uz
Feedback
Amhara Education Bureau

Amhara Education Bureau

Kanalga Telegram’da o‘tish

Quality Education

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Amhara Education Bureau analitikasi

Amhara Education Bureau (@anrse) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 39 405 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 4 652-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 871-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 39 405 obunachiga ega bo‘ldi.

02 Sentabr, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 2 047 ga, so‘nggi 24 soatda esa 4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 36.35% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.01% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 14 326 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 5 917 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 26 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Quality Education

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 03 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

39 405
Obunachilar
+424 soatlar
+417 kun
+2 04730 kun
Postlar arxiv
photo content
+5

"በክልሉ ቴክኖሎጂን የመጠቀም ልምድ እያደገ ነው" ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የአማራ ክልል ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጅ ቢሮ የበለጸጉ እና በሥራ ላይ የሚገኙ ችግር ፈች የኾኑ ሲስተሞችን በአውደ ርዕይ ለጎብኝዎች ክፍት አድርጓል። ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አውደ ርዕዩን አሥጀምረዋል። የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎችም ተገኝተዋል። በአውደ ርዕዩ "ኤሌክትሮኒክስ መንግሥት ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መሠረት" በሚል መሪ መልዕክት የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበትም የፓናል ውይይት ተካሂዷል። በመርሐ ግብሩ የተገኙት የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ መንግሥት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ቴክኖሎጂን እንደ አካታች ሀገራዊ ብልጽግና፤ ዘላቂ ልማት እና ለብቁ ሀገራዊ ተወዳዳሪነት ቁልፍ መሠረት አድርጎ እየሠራበት ነው ብለዋል። በኢኮኖሚ ዕድገት፤ ምርታማነትን በማሳደግ፤ በመንግሥት አገልግሎት ቅልጥፍናን በማሻሻል፤ የዜጎች ተሳትፎን በማሳደግ፤ የዲጂታል ክህሎትን በማጠናከር ግብ አድርጎ በትኩረት እየሠራ እንደኾነ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማት ለውጭ ኢንቨስትመንት እና ለቱሪዝም ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም አንስተዋል። በአማራ ክልል "ዲጂታል አማራ" በሚል በ25 ዓመቱ የዕድገት እና ትራንስፎርሜሽን ፍኖተ ካርታ ላይ ቴክኖሎጅ እንደ ልማት መዳረሻ መፍጠሪያ ተደርጎ ተይዟል ነው ያሉት። በ25 ዓመቱ ስትራቴጅክ ግብ ላይ በ2042 የአማራ ክልል ዋነኛ ሀብት፤ የአገልግሎት መስጫ እና የኢኮኖሚ የዕድገት ምንጭ ቴክኖሎጂ እንዲኾን ይሠራል ነው ያሉት። በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት ቴክኖሎጂን የመጠቀም፤ የማላመድ እና የመሥራት ልምምዳቸውን እንዲያጠናክሩም እየተሠራ ነው ብለዋል። በክልሉ ቴክኖሎጂን የመጠቀም ልምድ ዕድገት እያሳየ መጥቷልም ነው ያሉት። የክልሉ መንግሥት ቴክኖሎጂን በስፋት ለመጠቀም በትኩረት እየሠራ ነውም ብለዋል። ቴክኖሎጂን በመጠቀም ምርት እና ምርታማነትን ለማሳደግ እና ዜጎች በአገልግሎት ደስተኛ እንዲኾኑ እየተሠራ እንደኾነም ጠቁመዋል። የአማራ ክልል የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጅ ቢሮ ምክትል ኀላፊ የቻለ ይግዛው የመርሐ ግብሩ ዓላማ በአማራ ክልል የለሙ የዲጂታል መፍትሔዎችን በጋራ ለመመረቅ እና ወደ ሥራ ለማስገባት ነው ብለዋል። በርካታ የለሙ ሲስተሞች ወደ ሥራ መግባታቸውንም ገልጸዋል። ሌሎች የለሙ ሲስተሞችም ወደ ሥራ እንደሚገቡ ተናግረዋል። አውደ ርዕዩ የመንግሥት የአሠራር ሥርዓት ዲጂታላይዝድ እንዲኾን ለማፋጠን እና ዲጂታል 2030ን እውን ለማድረግ ያለመ ነውም ብለዋል። በመርሐ ግብሩ ከ35 በላይ ዲጂታል መፍትሔዎች ለምተው ለተቋማት እና ለኅብረተሰቡ ክፍት መኾናቸውንም ገልጸዋል። አውደ ርዕዩ አገልግሎት ሰጭው እና አገልግሎት ተጠቃሚው ስለ ዲጂታል መፍትሔዎች አውቆ እንዲጠቀም ለማድረግ እንደሚያስችልም ነው ያነሱት። የለሙ ሲስተሞች ለአገልግሎት ክፍት መኾናቸውንም ገልጸዋል። Amhara Communications #AmharaEducation #ትምህርትለትውልድ#በጎነትለኢትዮጵያከፍታ#አንድደርዘንደብተርለአንድተማሪ ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ 📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/ 📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w 📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau 📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse ያግኙን 📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau 📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau

photo content
+5

"በእጃችሁ የያዛችሁት ስማርት ስልክ የቴክኖሎጂ ትምህርት ቤት ነው" በለጠ ሞላ (ዶ.ር) የአማራ ክልል ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጅ ቢሮ "ኤሌክትሮኒክስ መንግሥት ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መሠረት" በሚል መሪ መልዕክት የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበት የፓናል ውይይት አካሂዷል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ.ር) ኢትዮጵያ ዲጂታል 2025 ስትራቴጅን ተግባራዊ በማድረግ የሕዝብ አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ ለማዘመን ያደረገችው ርብርብ ተጨባጭ ፍሬን አፍርቷል ብለዋል። የመንግሥት ተቋማት ከወረቀት አሠራር ወጥተው ወደ ዘመናዊ የዲጂታል አሠራር እየተሸጋገሩ መኾኑንም ተናግረዋል። ከ49 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት በመኾን፤ ዜጎች በቴሌ ብር እና በባንኮች በዲጂታል መድረኮች በመገበያየት እና በመሶብ አገልግሎት ፈጣን ተጠቃሚ ኾነዋል ነው ያሉት። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን እውን ለማድረግ ወደ ሥራ ተገብቷልም ብለዋል። ተደራሽነትን ማስፋት፤ ለሁሉም ዜጎች እኩል ዕድል መፍጠር፤ በዜጎች እና በተቋማት መካከል እምነትን ማጠናከር የዲጂታል 2030 የትኩረት አካል መኾናቸውን ገልጸዋል። የአማራ ክልል ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ቢሮ ያዘጋጀው አውደ ርዕይ የተቋማትን የዲጂታል ግንዛቤ ለማሳደግ፤ የፈጠራ ሥራዎችን ለሕዝብ ለማስተዋወቅ እና የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን የሚያግዝ ነው ብለዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የመንግሥት አጀንዳ ብቻ አይደለም ያሉት ሚኒስትሩ ሕዝብ እና መንግሥት የሚገናኙበት እውነተኛ መንገድ መኾኑን ተናግረዋል። የዲጂታል መሠረተ ልማትን ማግኘት ቅንጦት አይደለምም ብለዋል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለሁሉም ተጠቃሚዎች በእኩልነት የሚያገለግል አድሎ አልባ ድልድይ መኾኑንም አንስተዋል። ወጣቶች በእጃችሁ የያዛችሁት ስማርት ስልክ መዝናኛ ብቻ ሳይኾን የቴክኖሎጂ ትምህርት ቤት በመኾኑ በአግባቡ ልትጠቀሙበት ይገባል ነው ያሉት። የሚመጣው የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዘመን የሚፈልገው ወጣቶችን በመኾኑ ራሳችሁን ከአዲሱ ቴክኖሎጂ ጋር ልታላምዱ ይገባል ብለዋል። ቴክኖሎጂ መንግሥት ሠራተኛኞችን ለፈጠራ እና ለውሳኔ ሰጭነት የሚያበቃ በመኾኑ ቴክኖሎጂን መታጠቅ እና መላመድ ይገባል ብለዋል። የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ከዳር ለማድረስ በተቋማት መካከል ያሉ የዲጂታል መረጃ ቋቶች እርስ በዕርስ የሚናበቡበት እና በሕግ መሠረት መረጃ የሚለዋወጡበት ሀገራዊ ማዕቀፍ ተግባራዊ ይደረጋልም ብለዋል። እጅ ለእጅ ተያይዘን ትኩረታችንን በፈጠራ እና በግንባታ ላይ በማድረግ ልጆቻችን የሚኮሩባት ሀገር እንገነባለን ብለዋል። #አሚኮ #ቴክኖሎጂ #ኢትዮጵያ #AmharaEducation #ትምህርትለትውልድ#በጎነትለኢትዮጵያከፍታ#አንድደርዘንደብተርለአንድተማሪ ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ 📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/ 📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w 📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau 📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse ያግኙን 📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau 📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau

"የአንድ ተማሪ ህይወት የሙሉ ቤተሰብ ህይወት ነው" ዶ/ር መሉነሽ ደሴ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ
"የአንድ ተማሪ ህይወት የሙሉ ቤተሰብ ህይወት ነው" ዶ/ር መሉነሽ ደሴ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ

photo content
+9

photo content

"ጠንካራ አፈጻጸም ያላቸውን ተቋማት በማበረታታት ክፍተት ያለባቸውን በመደገፍ ወደ ተቀራራቢ አፈጻጸም እንዲመጡ እየተሰራ ነው።" ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ። ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የአማራ ክልል ማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች እየገመገመ ነው። በግምገማ መድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ በክልሉ ሰላም እና ልማትን ለማረጋገጥ ጉልህ ተግባራት መከወናቸውን ተናግረዋል። የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት እስከታችኛው መዋቅር ድረስ እየተከናወኑ ያሉ ቅንጅታዊ ተግባራት በሱፐርቪዥን ቡድን የድጋፍ እና ክትትል ስራዎች መከናወኑን ገልጸዋል። ድጋፍና ክትትሉ በትምህርት፣ በጤና ፣ በሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ በሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ መካሄዱ ተገልጿል። በተደረገው ድጋፍ እና ክትትል በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች እና በመንግስት የታቀዱ ኢኒሸቲቮች በመልካም አፈጻጸም ላይ እንደሚገኙ አመላክተዋል። የክላስተሩ ተቋማት በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ቤት የሚደርሱ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊዋ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለማሻሻል እየሰሩ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የማህበራዊ ክላስተር ዘርፍ ተቋማት እርስ በእርስ ተሞክሮዎችን እንዲለዋወጡ እንዲማማሩ ቅንጅታዊ አሰራሮችን እንዲያሳድጉ ተከታታይ ድጋፎች ይደረጋሉ ብለዋል። ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ 1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/ 2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w 3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau 4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse ያግኙን             ‎ ‎

የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ተመሳሳይ ውጤት ያስመዘገቡት መንትዮች‼️ ========= ነሐሴ 24/2018(ትምህርት ቢሮ)በአማራ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 15.56%ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ማምጣታቸው ይታወቃል። ከተመዘገበው ውጤት በተጨማሪ የባህርዳር ከተማ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሁለት መንትዮች ተመሳሳይ ውጤት ማስመዝገባቸው አስደናቂ ክስተት ሆኗል። ተማሪ በዕምነት መልካሙ እና ዮርዳኖስ መልካሙ የሚባሉ መንትዮች በባህርዳር ከተማ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ወስደው ሁለቱም ተመሳሳይ 413 ከ600 ውጤት ማስመዝገባቸው ብዙዎችን አስገርሟል። በዚህ ዙሪያ የዘርፉ የስነልቦና ባለሙያዎች አስተያየት ስጡበት‼️ #AmharaEducation #ትምህርትለትውልድ ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ 📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/ 📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w 📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau 📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse ያግኙን 📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau 📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau

photo content
+1

photo content
+8

ከ88 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባው የአጆ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተጠናቆ ርክክብ ተካሄደ ። በሰሜን ወሎ ዞን ሃብሩ ወረዳ በከተማና መሰረተ መሰረተልማት ሚኒስቴር የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ኘሮጀክት ከ88 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባው የአጆ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተጠናቆ የዞኑ የስራ ኀላፊዎች በተገኙበት ርክክብ ተካሂዷል። የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ሰጠ ታደሰ እንዳሉት፣ ትምህርት ቤቱ ሁለት መማሪያ ክፍሎችን ጨምሮ ዘጠኝ ብሎኮች አሉት ። በሁለት ፈረቃ እስከ አንድ ሺህ ተማሪዎችን ለማስተማር እንደሚያስችልም ገልፀዋል። ትምህርት ቤቱ በጃራ የስደተኞች ካምኘ ላሉ ታዳጊዎች መጋቢ ሆኖ ያገለግላልም ብለዋል። በርክክብ ሂደቱ ላይ የተገኙት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዱባለ አብራሬ፣ የሰሜን ወሎ ዞንን የትምህርት ሽፋን ከፍ ለማድረግና የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ቀደም ሲል ከተማ አስተዳደሩ በጉባላፍቶ ወረዳ ሁለት ትምህርት ቤቶችን ገንብቶ ለዞኑ አስተዳደር ማስረከቡን አስታውሰዋል። የአጆ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተፈናቃይ ወገኖች መጋቢ በመሆኑ ከተማ አስተዳደሩ በግንባታው ሂደት የበኩሉን ድርሻ ተወጥቷልም ነው ያሉት። ህብረተሰቡ ትምህርት ቤቱን እንዲጠብቅና እንዲንከባከብም አሳስበዋል። የሰሜን ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ገበያ ልማት መምሪያ ኀላፊ ታምራት ንጋቱ በበኩላቸው፣ ትምህርት ቤቱ ደረጃውን ጠብቆ ተገንብቶ መረከባቸውን አውስተዋል። ለ2019 የትምህርት ዘመን ማስጀመሪያ በቂ ግበዓት መኖሩን ጠቅሰው፣ ተጨማሪ የትምህርት ቁሳቁስ ለማሟላት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ዞን አስተዳደሩ መክሮ የመማሪያ ወንበር፣ ጥቁር ሰሌዳ፣ የቤተሙከራ፣ የቤተመጻህፍትና የአይሲቲ ማዕከሉን ሙሉ ለማድረግ እንደሚሰራም አስረድተዋል። የአካባቢው ሀገር ሽማግሌ ሸህ ሀሰን ከረሙ የትምህርት ቤቱ መገንባት የአካባቢው ወጣቶች አመለካከት በመለወጥ የህገወጥ ስደት ሰለባ ከመሆን ይታደጋል ሲሉ አስተያየታቸውን ለአሚኮ ተሰጥተዋል። አሚኮ #ደሴ #አሚኮ #ዜና #ሰሜን_ወሎ #ትምህርት #ወልድያ

photo content
+6

photo content
+9

ዓባይ ባንክ በትምህርት ቁሳቁስ ችግር ምክንያት መማር ለሚቸገሩ ተማሪዎች 50 ሺህ የመማሪያ ደብተሮችን ድጋፍ አደረገ። ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ ዓባይ ባንክ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እና የትምህርት ዘርፉን ከማሳደግ አኳያ በኢኮኖሚ ጫና ምክንያት ለልጆቻቸው የትምህርት ቁሳቁስ ማሟላት ለማይችሉ ወላጆች እና ልጆች ከትምሕርት ገበታቸው እንዳይቀሩ የሚያግዝ የ50,000 ባለ50 ገጽ ደብተሮችን ለአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስረክቧል፡፡ ድጋፉ በክልሉ በተለያየ ምክንያት ትምህርታቸውን መከታተል እየፈለጉ በቁሳቁስ ዕጥረት ለተቸገሩ ተማሪዎች በፍትሐዊነት ለሁሉም ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች የሚሰራጭ ነው። የትምሕርት ቁሳቁስ ድጋፉ በአማራ ክልል መማር እየፈለጉ በአቅም ማነስ እና በሌሎች ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ችግሮች ምክንያት እገዛ ማግኘት ላልቻሉ ተማሪዋች በባንኩ መለያ በልዩ ህትመት የተዘጋጁ ደብተሮች ናቸው። ርክክቡ ዛሬ ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በባሕርዳር ከተማ ሲካሄድ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መኳንንት አደመ ባደረጉት ንግግር፣ “የክልሉን የትምሕርት ስትራቴጂ ከማሳካት አኳያ እንደ ዓባይ ባንክ ያሉ አጋሮች የተቀናጀ ኢንቨስትመንት ከማካሄድ ባሻገር የማኅበራዊ ልማት ላይ በንቃት መሳተፍ ድርሻው ከፍ ያለ ነው” ብለዋል። ሀገራዊ የትምህርት ዘርፋን ለማሳደግ እና የተማሪዎችን ውጤታማነት ከፍ ለማድረግ ከሚደረገው እንቅስቃሴ ጎን ለጎን እንደ ዓባይ ባንክ ያሉ ቀዳሚ የልማት እና የፋይናንስ አጋሮች የሚያደርጉት ድጋፍ ለሌሎችም ምሣሌ የሚሆን ነው ተብሏል። ኃላፊው በክልሉ የትምህርት ዘርፍ የመሠረተ-ልማት እና የግብዓት እጥረቶችን ለመፍታት በሚያደርገው ጥረት የፋይናንስ ተቋማት እገዛ ወሳኝ መሆኑን ገልፀው፣ የዓባይ ባንክ የመማሪያ ደብተር ድጋፍም በከልሉ የተማሪዎችን የማቋረጥ ምጣኔን ለመቀነስ ለሚደረገው ጥረት ትልቅ ዐቅም ይኖረዋል ብለዋል። ድጋፋ በትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ እጥረት ወደ ትምህርት ገበታ መሄድ ያልቻሉ የክልሉ ተማሪዋችን ችግር ለመቅረፍ እና “በዚህ ችግር ወደ ትምህርት ገበታቸው ያልመጡ ተማሪዋችን ተስፋ የሚያለመልም ነው” በማለት ምስጋናቸውን ለባንኩ አቅርበዋል፡፡ የዓባይ ባንክ ስትራቴጂ ዋና መኮንን አቶ ወንድይፍራው ታደሰ ባንኩ የማኅበራዊ ልማት ዘርፉን ከማሳደግ አኳያ እያከናወነ ያለውን ድጋፍ አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል። ዓባይ ባንክ “በእያንዳንዱ የማኅበረሰብ ጎጆ ገብቶ ቀዳሚ የፋይናንስ አጋር የመሆን ፍኖት እና በቀጣዩ ትውልድ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ ዕውቀት-መር የኢንቨስትመንት አስተሳሰብ መገንባት” እየተተገበረ ያለ አቅጣጫ መሆኑን አሳውቀዋል። ባንኩ በተለያዩ ዘርፍች ማኅበረሰቡን የሚጠቅሙ እና የማህበራዊ ኃለፊነት የመወጣት ዕቅዱ አካል የሆኑ ድጋፎችን በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ለሚገኙ ተቋማት እና ዜጎች ሲያደርግ መቆየቱንም አውስተዋል። ዓባይ ባንክ በፋይናንሱ ዘርፍ ለብዙዎች የታላቅነት ምንጭ ከመሆን ባሻገር የኮርፖሬት ማኅበራዊ ኃላፊነትን እንደ ቁልፍ ስትራቴጂያዊ የማኅበረሰብ አጋርነት እና ተቋማዊ ትሥሥር ዓላማ የሚያውል መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ዓባይ ባንክ አሁን ላይ ካደረገው የትምህርት ግብዓት ድጋፍ ባሻገር በጥቅል የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ከ4.8 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ደንበኞቹ ሰፊ የዲጂታል የባንክ አገልግሎቶች በማቅረብ ግንባር ቀደም የፋይናንስ አጋር በመሆን እየሠራ መሆኑ ተጠቅሷል። ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ 1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/ 2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w 3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau 4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse ያግኙን             ‎ ‎

photo content
+9

ከ54 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት የመለሰው የበጎ ፈቃድ ሥራ። በደቡብ ጎንደር ዞን በተካሄደው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ51 ሺህ በላይ ዜጎች በማዕድ ማጋራት ተጠቃሚ ኾነዋል። "ለአንድ ተማሪ አንድ ደርዘን ደብተር" በሚል መሪ መልዕክትም ከ54 ሺህ በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል። የደቡብ ጎንደር ዞን ሴቶች፣ ወጣቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኀላፊ አንጓች ፋሲካው እንደገለጹት ይህ ስኬት በዞኑ በሚገኙ መምሪያዎች እና ተጠሪ ጽሕፈት ቤቶች የጋራ ርብርብ የተገኘ ነው። የበጎ ፈቃድ ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የደቡብ ጎንደር ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ መንበር ክፈተው ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች ቀድሞ መድረስ ለትውልድ የሚተርፍ ተግባር መኾኑን ጠቅሰዋል። የማኅበራዊ አገልግሎት ሥራዎችም በደም ልገሳ እና በቤት እድሳት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነው የጠቆሙት። በተደረገው ድጋፍ ከተጠቀሙ ወገኖች መካከል የሦሥት ልጆች እናት ወይዘሮ ደማም ተሾመ የተደረገላቸው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ልጆቻቸውን ከጎዳና ሕይወት ታድጎ በነጻነት እንዲማሩ ማድረጉን ገልጸዋል። የ7ኛ ክፍል ተማሪዋ ዳሳሽ ምሥጋናው የተደረገላት ድጋፍ ከጓደኞቿ ጋር እኩል እንድትሰለፍ የሞራል ስንቅ እንደኾናት እና ጠንክራ በመማር ዶክተር የመኾን ራዕይ እንድትሰንቅ እንዳስቻላት ተናግራለች። ነሐሴ 18/2018 አሚኮ

"እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል" አቶ ጥላሁን ወርቅነህ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ
"እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል" አቶ ጥላሁን ወርቅነህ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ

የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን እቅድ ትውውቅ መድረክ እያካሄደ ነው የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን አፈጻጸምን ለመገምገምና የ2019 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ዕቅድን ለማስተዋወቅ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በሰቆጣ ከተማ ውይይት እያካሄደ ነው። በመድረኩ የአለፈው የትምህርት ዘመን አፈጻጸም፣ የ2019 ዓ.ም. የተማሪዎች ምዝገባ ሁኔታ እና በቀጣዩ የትምህርት ዘመን ትምህርትን በተሻለ ሁኔታ ለማስፋፋት የሚያስፈልጉ ተግባራት በዝርዝር እንደሚመከር ተመላክቷል። የትምህርት መምሪያው ኃላፊ አቶ ሰይፉ ሞገስ፣ ለ2019 ዓ.ም. አዲሱ የትምህርት ዘመን ተማሪዎች ምዝገባን በተሳካ ሁኔታ ማከናወንና ተማሪዎች በወቅቱ ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመዘገቡ ማድረግ ትኩረት የሚሻ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በተያያዘም የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክትል አስተዳዳሪና የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሀላፊ አቶ ሹመት ጥላሁን በፕሮግራሙ ማስጀመሪያ እንደተናገሩት የትውልድ ግንባታ ላይ የትምህርት ሚና የላቀ መሆኑን ገልፀዋል። በመድረኩ በአለፈው ዓመት የተከናወኑ ስራዎችን በመገምገም ለቀጣይ ስራዎች ስኬታማነት መሠረት የሚጥልበት መሆኑን አክለዋል። በተለይም ባለፈው የበጀት ዓመት የታዩ ጥንካሬዎችን ማስቀጠል፣ የትምህርት ተደራሽነትን ማረጋገጥና ወደ 2019 ዓ.ም. ሊሸጋገሩ የማይገባቸውን እጥረቶች ከወዲሁ ማረም እንደሚገባ ባለድርሻ አካላት በትኩርት እንዲወያዩ አፅንኦት ሰጥተዋል። በተማሪዎች ምዝገባ ረገድም መሻሻል የሚያስፈልጋቸው ሁኔታዎች መኖራቸው አቶ ሹመት ተናግረዋል። በአለፈው አመት ከመማር ዕድሜያቸው ደርሰው መመዝገብ ከነበረባቸው ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ተማሪዎች 14 በመቶ ያህሉ አለመመዝገባቸው ጠቁመዋል፡፡ ከ9ኛ እስከ12ኛ ክፍል ተማሪዎች አኳያም በትምህርት ገበታ መግባትና መመዝገብ ጋር ተያይዞ 54 በመቶ የሚሆኑት ከትምህርት ገበታ ውጭ እንደነበሩ አቶ ሹመት አስረድተዋል። በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ የእቅድና በጀት ዝግጅት ቡድን መሪ በዲያቆን ስዩም አጠቃላይ ሪፖርት እየቀረበ ይገኛል። ነሐሴ 18/2018 መረጃው የዋግ-ኽምራ ኮሙኒኬሽን ነው

photo content
+5