ch
Feedback
Amhara Education Bureau

Amhara Education Bureau

前往频道在 Telegram

Quality Education

显示更多

📈 Telegram 频道 Amhara Education Bureau 的分析概览

频道 Amhara Education Bureau (@anrse) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 33 807 名订阅者,在 教育 类别中位列第 5 627,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 990

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 33 807 名订阅者。

根据 22 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 8 939,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 51.08%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.57% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 17 264 次浏览,首日通常累积 5 261 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 46

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Quality Education

凭借高频更新(最新数据采集于 24 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

33 807
订阅者
+824 小时
+1657
+8 93930
帖子存档
photo content
+2

photo content
+9

የተማሪዎች እና መምህራን የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ እና የጥናትና የምርምር ሲምፖዚየም እየተካሄደ ነው። ሰኔ 16/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የተማሪዎች እና መምህራን የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ እና የጥናትና የምርምር ሲምፖዚየም መካሄድ ጀምሯል። በመክፈቻው ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ ትልቅ ታሪክ ያላት የሰው ዘር መገኛ፣ የስልጣኔ ምንጭ የሆነችው ሀገራችን ዛሬም ብሩህ አእምሮ እና የተፍታታ እጅ ያላቸው ምሁራንን እየፈራች መሆኑን ገልጸዋል። የአድዋ ልጆች ከአባቶቻችን ዘመን የላቁ የፈጠራ ስራዎችን በመጠቀም ሀገራችን በዓለም አደባባይ ከፍ ለማድረግ መስራት ይገባል ብለዋል። ፈጠራ ከአካባቢያችን ከምናያቸው ትንንሽ ነገሮች የሚነሳ መሆኑን የገለጹት ሀላፊዋ የፈጠራ ዝንባሌና ሀሳብ ያላቸውን ልጆች ማበረታታትና መደገፍ ይገባል ብለዋል። ሀገራችን በየዘርፉ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት የፈጠራ ስራ፣ የጥናት እና ምርምር ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል። የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ እና የጥናትና የምርምር ሲምፖዚየሙ በትምህርት ዘርፍ የተከናወኑ ፈጠራዎችን ለማበረታታት፣ ጥናት እና ምርምሮችን ለማሳዬት፣ ልምዶችን ለመለዋወጥ፣ የተገኙ ውጤቶችን ለማጋራት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። አውደ ርዕዩ በክልሉ ውስጥ ያሉ የፈጠራ ስራዎችና የምርምር ውጤቶችን ማስተዋወቅ፣ የጋራ ትብብርን ለማጠናከርና በትምህርት ጥራት ላይ ሁለንተናዊ እድገት ለማምጣት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል። የሳይንስ የምርምርና የፈጠራ ስራ በክልሉ የ25 ዓመት የእድገትና ዘላቂ ልማት እቅድ፣ በ5 አመት ስትራቴጅክ እቅድ ትልቅ ትኩረት እንደተሰጠው አመላክተዋል። የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የሳይንስ የምርምርና የፈጠራ አቅሞችን ለማስተባበር፣ ለመደገፍና ለመጠቀም ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። በአውደ ርዕዩ ከየዞኖች እና ከተማ አስተዳደሮች የተመረጡ የተማሪዎች እና የመምህራን የፈጠራ ስራዎች ለእይታ ቀርበው በክብር እንግዶች እና በታዳሚዎች ተጎብኝተዋል። የፈጠራ ስራ አውደርዕይ እና ጥናትና ምርምር ሲፖዚየሙ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሰኔ 18/ 2108 ዓ.ም ድረስ የሚቀጥል ይሆናል። #AmharaEducationBureau #ትምህርትለትውልድ #Reasearch #Inovation #Creativity

photo content
+4

photo content
+9

ከ73 ሽህ በላይ ለሚሆኑ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የአይን ጤና ምርመራ ተደረገ። ሰኔ 14/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ ፓርትነርስ ኢን ኢዱኬሽን ኢትዮጵያ ከክሊንተን ሄልዝ አክሰስ ኢንሼቲቭ /CHAI/ ጋር በመተባበር ለሁለት ወራት ሲካሄድ የቆየውን የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የአይን ጤና ምርመራ ዘመቻ ማጠቃላያ መርሃ ግብር አካሂዷል። ለሁለት ወራት በተካሄደው በባህር ዳር፣ ጎንደር እና ደብረ ብርሃን ከተሞች ላይ የሚገኙ እድሜያቸው ከ3 እስከ 6 አመት የሆኑ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የአይን ምርመራ ዘመቻ 73 ሽህ 336 ህጻናት መመርመራቸውን የፓርትነርስ ኢን ኢዱኬሽን ኢትዮጵያ የአማራ ክልል አስተባባሪ አቶ አብዮት አሸናፊ ተናግረዋል። በምርመራ ሂደቱ የተለዩ የአይን ችግር የተገኘባቸውን ህጻናት ህክምና እንዲያገኙ መደረጉን አመላክተዋል። በተካሄደው የምርመራ ዘመቻ ማህበረሰቡ በአይን ጤና ላይ ያለውን ግንዛቤ ያሳደገ እንደነበር ተገልጿል። በማጠቃላያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ በርካታ ተማሪዎች በአይን ጤና ችግር ምክንያት ትምህርታቸው በአግባቡ ለመከታተል እንደሚቸገሩ ገልጸዋል። ፓርትነርስ ኢን ኢዱኬሽን ኢትዮጵያ ከክሊንተን ሄልዝ አክሰስ ኢንሼቲቭ /CHAI/ ጋር በመተባበር ያደረጉት ዘመቻ የበርካታ ተማሪዎችን ችግር በመለየት ህክምና እንዲያገኙ በማስቻላቸው አመሰግነዋል። በተደረገው የአይን ምርመራ የተገኙ ውጤቶች በተማሪዎች የአይን ህክምና ላይ የበለጠ መስራት እንደሚገባ ያመላከተ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ኦፕቶሜትሪ ማህበር የአማራ ክልል ተወካይ ዮሴፍ አንተሁን የህጻናት የአይን ጤና ጉዳይ ትኩረት የሚፈልግ መሆኑን ገልጸዋል። የማህበሩ አባላት በምርመራ ዘመቻው ትልቅ ተሳትፎ ማድረጋቸውን አመላክተዋል። ባለሙያዎች የተማሩትን ትምህርት ወደ ተግባር በመቀየር ለታካሚዎች ህክምና ለመስጠት የህክምና መሳሪያዎች እጥረትን ለመቅረፍ ፓርትነርስ ኢን ኢዱኬሽን ኢትዮጵያ ላደረገላቸው እገዛ አመስግነዋል። ወደፊት ከድርጅቱ ጋር በትብብር እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል። #AmharaEducationBureau #ትምህርትለትውልድ

photo content
+7

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ በባህርዳር ከተማ አስተዳደር የመምህራን ቀን አከባባር ላይ ተገኝተው ያስተላለፉት ሙሉ መልዕክት *** • ትምህርት ለአንድ ሃገር ዋነኛው የመወዳደሪያ አቅም ነው፡፡ በትምህርት ገፍተው የሄዱ ሃገራት ኢኮኖሚያቸው ያደገና በፈጠራ የተደገፈ ነው፤ፖለቲካቸው የሰለጠነ ፤የኑሮ ዘይቤያቸው ቀላልና ምቹ ነው፡፡ የደቡብ አፍሪካው ታላቁ የቀድሞ መሪ ኔልሰን ማንዴላ እንዳሉት ትምህርት አለምን ለመለወጥ የምንጠቀምበት በጣም ሃይለኛ መሳሪያ ነው ብለዋል፡፡ ይሄ ሃይለኛ መሳሪያ ደግሞ ባለቤትነቱ የናንተ መምህራን ነው፡፡ በዚህ ልትኮሩ ይገባል ብለዋል፡፡ • መምህራንና የትምህርት አመራሮች ባላተመቸና ባልተሟላ ሁኔታ ውስጥም ሆናችሁ ለትውልድ ግንባታ ለምታበረክቱት አስተዋፅኦ የክልሉ መንግስትና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ታላቅ አድናቆትና ክብር አለው ብለዋል፡፡ • የመምህርነት ሙያ ከፍ የሚለውና ወደ ቀደመ ክብሩ የሚመለሰው እኛ መምህራን በምንሰራው ስራና በትውልድ ግንባታ ላይ በምንፈጥረው በጎ ተፅዕኖ ነው፡፡ በመንግስት በኩል በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ትምህርትንና መምህርነትን ለመደገፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት በጎ ጥረቶች ተጀምረዋል፤የበለጠ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ • እንደ ሃገርም ሆነ እንደ ክልል መጭው ጊዜ ለትምህርትና ለመምህርነት ብሩህና የተሻለ እንደሚሆን እርግጠኞች ነን፡፡ • የመምህራንና የት/ቤት አመራሮችን በትርፍ ጊዜያቸው በተለይ በክረምት ከቅርብ አመታት ወዲህ የተጀመረው በሞያቸው የማሰልጠንና የማብቃት ስራ በዚህ ክረምትም በክልላችን አቅም ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ • መምህራን በተማሪዎቻችሁ፤ በወላጆችና በመላ ህዝቡ ልብ ውስጥ አሻራችሁ ለዘለዓለም ይኖራል፡፡ የመምህርነት ትልቁ ሽልማትም ይሄው ነው፡፡ • መምህር የሆነ ሁሉ በመምህርነቱ እንዲኮራ በጥረቱም በተማሪዎቹ ላይ በሚፈጥረው ብሩህ ነገ፤ሃገርን እንደሚገነባ ይታወቃል፡፡ • ከአለም ታሪክ እንደምንረዳው አሁን የበለፀጉ ሃገሮች የምንላቸው አሁን ወዳሉበት ደረጃ የደረሱት በትምህርት፤በሳይንስና ፈጠራ መንገድ ተጉዘው ነው፡፡ • አሁን በክልላችን የምናየው ጥሩውም ሆነ መጥፎው ነገር ያለፈው ትምህርት ስርዓታችን ውጤት ነው፡፡ ስለዚህ ለወደፊቱም ቢሆን የትምህርት ቅኝታችን ሁኔታን የሚቀይር ስጋቶችን ወደ እድል የሚያመጣ ሊሆን ይገባል፡፡ ለዚህም በጋራ የምንሰራ ይሆናል፡፡ • ከምንም በላይ የሰላም መኖር የሁሉም ነገሮች ቅድመ ሁኔታ ስለሆነ የክልላችን የትምህርት ማህበረሰብ ለክልላችን ሰላም ሊሰራ ይገባል፡፡ • በሰላም አለመኖር የክልላችን ትምህርት ክፉኛ ተጎድቷል፤በርካታ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ሆነዋል፤ትምህርት ቤቶች በግጭቱ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤የትምህርት ቤት ቁሳቁሶች ወድመዋል፡፡ ይሄ በጣም ያስቆጫል፡፡ • ትምህርት አለማዊ/ Secular/ በመሆኑ ከፖለቲካም ሆነ ከሃይማኖት ተፅዕኖ ነፃ ሆኖ እንዲቀጥል ሁላችንም የበኩላችንን ገንቢ ሚና በመጫዎች በመጭው የትምህርት ዘመን ህፃናት በነፃነት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ፤ነጋቸው እንዳይጨልም ወላጆች፤መምህራን፤ጠቅላላ ህዝባችንና፤የትምህርት ማህበረሰቡ የማይተካ ሚናችሁን እንድትጫወቱ ከወዲሁ ጥሪየን አስተላልፋለሁ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ #AmharaEducationBureau #ትምህርትለትውልድ

photo content

photo content
+9

"ባልተመቸ እና ባልተሟላ ሁኔታ ውስጥ ሆናችሁ ትውልድን ለመገንባት እያገለገላችሁ ለምትገኙ መምህራን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች እና ባለሙያዎች ሁሉ እናመሰግናለን።" አቶ ጥላሁን ወርቅነህ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ። ሰኔ 13/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ "መምህራን የነገ ትውልድ መሰረት ናቸው" በሚል መሪ ቃል የመምህራን ቀን እያከበረ ነው። በበዓሉ የተገኙት የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ ያደጉ ሀገራት የኢኮኖሚያቸው መዳበር፣ የፈጠራ ስራቸው እድገት እና የሰለጠነ ፖለቲካ እንዲኖራቸው ያስቻላቸው ትምህርት መሆኑን ገልጸዋል። የሀገር ዋነኛ የመወዳደሪያ አቅም የሚፈጥረውን ትምህርት እና መምህራንን ለመደገፍ መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ክረምት የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን አቅም ማሳዲጊያ ስልጠናዎች እንደሚቀጥሉ አመላክተዋል። ባልተመቸ እና ባልተሟላ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ትውልድን ለመገንባት እያገለገሉ ለሚገኙ መምህራን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች እና ባለሙያዎችን አመሰግነዋል። #ትምህርት #ባህር _ዳር_ከተማ #Amhara_Education_Bureau #ትምህርት_ለትውልድ

photo content
+1

photo content
+9

አዳዲስ ትምህርት ቤቶች ሲገነቡ  የአካባቢ እና ማህበራዊ ደህንነት መመሪያን መጠበቅ እንደሚገባ ተገለጸ።   ሰኔ 8/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ለአካባቢና ማህበራዊ ደህንነት ጉዳይ ባለሙያዎች  በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች የአካባቢ እና ማህበራዊ ደህንነት መመሪያን ማሟላት የሚገባቸውን ጉዳይ በተመለከተ በአራት ቀጠናዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡   የቢሮው በትምህርት ትራንስፎርሜሽን ትግበራ ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል /ኢቶል/ አስተባባሪ አቶ ካሳሁን እያዩ ትምህርት ቤቶች ሲገነቡ የአካባቢ እና ማህበራዊ ደህንነት መመሪያን መጠበቅ እንደሚገባቸው ገልጸዋል።   በአማራ ክልል በትምህርት ሚኒስቴር ፣ በክልሉ መንግስት እና ወረዳዎች መቀናጆ 308 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመገንባት ላይ ናቸው።   እነዚህ ግንባታዎች ለህጻናት ምቹ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጠቃሚ እና ከአለም ባንክ የአካባቢና ማህበራዊ መስፈርቶች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚገባው አቶ ካሳሁን አስገንዘበዋል፡፡   በአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በትምህርት ትራንስፎርሜሽን ትግበራ ፕሮጀክት የአካባቢና ማህበራዊ ደህንነት ባለሙያ አቶ ደባሱ ያየህ  በትምህርት ትራንስፎርሜሽን ትግበራ ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ፕሮግራም ውስጥ አካባቢና ማህበራዊ ጥበቃ ደህንነት ፕሮጀክቱ ሊፈጥር ከሚችለው አደጋ ህዝብን ለመጠበቅ፣ ፍትሃዊና ዘላቂ ውጤት ለማምጣት አስፈላጊ መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።   አዲስ የሚገነቡ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የአካባቢ እና ማህበራዊ ደህንነት የጠበቁ እንዲሆኑ ለማስቻል የህብረተሰብ ውይይት፣ የመለያ ቼክሊስት እና ሰርቲፊኬት ፣ የአካባቢ ማህበራዊ አስተዳደር እቅድ፣ የሰራተኞች ጤንነትና ደህንነት ማረጋገጥ የቆሻሻና ብክለት አወጋገድ ስርዓት ሊኖራቸው እንደሚገባ ገልጸዋል።   በስልጠናው የአካባቢ ጥበቃ፣ የሰራተኞች ጤና እና ደህንነት፣ የቆሻሻ አወጋገድ፣ የብዝሃ ህይወት ጥበቃ፣ የባህል ቅርስ ጥበቃ፣ የቅሬታ አፈታት ስርዓት እና የማህበረሰብ ተሳትፎ የመሳሰሉት ጉዳዮች በስፋት ተዳስሰዋል፡፡   #Education #ትምህርት_ለትውልድ #Amhara_Education_Bureau

photo content
+7

‎"የትምህርት ዘርፍ ኢንሸቲቮች ውጤታማ እንዲሆኑ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ንቁ ተሳትፎ ያስፈልጋል" ፦ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ‎ ሰኔ 5/2018(ትምህርት ቢሮ)‎የአብክመ ትምህርት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች እና በቢሮው የቀጣይ ወራት ተግባራት ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል። ‎ ‎ውይይቱን የመሩት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) ትምህርት ቀደም ብሎ ገጥሞት በነበረው ፈተና ከትምህርት ገበታ ርቀው የነበሩ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ለመመለስ በቀጣይ ክረምት ልዩ ዝግጅት ማድረግ ይገባል ብለዋል። አሁን ላይ ክልል አቀፍ ፈተናዎችን ለመስጠት ያለው ቅድመ ዝግጅት ጥሩ እንደሆነ የገለፁት ዶ/ር ሙሉነሽ የነገ የሀገርና ክልላችን ተስፋ የሆኑት ተማሪዎች ፈተናቸውን በሰላም እንዲያጠናቅቁ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ ነው ሲሉ ገልፀዋል። በትምህርት ዘርፍ ያሉ ኢንሸቲቮችን ለመተግበር እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ሲሉ አሳስበዋል። ‎በትምህርት ዘርፍ የተጀመሩትን የሪፎርም ስራዎችን ማጠናቀቅ፣የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ዝግጅት በጥራት ማቀድና ለባለድርሻ አካላት ማስተዋወቅ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። #AmharaEducationBureau #ትምህርትለትውልድ

photo content
+4

photo content
+9

በዋግህምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በ"ትምህርት ለትውልድ" ንቅናቄ በ2018 በጀት አመት በመንግስት፣ በህብረተሰቡ፣ አጋር ድርጅቶች ተሳትፎ ተገንብተው አገልግሎት የሚሰጡ የትምህርት ተቋማት በምስል‼️

photo content