ru
Feedback
Amhara Education Bureau

Amhara Education Bureau

Открыть в Telegram

Quality Education

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Amhara Education Bureau

Канал Amhara Education Bureau (@anrse) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 39 413 подписчиков, занимая 4 655 место в категории Образование и 870 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 39 413 подписчиков.

Согласно последним данным от 01 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 3 314, а за последние 24 часа — 42, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 36.11%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.06% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 14 230 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 5 937 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 27.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
Quality Education

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 02 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Образование.

39 413
Подписчики
+4224 часа
+767 дней
+3 31430 дней
Архив постов
"የአንድ ተማሪ ህይወት የሙሉ ቤተሰብ ህይወት ነው" ዶ/ር መሉነሽ ደሴ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ
"የአንድ ተማሪ ህይወት የሙሉ ቤተሰብ ህይወት ነው" ዶ/ር መሉነሽ ደሴ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ

photo content
+9

photo content

"ጠንካራ አፈጻጸም ያላቸውን ተቋማት በማበረታታት ክፍተት ያለባቸውን በመደገፍ ወደ ተቀራራቢ አፈጻጸም እንዲመጡ እየተሰራ ነው።" ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ። ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የአማራ ክልል ማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች እየገመገመ ነው። በግምገማ መድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ /ዶክተር/ በክልሉ ሰላም እና ልማትን ለማረጋገጥ ጉልህ ተግባራት መከወናቸውን ተናግረዋል። የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት እስከታችኛው መዋቅር ድረስ እየተከናወኑ ያሉ ቅንጅታዊ ተግባራት በሱፐርቪዥን ቡድን የድጋፍ እና ክትትል ስራዎች መከናወኑን ገልጸዋል። ድጋፍና ክትትሉ በትምህርት፣ በጤና ፣ በሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ በሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ መካሄዱ ተገልጿል። በተደረገው ድጋፍ እና ክትትል በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች እና በመንግስት የታቀዱ ኢኒሸቲቮች በመልካም አፈጻጸም ላይ እንደሚገኙ አመላክተዋል። የክላስተሩ ተቋማት በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ቤት የሚደርሱ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊዋ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለማሻሻል እየሰሩ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የማህበራዊ ክላስተር ዘርፍ ተቋማት እርስ በእርስ ተሞክሮዎችን እንዲለዋወጡ እንዲማማሩ ቅንጅታዊ አሰራሮችን እንዲያሳድጉ ተከታታይ ድጋፎች ይደረጋሉ ብለዋል። ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ 1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/ 2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w 3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau 4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse ያግኙን             ‎ ‎

የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ተመሳሳይ ውጤት ያስመዘገቡት መንትዮች‼️ ========= ነሐሴ 24/2018(ትምህርት ቢሮ)በአማራ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 15.56%ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ማምጣታቸው ይታወቃል። ከተመዘገበው ውጤት በተጨማሪ የባህርዳር ከተማ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሁለት መንትዮች ተመሳሳይ ውጤት ማስመዝገባቸው አስደናቂ ክስተት ሆኗል። ተማሪ በዕምነት መልካሙ እና ዮርዳኖስ መልካሙ የሚባሉ መንትዮች በባህርዳር ከተማ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ወስደው ሁለቱም ተመሳሳይ 413 ከ600 ውጤት ማስመዝገባቸው ብዙዎችን አስገርሟል። በዚህ ዙሪያ የዘርፉ የስነልቦና ባለሙያዎች አስተያየት ስጡበት‼️ #AmharaEducation #ትምህርትለትውልድ ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ 📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/ 📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w 📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau 📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse ያግኙን 📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau 📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau

photo content
+1

photo content
+8

ከ88 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባው የአጆ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተጠናቆ ርክክብ ተካሄደ ። በሰሜን ወሎ ዞን ሃብሩ ወረዳ በከተማና መሰረተ መሰረተልማት ሚኒስቴር የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ኘሮጀክት ከ88 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባው የአጆ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተጠናቆ የዞኑ የስራ ኀላፊዎች በተገኙበት ርክክብ ተካሂዷል። የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ሰጠ ታደሰ እንዳሉት፣ ትምህርት ቤቱ ሁለት መማሪያ ክፍሎችን ጨምሮ ዘጠኝ ብሎኮች አሉት ። በሁለት ፈረቃ እስከ አንድ ሺህ ተማሪዎችን ለማስተማር እንደሚያስችልም ገልፀዋል። ትምህርት ቤቱ በጃራ የስደተኞች ካምኘ ላሉ ታዳጊዎች መጋቢ ሆኖ ያገለግላልም ብለዋል። በርክክብ ሂደቱ ላይ የተገኙት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዱባለ አብራሬ፣ የሰሜን ወሎ ዞንን የትምህርት ሽፋን ከፍ ለማድረግና የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ቀደም ሲል ከተማ አስተዳደሩ በጉባላፍቶ ወረዳ ሁለት ትምህርት ቤቶችን ገንብቶ ለዞኑ አስተዳደር ማስረከቡን አስታውሰዋል። የአጆ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተፈናቃይ ወገኖች መጋቢ በመሆኑ ከተማ አስተዳደሩ በግንባታው ሂደት የበኩሉን ድርሻ ተወጥቷልም ነው ያሉት። ህብረተሰቡ ትምህርት ቤቱን እንዲጠብቅና እንዲንከባከብም አሳስበዋል። የሰሜን ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ገበያ ልማት መምሪያ ኀላፊ ታምራት ንጋቱ በበኩላቸው፣ ትምህርት ቤቱ ደረጃውን ጠብቆ ተገንብቶ መረከባቸውን አውስተዋል። ለ2019 የትምህርት ዘመን ማስጀመሪያ በቂ ግበዓት መኖሩን ጠቅሰው፣ ተጨማሪ የትምህርት ቁሳቁስ ለማሟላት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ዞን አስተዳደሩ መክሮ የመማሪያ ወንበር፣ ጥቁር ሰሌዳ፣ የቤተሙከራ፣ የቤተመጻህፍትና የአይሲቲ ማዕከሉን ሙሉ ለማድረግ እንደሚሰራም አስረድተዋል። የአካባቢው ሀገር ሽማግሌ ሸህ ሀሰን ከረሙ የትምህርት ቤቱ መገንባት የአካባቢው ወጣቶች አመለካከት በመለወጥ የህገወጥ ስደት ሰለባ ከመሆን ይታደጋል ሲሉ አስተያየታቸውን ለአሚኮ ተሰጥተዋል። አሚኮ #ደሴ #አሚኮ #ዜና #ሰሜን_ወሎ #ትምህርት #ወልድያ

photo content
+6

photo content
+9

ዓባይ ባንክ በትምህርት ቁሳቁስ ችግር ምክንያት መማር ለሚቸገሩ ተማሪዎች 50 ሺህ የመማሪያ ደብተሮችን ድጋፍ አደረገ። ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ ዓባይ ባንክ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እና የትምህርት ዘርፉን ከማሳደግ አኳያ በኢኮኖሚ ጫና ምክንያት ለልጆቻቸው የትምህርት ቁሳቁስ ማሟላት ለማይችሉ ወላጆች እና ልጆች ከትምሕርት ገበታቸው እንዳይቀሩ የሚያግዝ የ50,000 ባለ50 ገጽ ደብተሮችን ለአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስረክቧል፡፡ ድጋፉ በክልሉ በተለያየ ምክንያት ትምህርታቸውን መከታተል እየፈለጉ በቁሳቁስ ዕጥረት ለተቸገሩ ተማሪዎች በፍትሐዊነት ለሁሉም ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች የሚሰራጭ ነው። የትምሕርት ቁሳቁስ ድጋፉ በአማራ ክልል መማር እየፈለጉ በአቅም ማነስ እና በሌሎች ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ችግሮች ምክንያት እገዛ ማግኘት ላልቻሉ ተማሪዋች በባንኩ መለያ በልዩ ህትመት የተዘጋጁ ደብተሮች ናቸው። ርክክቡ ዛሬ ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በባሕርዳር ከተማ ሲካሄድ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መኳንንት አደመ ባደረጉት ንግግር፣ “የክልሉን የትምሕርት ስትራቴጂ ከማሳካት አኳያ እንደ ዓባይ ባንክ ያሉ አጋሮች የተቀናጀ ኢንቨስትመንት ከማካሄድ ባሻገር የማኅበራዊ ልማት ላይ በንቃት መሳተፍ ድርሻው ከፍ ያለ ነው” ብለዋል። ሀገራዊ የትምህርት ዘርፋን ለማሳደግ እና የተማሪዎችን ውጤታማነት ከፍ ለማድረግ ከሚደረገው እንቅስቃሴ ጎን ለጎን እንደ ዓባይ ባንክ ያሉ ቀዳሚ የልማት እና የፋይናንስ አጋሮች የሚያደርጉት ድጋፍ ለሌሎችም ምሣሌ የሚሆን ነው ተብሏል። ኃላፊው በክልሉ የትምህርት ዘርፍ የመሠረተ-ልማት እና የግብዓት እጥረቶችን ለመፍታት በሚያደርገው ጥረት የፋይናንስ ተቋማት እገዛ ወሳኝ መሆኑን ገልፀው፣ የዓባይ ባንክ የመማሪያ ደብተር ድጋፍም በከልሉ የተማሪዎችን የማቋረጥ ምጣኔን ለመቀነስ ለሚደረገው ጥረት ትልቅ ዐቅም ይኖረዋል ብለዋል። ድጋፋ በትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ እጥረት ወደ ትምህርት ገበታ መሄድ ያልቻሉ የክልሉ ተማሪዋችን ችግር ለመቅረፍ እና “በዚህ ችግር ወደ ትምህርት ገበታቸው ያልመጡ ተማሪዋችን ተስፋ የሚያለመልም ነው” በማለት ምስጋናቸውን ለባንኩ አቅርበዋል፡፡ የዓባይ ባንክ ስትራቴጂ ዋና መኮንን አቶ ወንድይፍራው ታደሰ ባንኩ የማኅበራዊ ልማት ዘርፉን ከማሳደግ አኳያ እያከናወነ ያለውን ድጋፍ አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል። ዓባይ ባንክ “በእያንዳንዱ የማኅበረሰብ ጎጆ ገብቶ ቀዳሚ የፋይናንስ አጋር የመሆን ፍኖት እና በቀጣዩ ትውልድ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ ዕውቀት-መር የኢንቨስትመንት አስተሳሰብ መገንባት” እየተተገበረ ያለ አቅጣጫ መሆኑን አሳውቀዋል። ባንኩ በተለያዩ ዘርፍች ማኅበረሰቡን የሚጠቅሙ እና የማህበራዊ ኃለፊነት የመወጣት ዕቅዱ አካል የሆኑ ድጋፎችን በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ለሚገኙ ተቋማት እና ዜጎች ሲያደርግ መቆየቱንም አውስተዋል። ዓባይ ባንክ በፋይናንሱ ዘርፍ ለብዙዎች የታላቅነት ምንጭ ከመሆን ባሻገር የኮርፖሬት ማኅበራዊ ኃላፊነትን እንደ ቁልፍ ስትራቴጂያዊ የማኅበረሰብ አጋርነት እና ተቋማዊ ትሥሥር ዓላማ የሚያውል መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ዓባይ ባንክ አሁን ላይ ካደረገው የትምህርት ግብዓት ድጋፍ ባሻገር በጥቅል የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ከ4.8 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ደንበኞቹ ሰፊ የዲጂታል የባንክ አገልግሎቶች በማቅረብ ግንባር ቀደም የፋይናንስ አጋር በመሆን እየሠራ መሆኑ ተጠቅሷል። ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ 1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/ 2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w 3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau 4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse ያግኙን             ‎ ‎

photo content
+9

ከ54 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት የመለሰው የበጎ ፈቃድ ሥራ። በደቡብ ጎንደር ዞን በተካሄደው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ51 ሺህ በላይ ዜጎች በማዕድ ማጋራት ተጠቃሚ ኾነዋል። "ለአንድ ተማሪ አንድ ደርዘን ደብተር" በሚል መሪ መልዕክትም ከ54 ሺህ በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል። የደቡብ ጎንደር ዞን ሴቶች፣ ወጣቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኀላፊ አንጓች ፋሲካው እንደገለጹት ይህ ስኬት በዞኑ በሚገኙ መምሪያዎች እና ተጠሪ ጽሕፈት ቤቶች የጋራ ርብርብ የተገኘ ነው። የበጎ ፈቃድ ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የደቡብ ጎንደር ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ መንበር ክፈተው ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች ቀድሞ መድረስ ለትውልድ የሚተርፍ ተግባር መኾኑን ጠቅሰዋል። የማኅበራዊ አገልግሎት ሥራዎችም በደም ልገሳ እና በቤት እድሳት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነው የጠቆሙት። በተደረገው ድጋፍ ከተጠቀሙ ወገኖች መካከል የሦሥት ልጆች እናት ወይዘሮ ደማም ተሾመ የተደረገላቸው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ልጆቻቸውን ከጎዳና ሕይወት ታድጎ በነጻነት እንዲማሩ ማድረጉን ገልጸዋል። የ7ኛ ክፍል ተማሪዋ ዳሳሽ ምሥጋናው የተደረገላት ድጋፍ ከጓደኞቿ ጋር እኩል እንድትሰለፍ የሞራል ስንቅ እንደኾናት እና ጠንክራ በመማር ዶክተር የመኾን ራዕይ እንድትሰንቅ እንዳስቻላት ተናግራለች። ነሐሴ 18/2018 አሚኮ

"እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል" አቶ ጥላሁን ወርቅነህ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ
"እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል" አቶ ጥላሁን ወርቅነህ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ

የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን እቅድ ትውውቅ መድረክ እያካሄደ ነው የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን አፈጻጸምን ለመገምገምና የ2019 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ዕቅድን ለማስተዋወቅ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በሰቆጣ ከተማ ውይይት እያካሄደ ነው። በመድረኩ የአለፈው የትምህርት ዘመን አፈጻጸም፣ የ2019 ዓ.ም. የተማሪዎች ምዝገባ ሁኔታ እና በቀጣዩ የትምህርት ዘመን ትምህርትን በተሻለ ሁኔታ ለማስፋፋት የሚያስፈልጉ ተግባራት በዝርዝር እንደሚመከር ተመላክቷል። የትምህርት መምሪያው ኃላፊ አቶ ሰይፉ ሞገስ፣ ለ2019 ዓ.ም. አዲሱ የትምህርት ዘመን ተማሪዎች ምዝገባን በተሳካ ሁኔታ ማከናወንና ተማሪዎች በወቅቱ ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመዘገቡ ማድረግ ትኩረት የሚሻ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በተያያዘም የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክትል አስተዳዳሪና የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሀላፊ አቶ ሹመት ጥላሁን በፕሮግራሙ ማስጀመሪያ እንደተናገሩት የትውልድ ግንባታ ላይ የትምህርት ሚና የላቀ መሆኑን ገልፀዋል። በመድረኩ በአለፈው ዓመት የተከናወኑ ስራዎችን በመገምገም ለቀጣይ ስራዎች ስኬታማነት መሠረት የሚጥልበት መሆኑን አክለዋል። በተለይም ባለፈው የበጀት ዓመት የታዩ ጥንካሬዎችን ማስቀጠል፣ የትምህርት ተደራሽነትን ማረጋገጥና ወደ 2019 ዓ.ም. ሊሸጋገሩ የማይገባቸውን እጥረቶች ከወዲሁ ማረም እንደሚገባ ባለድርሻ አካላት በትኩርት እንዲወያዩ አፅንኦት ሰጥተዋል። በተማሪዎች ምዝገባ ረገድም መሻሻል የሚያስፈልጋቸው ሁኔታዎች መኖራቸው አቶ ሹመት ተናግረዋል። በአለፈው አመት ከመማር ዕድሜያቸው ደርሰው መመዝገብ ከነበረባቸው ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ተማሪዎች 14 በመቶ ያህሉ አለመመዝገባቸው ጠቁመዋል፡፡ ከ9ኛ እስከ12ኛ ክፍል ተማሪዎች አኳያም በትምህርት ገበታ መግባትና መመዝገብ ጋር ተያይዞ 54 በመቶ የሚሆኑት ከትምህርት ገበታ ውጭ እንደነበሩ አቶ ሹመት አስረድተዋል። በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ የእቅድና በጀት ዝግጅት ቡድን መሪ በዲያቆን ስዩም አጠቃላይ ሪፖርት እየቀረበ ይገኛል። ነሐሴ 18/2018 መረጃው የዋግ-ኽምራ ኮሙኒኬሽን ነው

photo content
+5

photo content

photo content

በ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና የአማራ ክልል ከክልሎች መካከል ቀዳሚ መሆኑ ተገለፀ። ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ነሐሴ 16/2018(ትምህርት ቢሮ)በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 70ሺህ 544 ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ማስመዝገባቸውን የትምህርት ሚኒስቴሩ የተከበሩ ፕሮፌሰር ብርሐኑ ነጋ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አብራርተዋል። አዲስ አበባ 32.3 በመቶ በማሳለፍ የተሻለ መሆኑን የገለፁት ሚኒስተሩ የአማራ ክልል ደግሞ ከድሬድዋ ቀጥሎ 15.56 በማሳለፍ ከክልሎች ቀዳሚ መሆኑን ገልፀዋል። በክልሉ የተመዘገበው ውጤትም ከአገራዊ አማካይ በላይ መሆኑን ተገልጿል። የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮም ለተመዘገበው ውጤት ለክልሉ የትምህርት ባለድርሻ አካላት በሙሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል። ይህ ውጤት የተመዘገበው ባለፉት ሁለትና ሶስት አመታት የክልሉ ትምህርት በፈተና ውስጥ ሆኖ የተመዘገበ በመሆኑ ለቀጣይ የትምህርት ስራ ትልቅ መነቃቃት እንደሚፈጥር ነው የተገለፀው። ያም ሆኖ የተመዘገበው ውጤት የክልሉ ትምህርት በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ሆኖ የተመዘገበ በመሆኑ ለመላው የክልላችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እንወዳለን። የክልላችን ሰላም ቢረጋገጥና ሙሉ ትምህርትቤቶቻችን ተከፍተው ተማሪዎችን ማስተማር ብንችል ከዚህ የላቀ ውጤት ማምጣት እንደምንችል ትልቅ ማሳያ ነው። ይህ ውጤት ለቀጣይ 2019 የትምህርት ዘመን መስፈንጠሪያ በመውሰድ ሁሉም ትምህርት ቤቶቻችን ተከፍ።ው ሁሉም ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ነባርና አዲስ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ማህበረሰባችን ርብርብ እንዲያደርግ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ይህ ውጤት እንዲመዘገብ ሌት ተቀን የሰራችሁ መምህራን፣ የትምህርት አመራሮች፣ በፈተና ሳትበገሩ ዓላማችሁን ለማሳካት የተጋችሁ እንቁ ተማሪዎቻችን፣ የተማሪ ወላጆች፣ ፈተና የማይበግረው የትምህርት ስርዓት ለመገንባት ሌት ተቀን እየደገፋችሁን ያላችሁ ከፍተኛ የክልላችን አመራሮች ለተመዘገበው ውጤት በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ። የአማራ ክልል ትምህርት በፈተናዎች ውስጥ እያለፈ ቢሆንም ፈተናዎችን ተቋቁሞ ውጤት ከማስመዝገብ የሚያቆመው መሰናክል እንደሌለ የተመዘገበው ውጤት ማሳያ ነው። ከተባበርን፣ ከተደጋገፍን፣ የትምህርት ፋይዳ ከተረዳንና፣ ትምህርት የትውልድ መቅረጫ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን ከተረዳን የማናስመዘግበው ውጤት፣ የማናልፈው ፈተና አይኖርም። በውጤት ደረጃም 583 ውጤት በማምጣት በአማራ ክልል ሁለተኛው ከፍተኛ ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል። ፈተናውን ከወሰዱ ሴት ተፈታኞች መካከል 583 ውጤት በማስመዝገብ የክልላችን ተማሪ ህዳሴ ዘመኑ ከአገው ምድር ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአገር አቀፍ ደረጃ ከሴቶች ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች። ይህም በትምህርት ፍትሐዊነት፣ ጥራት ላይ እያደረግነው ላለው ሁለንተናዊ ስራ ማሳያ ነው። ሌላው በክልላችን ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች መካከል ስምንት ትምህርት ቤቶች ሙሉ ለሙሉ ተማሪዎቻቸውን አሳልፈዋል። የእነዚህን ትምህርት ቤቶች ቁጥር ለማሳደግ በቀጣይ ተግተን እንሰራለን። 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከቀጣይ ሰኞ ጀምሮ ማወቅ እንደሚችሉ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። #AmharaEducationBureau #AmharaEducation #ትምህርትለትውልድ#በጎነትለኢትዮጵያከፍታ#አንድደርዘንደብተርለአንድተማሪ ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ 📌 በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/ 📌 በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w 📌 በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau 📌 በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse ያግኙን 📌 በቲክቶክ ገፃችን @amharaeducation bureau 📌 X ገፃችን@amharaeducationbureau

photo content