሳ አንዴኮ ተፈቅዶዋል ፣ የአላህን ቁድራ እያስተነተንን ነው ። በሚል ደሊል አትደርድሩ¡....ማን እንደሆክ ተቀዋለህ መልካም ምሽት!

Halal Fkr
13 374
ሊጥ ሲከፋፍል ሰምታችሁ ታቃላችሁ😭ሰደቃ ሲሰጥስ አይታችሁ ታቃላችሁ🫪 እኛ ሰፍር የሆነው ይሄ ነው😭

Halal Fkr
13 374
ከ.......ዝንቅ... በቅርቡ እስልምናን የተቀበለ አንድ ወጣት በጀለቢያና በጥምጣም አምሮበት ወደ መስጂድ ብቅ ይላል። መስጂድ ሲደርስ ግን እንደ አጋጣሚ ሆኖ ዋናው ኢማም ሶላታቸውን አጠናቅቀው አሰላምተው ነበር። ወጣቱም ሁለተኛ ጀማዓ ለማቋቋም ሌሎች ሰዎችን እየጠበቀ ሳለ፣ የተወሰኑ ሰዎች ተሰባሰቡና ከመካከላቸው አንዱ ፈጠን ብሎ ኢቃማ አደረገ። ከመሀላቸው በውጫዊ ገጽታው ሱናን አሟልቶ የተገኘው ይሄው ወጣት ስለነበር፣ ሰዎቹ "አንተ ካላሰገድከን" ብለው ሙጥኝ አሉ። ወጣቱም "አዲስ ሰለምቴ ነኝ፣ ምንም አላውቅም" ብሎ ቢማጸንም፣ ምዕመናኑ አጥብቀው ወደ ፊት ገፍትረው አቆሙት። እሱም የሚያደርገው ሲጠፋው፣ በቅርቡ የተማራትን "አላሁ አክበር" ካለ በኋላ ድምጹን አሳምሮ "ኢኒ ቢኒ ቲኒ..." ብሎ ቀራላቸው ይባላል (አሉባልታም ሊሆን ይችላል)። ይህ ቀልድ ድሮ የሰማሁት ቢሆንም፣ በዚህ ዘመን ያለቦታው የቁርአን አንቀጽ እና ሐዲስ የሚጠቃቅሱ ሰዎችን ስመለከት ትዝ ይለኛል። የሚያውቁትን አንቀጽ ሁሉ ዝም ብሎ እንደ መረጃ ማምጣት፣ ከዚህ ወጣት "ኢኒ ቢኒ ቲኒ" የተለየ ትርጉም አይኖረውም። መረጃን ማምጣት ማለት ከዐውዱና ከቦታው ጋር አገናዝቦ ማቅረብ እንጂ በአፍ የያዙትን መወርወር አይደለም يا أخي! JOIN US: ❯❯ 𝓗𝓪𝓵𝓪𝓵 𝓕𝓴𝓻 ™

Halal Fkr
13 374
አንተስ ማን ልትሆን ነው?

Halal Fkr
13 374
በታሪኩ ላይ ያሉትን ከክተሮች እዚህ ግሩፕ ላይ ባሉ ወንድ እና እህቶች ቢቀየር የምትሉ❤️

Halal Fkr
13 374
በዚህ ቻናል ላይ የእውነት በት/ቤት ቆይታ እንዲህ አይነት መደነባበር (የአይን ፍቅር) ውስጥ የገባቹህ❤️ ያልታደላችሁ ደሞ😁

Halal Fkr
13 374
"መድረሻ አልባ" ክፍል አምስት ሲጠብቅ እንዳልነበር ሲደወል ደነገጠ። ሄሎ...."____" 'ዋአለይኪ ሰላም''................ ደረስሽ? በቃ እሱ ጋ ጠብቂኝ" አለና ወጣ። ብዙም ሳይቆዩ መጡ።"አሰላሙ ዋአለይኩም" ብለው ገቡ።መለሱላቸው። ምሳ ቀርቦ ከበሉ በኋላ ካሊድ ሻይ አፍልቶላቸው እየጠጡ፥የካሊድ እናት እየመከረቻቸው አስር አዛን ሲል ተሠናብተው ወጡ።ካሊድ ና ሰለሀዲን ሰዐዳን ሸኝተው ወደ መስጂድ ሄዱ። ሰዐዳ ከዚያን ቀን ጀምሮ በዕረፍት ጊዜዋ እየሄደች ታግዛቸዋለች። (የካሊድን እናት)። እቃ፣ልብስ ታጥብላቸዋለች፥ቡና አፍልታለቸውም ያወራሉ።የፈተና ጊዜ እየቀረበ ስለሆነ ከጓደኛዋ ያስሚን እና ከነካሊድ ጋ እየሆኑ ላይብረሪ እየሄዱ ያጠናሉ።ተፈታኝ ስለሆኑ እንዲያጠኑ በሚል አንድ ወር ቀደም ብለው ትምህርት ዘግተዋል። ከላይብረሪ ወጥተው ወደ ቤት እየሄዱ ሰዐዳ ለካሊድ አንድ መፅሐፍ ሰጠችው።ኢሻ ሰግዶ ከእናቱ ጋ እራት በልተው ትንሽ አውርተው ወደ መኝታቸው ገቡ።የተሰጠውን መፅሐፍ ሊያነብ ሲያነሳው ከውስጡ የተጣጠፉ ወረቀቶች ወደቁ።ከሁሉም ወረቀቶች ጀርባ ላይ 'መጀመሪያ መፅሐፉን አንብብ' ይላል።ወረቀቱን አስቀምጦ መፅሐፉን ማንበብ ጀመረ።እያነበበ ስድስት ሰዐት አለፈ።እንቅልፉ መጣና ዘግቶት ተኛ።……............ ሌላ ጊዜ አዛን ሲል ይቀሰቅሳቸው የነበረውን ዛሬ ሳይመጣ ሲቆይ እናቱ ተነስተው ወደ ክፍሉ ሄደው ቀሰቀሰት።"አውፍ በዪኝ እማ! ማታ እያነበብኩ አርፍጄ ነው'' አላቸውና ወዱዕ አርጎ መስጂድ ሄደ። + በሁለት ቀን ውስጥ መፅሐፉን አንብቦ ጨረሰ።የጓጓለትን ወረቀትም አንስቶ ማንበብ ጀመረ። 'መድረሻ አልባ ደብዳቤዎች 4' ይላል። ሌሎቹን እየከፈተ ቁጥር አንድን አገኘና ማንበብ ቀጠለ። 'መድረሻ አልባ ደብዳቤዎች 1' አሰላሙ ዋአለይኩም ወራህመቱላህ! ካሊድ እንዴት ነህ? እኔ አልሐምዱሊላህ! አለህ አላህ ብሎልኝ ይህን ደብዳቤ ካነበብከው ለምን 'መድረሻ አልባ' አለሽው? ልተለኝ ትችላለህ(ኢንሻአላህ) እና እኔም ይሄን ደብዳቤ እየፃፍኩ ያለሁት ትምህርት ከጀመርን ኹለት ወር ከሆነን በኋላ ነው።አሁን እኔና አንተ አንተዋወቅም ለዛ ነው፥ ላታነበው(ላልሰጥህ) እችላለሁ ብዬ ርዕሱን እንዲህ ያልኩት።ታዲያ ለምን እፅፋለሁ? ም/ቱም አንተን ያየሁህ ቀን ነው ልቤን(ቀልቤን) (እንደውም እኔን ራሴን የሳብከኝ) ለዛም ነው አንተ ፊት መጥቼ መቀመጤ።አላህ ብሎልኝ እስካገኝህ ይህን እፅፍልሃለሁ። -እኔ ሰዐዳ ጀማል እባላለሁ።እዚህ ት/ቤት የገባሁት በዚህ አመት ነው።አዲሱ ቤታችን ተሰርቶ ስላለቀ የበፊቱን ሰፈሬንና ት/ቤቴን ትቼ እዚህ ገባሁ። አባቴ አስመጪና ላኪ ነው።እና ሱቆችም አሉት እናቴና ታላቅ ወንድሜ ናቸው የሚሰሩት።እዚህ ት/ቤት የመጀመሪያ ጓደኛዬ ያስሚን ትባላለች።ታስተውስ ከሆነ እናንተ ክፍል የገባሁት ከሁለት ሳምንት በኋላ ነው።ወደ አንተ ክፍል እንደገባሁ(12 08) ስነግራት 'ይሄን ልጅ አትቅረቢው....ብዙ ሴቶችን አብሯቸው ይሆንና ትቷቸው ይሄዳል' አለቺኝ።እኔ ግን እንዳየሁህ ነበር የወደድኩህ(የአይን ፍቅር ነው?ምናምን እንደሚሉት) ነገር ግን ባንተ ላይ እያየሁት ያለሁት ባህሪ የሙስሊም ባህሪይ አይደለም።በሰላት ሰዐት ላይ ራሱ ተከትዬህ ሄጄ አውቃለሁ ግን ጓደኛህ ሰለሀዲን መስጂድ ሲገባ አንተና ዳኒ ግን ሌላ ቦታ ነው የምትሄዱት።አላህ እንዲያስተካክልህ ሁሌ ዱዐ አረግልሃለሁ!" -ሁለተኛውን ደብዳቤ ጀመረ። 'መድረሻ አልባ ደብዳቤዎች 2' አሰላሙ ዋአለይኩም ወራህመቱላህ ካላ(ዳኒ ሲጠራህ ሰምቼ ነው) ዛሬ'ኮ አናገርከኝ።መስጂድ ልንሄድ ያስሚንን እየጠበኳት እያለ "ብቻሽን ነሽ?ጓደኛሽስ?" ስትለኝ እዚህ መፅሐፍ ላይ ምናምን ብዬ ግራ አጋባሁሃ? ሀሀሀሀሀ...... ግን ብታይ ስላናገርከኝ እንዴት ደስ እንዳለኝ! ፍቅር እንደዚ ያደርጋል'ንዴ!? ፍቅር ማለት እንዲህ ነው ብለው ያብራሩ ብዙ ሰዎች አሊ።ሰብሰብ አርጌ ኢንሻአላህ እፅፍልሃለሁ።ግን…………….....… ግን ፍቅርቢይዘኝም ካንተ ጋ መሆን አልችልም።ምክንያቱም ግንኙነታችን የሐራም ነው የሚሆነው።ሁለተኛ ያንተ ባህሪ ሳይስተካከል(እዚህ ጋ ላብራራልህ ባህሪህ እንዲስተካከል እኔ ማገዝ አለብኝ ግን ላናግርህ ፈራሁ። ኢንሻአላህ ግን እንድስተካከል አግዝሃለሁ) እንዴት? የኔና ያንተ ግንኙነት ሐላል ሲሆን ብቻ! ሰላት መስገድ አለብህ ሌላም ሌላም........ ለዛሬ ይብቃኝ በቃ! 'መድረሻ አልባ ደብዳቤዎች 3' የባለፈው ደብዳቤ ላይ አናገርከኝ ብዬ ጀምሬ ነበር ዛሬ ደሞ አናገርኩህ ብዬ ነው የምጀምረው(ቢስሚላህ!) ልትጨብጠኝ እጅህን ስትዘረጋ እንቢ ያልኩት አንተ ለኔ(እኔ ላንተ) ሐላል ስላልሆንክ ነው። (ኢንሻአላህ ወደፊት) አሁን ግን NO! ደግሞ............. አሁንም ስላናገርኩህ በጣም ደስ ብሎኛል።እና አሁንም ደግሞ ልበላ? ደግሞ..... ፀጉርህን ስትቆረጥ እንዴት እንዳማረብህ (መች አየሺኝ እንዳትለኝ ለሰለሀዲን አውጥተህ ስታሳየው አይቼህ ነው) እንደ ፀጉርህ መጥፎ ባህሪህም መቆረጥ ቢችል! ባለፈው እፅፍልሃለሁ ብዬህ እንደነበረው ልቀጥል "ፍቅር ማለት አንድ ነፍስ በሁለት ስጋ ውስጥ ሲሆን ማለት ነው።"(አርስቶትል) 'በዚህ አለም ላይ አንድ ደስታ ብቻ ነው ያለው እሱም ማፍቀር እና መፈቀር ነው። (ጀርጅ ሳንድ) 'ማፍቀር አለመቻል ትልቁ እድለቢስነት ነው።” (ፊዮዶር ዶስትዮቭስኪ) አይበቃም? ላሁን ያገኘሁት እነዚህን ነው በቀጣይ ደሞ ሌላ ካገኘሁ በሱ እጀምርልሃለሁ። በቃ ካሊድ(ዬ) ደና እደር! ''መድረሻ አልባ ደብዳቤዎች 4'' ይቀጥላል .... JOIN US: ❯❯ 𝓗𝓪𝓵𝓪𝓵 𝓕𝓴𝓻 ™

Halal Fkr
13 374
ለምንድነው የምታጓጓን😭ካልሆነልህ አትነግረንም

Halal Fkr
13 374
ለቻይና ልጁን ሲድር እምነቱን ማይጠይቅ ሀበሻ ሀበሻዊ ስትሆን ኢማን አለው ይላል !😭 ኢማን ሸርጥ የሆነው ለሀበሻ ብቻ ነው እንዴ?

Halal Fkr
13 374
ቀጣይ ክፍል ዛሬ ማታ 3 ሰአት ይጠብቁን!! እስከዛ.... ♡ ㅤ     ❍ㅤ       ⎙ㅤ     ⌲             ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ       ˢʰᵃʳᵉ JOIN US: ❯❯ 𝓗𝓪𝓵𝓪𝓵 𝓕𝓴𝓻 ™

Halal Fkr
13 374
ጁመዓ የት አካባቢ ምን መስጂድ ሰገዳቹህ!! የቤተል ሮም ሰፈር አል ፋሩቅ መስጂድ በአጭሩ የጁመአ መልዕክት ፦ እውነተኛ እምነትና ታዛዥነት፡ ወደ አስር ባህሪያት ተጠቅሶ ነበር የማስታውሰውን ለአላህና
ጁመዓ የት አካባቢ ምን መስጂድ ሰገዳቹህ!! የቤተል ሮም ሰፈር አል ፋሩቅ መስጂድ በአጭሩ የጁመአ መልዕክት ፦ እውነተኛ እምነትና ታዛዥነት፡ ወደ አስር ባህሪያት ተጠቅሶ ነበር የማስታውሰውን  ለአላህና ለ መልእክተኛው (ሜ.ዐ.ወ) ሙሉ በሙሉ እጅ መስጠት፣ ስሜትን ትቶ ትእዛዛትን ማክበርና ክልከላዎችን መራቅ። ጽናትና ትዕግሥት (ሶብር)፡ በፈተናዎችና መከራዎች ወቅት በአላህ መንገድ ላይ መጽናት፤ ዓላማው ጀነት መግባትና ከእሳት መዳን ብቻ እንደሆነ ማወቅ። የተሟላ አምልኮ (ኢባዳ) ሰላትን በልብ ተመስጦ (ኹሹዕ) መስገድ፣ ጾምን በህግጋቱ መጾም እና ሌሊትን በኢባዳ ማሳለፍ። መልካም ስነ-ምግባርና ለግስና ገንዘብን ለበጎ ነገርና ለችግረኞች ማዋል (ሶደቃ)፣ ከወንጀል (እንደ ዝሙትና ሐሰት) መራቅ እና ለቤተሰብ መልካምነት መጸለይ።
ባጭሩ፡ የአማኞች ዋና ግብ ራሳቸውን ገዝተውና በጽናት አላህን በመታዘዝ የጀነት ሰዎችን ባህሪ መላበስ ነው።
የጀነት ሰዋችን ባህሪያት ተቅሰውልንም ነበር። በተመስጦ እንድናዳምጥ የሚያደርጉ ምርጥ ኻጢብ 🖤 JOIN US: ❯❯ 𝓗𝓪𝓵𝓪𝓵 𝓕𝓴𝓻 ™

Halal Fkr
13 374
" አንድ ሰው በሕይወቱ ውስጥ ከሚያጋጥሙት ውጊያዎች መካከል ከባዱ ውጊያ...  " የራሱ ነፍስ " የርሱ ጠላት የሆነችበት ውጊያ ነው። ነፍስህን አደራ ፣ ከአንተ በላይ የሚያውቃት የለም ፤ ወይ አንተ ትገዛታለህ (ታሸንፋታለህ ) ፣ ካልሆነ ግን እሷ ትገዛሃለች። ስለዚህ ተጠንቀቅ! JOIN US: ❯❯ 𝓗𝓪𝓵𝓪𝓵 𝓕𝓴𝓻 ™

Halal Fkr
13 374
"ሳታገባኝ በፊት ለምን ደሀ እንደሆንክ አልነገርከኝም ?" ካንቺ ዉጪ ምንም የለኝም ስልሽ እንድትሽኮረመሚ መስሎሽ ነበር እንዴ ?😭

Halal Fkr
13 374
አላህዬ ሀብታም ብንሆን እንኳን ከአንተ ቸርንት ከጃይ ነን ከድህነታችን ጋር እንዴት አንከጅልም።!! 🫧𝐌.𝐑 𝐁𝐄𝐊𝑹𝐈 JOIN US: ❯❯ 𝓗𝓪𝓵𝓪𝓵 𝓕𝓴𝓻 ™ tiktok group https://tiktok.me/group/ZSXSUaq4q/

Halal Fkr
13 374
ፍቅር....    የሰይዱና አቡ በክሪን ልጅ የሆነችው ኩሉሱም ረዐ እንዲህ ትላለች :- ፍቅርን በደንብ ሚያፈስብኝ ለአላህ ተገዢ የሆነ ባል ተመኘው። አላህም ምኞቷን ተመልክቶ ከአስሩ ጀነተ ከተመሰከረላቸው አንዱ የሆኑት ጠለሀት ኢብኑ ኡበይዲላህን ለገሳት።እሶም እንዲህ ስትል ለእሷ የነበረውን ፍቅር ትገልፃለች :- ሲያየኝ ፊቱ ያበራል፤ ድምፄን ሲሰማ ፈገገ ይላል፤ ካለቀስኩኝ ያለቅሳል፤በፍራሽ ላይ በትንፍሽ ሲያረጋጋ እንቅልፍ አያወስደውም ፣ ሰላቱ ውስጥ ከራሱ በፊት ዱአ ሳያደርግ አይተወኝም ነበረ ፤ ሲያመኝ ህመሙ ከኔ ይብስ ነበር እንደውም ህመሙ እሱ ላይ ያለ ይመስል ነበር ፤ ከበላ አስቀድሞ ያጎርሰኝ ነበር ፤ በእጁም ነበር የሚያበላኝ በውስጥም በውጪም ኩራቱ ልእልናው ነበርኩ።   ﴿وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً﴾ (ሱረቱ አር-ሩም ፡ 21) 🫧𝐌.𝐑 𝐁𝐄𝐊𝑹𝐈

Halal Fkr
13 374
ድንች ፣ በቆሎ ሻይ ..............ለብርዱ አሪፍ ነው።

Halal Fkr
13 374
አልገባኝም ምትሉ ሰዎች ግን ምናችሁን ነው ምያማችሁ. እሄ እኮ በጣም ትልቅ ጥበብ ነው. ዉጭ ሀገር ብሆን በጨረታ ነው ምሸጠው. እሄንን ጥበብ ለመጀመሪያ ግዜ ለ ዓለም ያስተዋወቀው እንግልዛዊው josef robensen ይባላል. በዝህ ስራው ብዙ የወርቅ ሜዳልያ እና ከ Victoria University የክብር doctorate አግኝቷል. አሁን ደግሞ ኢትዮጵያዊ ወንድማችን...... ኡኡፍፍ እኔ ቡና ስላልጠጣሁ ዝም ብዬ ነው የቃባጠርኩት... ©ziz አጋብቶብን