uz
Feedback
Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

Kanalga Telegram’da o‘tish

EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት analitikasi

Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (@ethphi) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 945 obunachidan iborat bo'lib, Tibbiyot toifasida 1 513-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 150-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 945 obunachiga ega bo‘ldi.

17 Sentabr, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 259 ga, so‘nggi 24 soatda esa 16 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 13.47% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 7.90% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 147 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 259 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 18 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Tibbiyot toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 945
Obunachilar
+1624 soatlar
+897 kun
+25930 kun
Postlar arxiv
የኢትዮጵያ የድንገተኛ ህክምና ቡድን በዓለም ጤና ድርጅት እውቅና ባገኘበት ወቅት ከፋና ብሮድካስት ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ፡

Ethiopia Achieves Historic Milestone as First Civilian EMT Classified in WHO African Region ----------------------------------- National Emergency Medical Team (EMT) receives World Health Organization (WHO) Classification for Type 1 Fixed EMT, Strengthening Ethiopia’s Emergency Response Capacity Ethiopia has achieved a historic milestone in emergency medical response after its National Emergency Medical Team successfully obtained international classification from the WHO, becoming the first civilian EMT in the WHO African Region to be classified as a Type 1 Fixed Emergency Medical Team. The landmark achievement places Ethiopia among the pioneers in strengthening standardized emergency medical response capacity in the African Region, alongside Senegal’s military EMT, which has also achieved WHO classification. Prior to the verification, Ethiopia’s National EMT achieved a 96 out of 96 score against the WHO African Region EMT implementation framework, demonstrating its preparedness and compliance with the required standards. The team has evolved from Ethiopia’s Disaster Medical Assistance Team (DMAT), established in 2018, into a nationally structured emergency medical response team. The achievement was officially recognized during a ceremony jointly organized by the Ministry of Health and the Ethiopian Public Health Institute (EPHI) on September 15, 2026 in Addis Ababa. Ethiopia’s National EMT has already demonstrated its ability to respond to diverse emergencies and operate in challenging environments. Its previous deployments include the Gamo Zone landslide response in southern Ethiopia and emergency response activities related to Marburg Virus Disease, providing practical experience in rapid deployment, clinical care, coordination, and emergency operations. The development and strengthening of Ethiopia’s National EMT has been led by the Ministry of Health and EPHI, with technical and operational support from WHO, UK-Med, European Civil Protection and Humanitarian Aid Operations (ECHO), and partners of the Global EMT Network. Minister of Health Dr. Mekdes Daba emphasized that in an era of escalating global crises, standardized emergency preparation is essential, attributing the success to dedicated local responders and international partners including the WHO, UK-Med, the UK Foreign, Commonwealth & Development Office (FCDO), European Civil Protection and Humanitarian Aid Operations (ECHO), and the Spanish EMT. Deputy Minister of Health Dr. Dereje Duguma on his behalf commended the dedication of the clinicians, nurses, logisticians, and specialists who form the backbone of the team. The Director General of EPHI Dr. Mesay Hailu affirmed that the independent verification solidifies EPHI’s vision of serving as a continental center of excellence following its centennial, while Dr. Melkamu Abte, Dupty Director General of EPHI noted that the classification builds on the team's evolution since 2018—from its origins as a Disaster Medical Assistance Team (DMAT) responding to major mass casualty events and landslides to a fully integrated national and subnational emergency response architecture. Speaking for the global body, Prof. Francis Chisaka Kasolo commended Ethiopia’s sustained investment and leadership, noting that the country now sets a benchmark for thirty other African nations currently establishing national EMT units. The achievement further strengthens Ethiopia’s role in the regional and global EMT community ahead of the 7th EMT Global Meeting, scheduled to take place in Addis Ababa from November 3–5, 2026. The meeting will be particularly significant as it will be the first global EMT meeting to be hosted in the WHO African Region. Ministry of Health,Ethiopia, British Council Ethiopia, British Embassy, Addis Ababa - UK in Ethiopia, World Health Organization Ethiopia, World Health Organization (WHO), Africa CDC

Ethiopia achieves historic WHO verification of national Emergency Medical Team, becoming first civilian EMT in Africa to attain international classification https://www.afro.who.int/countries/ethiopia/news/ethiopia-achieves-historic-who-verification-national-emergency-medical-team-becoming-first-civilian

የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ግብዓቶች አቅርቦት ሰንሰለትን ለማጠናከር ሀገር አቀፍ ዕቅድ በመዘጋጀት ላይ ነው -------------------------------------- የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከዩኤስ አስፐር (US ASPR)፣ ከአሜሪካው የበሽታዎች ቁጥጥርና መከላከያ ማዕከል (US CDC) እና ከግሎባል ዋን ሄልዝ ጋር በመተባበር በድንገተኛ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ወቅት አስፈላጊዎቹን የቁጥጥር አቅርቦቶችን በወቅቱና በተቀናጀ መልኩ ለማድረስ የሚያስችል ብሔራዊ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች አቅርቦት ሰንሰለት ዕቅድ (National PHE MCM Plan) እያዘጋጀ ነው። ዕቅዱ በአደጋ ጊዜ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች አቅርቦት በትክክለኛው ጊዜ፣ በተገቢው መጠንና በሚያስፈልገው ቦታ እንዲደርሱ የሚያስችል የተቀናጀ ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችል ነው። በዕቅድ ዝግጅት አዉዳ ጥናቱ ላይ የተገኙት የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መልካሙ አብቴ፣ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች መኖራቸው ብቻ የሚሰጠውን ምላሽ ውጤታማ አያደርጉትም። የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች አቅርቦት በተገቢው ሁኔታ መለየት፣ ማሰራጨት፣ በአግባቡ አገልግሎት ላይ ኢንድዉልና የሰለጠኑ ባለሙያዎች እንዲኖሩ መደረጉ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል። ዶ/ር መልካሙ፣ ኢንስቲትዩቱ በሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ የልህቀት ማዕከል ለመሆን በሚያደርገው ጥረት፣ የበሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች አቅርቦትና የሎጂስቲክስ አስተዳደርን ማጠናከር ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑን ጠቁመው፣ ከማዕከላዊ የአቅርቦት ሥርዓት እስከ ክልሎች፣ የጤና ተቋማትና ታችኛው የማሕበረሰብ ክፍል ድረስ ያለውን የማከማቻ፣ የማሰራጨትና ምላሽ መስጫ ቦታ ድረስ (Last mile) የማድረስ ሂደት በተቀናጀ መልኩ ማስተዳደር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የኢንስቲትዩቱ የበሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ዝግጁነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ነኢማ ዘይኑ በበኩላቸው፣ ዕቅዱ በሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ ሁኔታዎች ወቅት ሕይወት አድን የሆኑ ግብዓቶች አቅርቦት በተፈለገው ጊዜና ቦታ እንዲደርሱ በማስቻል የሀገሪቱን የአደጋ ምላሽ አቅም እንደሚያጠናክር ገልጸው ዕቅዱ ተቋማት በቅንጅት እንዲሰሩ፣ የግብዓት ፍላጎትን በቅድሚያ መተንበይ ከማስቻሉም በላይ የክምችትና የስርጭት ሥርዓቶች እንዲጠናከሩ ጠንካራ መሠረት እንደሚፈጥርም አመላክተዋል። በአሜሪካው አስፐር ስር ያለው የስትራቴጂክ ናሽናል ስቶክፓይል (SNS) ከፍተኛ አማካሪ ማይክል አየርስ፣ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነት በማውሳት፣ በተቀናጀ መልኩ መሥራት በአደጋ ጊዜ አስፈላጊ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች በፍጥነት ለሚያስፈልጋቸው ሕብረተሰቦች እንዲደርሱ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ከኢንስቲትዩቱ ጋር ያለውን ቀጣይ ትብብር ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነትም አረጋግጠዋል። በአዉደ ጥናቱ የአቅርቦት ሰንሰለቱን ከመነሻ እስከ መድረሻ ያሉ የባለድርሻ አካላት ሚናና ኃላፊነትን መለየት፣ ማከማቸት፣ ማሰራጨት እና ከመነሻ እስከ መድረሻ ድረስ ያሉ ሂደቶች ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን መለየት፣ የአደጋ ምላሽ የቅንጅት ሥርዓትን ማጠናከር እንዲሁም የዝግጁነትና የምላሽ ዕቅድ ማዘጋጀት ላይ ውይይቶች ይካሄዳሉ። ዕቅዱ ተግባራዊ ሲሆን፣ በሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ወቅት የድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች አቅርቦቶች በፍጥነት፣ በተቀናጀና በውጤታማ ሁኔታ እንዲደርሱ በማስቻል የኢትዮጵያን የሕብረተሰብ ጤና ደህንነትና የአደጋ ምላሽ አቅምን ለማጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለሀገራችን ብሔራዊ የጤና ደህንነት የሚጠበቅበትን ኃላ
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለሀገራችን ብሔራዊ የጤና ደህንነት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በብቃት በመወጣት ላይ ይገኛል። ኢንስቲትዩቱ የጤና ላብራቶሪ አቅም ግንባታ ሥራዎችን በማጠናከር፣ የላቁ የሪፈራል እና ሪፈረንስ ላብራቶሪ ምርመራዎችን በማስፋፋት፣ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝት፣ ዝግጁነትና ምላሽ ሥራዎችን በማጠናከር፣ የጤናና ጤና ነክ መረጃዎችን በማደራጀትና በመተንተን፣ እንዲሁም የሕብረተሰብ ጤና ምርምሮችን በማካሄድ ተአማኒነት ያለው መረጃ በማመንጨት ለጤና ፕሮግራሞች እና ለፖሊሲ ግብዓትነት እንዲውል እያደረገ ይገኛል። ባለፈው ዓመት የጤና ሥጋቶችን በመከላከል፣ በምርምር፣ በላቦራቶሪ አቅም ግንባታ እና በጤና ደህንነት ሥራዎች አፈጻጸም ረገድ በርካታ ስኬታማ ተግባራትን አከናውነናል፡፡ በ2019 ዓ.ም. የሕብረተሰብ ጤናን ለመጠበቅ፣ የጤና ሥጋቶችን ቀድሞ በመለየትና በመከላከል፣ እንዲሁም ለችግሮች ፈጣን ምላሽ በመስጠት የጤና ደህንነት አቅማችንን ይበልጥ ለማጠናከር ከሁሉም አጋር ተቋማትና ከሕብረተሰባችን ጋር በላቀ ቅንጅትና ቁርጠኝነት የምናገለግል መሆኑን እንገልጻለን፡፡ እንኳን ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን!! አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የጤና እና የስኬት ዓመት ይሁንልን! ዶ /ር መሳይ ኃይሉ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር

አረንጓዴ አሻራን ከጤና ጋር በማጣመር የአየር ንብረት ስጋትን ቀድሞ ለመከላከል እየተሰራ ነው -------------- ኢትዮጵያ፦ የአየር ንብረት ሳይንስን ከሕብረተሰብ ጤናና ከሥነ-ምግብ ሳይንስ ጋር በማቀናጀት የቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ የትንበያና የዝግጁነት ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ። “A Centennial Legacy and Beyond: Transforming Risk Forecast into Health and Nutrition Action in Climate Impact Ethiopia” በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደው መድረክ፣ የአየር ንብረት መረጃና ትንበያን ከጤናና ከሥነ-ምግብ ውሳኔዎች ጋር በማገናኘት የሚከሰቱ የጤና ስጋቶችን ቀድሞ ለመለየት፣ ለመከላከልና ለመመለስ የተሰሩ ሥራዎች፣ የተገኙ ውጤቶችና የወደፊት አቅጣጫዎች ተመልክተዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ ኢንስቲትዩቱ ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ ያካበተውን የጤናና የሥነ-ምግብ ምርምር ልምድ በመጠቀም የአየር ንብረት ስጋቶችን ቀድሞ ለመለየት፣ ለመተንበይና ለመዘጋጀት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ድርቅ፣ ጎርፍ፣ ከፍተኛ ሙቀትና የምግብ እጥረት በሕብረተሰቡ ጤና ላይ የሚያሳድሩትን ተፅዕኖ ለመቀነስ የምርምርና የትንበያ መረጃን ወደ ተጨባጭ የጤና እርምጃ መቀየር ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ዶ/ር መሳይ በንግግራቸው አረንጓዴ አሻራ የአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን የጤና ልማት አካል መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች የአየር ጥራትን ከማሻሻል፣ የከተማ ሙቀትን ከመቀነስና የተፈጥሮ ሀብትን ከመጠበቅ ባለፈ ለሕብረተሰቡ አካላዊና አእምሯዊ ደህንነት አዎንታዊ አስተዋፅኦ እንዳላቸው ገልጸዋል። “አየር ንብረትና ጤና የተለያዩ ጉዳዮች ሳይሆኑ በአንድ የሕይወት ሰንሰለት የተሳሰሩ ጉዳዮች ናቸው” ያሉት ዶ/ር መሳይ፣ የአየር ንብረት ስጋትን መቀነስ የጤና ስጋትንም ቀድሞ መቀነስ መሆኑን አመልክተዋል። በመድረኩ የቀረቡት ሳይንሳዊ ጥናቶችም በተለይ የአረንጓዴ አሻራ ሥራዎች በአካባቢ፣ በአየር ንብረትና በሕብረተሰብ ጤና ላይ ያላቸውን ተፅዕኖ ለመረዳት ላይ ያተኮሩ መሆናቸው ተገልጿል። በተለይም በከተሞች የሚከናወኑ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ለአየር ንብረት መላመድ፣ ለአካባቢ ጤናና ለጤናማ ኑሮ ያላቸውን ሚና የሚያሳዩ ማስረጃዎች ቀርበዋል። ዶ/ር መሳይ እንዳሉት፣ “አረንጓዴ አሻራ የምንተክለው ዛፍ ብቻ ሳይሆን፣ ለትውልድ የምንገነባው የጤናማ አካባቢና የተሻለ ሕይወት መሠረት ነው።” በመሆኑም የአረንጓዴ ልማትን ከጤና ልማት ጋር በማጣመር የአየር ንብረት-ተቋቋሚ የጤና ሥርዓት መገንባት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ሜትሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ፈጠነ ተሸመ በበኩላቸው፣ የአየር ንብረት ሳይንስን ወደ ጤና ትንበያና ውሳኔ ለመቀየር ተቋማዊ ቅንጅት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። እንደ ኤልኒኖ ያሉ የአየር ንብረት ክስተቶች የውሃ ወለድ በሽታዎችን፣ ወባንና ሌሎች በሽታዎችን ሊያባብሱ በመቻላቸው፣ ቅድመ ማስጠንቀቂያንና የጤና ሥርዓት ዝግጁነትን ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል። የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ የአየር ንብረት ለውጥ ከአካባቢ ጉዳይ ባለፈ ቀጥተኛ የሕብረተሰብ ጤና ስጋት መሆኑን ጠቁመዋል። የአየር ንብረት፣ የጤናና የሥነ-ምግብ መረጃዎችን በማቀናጀት በጥናት፣ በቅድመ ትንበያና በፈጣን ምላሽ ላይ መስራት እንደሚገባም አመልክተዋል። ኢንስቲትዩቱ ኮሌራ፣ ወባና ዴንጊ ትኩሳትን ጨምሮ በአየር ንብረት ሊባባሱ የሚችሉ በሽታዎችን ቀድሞ ለመተንበይና የላብራቶሪ አቅምን ለማጠናከር እየሰራ መሆኑንም ዶ/ር ጌታቸው ገልጸዋል። የሥርዓተ-ምግብ፣ አካባቢ ጤና እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ማስረሻ ተሰማ መድረኩ የአየር ንብረት ቅኝትንና ሳይንሳዊ ምርምርን በማገናኘት የጤና ስጋቶችን ቀድሞ ለመለየትና ለመከላከል የሚያስችል መፍትሄ-ተኮር መድረክ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህን የተቀናጀ ሥራ በተሳለጠ መልኩ ለማስኬድ “የአየር ንብረት፣ ጤና እና አመጋገብ የዕውቀት ማዕከል” ተቋቁሞ በኢንስቲትዩቱ መሪነት ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በጥምረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል። ማዕከሉ የአየር ንብረት፣ ጤናና ሥነ-ምግብ መረጃዎችን በማጣመር ለውሳኔ ሰጪዎችና ለጤና ሥርዓቱ ቀድሞ የሚያስጠነቅቁ ሳይንሳዊ መረጃዎችን ለማቅረብ እንዲሁም ምርምርን ወደ ተግባራዊ የጤና እርምጃ ለመቀየር የሚያግዝ መድረክ መሆኑ ተጠቁሟል። በተጨማሪም በመድረኩ የቀረቡ ጥናቶች በተለይ በአዲስ አበባ በኮሪደር ልማት የተከናወኑ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች በአካባቢ ጤናና በአየር ንብረት መላመድ ላይ ያላቸውን አዎንታዊ አስተዋፅኦ ያሳዩ መሆናቸው ተገልጿል። የአረንጓዴ አሻራን በማበረታታት የሕብረተሰብ ጤናን ለማጠናከር የተያዘውን ቁርጠኝነት በተግባር ለማሳየትም የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተርና ም/ዋና ዳይሬክተሮች በኢንስቲትዩቱ ግቢ ውስጥ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ እፅዋትን ተክለዋል። በአጠቃላይ፣ የአየር ንብረት መረጃን ወደ ተጨባጭ የጤና እርምጃ መቀየር፣ ምርምርን ማጠናከር፣ የአረንጓዴ ልማትን ማስፋፋትና ተቋማዊ ቅንጅትን ማሳደግ አየር ንብረት-ተቋቋሚ የጤና ሥርዓት ለመገንባት ቁልፍ መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በወረርሽኝና በሌሎች የሕብረተሰብ ድንገተኛ የጤና አደጋዎች ወቅት የሚያገለግሉ የለይቶ ማከሚያና ማቆያ ማዕከላትን አቅም ለማጠናከር የሚያስችል በክልል ሆስፒታሎች ለሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ። ——————————————- ስልጠናው በተለይም በድንበርና በድንበር አካባቢ ያሉ የጤና ተቋማት የበሽታ ስርጭት ስጋትን በመቀነስ፣ ወረርሽኝ ሲከሰት የተጠረጠሩና የተረጋገጡ ታካሚዎችን በተገቢው አለማቀፍ መመዘኛን ባሟላ መልኩ ለይቶ ለማከምና ለማቆየት የሚያስችል አቅምን በማጠናከር ላይ አተኩሯል። በዚህም በለይቶ ማከሚያና ማቆያ ማዕከላት የኢንፌክሽን መከላከልና ቁጥጥር (IPC)፣ የግል መከላከያ መሳሪያዎች (PPE) እና ውሃ፣ ንጽህናና ንጽህና አጠባበቅ (WASH) ዝግጁነትን በማጠናከር የበሽታ ስርጭትን በተለይም በድንበር አካባቢ ለመቆጣጠር የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ትኩረት የሰጠ ነበር። የ አንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ምላሽና መልሶ ማገገም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መድሀንዬ ተክለጺዮን፣ በስልጠናው እንደተናገሩት ኢንስቲትዩቱ በድንገተኛ የጤና አደጋም ሆነ በወረርሽኝ ወቅት ትክክለኛና ውጤታማ ምላሽ ለመስጠት የለይቶ ማከሚያ ማዕከላትን ማጠናከርና ባለሙያዎችን በማብቃት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ መድሀንዬ፣ የኢንፌክሽን መከላከልና ቁጥጥር ሥርዓትን ማጠናከር የጤና ባለሙያዎችን ወረርሽኝ ሲከሰት የሕክምና አገልግሎት ሲሰጡ ከኢንፌክሽን ለመጠበቅ፣ በጤና ተቋማት የሚከሰትን የኢንፌክሽን ስርጭት ለመቀነስና በተለይም በድንበር አካባቢ የበሽታ ስርጭት ስጋትን ለመቆጣጠር ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። የውኃ፣ የንፅህና እና የንጽህና አጠባበቅ አገልግሎት (WASH) ዲቪዥን ኃላፊ ወ/ሮ ሀና መኮንን በበኩላቸው፣ ስልጠናው ከWHO/ከአለም ጤና ድርጅት እና ሌሎች አጋሬች በትብብር የተሰጠ መሆኑን ተናግረው በወረርሽኝና በሌሎች የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ወቅት በይበልጥም የለይቶ ማከሚያ ማእከላት እንዲጠናከሩ በተጨማሩም በማቆያ የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ለኢንፌክሽን እንዳይጋለጡ ፣ ተገቢውን PPE መጠቀምና የIPC መርሆችን በትክክል መተግበር ራሳቸውን፣ ባልደረቦቻቸውን፣ ታካሚዎችንና ማኅበረሰቡን ለመጠበቅ ስልጠናው እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል። ስልጠናው በጤና ተቋማት በተለይም ደግሞ በለይቶ ማከሚያ ወይም ማቆያ ማዕከላት ሊከሰቱ የሚችሉ የኢንፌክሽን ስጋቶችን በተሻለ ለመረዳትና ተግባራዊ የመከላከያ እርምጃዎችን ለመውሰድ የሚረዳ ሲሆን፣ በተለይም ደግሞ PPEን በትክክል የመልበስና የማውለቅ ልምምድ ተግባራዊ እውቀት እንዳስጨበጣቸው ሰልጣኞች ተናግረዋል።