ch
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

前往频道在 Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

显示更多
2 604
订阅者
+324 小时
+87
+2430
帖子存档
በዓለ ዕርገት "ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን" "አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር በመለከት ድምጽ ዐረገ" መዝ 46፡5 ዕርገት ከዘጠኙ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዐ
በዓለ ዕርገት "ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን" "አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር በመለከት ድምጽ ዐረገ" መዝ 46፡5 ዕርገት ከዘጠኙ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዐበይት በዓላት አንዱ ነው፡፡ ዕርገት ማለት ዐረገ ከሚለው የግእዝ ግሥ የወጣ ቃል ሲሆን ትርጉሙም ወደ ላይ መውጣት ፣ ከምድር ከፍ ከፍ ማለት ፣ እስከ ሰማየ ሰማያት መመጠቅ ማለት ነው። እንኳን ለጌታችን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ዕርገት በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!

እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ ዛሬ በቤተክርስቲያናችን የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ እና የሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ዓመታዊ ክብረ በዓል ሲሆን ቅዱሳንን እና እኛ
እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ ዛሬ በቤተክርስቲያናችን የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ እና የሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ዓመታዊ ክብረ በዓል ሲሆን ቅዱሳንን እና እኛን የሚረዳን የቅዱስ ሚካኤል ወራዊ በዓል በድጋሚ እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ሚካኤል ማለት የስሙ ትርጓሜ “መኑ ከመ አምላክ፥ ማን እንደ እግዚአብሔር” ማለት ነው። ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከወርሐዊ በዓሉ በረከት ረድኤት ይክፈለን፤ ጥበቃውና አማላጅነቱ አይለየን፡፡ አሜን፡
ሚካኤል ማለት የስሙ ትርጓሜ “መኑ ከመ አምላክ፥ ማን እንደ እግዚአብሔር” ማለት ነው። ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከወርሐዊ በዓሉ በረከት ረድኤት ይክፈለን፤ ጥበቃውና አማላጅነቱ አይለየን፡፡ አሜን፡፡ ሰላም ለአዕይንቲከ እለ ኀበ ልዑል ያንቃዐድዋ ለውሉደ ሰብእ ሣህለ እንዘ ይሴፈዋ ሚካኤል ቀዋሚ ለደቂቀ ጼዋ ለምክረ ጸርየ በትንባሌከ ዕልዋ ምዕቅብና ነፍስየ ወሥጋየ ወሀብኩከ ነዋ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሰንበት ትምህርት ቤታችን የበጎ አድራጎት ክፍል ባደረገው አገልግሎት ባለፈው ሰንበት 1. ለ250 ነዳያን መርሐግብር የተደረገ ሲሆን በመርሐግብሩ ዝማሬ ፣ትምህርት እና ምገባ ተደርጓል በዚህም ቀን ሁለት በሌላ ቤተ እምነት የነበሩ ወገኖቻችንን ወደ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት መመለስ እንፈልጋለን በማለት በራሳቸው ፈቃድ የጠየቁ በመሆኑ ክፍሉክፍሉ  ከንስሐ አባት ጋር አገናኝቷቸዋል ክትትልም እያደረገ ይገኛል ሰዎቹን ማገዝ የሚችል/የሚፈልግ ከታች በተቀመጡት ስልኮች መደወል ይቻላል። 2. ለ25 ነዳያን ለወንዶች ንጽህናቸውን የመጠበቅ እና የልብስ ልገሳ የተከናወነ ሲሆን በተጨማሪ፣ ለ25 ነዳያን ለሴቶች የልብስ ልገሳ ተከናውኗል። እግዚአብሔር አገልግሎታችንን ይቀበልልን!! የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት በጎ አድራጎት ክፍል አገልግሎቱን ለመደገፍ 0931 144444 0911 091598 0912 419772 የበጎ አድራጎት ክፍል

የሰንበት ትምህርት ቤታችን የበጎ አድራጎት ክፍል ባደረገው አገልግሎት ባለፈው ሰንበት 1. ለ250 ነዳያን መርሐግብር የተደረገ ሲሆን በመርሐግብሩ ዝማሬ ፣ትምህርት እና ምገባ ተደርጓል በዚህም ቀን ሁ
+9
የሰንበት ትምህርት ቤታችን የበጎ አድራጎት ክፍል ባደረገው አገልግሎት ባለፈው ሰንበት 1. ለ250 ነዳያን መርሐግብር የተደረገ ሲሆን በመርሐግብሩ ዝማሬ ፣ትምህርት እና ምገባ ተደርጓል በዚህም ቀን ሁለት በሌላ ቤተ እምነት የነበሩ ወገኖቻችንን ወደ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት መመለስ እንፈልጋለን በማለት በራሳቸው ፈቃድ የጠየቁ በመሆኑ ክፍሉክፍሉ  ከንስሐ አባት ጋር አገናኝቷቸዋል ክትትልም እያደረገ ይገኛል ሰዎቹን ማገዝ የሚችል/የሚፈልግ ከታች በተቀመጡት ስልኮች መደወል ይቻላል። 2. ለ25 ነዳያን ለወንዶች ንጽህናቸውን የመጠበቅ እና የልብስ ልገሳ የተከናወነ ሲሆን በተጨማሪ፣ ለ25 ነዳያን ለሴቶች የልብስ ልገሳ ተከናውኗል። እግዚአብሔር አገልግሎታችንን ይቀበልልን!! የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት በጎ አድራጎት ክፍል አገልግሎቱን ለመደገፍ 0931 144444 0911 091598 0912 419772 የበጎ አድራጎት ክፍል

የሰንበት ትምህርት ቤታችን የበጎ አድራጎት ክፍል ባደረገው አገልግሎት ባለፈው ሰንበት 1. ለ250 ነዳያን መርሐግብር የተደረገ ሲሆን በመርሐግብሩ ዝማሬ ፣ትምህርት እና ምገባ ተደርጓል በዚህም ቀን ሁለት በሌላ ቤተ እምነት የነበሩ ወገኖቻችንን ወደ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት መመለስ እንፈልጋለን በማለት በራሳቸው ፈቃድ የጠየቁ በመሆኑ ክፍሉክፍሉ  ከንስሐ አባት ጋር አገናኝቷቸዋል ክትትልም እያደረገ ይገኛል ሰዎቹን ማገዝ የሚችል/የሚፈልግ ከታች በተቀመጡት ስልኮች መደወል ይቻላል። 2. ለ25 ነዳያን ለወንዶች ንጽህናቸውን የመጠበቅ እና የልብስ ልገሳ የተከናወነ ሲሆን በተጨማሪ፣ ለ25 ነዳያን ለሴቶች የልብስ ልገሳ ተከናውኗል። እግዚአብሔር አገልግሎታችንን ይቀበልልን!! የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት በጎ አድራጎት ክፍል አገልግሎቱን ለመደገፍ 0931 144444 0911 091598 0912 419772 የበጎ አድራጎት ክፍል

ልደታ ለማርያም  አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በግንቦት አንድ ቀን ተወለደች እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኀነት የሆነባት ናት። ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ።  “ወክልኤሆሙ ኄራን ወሥሙራን እሙንቱ ወየሐውሩ በሕገ እግዚአብሔር እስመ እግዚአብሔር ኀረዮሙ ወአፍቀሮሙ ትካት” ይላቸዋል እግዚአብሔርን የሚወድዱ በሕጉ የሚኖሩ ደጋጎችና አምላክም የመረጣቸው ነበሩ።  ልጅ ስላልነበራቸው ሲያዝኑ ኖሩ በዚያ ወራት የመካኖችን መብዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበርና። እነርሱም ለዓይናቸው ማረፊያ ለልባቸው ተስፋ የሚሆን እንዲሁም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ልጅ እንዲሰጣቸው ይማልዱ ነበር። ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ሃሳባቸውን ተመለከተ። ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኀነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው። በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ ለተመሰገነች ሚስቱ ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት ቃሉ እውነት እንደሆነ እርሷም አመነች ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። “ከሰው የበለጠች ከመላእክት ኹሉ የከበረች ልጅ ትወልዳላችኊ" ብሎ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለሐና ነግሯት በፈቃደ እግዚአብሔር በብሥራተ መልአክ እመቤታችን ነሐሴ ሰባት ተጸነሰች፤ በእናቷ ማሕፀን ሳለችም “መንፈስ ቅዱስ ዐቀባ እምከርሠ እማ” እንዲል እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጥንተ አብሶ ባመጣው መርገም እንዳትያዝ ጠብቋታል፡፡ የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን ወንድ ከሆነ በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርገው ዘንድ ሴትም ብትሆን እግዚአብሔርን  ታገለግል ዘንድ ብጽአት አድርጋ እንደምትሰጥ ስለትን ተሳለች። ከዚህም በኋላ ይቺን የከበረች ሕፃን ፀንሳ በግንቦት አንድ ቀን በደብረ ሊባኖስ(በሊባኖስ ተራራ ስር) ወለደች። ስሟንም ማርያም ብላ ጠራቻት። ጠቢቡ ሰሎሞን አስቀድሞ በመንፈሰ እግዚአብሔር ተቃኝቶ  “መኑ ይእቲ ዛቲ እንተ ትሔውጽ ከመ ጎሕ ሠናይት ከመ ወርኅ ወብርህት ከመ ፀሓይ” (ይኽቺ እንደ ማለዳ ብርሃን የምትጐበኝ እንደ ጨረቃ የተዋበች፤ እንደ ፀሓይም የጠራች ዐላማ ይዞ እንደተሰለፈ ሰራዊት የምታስፈራ ማን ናት?) በማለት እንደ ፀሓይ የሞቀ እንደ ጨረቃ የደመቀ ንጽሕናዋና ቅድስናዋ የመልኳ ደም ግባት በነቢያት ትንቢት አስቀድሞ የተጐበኘላት የእውነት ፀሓይ የክርስቶስ እናት የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብርና ደም ግባቷን እንደተናገረ በሊባኖስ ተራራ በግንቦት አንድ በተወለደች ጊዜ ፊቷ በእጅጉ ያበራ ነበር፤ መዐዛዋም ከሽቱ ኹሉ ይበልጥ ነበር፡፡ የፈጣሪያችን እናት ቅድስት ድንግል የተወለደችበትን ግንቦት አንድን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን “ልደታ ለማርያም” በማለት ከጥንት ጀምሮ በታላቅ መንፈሳዊ ደስታ በቅዳሴ፣ በማሕሌት ታከብረዋለች። ምክንያቱም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የሁላችንም ልደታችን ነውና።   እንኳን ለእመቤታችን በዓለ ልደት (ልደታ ለማርያም)  አደረሳችሁ። የእናታችን ረድኤት በረከት አማላጅነቷ በሁላችንም ላይ ለዘለዓለሙ ጸንቶ ይኑር አሜን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን “ወንድሞች ሆይ፥ በመልካም የተመሰከረላቸውን መንፈስ ቅዱስና ጥበብም የሞላባቸውን ሰባት ሰዎች ከእናንተ ምረጡ፥ ለዚህም ጉዳይ እንሾማቸዋለን፤” (ሐዋ. 6÷3) የፍኖተ ብርሃን አባላት ወንድምና እህቶች በቀጣይ ሦስት ዓመታት ሰ/ት/ቤታችንን በአመራርት ቢያገለግሉ መልካም ናቸው ብላችሁ ከምታስቧቸው አባላት ውስጥ በልምድ ከካበቱት: በመካከል እንደ ሰንሰለት ሊያስተሳስሩ ከሚችሉትና ልምድ ቢወስዱ ለወደፊት በመልካም ሥነ ምግባርና አመራራቸው ሰ/ት/ቤታችንን በጥሩ ያገለግላሉ ብላችሁ የምታስቧቸውን አባላት ትጠቁሙን ዘንድ በአምላከ ሚካኤል ስም እንጠይቃለን። ጥቆማ መስጠት የሚቻለው እስከ ግንቦት 6/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ በመሆኑ አስቀድማችሁ በአመራርነት ያገለግላሉ ብላችሁ የምታስቧቸውን እንድትጠቁሙ በድጋሚ ለማሳሰብ እንወድዳለን። ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን!! የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አስመራጭ ኮሚቴ https://forms.gle/tQbQgAknuDCo79Ee8

በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ላይ የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ አባላት መመረጣቸው ተገለጸ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ከበዓለ ትንሣኤ በኋላ በሃያ አምስተኛው ቀን የሚካሄደው ዓመታዊው የርክበ ካህናት
በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ላይ የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ አባላት መመረጣቸው ተገለጸ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ከበዓለ ትንሣኤ በኋላ በሃያ አምስተኛው ቀን የሚካሄደው ዓመታዊው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የመግቢያ ንግግር ተጀምሯል። ጉባኤው በይፋ መጀመሩን ተከትሎ የቋሚ ሲኖዶስ ሪፖርት ለምልዓተ ጉባኤው የቀረበ ሲሆን በመቀጠልም የሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የሚወያይባቸውን አጀንዳዎች የሚያቀርብ አርቃቂ ኮሚቴ አባላት ተመረጠዋል። የኮሚቴ አባላቱም 1. ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ 2. ብፁዕ አቡነ ኤውስጣቴዎስ (ዶ/ር) ሊቀ ጳጳስ 3. ብፁዕ አቡነ እንጦንስ ሊቀ ጳጳስ 4.ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ ሊቀ ጳጳስ 5. ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሊቀ ጳጳስ 6. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ሊቀ ጳጳስ 7.ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ ጳጳስ መሆናቸው ተገልጿል።

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ አምላክ አሜን! ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ፤ ብፁዕ ኣቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣ በአጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፦ ማሕየዊት በምትሆን ሞቱ ሰማያውያንና ምድራውያንን ያስታረቀ፣ በቅድስት ትንሣኤውም የሙታንን ሕይወት በተስፋ ያለመለመ ጌታችን፣ አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ እንኳን ለዓመታዊው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አደረሰን አደረሳችሁ! “እስመ ተዋለጠ እግዚአብሔር ዓለመ በክርስቶስ ኣናኅስዮ ኃጢኣቶሙ ወኢነጺሮ ጌጋዮሙ፤ ወረሰየ ላዕሌነ ቃለ ሥምረቱ፤ ወወሃበነ መልእክተ ሣህሉ፡- እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና በደላቸውን ኣይቈጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል ኣኖረ” (2ቆሮ. 5፥19)። የእግዚአብሔርም ልጅ፣ የሰውም ልጅ የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም በሰብእነት ሲገለጽ ግልጽ የሆነ ዓላማና ግብ እንደነበረው ቅዱስ መጽሓፍ ይነግረናል፤ እሱም በሰማይም፣ በምድርም ያሉትን በሙሉ ማስታረቅ፣ ማገናኘትና ኣንድ ማድረግ ነበረ፤ ጌታችን ይህንን ሲያደርግ ሰማያውያኑንና ምድራውያኑን የለያየው ምክንያት በማስወገድ ነው፤ የመለያየቱ ምክንያት ክፉ ኅሊና ኣምጦ የወለደው በደልና እሱን ተከትሎ የተከሠተው ኃጢኣት ነበረ፤ በኃጢኣት ምክንያት የገባው ሞት ደግሞ የቅጣቱ ማሳያ ፍርድ ነበረ። የመጀመሪያዎቹ ሰዎች በፈጸሙት ስሕተት መነሻነት ምድርንና ምድራውያንን ለከባድ ቅጣትና መርገም የዳረገው ይህ መለያየት ለሰማያውያኑም ተርፎኣል፤ ምክንያቱም መለያየቱ በእግዚአብሔርና በሰው፣ በመላእክትና በሰው፣ በሰውና በሰው፣ በነፍስና በሥጋ ጭምር የጥል ግድግዳን ገንብቶ እስከ ክርስቶስ ዕለተ ስቅለት መዝለቁን በቅዱስ መጽሓፍ የምናውቀው ስለሆነ ማለት ነው። ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት! ቀዳማዊና ዘላለማዊ የሆነው ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ሰብእናችንን ተዋሕዶ በዚህ ዓለም የተገለጸው ሰማያውያንንና ምድራውያንን የለያየው  የጥል ግድግዳን ለማፈራረስ ነው፤ ለመለያየት ምክንያት የሆነችውን ኃጢኣት በሰውነቱ በመቅጣት የሕግን ትእዛዝ ከፈጸመ በኋላ የዕርቁን ተግባር በወሳኝ መልኩ ኣከናውኖታል፤ በክርስቶስ ቤዛነት የሆነው ይህ ዕርቅ በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የተወደደ ነበረና እሱ ራሱ በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ኣስታረቀ፤ ለዚህም ነው ተበዳይ እሱ፣ ቤዛዊ መሥዋዕት ሆኖ የቀረበው እሱ፣ ኣስታራቂ እሱ፣ ታራቂ እሱ ሆኖ የምናገኘው፤ ለሱ የሚሳነው ነገር የለምና ለኛ ግር የሚል ቢመስልም ለሱ ቀላል ነበረ። በዚህ የዕርቅ ተግባር ሰውና እግዚአብሔር፣ ሰውና መላእክት፣ ሰውና ሰው፣ ነፍስና ሥጋ ታርቀው በይፋ ተገናኙ፤ በኅብረትና በኣንድነትም መኖር ቻሉ፤ በቀኙ ለተሰቀለው ሽፍታ “ዛሬውኑ ከኔ ጋር በገነት ትኖራለህ” የሚለው ቃለ ምሕረትና “ኣባት ሆይ፥ ነፍሴን በእጅህ ኣደራ እሰጣለሁ” የሚለው ቃለ አማሕፅኖ የዕርቁ፣ የግንኙነቱና የኣንድነቱ ማሳያ ኣስረጅ ናቸው። ስቅለተ ክርስቶስ ነፍሶቻችን ወደ ግዞት ቤት ሳይሆን ወደ ገነት እንዲገቡ፣ የሚቀበላቸውም ራሱ እግዚአብሔር እንዲሆን ያስቻለ ታላቅ መለኮታዊ ፍጻሜ ነው፤ እኛ “ክርስቶስ መድኃኒታችን ነው፤ አድኖናል” ብለን በልበ ሙሉነት የምንመሰክረው፣ እሱም “ሰላሜን ሰጠኋችሁ” ብሎ የሚያረጋጋን በመሰቀሉ ይህንን ውጤት ስላስገኘልን ነው። ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት! የድኅነታችንና የሰላማችን መሠረት የሆኑትን የክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ለዓለም ማኅበረ ሰብ የማብሰርና የማሥረጽ ተግባር የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቍጥር አንድ ተልእኮ ነው፤ ነገረ ሞቱና ነገረ ትንሣኤው በአስተውሎት፣ በጥልቀትና በተመሥጦ ስናስተምር በውስጡ የምናገኘው የዕርቅ፣ የሰላምና የአንድነት ምስጢር ነው፤ እንደ እውነቱ ከሆነ እኛ የክርስቶስ መልእክተኞች እንደ ቃሉ ራሳችንን ክደን በሚጠበቀው መጠን ተልእኮኣችንን መወጣት ብንችል ኖሮ፣ አሁን በዓለማችን የተፈጠረው መለያየትና ግጭት ኣይኖርም ነበር፤ ችግሩን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት ባንችልም በእጅጉ መቀነስና ዓቅሙን ማዳከም እንችል ነበር፤ ነገር ግን ተልእኮኣችንን በኣግባቡ ኣለመወጣት ኣንድ ነገር ሆኖ የዓለሙ መሳሪያ ሆነን መገኘታችን “በዕንቅርት ላይ…” ሆኖ ይስተዋላል። ይሁንና ኣሁንም ሕዝቡን ወደ ኣንድነት፣ ወደ ፍቅር፣ ወደ ሰላም፣ ወደ ዘላቂ የጋራ ጥቅምና ወደ ፈሪሐ እግዚአብሔር ማምጣት የጉባኤያችን ዓቢይ ተግባር ሊሆን ይገባል፤ እነዚህ ካሉ የምናጣውም ሆነ የሚያመልጠን የለምና ነው፤ ሃገርን በኃላፊነት ተረክባችሁ በላዕላዊ፣ በማእከላዊና በታሕታዊ መዋቅር የምትገኙ፣ እንደዚሁም ኣማራጭ ሓሳብ ኣለን ብላችሁ የምትንቀሳቀሱ ልኂቃነ ሃገር ፣ ሁላችሁም እግዚአብሔርን ከሚያውቅ፣ ከሚያመልክና ከሚፈራ ሕዝብ የተገኛችሁ ናችሁና በልባችሁ እግዚአብሔርን ፍሩ፤ ድምፁንም ስሙ፤ የሱ ገንዘብ በሆኑ ፍጡራንም ኣትጨክኑ፤ ሰውን መያዝ የሚቻለው ኅሊናን በመርታት እንጂ በሌላ ኣይደለምና፣ የሕዝቡን ፍላጎትና የልብ ትርታ በሚገባ ኣዳምጡ፤ ሕዝቡ የሚፈልገው በኣንድነትና በእኩልነት መኖር፣ በሰላም ወጥቶ መግባት፣ ፍትሕን ማስፈን፣ ለኑሮው የሚበቃ ምጣኔ ሃብትን ማግኘት፣ የእምነት ነጻነትና እኩልነት መረጋገጥ የመሳሰሉት ናቸው። ሕዝቡ እነዚህ ከተሟሉለት ተደመጠ ማለት ነው፤ ከተደመጠ ደግሞ እሱም በበኩሉ ያደምጣል፤ ይከተላልም፤ ስለሆነም ለሁሉም ልጆቻችንና ወገኖቻችን የምናስተላልፈው ወቅታዊ ጥሪ  ሁሉንም ችግሮቻችን በሰላምና በሰላም ብቻ ለመፍታት ተባበሩ የሚል ነው፤ ከዚህ ውጭ የሚደረገው ኣማራጭ ሁሉ ለዘላቂ ሰላማችን አይበጅም እንላለን።            በመጨረሻም፦ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ከበዓለ ትንሣኤ በኋላ በሃያ አምስተኛው ቀን የሚካሄደው ዓመታዊው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተጀመረ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑና ለመላው ኢትዮጵያውያን እናበስራለን!!! እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ! እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን!!! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ ኣበባ - ኢትዮጵያ

የ2018 ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ መክፈቻ በትላንትናው እለት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በጸሎት ተጀመረ። ©EOTC_TV
+2
የ2018 ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ መክፈቻ በትላንትናው እለት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በጸሎት ተጀመረ። ©EOTC_TV

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን ብሩክ ተክለሃይማኖት እናት አርፈው ሥርዓተ ቀብራቸውን ክፍለ ሐገር ፈጽመው የተመለሱ በመሆኑ መኖሪያ ቤታቸው ጎላ በታችኛው በር ድልድዩ አካባቢ በመገኘት እንዲሁም በ 0965561047 መደወል እንድናጽናናቸው  ይሁን።  የእናታችንን ነፍስ  ይማርልን ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com