uz
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Ko'proq ko'rsatish
2 758
Obunachilar
+324 soatlar
+97 kunlar
+4630 kunlar
Postlar arxiv
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን 325 የተልዕኮ ትምህርት ተማሪዎች ተመረቁ። በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የተልዕኮ ትምህር
+9
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን 325 የተልዕኮ ትምህርት ተማሪዎች ተመረቁ። በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት  የተልዕኮ ትምህርት ማስተባበሪያ ለአንድ ዓመት እና ለሶስት ዓመታት መንፈሳዊ ተከታታይ ትምህርት ሲያስተምራቸው የቆዩ 325 ተማሪዎችን ትላንት ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስመርቋል። በዕለቱ ትምህርተ ወንጌል በመ/ር ኢዩኤል የተሰጠ ሲሆን የዝማሬ አገልግሎት በዘማሪት ሲ/ር ሕይወት ተፈሪ  እና በተመራቂ ተማሪዎች ቀርቧል። በዕለቱ የደብራችን ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃናት አዕምሮ ምስጋናው መምህራነ ቤተ ክርስቲያን ፣ ተመራቂ ተማሪዎች ፣የተመራቂ ቤተሰቦች እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የዕለቱ የአገልግሎት ዜና ሰኔ 28/2018 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤታችን በሥራ አመራርነት፣ በኦዲትና ኢንስፔክሽን እንዲሁም በሥራ አስፈጻሚ
+1
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የዕለቱ የአገልግሎት ዜና ሰኔ 28/2018 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤታችን በሥራ አመራርነት፣ በኦዲትና ኢንስፔክሽን እንዲሁም በሥራ አስፈጻሚነት እንዲያገለግሉ ለተመረጡ አመራሮች በመልአከ ሰላም መ/ር ታዬ አብርሃም (ጋሽ ታዬ) የአባታዊ ምክር ተሰጥቷል። በዚህ የትምህርታዊ ምክር ጉባኤ 'የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንን ሥርዓት ጠብቆ በፍቅርና በአንድነት ማገልገል እንደሚገባ የተመከረ ሲሆን፤ እርስ በእርሳችን ከመነቃቀፍ ወጥተን ለቤተክርስቲያን በአንድነት ቆመን ማገልገል ይገባናል ሲሉ መልአከ ሰላም ታዬ አስረድተዋል።  በአገልግሎት ጸንቶ ለሌሎች ሕይወት ለመትረፍ በዘመኑ ያሉ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለብንም  አሳስበውናል። መረጃውን የሥራ አመራር ጽ/ቤት አድርሶናል። እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የዕለቱ የአገልግሎት ዜና ዛሬ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤታችን በሥራ አመራርነት፣ በኦዲትና ኢንስፔክሽን እንዲሁም በሥራ አስፈጻሚነት እንዲያገለግሉ ለተመረጡ አመራሮች በመልአከ ሰላም መ/ር ታዬ አብርሃም (ጋሽ ታዬ) የአባታዊ ምክር ተሰጥቷል። በዚህ የትምህርታዊ ምክር ጉባኤ 'የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንን ሥርዓት ጠብቆ በፍቅርና በአንድነት ማገልገል እንደሚገባ የተመከረ ሲሆን፤ እርስ በእርሳችን ከመነቃቀፍ ወጥተን ለቤተክርስቲያን በአንድነት ቆመን ማገልገል ይገባናል ሲሉ መልአከ ሰላም ታዬ አስረድተዋል።  በአገልግሎት ጸንቶ ለሌሎች ሕይወት ለመትረፍ በዘመኑ ያሉ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለብንም  አሳስበውናል። መረጃውን የሥራ አመራር ጽ/ቤት አድርሶናል። እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር

የክረምት ኮርስ ለሕፃናት ትምህርቱ፦ ሐምሌ 6/2018 ዓ.ም ይጀምራል። ይምጡ ይመዝገቡ ይማሩ ትምህርቱ ሰኞ፣ ረቡዕ እና አርብ ከ3:00-5:30 ድረስ ይሰጣል። የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
የክረምት ኮርስ ለሕፃናት ትምህርቱ፦ ሐምሌ 6/2018 ዓ.ም ይጀምራል። ይምጡ ይመዝገቡ ይማሩ ትምህርቱ ሰኞ፣ ረቡዕ እና አርብ ከ3:00-5:30  ድረስ ይሰጣል። የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የአገልግሎት ዜና ለሰንበት ትምህርት ቤታችን በሥራ አመራር፣ በኦዲትና ኢንስፔክሽን፣ እንዲሁም በሥራ አስፈጻሚነት እንዲያገለግሉ ለተመረጡ አመራሮች የተዘጋጀውን የመዋቅር ሥልጠና በመ/ር ቃልኪዳን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሥልጠና ክፍል ተሰጠ።በዕለቱ ስለ አዲሱ የመዋቅር አደረጃጀት በሰፊው ገለጻ የተሰጠ ሲሆን ከአመራሮች የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው በአሰልጣኙ መልስና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። መረጃውን የሥራ አመራር ጽ/ቤት አድርሶናል። እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር

የክረምት ኮርስ ለማዕከላውያን እድሜያችሁ ከ13-18 ድረስ የሆነ በሙሉ ትምህርቱ: - ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም ይጀምራል። ይምጡ ይመዝገቡ ይማሩ ትምህርቱ ሰኞ ፣ ረቡዕ ፣ አርብ ከ9:00-11:00 እ
የክረምት ኮርስ ለማዕከላውያን እድሜያችሁ ከ13-18 ድረስ የሆነ በሙሉ ትምህርቱ: - ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም ይጀምራል። ይምጡ ይመዝገቡ ይማሩ ትምህርቱ ሰኞ ፣ ረቡዕ ፣ አርብ ከ9:00-11:00  እና እሑድ ከ4:00-6:30 ድረስ ይሰጣል። የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

የክረምት ኮርስ ለወጣቶች ትምህርቱ- ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም ይጀምራል። ይምጡ ይመዝገቡ ይማሩ ትምህርቱ ሰኞ ፣ ረቡዕ ፣ አርብ ከ12:00-1:30 እና እሑድ ከ4:00-6:30 ድረስ ይሰጣል። የፍኖተ
የክረምት ኮርስ ለወጣቶች ትምህርቱ- ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም ይጀምራል። ይምጡ ይመዝገቡ ይማሩ ትምህርቱ ሰኞ ፣ ረቡዕ ፣ አርብ ከ12:00-1:30 እና እሑድ ከ4:00-6:30 ድረስ ይሰጣል። የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

የተልዕኮ ተማሪዎች የምርቃት መርሐግብር የፊታችን እሑድ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ በደብራችን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ
የተልዕኮ ተማሪዎች የምርቃት መርሐግብር የፊታችን እሑድ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ በደብራችን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የሰሞኑ የአገልግሎት መረጃ ባሳለፍነው ቅዳሜ በነበረው የሥራ አመራር ስብሰባ ላይ የአመራሩን የአገልግሎት ማስተባበሪያ ክፍል ድልድል እና የሥራ አስፈጻሚን እጩዎችን ከሦስት ቀን የጸሎተ እጣን እና የጸሎተ ማርያም ልመና በኃላ በእጣ የመለየት ተግባራት ተከናውኗል። በዚህም መሠረት የሥራ አመራር አጠቃላይ የአገልግሎት ማስተባበሪያ ክፍሎች ድልድል እንደሚከተለው ሲሆን 1. መ/ር ኢ/ር ዳዊት አበበ፦ የሥራ አመራር ሰብሳቢ 2. አቶ ላቀው ይርጋ ፦ የሥራ አመራር ም/ሰብሳቢ 3. ወ/ሮ ዮርዳኖስ ገ/ሚካኤል ፦ የሥራ አመራር ጸኃፊ 4. ወጣት አበራ መላኩ ፦ የሥራ አስፈጻሚ ሰብሳቢ (ዋና ሥራ አስፈጻሚ) 5. ወጣት በረከት ፍቅሩ ፦ እቅድ፣ ጥናትና ምርምር ማስተባበሪያ 6. ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖአምላክ ፦ ትምህርትና እቅበተ እምነት ማስተባበሪያ 7. ዲ/ን አሌክሳንደር ወ/ገብርኤል፦ አባላትና ተቋም አደረጃጀት ማስተባበሪያ 8. ዲ/ን ዳንኤል ተክሌ፦ ሚዲያና ሕዝብ ግንኙነት ማስተባበሪያ 9. መ/ሰ ዲ/ን ወንድወሰን መኮንን ፦ መረጃና ወቅታዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ 10. ወጣት አብርሃም አስራት ፦ ሒሳብና ንብረት አስተዳደር ማስተባበሪያ 11. አቶ ሙሉጌታ ሰማን ፦ ምጣኔ ሀብትና ማኅበራዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ 12. ወጣት ዮናታን ብርሃኔ ፦ ቴክኖሎጂ ትስስር ማስተባበሪያ በተጨማሪም የሥራ አስፈጻሚ የአገልግሎት ክፍል ድልድል 1. ወ/ሮ ቤተልሔም ገነነው ፦ ም/ዋና ሥራ አስፈጻሚና ጸሐፊ 2. አቶ ዮናስ ይርዳው፦ ዕቅድ ትግበራ እና ክትትል ክፍል 3. ዲ/ን አብርሃም ታደሰ ፦ ትምህርትና ሥልጠና ክፍል 4. ዲ/ን ኪሩቤል መንገሻ ፦ መርሐግብር እና ጉባኤያት ክፍል 5. አቶ አለሙ ጉደታ ፦ መረጃ እና የውስጥ ግንኙነት ክፍል 6. አቶ እንግዳወርቅ አረፋይኔ ፦ መዝሙርና በዓላት ክፍል 7. አቶ ሔኖክ ኃይሉ ፦ ኪነ ጥበብና ሥነ ጥበብ ክፍል 8. አቶ ፍቃዱ ኪሮስ ፦ የሰው ሀብት አስተዳደር ክፍል 9. አቶ ተሾመ እንዳለ ፦ ልማትና በጎ አድራጎት ክፍል 10. ወ/ሮ አቻምየለሽ ደምሴ ፦ በጀትና ንብረት አስተዳደር ክፍል መሆናቸውን እያሳወቅን። በቀጣይ ጊዜ ሥራ አመራሩና ሥራ አስፈጻሚው በየንዑስ ክፍላት የሚያገለግሉ አባላትን በጋራ ተወያይተን እንደምናሳውቅ ለመግለጽ እንወዳለን። የሥራ አመራር ጽ/ቤት እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር

እግዚአብሔር አምላካችን ለኢትዮጵያ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ ለመረጣቸው ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ወርሐዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤት በረከት አይለየን!
እግዚአብሔር አምላካችን ለኢትዮጵያ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ ለመረጣቸው ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ወርሐዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤት በረከት አይለየን!!

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ማስታወቂያ ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ! ሰንበት ትምህርት ቤታችን በተለያዩ ክፍላት ለአገልግሎት ስንጠቀምባቸው የነበሩት ሁሉም የባንክ አካውንቶች በጊዜያዊነት ስለተዘጉ በቀጣይ ለአገልግሎት የምንጠቀምበትን አካውንት እስከምንገልጽላችሁ ድረስ ምንም ዓይነት ገንዘብ ወደ አካውንት ቁጥራችን ገቢ እንዳትፈጽሙ ለማሳሰብ እንወዳለን። እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር