ar
Feedback
Amhara Education Bureau

Amhara Education Bureau

الذهاب إلى القناة على Telegram

Quality Education

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Amhara Education Bureau

تُعد قناة Amhara Education Bureau (@anrse) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 33 807 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 627 في فئة التعليم والمرتبة 990 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 33 807 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 22 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 8 939، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 51.08‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.57‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 17 264 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 5 261 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 46.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Quality Education

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 24 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

33 807
المشتركون
+824 ساعات
+1657 أيام
+8 93930 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+2

photo content
+9

የተማሪዎች እና መምህራን የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ እና የጥናትና የምርምር ሲምፖዚየም እየተካሄደ ነው። ሰኔ 16/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የተማሪዎች እና መምህራን የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ እና የጥናትና የምርምር ሲምፖዚየም መካሄድ ጀምሯል። በመክፈቻው ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ ትልቅ ታሪክ ያላት የሰው ዘር መገኛ፣ የስልጣኔ ምንጭ የሆነችው ሀገራችን ዛሬም ብሩህ አእምሮ እና የተፍታታ እጅ ያላቸው ምሁራንን እየፈራች መሆኑን ገልጸዋል። የአድዋ ልጆች ከአባቶቻችን ዘመን የላቁ የፈጠራ ስራዎችን በመጠቀም ሀገራችን በዓለም አደባባይ ከፍ ለማድረግ መስራት ይገባል ብለዋል። ፈጠራ ከአካባቢያችን ከምናያቸው ትንንሽ ነገሮች የሚነሳ መሆኑን የገለጹት ሀላፊዋ የፈጠራ ዝንባሌና ሀሳብ ያላቸውን ልጆች ማበረታታትና መደገፍ ይገባል ብለዋል። ሀገራችን በየዘርፉ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት የፈጠራ ስራ፣ የጥናት እና ምርምር ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል። የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ እና የጥናትና የምርምር ሲምፖዚየሙ በትምህርት ዘርፍ የተከናወኑ ፈጠራዎችን ለማበረታታት፣ ጥናት እና ምርምሮችን ለማሳዬት፣ ልምዶችን ለመለዋወጥ፣ የተገኙ ውጤቶችን ለማጋራት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። አውደ ርዕዩ በክልሉ ውስጥ ያሉ የፈጠራ ስራዎችና የምርምር ውጤቶችን ማስተዋወቅ፣ የጋራ ትብብርን ለማጠናከርና በትምህርት ጥራት ላይ ሁለንተናዊ እድገት ለማምጣት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል። የሳይንስ የምርምርና የፈጠራ ስራ በክልሉ የ25 ዓመት የእድገትና ዘላቂ ልማት እቅድ፣ በ5 አመት ስትራቴጅክ እቅድ ትልቅ ትኩረት እንደተሰጠው አመላክተዋል። የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የሳይንስ የምርምርና የፈጠራ አቅሞችን ለማስተባበር፣ ለመደገፍና ለመጠቀም ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። በአውደ ርዕዩ ከየዞኖች እና ከተማ አስተዳደሮች የተመረጡ የተማሪዎች እና የመምህራን የፈጠራ ስራዎች ለእይታ ቀርበው በክብር እንግዶች እና በታዳሚዎች ተጎብኝተዋል። የፈጠራ ስራ አውደርዕይ እና ጥናትና ምርምር ሲፖዚየሙ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሰኔ 18/ 2108 ዓ.ም ድረስ የሚቀጥል ይሆናል። #AmharaEducationBureau #ትምህርትለትውልድ #Reasearch #Inovation #Creativity

photo content
+4

photo content
+9

ከ73 ሽህ በላይ ለሚሆኑ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የአይን ጤና ምርመራ ተደረገ። ሰኔ 14/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ ፓርትነርስ ኢን ኢዱኬሽን ኢትዮጵያ ከክሊንተን ሄልዝ አክሰስ ኢንሼቲቭ /CHAI/ ጋር በመተባበር ለሁለት ወራት ሲካሄድ የቆየውን የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የአይን ጤና ምርመራ ዘመቻ ማጠቃላያ መርሃ ግብር አካሂዷል። ለሁለት ወራት በተካሄደው በባህር ዳር፣ ጎንደር እና ደብረ ብርሃን ከተሞች ላይ የሚገኙ እድሜያቸው ከ3 እስከ 6 አመት የሆኑ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የአይን ምርመራ ዘመቻ 73 ሽህ 336 ህጻናት መመርመራቸውን የፓርትነርስ ኢን ኢዱኬሽን ኢትዮጵያ የአማራ ክልል አስተባባሪ አቶ አብዮት አሸናፊ ተናግረዋል። በምርመራ ሂደቱ የተለዩ የአይን ችግር የተገኘባቸውን ህጻናት ህክምና እንዲያገኙ መደረጉን አመላክተዋል። በተካሄደው የምርመራ ዘመቻ ማህበረሰቡ በአይን ጤና ላይ ያለውን ግንዛቤ ያሳደገ እንደነበር ተገልጿል። በማጠቃላያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ በርካታ ተማሪዎች በአይን ጤና ችግር ምክንያት ትምህርታቸው በአግባቡ ለመከታተል እንደሚቸገሩ ገልጸዋል። ፓርትነርስ ኢን ኢዱኬሽን ኢትዮጵያ ከክሊንተን ሄልዝ አክሰስ ኢንሼቲቭ /CHAI/ ጋር በመተባበር ያደረጉት ዘመቻ የበርካታ ተማሪዎችን ችግር በመለየት ህክምና እንዲያገኙ በማስቻላቸው አመሰግነዋል። በተደረገው የአይን ምርመራ የተገኙ ውጤቶች በተማሪዎች የአይን ህክምና ላይ የበለጠ መስራት እንደሚገባ ያመላከተ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ኦፕቶሜትሪ ማህበር የአማራ ክልል ተወካይ ዮሴፍ አንተሁን የህጻናት የአይን ጤና ጉዳይ ትኩረት የሚፈልግ መሆኑን ገልጸዋል። የማህበሩ አባላት በምርመራ ዘመቻው ትልቅ ተሳትፎ ማድረጋቸውን አመላክተዋል። ባለሙያዎች የተማሩትን ትምህርት ወደ ተግባር በመቀየር ለታካሚዎች ህክምና ለመስጠት የህክምና መሳሪያዎች እጥረትን ለመቅረፍ ፓርትነርስ ኢን ኢዱኬሽን ኢትዮጵያ ላደረገላቸው እገዛ አመስግነዋል። ወደፊት ከድርጅቱ ጋር በትብብር እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል። #AmharaEducationBureau #ትምህርትለትውልድ

photo content
+7

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ በባህርዳር ከተማ አስተዳደር የመምህራን ቀን አከባባር ላይ ተገኝተው ያስተላለፉት ሙሉ መልዕክት *** • ትምህርት ለአንድ ሃገር ዋነኛው የመወዳደሪያ አቅም ነው፡፡ በትምህርት ገፍተው የሄዱ ሃገራት ኢኮኖሚያቸው ያደገና በፈጠራ የተደገፈ ነው፤ፖለቲካቸው የሰለጠነ ፤የኑሮ ዘይቤያቸው ቀላልና ምቹ ነው፡፡ የደቡብ አፍሪካው ታላቁ የቀድሞ መሪ ኔልሰን ማንዴላ እንዳሉት ትምህርት አለምን ለመለወጥ የምንጠቀምበት በጣም ሃይለኛ መሳሪያ ነው ብለዋል፡፡ ይሄ ሃይለኛ መሳሪያ ደግሞ ባለቤትነቱ የናንተ መምህራን ነው፡፡ በዚህ ልትኮሩ ይገባል ብለዋል፡፡ • መምህራንና የትምህርት አመራሮች ባላተመቸና ባልተሟላ ሁኔታ ውስጥም ሆናችሁ ለትውልድ ግንባታ ለምታበረክቱት አስተዋፅኦ የክልሉ መንግስትና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ታላቅ አድናቆትና ክብር አለው ብለዋል፡፡ • የመምህርነት ሙያ ከፍ የሚለውና ወደ ቀደመ ክብሩ የሚመለሰው እኛ መምህራን በምንሰራው ስራና በትውልድ ግንባታ ላይ በምንፈጥረው በጎ ተፅዕኖ ነው፡፡ በመንግስት በኩል በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ትምህርትንና መምህርነትን ለመደገፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት በጎ ጥረቶች ተጀምረዋል፤የበለጠ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ • እንደ ሃገርም ሆነ እንደ ክልል መጭው ጊዜ ለትምህርትና ለመምህርነት ብሩህና የተሻለ እንደሚሆን እርግጠኞች ነን፡፡ • የመምህራንና የት/ቤት አመራሮችን በትርፍ ጊዜያቸው በተለይ በክረምት ከቅርብ አመታት ወዲህ የተጀመረው በሞያቸው የማሰልጠንና የማብቃት ስራ በዚህ ክረምትም በክልላችን አቅም ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ • መምህራን በተማሪዎቻችሁ፤ በወላጆችና በመላ ህዝቡ ልብ ውስጥ አሻራችሁ ለዘለዓለም ይኖራል፡፡ የመምህርነት ትልቁ ሽልማትም ይሄው ነው፡፡ • መምህር የሆነ ሁሉ በመምህርነቱ እንዲኮራ በጥረቱም በተማሪዎቹ ላይ በሚፈጥረው ብሩህ ነገ፤ሃገርን እንደሚገነባ ይታወቃል፡፡ • ከአለም ታሪክ እንደምንረዳው አሁን የበለፀጉ ሃገሮች የምንላቸው አሁን ወዳሉበት ደረጃ የደረሱት በትምህርት፤በሳይንስና ፈጠራ መንገድ ተጉዘው ነው፡፡ • አሁን በክልላችን የምናየው ጥሩውም ሆነ መጥፎው ነገር ያለፈው ትምህርት ስርዓታችን ውጤት ነው፡፡ ስለዚህ ለወደፊቱም ቢሆን የትምህርት ቅኝታችን ሁኔታን የሚቀይር ስጋቶችን ወደ እድል የሚያመጣ ሊሆን ይገባል፡፡ ለዚህም በጋራ የምንሰራ ይሆናል፡፡ • ከምንም በላይ የሰላም መኖር የሁሉም ነገሮች ቅድመ ሁኔታ ስለሆነ የክልላችን የትምህርት ማህበረሰብ ለክልላችን ሰላም ሊሰራ ይገባል፡፡ • በሰላም አለመኖር የክልላችን ትምህርት ክፉኛ ተጎድቷል፤በርካታ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ሆነዋል፤ትምህርት ቤቶች በግጭቱ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤የትምህርት ቤት ቁሳቁሶች ወድመዋል፡፡ ይሄ በጣም ያስቆጫል፡፡ • ትምህርት አለማዊ/ Secular/ በመሆኑ ከፖለቲካም ሆነ ከሃይማኖት ተፅዕኖ ነፃ ሆኖ እንዲቀጥል ሁላችንም የበኩላችንን ገንቢ ሚና በመጫዎች በመጭው የትምህርት ዘመን ህፃናት በነፃነት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ፤ነጋቸው እንዳይጨልም ወላጆች፤መምህራን፤ጠቅላላ ህዝባችንና፤የትምህርት ማህበረሰቡ የማይተካ ሚናችሁን እንድትጫወቱ ከወዲሁ ጥሪየን አስተላልፋለሁ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ #AmharaEducationBureau #ትምህርትለትውልድ

photo content

photo content
+9

"ባልተመቸ እና ባልተሟላ ሁኔታ ውስጥ ሆናችሁ ትውልድን ለመገንባት እያገለገላችሁ ለምትገኙ መምህራን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች እና ባለሙያዎች ሁሉ እናመሰግናለን።" አቶ ጥላሁን ወርቅነህ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ። ሰኔ 13/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ "መምህራን የነገ ትውልድ መሰረት ናቸው" በሚል መሪ ቃል የመምህራን ቀን እያከበረ ነው። በበዓሉ የተገኙት የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ ያደጉ ሀገራት የኢኮኖሚያቸው መዳበር፣ የፈጠራ ስራቸው እድገት እና የሰለጠነ ፖለቲካ እንዲኖራቸው ያስቻላቸው ትምህርት መሆኑን ገልጸዋል። የሀገር ዋነኛ የመወዳደሪያ አቅም የሚፈጥረውን ትምህርት እና መምህራንን ለመደገፍ መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ክረምት የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን አቅም ማሳዲጊያ ስልጠናዎች እንደሚቀጥሉ አመላክተዋል። ባልተመቸ እና ባልተሟላ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ትውልድን ለመገንባት እያገለገሉ ለሚገኙ መምህራን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች እና ባለሙያዎችን አመሰግነዋል። #ትምህርት #ባህር _ዳር_ከተማ #Amhara_Education_Bureau #ትምህርት_ለትውልድ

photo content
+1

photo content
+9

አዳዲስ ትምህርት ቤቶች ሲገነቡ  የአካባቢ እና ማህበራዊ ደህንነት መመሪያን መጠበቅ እንደሚገባ ተገለጸ።   ሰኔ 8/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ለአካባቢና ማህበራዊ ደህንነት ጉዳይ ባለሙያዎች  በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች የአካባቢ እና ማህበራዊ ደህንነት መመሪያን ማሟላት የሚገባቸውን ጉዳይ በተመለከተ በአራት ቀጠናዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡   የቢሮው በትምህርት ትራንስፎርሜሽን ትግበራ ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል /ኢቶል/ አስተባባሪ አቶ ካሳሁን እያዩ ትምህርት ቤቶች ሲገነቡ የአካባቢ እና ማህበራዊ ደህንነት መመሪያን መጠበቅ እንደሚገባቸው ገልጸዋል።   በአማራ ክልል በትምህርት ሚኒስቴር ፣ በክልሉ መንግስት እና ወረዳዎች መቀናጆ 308 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመገንባት ላይ ናቸው።   እነዚህ ግንባታዎች ለህጻናት ምቹ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጠቃሚ እና ከአለም ባንክ የአካባቢና ማህበራዊ መስፈርቶች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚገባው አቶ ካሳሁን አስገንዘበዋል፡፡   በአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በትምህርት ትራንስፎርሜሽን ትግበራ ፕሮጀክት የአካባቢና ማህበራዊ ደህንነት ባለሙያ አቶ ደባሱ ያየህ  በትምህርት ትራንስፎርሜሽን ትግበራ ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ፕሮግራም ውስጥ አካባቢና ማህበራዊ ጥበቃ ደህንነት ፕሮጀክቱ ሊፈጥር ከሚችለው አደጋ ህዝብን ለመጠበቅ፣ ፍትሃዊና ዘላቂ ውጤት ለማምጣት አስፈላጊ መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።   አዲስ የሚገነቡ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የአካባቢ እና ማህበራዊ ደህንነት የጠበቁ እንዲሆኑ ለማስቻል የህብረተሰብ ውይይት፣ የመለያ ቼክሊስት እና ሰርቲፊኬት ፣ የአካባቢ ማህበራዊ አስተዳደር እቅድ፣ የሰራተኞች ጤንነትና ደህንነት ማረጋገጥ የቆሻሻና ብክለት አወጋገድ ስርዓት ሊኖራቸው እንደሚገባ ገልጸዋል።   በስልጠናው የአካባቢ ጥበቃ፣ የሰራተኞች ጤና እና ደህንነት፣ የቆሻሻ አወጋገድ፣ የብዝሃ ህይወት ጥበቃ፣ የባህል ቅርስ ጥበቃ፣ የቅሬታ አፈታት ስርዓት እና የማህበረሰብ ተሳትፎ የመሳሰሉት ጉዳዮች በስፋት ተዳስሰዋል፡፡   #Education #ትምህርት_ለትውልድ #Amhara_Education_Bureau

photo content
+7

‎"የትምህርት ዘርፍ ኢንሸቲቮች ውጤታማ እንዲሆኑ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ንቁ ተሳትፎ ያስፈልጋል" ፦ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ‎ ሰኔ 5/2018(ትምህርት ቢሮ)‎የአብክመ ትምህርት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች እና በቢሮው የቀጣይ ወራት ተግባራት ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል። ‎ ‎ውይይቱን የመሩት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) ትምህርት ቀደም ብሎ ገጥሞት በነበረው ፈተና ከትምህርት ገበታ ርቀው የነበሩ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ለመመለስ በቀጣይ ክረምት ልዩ ዝግጅት ማድረግ ይገባል ብለዋል። አሁን ላይ ክልል አቀፍ ፈተናዎችን ለመስጠት ያለው ቅድመ ዝግጅት ጥሩ እንደሆነ የገለፁት ዶ/ር ሙሉነሽ የነገ የሀገርና ክልላችን ተስፋ የሆኑት ተማሪዎች ፈተናቸውን በሰላም እንዲያጠናቅቁ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ ነው ሲሉ ገልፀዋል። በትምህርት ዘርፍ ያሉ ኢንሸቲቮችን ለመተግበር እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ሲሉ አሳስበዋል። ‎በትምህርት ዘርፍ የተጀመሩትን የሪፎርም ስራዎችን ማጠናቀቅ፣የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ዝግጅት በጥራት ማቀድና ለባለድርሻ አካላት ማስተዋወቅ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። #AmharaEducationBureau #ትምህርትለትውልድ

photo content
+4

photo content
+9

በዋግህምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በ"ትምህርት ለትውልድ" ንቅናቄ በ2018 በጀት አመት በመንግስት፣ በህብረተሰቡ፣ አጋር ድርጅቶች ተሳትፎ ተገንብተው አገልግሎት የሚሰጡ የትምህርት ተቋማት በምስል‼️

photo content