የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
رفتن به کانال در Telegram
2 752
مشترکین
-224 ساعت
+197 روز
+5130 روز
آرشیو پست ها
+1
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የዕለቱ የአገልግሎት ዜና
ሰኔ 28/2018 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤታችን በሥራ አመራርነት፣ በኦዲትና ኢንስፔክሽን እንዲሁም በሥራ አስፈጻሚነት እንዲያገለግሉ ለተመረጡ አመራሮች በመልአከ ሰላም መ/ር ታዬ አብርሃም (ጋሽ ታዬ) የአባታዊ ምክር ተሰጥቷል። በዚህ የትምህርታዊ ምክር ጉባኤ 'የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንን ሥርዓት ጠብቆ በፍቅርና በአንድነት ማገልገል እንደሚገባ የተመከረ ሲሆን፤ እርስ በእርሳችን ከመነቃቀፍ ወጥተን ለቤተክርስቲያን በአንድነት ቆመን ማገልገል ይገባናል ሲሉ መልአከ ሰላም ታዬ አስረድተዋል።
በአገልግሎት ጸንቶ ለሌሎች ሕይወት ለመትረፍ በዘመኑ ያሉ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለብንም አሳስበውናል።
መረጃውን የሥራ አመራር ጽ/ቤት አድርሶናል።
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የዕለቱ የአገልግሎት ዜና
ዛሬ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤታችን በሥራ አመራርነት፣ በኦዲትና ኢንስፔክሽን እንዲሁም በሥራ አስፈጻሚነት እንዲያገለግሉ ለተመረጡ አመራሮች በመልአከ ሰላም መ/ር ታዬ አብርሃም (ጋሽ ታዬ) የአባታዊ ምክር ተሰጥቷል። በዚህ የትምህርታዊ ምክር ጉባኤ 'የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንን ሥርዓት ጠብቆ በፍቅርና በአንድነት ማገልገል እንደሚገባ የተመከረ ሲሆን፤ እርስ በእርሳችን ከመነቃቀፍ ወጥተን ለቤተክርስቲያን በአንድነት ቆመን ማገልገል ይገባናል ሲሉ መልአከ ሰላም ታዬ አስረድተዋል።
በአገልግሎት ጸንቶ ለሌሎች ሕይወት ለመትረፍ በዘመኑ ያሉ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለብንም አሳስበውናል።
መረጃውን የሥራ አመራር ጽ/ቤት አድርሶናል።
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
የክረምት ኮርስ ለሕፃናት
ትምህርቱ፦ ሐምሌ 6/2018 ዓ.ም ይጀምራል።
ይምጡ ይመዝገቡ ይማሩ ትምህርቱ ሰኞ፣ ረቡዕ እና አርብ ከ3:00-5:30 ድረስ ይሰጣል።
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የአገልግሎት ዜና
ለሰንበት ትምህርት ቤታችን በሥራ አመራር፣ በኦዲትና ኢንስፔክሽን፣ እንዲሁም በሥራ አስፈጻሚነት እንዲያገለግሉ ለተመረጡ አመራሮች የተዘጋጀውን የመዋቅር ሥልጠና በመ/ር ቃልኪዳን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሥልጠና ክፍል ተሰጠ።በዕለቱ ስለ አዲሱ የመዋቅር አደረጃጀት በሰፊው ገለጻ የተሰጠ ሲሆን ከአመራሮች የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው በአሰልጣኙ መልስና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
መረጃውን የሥራ አመራር ጽ/ቤት አድርሶናል።
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
የክረምት ኮርስ ለማዕከላውያን
እድሜያችሁ ከ13-18 ድረስ የሆነ በሙሉ
ትምህርቱ: - ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም ይጀምራል።
ይምጡ ይመዝገቡ ይማሩ ትምህርቱ ሰኞ ፣ ረቡዕ ፣ አርብ ከ9:00-11:00 እና እሑድ ከ4:00-6:30 ድረስ ይሰጣል።
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
የክረምት ኮርስ ለወጣቶች
ትምህርቱ- ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም ይጀምራል።
ይምጡ ይመዝገቡ ይማሩ ትምህርቱ ሰኞ ፣ ረቡዕ ፣ አርብ ከ12:00-1:30 እና እሑድ ከ4:00-6:30 ድረስ ይሰጣል።
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
የተልዕኮ ተማሪዎች የምርቃት መርሐግብር
የፊታችን እሑድ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም
ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ
በደብራችን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የሰሞኑ የአገልግሎት መረጃ
ባሳለፍነው ቅዳሜ በነበረው የሥራ አመራር ስብሰባ ላይ የአመራሩን የአገልግሎት ማስተባበሪያ ክፍል ድልድል እና የሥራ አስፈጻሚን እጩዎችን ከሦስት ቀን የጸሎተ እጣን እና የጸሎተ ማርያም ልመና በኃላ በእጣ የመለየት ተግባራት ተከናውኗል። በዚህም መሠረት የሥራ አመራር አጠቃላይ የአገልግሎት ማስተባበሪያ ክፍሎች ድልድል እንደሚከተለው ሲሆን
1. መ/ር ኢ/ር ዳዊት አበበ፦ የሥራ አመራር ሰብሳቢ
2. አቶ ላቀው ይርጋ ፦ የሥራ አመራር ም/ሰብሳቢ
3. ወ/ሮ ዮርዳኖስ ገ/ሚካኤል ፦ የሥራ አመራር ጸኃፊ
4. ወጣት አበራ መላኩ ፦ የሥራ አስፈጻሚ ሰብሳቢ (ዋና ሥራ አስፈጻሚ)
5. ወጣት በረከት ፍቅሩ ፦ እቅድ፣ ጥናትና ምርምር ማስተባበሪያ
6. ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖአምላክ ፦ ትምህርትና እቅበተ እምነት ማስተባበሪያ
7. ዲ/ን አሌክሳንደር ወ/ገብርኤል፦ አባላትና ተቋም አደረጃጀት ማስተባበሪያ
8. ዲ/ን ዳንኤል ተክሌ፦ ሚዲያና ሕዝብ ግንኙነት ማስተባበሪያ
9. መ/ሰ ዲ/ን ወንድወሰን መኮንን ፦ መረጃና ወቅታዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ
10. ወጣት አብርሃም አስራት ፦ ሒሳብና ንብረት አስተዳደር ማስተባበሪያ
11. አቶ ሙሉጌታ ሰማን ፦ ምጣኔ ሀብትና ማኅበራዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ
12. ወጣት ዮናታን ብርሃኔ ፦ ቴክኖሎጂ ትስስር ማስተባበሪያ
በተጨማሪም የሥራ አስፈጻሚ የአገልግሎት ክፍል ድልድል
1. ወ/ሮ ቤተልሔም ገነነው ፦ ም/ዋና ሥራ አስፈጻሚና ጸሐፊ
2. አቶ ዮናስ ይርዳው፦ ዕቅድ ትግበራ እና ክትትል ክፍል
3. ዲ/ን አብርሃም ታደሰ ፦ ትምህርትና ሥልጠና ክፍል
4. ዲ/ን ኪሩቤል መንገሻ ፦ መርሐግብር እና ጉባኤያት ክፍል
5. አቶ አለሙ ጉደታ ፦ መረጃ እና የውስጥ ግንኙነት ክፍል
6. አቶ እንግዳወርቅ አረፋይኔ ፦ መዝሙርና በዓላት ክፍል
7. አቶ ሔኖክ ኃይሉ ፦ ኪነ ጥበብና ሥነ ጥበብ ክፍል
8. አቶ ፍቃዱ ኪሮስ ፦ የሰው ሀብት አስተዳደር ክፍል
9. አቶ ተሾመ እንዳለ ፦ ልማትና በጎ አድራጎት ክፍል
10. ወ/ሮ አቻምየለሽ ደምሴ ፦ በጀትና ንብረት አስተዳደር ክፍል
መሆናቸውን እያሳወቅን። በቀጣይ ጊዜ ሥራ አመራሩና ሥራ አስፈጻሚው በየንዑስ ክፍላት የሚያገለግሉ አባላትን በጋራ ተወያይተን እንደምናሳውቅ ለመግለጽ እንወዳለን።
የሥራ አመራር ጽ/ቤት
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
እግዚአብሔር አምላካችን ለኢትዮጵያ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ ለመረጣቸው ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ወርሐዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ
የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤት በረከት አይለየን!!
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ማስታወቂያ ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ!
ሰንበት ትምህርት ቤታችን በተለያዩ ክፍላት ለአገልግሎት ስንጠቀምባቸው የነበሩት ሁሉም የባንክ አካውንቶች በጊዜያዊነት ስለተዘጉ በቀጣይ ለአገልግሎት የምንጠቀምበትን አካውንት እስከምንገልጽላችሁ ድረስ ምንም ዓይነት ገንዘብ ወደ አካውንት ቁጥራችን ገቢ እንዳትፈጽሙ ለማሳሰብ እንወዳለን።
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ሰኔ ሃያ ሦስት
በዚህች ቀን በእስራኤል ሁሉ ላይ የነገሠ በእግዚአብሔር የተመረጠ ንጉሠ እስራኤል ፣ ጠቢበ ጠቢባን ወልደ ዳዊት የሰሎሞን የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ማስታወቂያ ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ!
በተለያዩ ጊዜያት በአገልግሎት አማካኝነት በእጃችሁ ላይ የሚገኝን ማንኛውንም የሰንበት ት/ቤታችንን ንብረት እስከ ሰኔ 24/2018 ዓ.ም ለሚመለከተው የአገልግሎት ክፍል በመመለስ እንድትተባበሩን በአምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስም እናሳስባለን። በአካባቢያችሁ መራቅ ምክንያት እስከ ረቡዕ ድረስ መመለስ የማትችሉ አባላት ካላችሁ፤ ንብረቱ በእጃችሁ ላይ መኖሩን ለንብረትና ሒሳብ አስተዳደር ክፍል እንድታሳውቁ በአክብሮት እንጠይቃለን።
እግዚአብሔር ማኅበራችንን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
እመቤታችን
ሰኔ ሃያ አንድ በዚች ዕለት የአዳምና የዘሩ ድኅነት የተደረገባት አምላክን የወለደች የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የታላቁ በዓል መታሰቢያና በዓለም ሁሉ የቤተ ክርስቲያን መታነፅ መታሰቢያ ነው። ከሁሉ አስቀድሞ ያቺ ቤተ ክርስቲያን በሐዋርያት ዘመን ብቻዋን ታነፀች።
ይኸውም ጳውሎስና በርናባስ በአሕዛብ ውስጥ በሰበኩ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ከሰዎች ቤቶች በቀር ቅዱስ ቊርባንን የሚቀበሉበት ቤተ ክርስቲያንም አልነበራቸውም ነበር። ስለዚህም ወደ ጴጥሮስና ወደ ሐዋርያት ሁሉ ስለ ቤተ ክርስቲያን መታነፅ ጉዳይ እየለመኑ መልእክትን ላኩ።
ሐዋርያትም እንዲህ ብለው መለሱላቸው ክብር ይግባውና ያለ ጌታችን ፈቃድ እኛ ምንም ምን አንሠራም። ነገር ግን የምንሠራውን እስኪያስረዳን ድረስ ወደ እግዚአብሔር እየጸለዩና እየማለዱ አንድ ሱባኤ ይጾሙ ዘንድ ወደ ሃይማኖት የተመለሱ አሕዛብን እዘዙአቸው እንዲህም አዘዙአቸው።
በሱባዔውም ፍጻሜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጸላቸው ሐዋርያትንም ሁሉ ከየአገሮች ሁሉ እስከ ፊልጵስዮስ በደመና ሰበሰባቸው ከእርሳቸውም ጋር ጳውሎስና በርናባስ ነበሩ ጌታችንም ባረካቸው እንዲህም ብሎ ነገራቸው "ይቺ ዕለት በእናቴ በማርያም ስም በአራቱ ማእዘነ ዓለም አብያተ ክርስቲያናት እንድታንፁ የፈቀድኩባት ናት።"
ይህንንም ብሎ ከከተማዋ በስተ ምሥራቅ በኲል አወጣቸው የቤተ ክርስቲያኒቱንም ቦታና መሠረቷን ወሰነላቸው ከእርሳቸውም ጋራ የእግዚአብሔር ኃይል ነበረ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕንፃዋ እስከ ተፈፀመ ድረስ ደንጊያዎች በሐዋርያት እጆች ውስጥ ይለመልሙ ነበረ ጌታችንም ነዋየ ቅድሳቷን አልባሳትዋንና መሠዊያዋን አዘጋጀ።
ከዚህ በኋላ ጌታችን እጁን በጴጥሮስ ራስ ላይ ጭኖ በአራቱ ማእዘነ ዓለም ውስጥ "አርሳይሮስ" ብሎ ሾመው ይህም "ሊቀ ጳጳሳት" ማለት ነው። ለሐዋርያት አለቃ ጴጥሮስ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የጳጳሳት አለቃ ይሆን ዘንድ ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያሉ ሰማያውያን መላእክትና ምድራውያን ሰዎች ሦስት ጊዜ አሰምተው ተናገሩ።
ከዚህም በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን የቊርባኑን ቅዳሴ ሥርዓት ያከናውኑ ዘንድ ለሕዝቡም ሥጋውን ደሙን ያቀብሏቸው ዘንድ አዘዛቸው እንዲህም የሚል አለ ራሱ መድኃኒታችን ቀድሶ ሥጋውንና ደሙን ለሐዋርያት አቀበላቸው። እንዲህም አላቸው በዚች ቀን የእጃቸውን ሥራ እንዳይሠሩ ሕዝቡን ሁሉ አዘዙአቸው ይኸውም በሰኔ ወር ሃያ አንድ ቀን ነው።
ከዚህም በኋላ መድኃኒታችን ከእርሳቸው ዘንድ በታላቅ ክብር ወደ ሰማያት ዐረገ። ከዚያችም ቀን ጀምሮ አባቶቻችን ሐዋርያት በዓለሙ ሁሉ ውስጥ አምላክን በወለደች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም ቤተ ክርስቲያን የሚያሳንፁ ሆኑ።
የእመቤታችን በረከት በሁላችንም ላይ ይደር አሜን።
