uz
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

Kanalga Telegram’da o‘tish

ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali የጥበብ ማዕድ analitikasi

የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 974 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 411-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 116-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 974 obunachiga ega bo‘ldi.

25 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 604 ga, so‘nggi 24 soatda esa -23 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 2.64% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 2.10% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 419 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 334 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 26 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 974
Obunachilar
-2324 soatlar
+1447 kunlar
+60430 kunlar
Postlar arxiv
ዛሬ እንዴት እንደሆነ አላወኩም ግን ራሴን ቤተክርስቲያን ደጅ አገኘሁት እኔ ማለት ሰው የሚፀየፈኝ፣ ይሄን ልጅና ሽንት ቤትን በሩቁ ብለው የሚተርቱብኝ ፣ ጎረቤት ገብቸ እንኳን እንደ ሰው ኖር ኖር ተብሎ ቦታ ማይሰጠኝ እኔ አንድ ቀበሌ ሚያክል ዘመድ ኑሮን ብቸኛ የሆንኩ እኔ ። እንዴት እንደሄድኩ አላውቅም ግን ራሴን ቤተክርስቲያን አገኘሁ ። እኔ ማለት የሰፈራችን ወላጆች ልጆቻቸውን ከዚህ ከይሲ ልጅ ጋ እንዳትውል እያሉ የገፉኝ ፣ የተደገፍኩት ፣ አለኝ ያልኩት እንደ ሸምበቆ ተሰብሮ ሲወጋኝ አየሁ። ራሴን ቤተክርስቲያን አገኘሁ ቤተክርስቲያን ደጃፍ ብቻዬን ቁጭ ብዬ እያለቀስኩ የሆነ ድምፅ መጥቶ ሲያወራኝ ታወቀኝ ። አይዞህ ልጄ! ሰው ባያውቅህም እኔ አውቅሃለሁ ፣ ሰው ቢገፋህም እኔ አሁን ክንዶቼን ዘርግቻለሁ ና ና እቅፌ ውስጥ ግባ ። አንተ ተውከኝ እንጂ እኔ አልተውኩህም ለዘላለምም አልለቅህም ። አሁን እኔ የልብ ወዳጅህ ነኝ የውስጥህን ለኔ ተናገር ። እነሱም አንተን ወደ እኔ ነው ያመጡህ በማንም ላይ ቂምም ሆነ በቀል እንዳይኖርብህ ። በል እንባህን ጥረግና በሰላም ወደ ቤት ሂድ አለኝ ። ከተቀመጥኩበት ብድግ ብየ ተነሳሁ እንባዬን ጠራርግ ለራሴ እንዲህ አልኩኝ .... ለካ እግዚአብሔር እንደሚያውቀኝ ማንም አያውቀኝም ።🙏🙏🙏🙏🙏 ✍ Henok

እንግሊዛዊ ደራሲና ፈላስፋ Alduos Huxley ስለ ምሁራን ከተናገረው :- ከብዙኃኑ በተለየ መልኩ ፣ ምሁራን ምክኒያታዊነትንና በእውነታዎች ላይ ፍላጎት አላቸው ። የአስተሳሰብ ትችታቸው በብዙኃኑ ላይ በጥሩ ሁኔታ የሚሰራውን አይነት ፕሮፖጋንዳ እንዲቋቋሙ ያደርጋቸዋል ።

ሳይኖረኝ ጦረኛ ከጎኔ መሳፍንት ወጣው ለጦርነት እንዲሁ ለብቻዬ ሰራዊት ላይ ልዘምት ምሽግ ምን ሊረባኝ ኣልሆንም ምርኮኛ ኣቅም ስላነሰኝ ኣያስፈልገኝም ሰገባ ለሰይፌ በኩራት ሞታለው ብቻ ተሰልፌ meron

የአንዳንድ ሰው እድል ትንሳዔ ያለው ሲመስል ፤ የአንዳንዱ ደግም ከእትብቱ ጋር አብሮ የተቀበረ ይመስላል።

ብዙ ግዜ የሰቀልከው ተስፋ ጋ ለመድረስ መንጠራራት ተስፋውን ከመጨበጥ በላይ ደስታ አለው ። ጉልበትና የተስፋ ስንቅ ያጅቡታል ። 📖 ጠበኛ እውነቶች

፡፥፡ አስኳላ ፡፡፥፡፡
ሁለት ሎሌዎች ተመሳሳይ መጠን በሚይዙ ሁለት ጋኖች ውሀ እንዲቀዱ ይታዘዛሉ። አንደኛው ችኩል፣ስልቹ፣እናም ያን ያህል ለነገሮች ትርጉም የማይሰጥ ስለነበር በቅርቡ ካለችዋ ምንጭ ለመቅዳት ይወርዳል፤ ያችውም ከብቶች እና ውሾች ያረከሷት ብትሆንም ሎሌው ርቆ መሄድ አልፈለገም። ይህም ለጌታው በፍጥነት ውሀውን ይዞ ተመለሰ።  ሌላኛው ሎሌ ግን ህሊናውን የገዛ፣ ነገሮችን የሚመዝን ስለነበር እንዲሁ የረከሰውን ለክቡር ጌታው ማቅረብ አልፈለገም። እናም በሩቅ ከሚገኝ ንፁህ እና ለጤናም ተስማሚ የሆነውን ውሀ ከባሕር ቀድቶ ይመለሳል ። ታዲያ ጌታው ጐርበጥ አድርጎ በማየት የት ቆየህ ብሎ ይወቅሰዋል፣ይቀጣውማል ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እኩል ለመታየት ሲል ቀድሞ በመሄድ ከባህር ቀድቶ ከምንጯ ከቀዳው ጋር እኩል መድረስ ስለቻል እኩል እይታን አግኝቷል። Our learning style don't judge or evaluate our mind or perspective rather it's all about showing the ultimate result!!!
✍ Tewodros D.

አንዳንዶቻችን የሰው መለማመጥ በራስ መተማመን ሚመስለን አለን መፈለጋችን የተለየ ማንነት የተላበስን እስኪመስለን ድረስ!      ያ ግን አብዝቶ ገዳይ ነው ሲፈልግህ የቆየ ሁሉ ለሁል ጊዜው በዛ ጥያቄ ውስጥ አይቀጥልም!!!      ፈላጊ ያጣህ ቀን እንዳንተ ከነበረበት የሚወርድና ድጋሚ ራሱን መገንባት ሚያቅተው አይኖርም!      ስለዚህ በሰው ስሜት ላይ ሳይሆን በራስ መቻል ላይ በራስ መተማመንህን አኑር።

አንዳንድ ችግሮቻችንን ጊዜ ፈታው ስንል ጊዜ መፍትሔ በራሱ ሰጠው ማለት አይደለም!      በጊዜ ውስጥ የተፈጠረው መረጋጋታችን እንጂ መፍትሔ የሆነው!!!       ስለዚህ በቀላሉ መረዳት ያለብን በየተኛውም ሁኔታ ውስጥ መረጋጋት መፍትሔ ሰጪ ነው።

እያንዳንዱ ሰው ውስጡ ላይ የሆነ ማዕበል አለው ። ይህም ማዕበል እኛን ሊሰራንና ሊያጠነክረን እንጂ ሊገድለን ወይም ሊያጠፋን የመጣ አይደለም ። ማዕበል እንደ ማዕበልነቱ ይለያያል አንዳንዴም ጠራርጎ የሚወስደን ማዕበል ሊመጣ ይችላል ። አንድ መርከበኛ ችሎታው የሚለካው ፀጥ ባለ ውሃ ላይ በመቅዘፍ ሳይሆን የሱ ፈተናው እና ችሎታው የሚታየው ማዕበሉ ውስጥ ቀዝፎ ከተሻገረ ነው ። ያኔ ማዕበሉ እሱን ጎበዝ ቀዛፊ ያደርገዋል ። በህይወታችንም ላይ የሚገጥሙን ማዕበሎች እኛን ይሰሩናል ያጎብዙናል እንጂ አያጠፉንም ። የህይወትህን መስመር ማዕበሉ የሚመጣበትን አቅጣጫ አይተህ መሪህን ዞር አድርገህ እለፈው ። አለበለዚያ በህይወት መንገድ ላይ እንደገና የሚባል ነገር የለም ዙርያህን ቃኝ በምን አይነት ማዕበል ውስጥ እንዳለህ አይተህ መሪህን ወደ ሌላ አቅጣጫ አዙረውና በሰላም ሂድ ። አይዞህ! ፈጣሪህን ብቻ ያዝ ታልፋለህ 🙏🙏 ✍ Henok

"ሄኒ ምንድነው በጣም የምትወደውና የሚያስፈልግህ ነገር "? አለችኝ ትከሻዬ ላይ ራሷን ጥላ ሁሌ ምሸት ለ sun set አዘዉትረን የምንቀመጥቀት ቦታ ላይ በሰዓቱ ተገኝተን እንዴ ! ሜሉ አንቺና አንቺ ነሻ አልኩኝ ከፏ ወዲያው ተቀብዬ እሺ ከኔ ቀጥሎ ? አለች ካንቺ ቀጥሎ 🤔 ትንሽ አሰብኩና ማስተርሴን መማር አልኩኝ እሺ ሌላስ አለችኝ ውስጤ ላይ የቀረ ነገር መኖሩን ያወቀች ይመስል ሌላው ከዚህ ላቅ ያለ ነው ኢትዮጲያ ውስጥ አለ የለም የተባልኩ የዩንቨርስቲ መምህር መሆን ነው ምፈልግ አልኳት አየህ ሄኒዬ አሁን በምናብህ ያሰብከው እውን የሚሆነው አንተ ስትንቀሳቀስ ነው። ያመለጡህን ነገሮች እርሳቸው አንዳንዴ እያስፈለገንም አለመፈለግ ጥሩ ነው ። ብላ ሳም አድርጋኝ ተነሳች ። እንዴ 🤔 የሚያስፈልጉንን ነገሮች አለመፈለግ ይቻላል እንዴ ? ✍ Henok

፡፡፤፤፡ አዲስ ሕይወት ፡፡፤፤፡
ህይወት እንደ ዛፍ በተመሳሳይ ነፋስ ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ማሳየት ስትጀምር ፤ የመሻት አቅሟ እየተሟጠጠ ፣ መሰላቸት እየፀና ይመጣል። ወዳጄ የምታማርረው እና ነገ በእራሷ ብርሃን ሆና ሳለ ዓይንህን ጋርዶ በብርሃኗ መሻትክን እንዳትዘራ ያሰረህ ዛሬ ላይ የምታደርገው ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ነው። ይህን ደግሞ መቀየር የምትችለው አንት ብቻ ነህ። ነገሮች ህይወትህን ተመሳሳይ ሊያደርጉብህ ቢሞክሩ እንኳን ነገሮችን ተጠቅመህ ህይወትህን አዲስ ማድረግ። እስረኞች ዓለም ፣ ቤተሰብ ፣ አካባቢ ፣ ጓደኛ ከመራቃቸው በተጨማሪ ህልማቸውን ይነጠቃሉ።ሁሌም ተመሳሳይ ምግብ ፣ ልብስ ፣ ድምፅ ፣ ምኞት፣....ኡፍፍ..ፍፍፍ...አሰልቺ ነው። ታዲያ ብልሆቹ ፍቱን መድሀኒት አግኝተዋል ...መ..ፅ...ሐ..ፍ ማንበብ። መፅሐፍ... ሰውሰራሽ ካቦች የጋረዱት ዓይንህን በማገዝ አዲስ አለም ፣ ህይወት ፣ ተስፋ ፣ የዛፎች እንቅስቃሴ ፣ የወፎች ዝማሬ ፣ ...ሁሌም አዲስ ህይወት ያጎናፅፍሃል። ብቻ አዕምሮህ አዲስ ህይወት ማየት የሚችልበትን መንገድ ተጠቀም ...ያኔም ሕልምህ ያቆጠቁጣል ፣ ዓላማህ እራሱን ግልፅ ያደርጋል ፤ ብርሃን ለእናንተ!!!
Simple and new way of life lets you survive on the way to your goal,let yourself progress through reading or an action that makes you sense new smells, and feel new all. ✍✍ T,,,,,,D.....

፤፥፡አለመማር መቃጠል ነው ፡፡፤
ባለፈው አንዱ ተማሪ "መማር መቃጠል ነው" ሲል ሰማሁት። እኔም በቅርበት ጠየቅሁት ፣ እንዴት? አልኩት። እርሱም በብስጭት ... እንዴት ትለኛለህ ... መዓት.. X... እያነደደኝ ይለኛል። እኔም ለማረጋጋት እየሞከርኩ ... እርሱማ የሁላችንም ነው ... እእ.. ግን እንዴት መማር መቃጠል ሊሆን ቻለ? አልኩኝ ባለመሰልቸት። X..ከየት ሊመጣ ቻለ አልኩት? አይይ... እኛ እምናነበው እና እሚያስተምሩን ቆሎ ቆሎውን,... እ.., ፈተና እሚያመጡት .. ያልበሰለ ጥሬውን ... የበሰለ ቆሎ መብላት ለምደን ... ማብሰሉን ከየት እናምጣው.. ሳንማረው? ታዲያ ጀግኖቹ ቆሎ ሲሰጧቸው የት እና እንዴት እንደበሰለ ይጠይቃሉ? ይህ ነው ማወቅ ... ለካስ እየተማርን አልነበረም... መማር ማሰብ ነው እንጂ የሰጡትን መቀበል አይደለም። ቆሎ ሲሰጡህ የት መጣ በል? ከሰማይ እንዳልሆነ ታውቃለህ... ያኔ አዕምሮህ ስራውን ይጀምራል ... የጥርስ ስራን ..ለጥርስ
Learning is analyzing, not burning bro

ውጪ እንደ ዘመዱ የተላፋህ ውሻ ነው ቤቱ እግርህን በቀዳዳ ሚነቅስህ።       መቼ እንደሚቀየሩ አታቃቸውም!

።።።። ዝምታ ከመረጥን ባፍ ከፋቾች መሀል በደበዘዙት ፊት ደምቀን ከተገኘን በአንካሶች መሀል በእግሮቻችን ከቆምን ከህዝበቱ ጋራ ካልተመሳሰልን ለሁሉም ጠላት ነን አርቀን ካስተዋልን በእውሮች መሀል ሁሉም ሰው ያማናል ሁሉም ይዘልፈናል ደህና መሆን ባልሆኑት ውስጥ ያስነቅፋል ያስገልላል ለምን?  ቢባል በሽታን  ለለመደ                ጤነኝነት በጣም ያማል       .meron

አንተ ሁለነገርህን ታውቀዋለህ እነሱ ደግሞ ያሳየኻቸውን!           አንተ ምትፈልገው የጎደለህን አይደለም እንዲኖርህ እንጂ! እነሱ ደግሞ የእነሱን መሻት እንድታሟላ ነው።     የምሬን አንዳንድ ሰው ሊሰራህ ሲሞክር እያስተካከለህ አይምሰልህ እንደራሱ ሊቀርጽህ ነው እንጂ!!!

ያውቃሉ ለመባል እውቀትን ለፈለግን በልጦ ለመታየት ሰውን ላሳነስን ነበሩ ለመባል ግን ኖረን ላልጠቀምን ይብላኝልኝ ለኛ ሰው መስለን ግን ላልሆን #meron

ቤተሰቦች የስነ_ጽሁፍ ችሎታና የጻፋችሁት ካላቹ በቻናላችን በመለጠፍ ለአንባቢያን ቤተሰቦች ስራዎቻችሁን ማስገምገም ትችላላቹ!!! አድሚን እንሰጣለን።

ሁሉም እንደሚያምርብህ ማሰብ በራስ መተማመን ነው! አንዳንዴ ብቻ ትንሽ ራስን አለማወቅ ሊገባበት ይችላል እንጂ።

አበባን ያሳመራት ፍሬዋ ብቻ አልነበረም ፈንቅላ የወጣችውም ጭቃ እንጂ!

ለአንድ ጎል አስራ አንዱን መጣል ግድ ነው።