fa
Feedback
Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

رفتن به کانال در Telegram

EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

کانال Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (@ethphi) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 747 مشترک است و جایگاه 1 688 را در دسته پزشکی و رتبه 2 290 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 747 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 30 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 270 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 14 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 16.50% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.28% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 2 432 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 221 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 01 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته پزشکی تبدیل کرده‌اند.

14 747
مشترکین
+1424 ساعت
+1077 روز
+27030 روز
آرشیو پست ها
  The workshop concluded with a shared commitment among participating countries and partners to advance data harmonization, strengthen interoperability, and promote regional collaboration. The agreed roadmap is expected to enhance research quality, improve health information systems, and support more effective national and regional health policies, ultimately contributing to better maternal, newborn, and child health outcomes across the region.

EPHI Leads Regional Workshop to Advance Data Harmonization and Interoperability for Maternal and Child Health Systems -----------------   The Ethiopian Public Health Institute (EPHI), through its Health System Research Directorate, successfully concluded a four-day Data Harmonization and Interoperability Systems Workshop under the Horizon Europe-funded LINDA-FAMILIA Project, reaffirming its commitment to strengthening digital health systems and evidence-based healthcare across Africa.   Held from June 28 to July 1, 2026, at the Capital Hotel and Spa in Addis Ababa, the workshop brought together experts and partners from Ethiopia, Rwanda, Uganda, Tanzania, to harmonize maternal, newborn, child health, and infectious disease data systems. The LINDA-FAMILIA project is being implemented across Ethiopia, Rwanda, Uganda, and Tanzania to improve health systems through interoperable digital platforms that enhance maternal, newborn, and child health services, disease surveillance, clinical decision-making, and the use of real-time health data.   Opening the workshop, Dr. Aderajew Mekonnen, Director of EPHI's Health System Research Directorate and Principal Investigator of the LINDA-FAMILIA Project in Ethiopia, emphasized that harmonized data standards are fundamental to improving data quality, strengthening evidence-based decision-making, and achieving better health outcomes.   He noted that the workshop would establish a shared understanding of existing maternal and child health data dictionaries, develop a standardized framework, and define a core set of harmonized variables aligned with World Health Organization recommendations while addressing country-specific priorities. Dr. Aderajew also underscored the importance of achieving technical interoperability, particularly through the integration of Electronic Medical Record (EMR) systems with District Health Information Software 2 (DHIS2), to enhance data exchange and support more efficient health information systems.   Dr. Aderajew acknowledged the technical leadership of Professor Ali Kashan of University College Cork, Ireland, and Dr. Mahima Venkateswar of the Norwegian Institute of Public Health, as well as the contributions of the Ministry of Health and other project partners. He encouraged participants to actively share experiences, identify common data elements and existing gaps, and jointly develop harmonized definitions and coding standards to strengthen maternal and child health information systems and disease surveillance across participating countries.   Throughout the workshop, participants reviewed existing national data dictionaries, mapped variables against World Health Organization recommendations, and discussed the development of standardized datasets to support interoperable digital health systems. The discussions focused on producing harmonized data definitions, standardized coding rules, and a practical implementation framework to improve data quality, reporting, and health service delivery.   Prof. AliAli Kashan facilitated technical sessions aimed at improving the comparability of maternal health data across participating countries. Participants assessed existing data collection tools using a structured 50-variable framework, examined the availability and quality of priority data elements, explored opportunities for federated research, identified implementation gaps, and developed country-specific policy briefs. The workshop also produced a joint regional roadmap outlining shared priorities, implementation timelines, and collaborative actions.   In parallel, Dr. Mahima Venkateswar led practical sessions on strengthening interoperability between health information systems, with particular emphasis on integrating EMR platforms with DHIS2. Through technical presentations and hands-on discussions, participants enhanced their understanding of system integration, data exchange mechanisms, and real-time reporting processes tailored to country-specific contexts.

ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቫይራል ሎድ (VL) እና የጨቅላ ህጻናት የኤች አይ ቪ ምርመራ (EID) ፕሮግራሞች የ2018 ዓ.ም. አገር አቀፍ የአፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ከጤና ሚኒስቴር እና ከCU-ICAP ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የ2018 ዓ.ም. አገር አቀፍ የኤች አይ ቪ ቫይራል ሎድ (HIV Viral Load/VL testing) እና የጨቅላ ህጻናት የኤች አይ ቪ ምርመራ (Early Infant Diagnosis/EID) የአፈጻጸም ግምገማ መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ ከሰኔ 22-24/ 2018 ዓ.ም አካሂዷል። በመድረኩ የጤና ሚኒስቴር፣ የክልል ጤና ቢሮዎች፣ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ የክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች/የክልል ሪፈራል ላቦራቶሪዎች፣ የናሙና ማጓጓዣ አገልግሎት ሰጪ ተቋም፣ አጋር ድርጅቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሳሮ አብደላ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ በበጀት ዓመቱ በዚህ ዘርፍ የተገኙ አበረታች ውጤቶች እና በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ መፍታት ያለባቸውን ተግዳሮቶች የዳሰሱ ሲሆን፣ አያይዘውም የኤች አይ ቪ ቫይራል ሎድ እና የጨቅላ ህጻናት የኤች አይ ቪ ምርመራ አገልግሎቶች የኤች አይ ቪ ህክምናን ውጤታማ ለማድረግ እና በማስረጃ ላይ የተመሰረተ የህክምና ውሳኔ ለመስጠት ያላቸውን ወሳኝ ሚና አጽንኦት ሰጥተዋል። በተጨማሪም ይህንን እና ሌሎች የጤና የላቦራቶሪ አገልግሎቶችን ጥራት፣ ተደራሽነትና ቀጣይነት ለማሻሻል የሰው ኃይል አቅምን፣ መሣሪያዎችንና ግብዓቶችን ለማጠናከር ኢንስቲትዩቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በጤና ሚኒስቴር የኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ያደታ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ይህ አውደ-ጥናት በዋናነት የተዘጋጀበትን ዓላማ እና ከዚህ ዓመታዊ የስራ አፈጻጸም ግምገማ የሚገኙ ግኝቶችን በተግባር በመተግበር ሀገራዊ ግቦችን ለማሳካት ሁሉም አካላት በትብብርና በባለቤትነት እንዲሰሩ አሳስበዋል። በበጀት ዓመቱ ለተገኙ ቁልፍ ውጤቶችም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት አመስግነዋል። በአውደ-ጥናቱ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ከክልሎች እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት አፈጻጸም በጽሑፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ በዋናነትም በክፍተት የተገመገሙ እና መሻሻል ያለባቸው ሥራዎች ተለይተው የማሻሻያ ዕቅድ በማውጣት አውደ-ጥናቱ ተጠናቋል።

የካውንት ዳውን 2030 ጉባኤ በአዲስ አበባ ተጀምሯል ---------------------- የዘላቂ ልማት ግቦችን (Sustainable Development Goals 2030 /SDG/) መነሻ በማድረግ በመላው አፍሪካ የሚገኙ የጤና መረጃዎችን፣ የእናቶች እና የህፃናት ጤና አፈጻጸምን ለመገምገም የተዘጋጀው “ካውንትዳውን 2030” (Countdown 2030) የተሰኘው አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ። በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በተዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ ከ36 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የጤና ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች እና የአለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ ኢትዮጵያ በእናቶችና ህፃናት ጤና ላይ ያስመዘገበችውን ፈጣን ለውጥ አብራርተዋል። ሚኒስትሯ እንደገለጹት፣ ሀገሪቱ ባደረገችው የተቀናጀ ጥረት የእናቶች ሞት ምጣኔን በ100 ሺህ በህይወት ከሚወልዱ ህፃናት ውስጥ ወደ 141 ዝቅ ማድረግ የቻለች ሲሆን፣ ይህም በአህጉር ደረጃ ካሉ ምርጥ ተሞክሮዎች አንዱ ነው። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያና መከላከል ማዕከል (Africa-CDC) መቀመጫ መሆኗ፣ አህጉራዊ ድንበር ዘለል የጤና ስጋቶችንና ወረርሽኞችን በጋራ ለመከላከል ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አክለዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ በበኩላቸው፣ ኢንስቲትዩቱ ጥራት ያለው መረጃ በማመንጨትና እንደ ማርበርግ ቫይረስ በሽታ እና ኤምፖክስ ያሉ አደገኛ በሽታዎችን በፍጥነት በመለየት ረገድ የዳበረ አቅም እንዳለው ገልጸው ይህም አፍሪካውያን በራሳቸው አቅም ሀገር-በቀል የጤና መረጃ ባለቤትነት በመሸጋገር ላይ እንደሚገኙ ማሳያ መሆኑንና ይህም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል። በተጨማሪም ዶ/ር መሳይ በሳምንቱ ውስጥ የሚከናወኑት የቴክኒክ ስራዎች በመረጃ ትንተና ላይ የዘመኑ መገልገያዎችን እና ዘዴዎችን በመጠቀም የቴክኒክ ክህሎትን ማሳደግ፣ ጥራት ያላቸው የትንታኔ ሪፖርቶችን ማውጣት፣ የአገልግሎት ተደራሽነትን በመፈተሽና ተሞክሮዎችን በመካፈል በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር እና መረጃዎች ከፖሊሲ ግብአትነት ወደ ተግባር መተርጎማቸውን ማረጋገጥ ከጉባኤው አላማዎች ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑ በዝርዝር አብራርተዋል። የ“ካውንትዳውን 2030” ዳይሬክተር ዶ/ር ቼኪህ ፋይ፣ ይህ ስብስብ የቴክኒክ ትንታኔን ከአመራር ቁርጠኝነት ጋር ያቀናጀ መሆኑን ገልጸው፣ ዋናው ዓላማው የተሻለ መረጃን ወደተሻለ የፖሊሲ ውሳኔና ውጤት መቀየር እንደሆነ አስገንዝበዋል። ጉባኤው እስከ ሳምንቱ መጨረሻ የሚቀጥል ሲሆን፣ ሀገራት እስከ 2030 በቀሩት ጥቂት ዓመታት ውስጥ በጤናው ዘርፍ ሊያከናውኗቸው በሚገቡ ስልታዊ ኢንቨስትመንቶች ላይ የጋራ መግባባት ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በማስረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ አሰጣጥ ለሕብረተሰብ ጤና ወሳኝ መሆ ኑ ተገልጿል:: በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ አሰጣጥ (Evidence-Informed Decision-Making – EIDM) ጉባኤ በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ እየተካሄደ ሲሆን የጤና ስርዓቶችን በዕውቀት፣ በማስረጃና በትብብር ማጠናከር የወቅቱ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተገለጸ። በጉባኤው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ፣ ጉባኤው የጤና ስርዓቶችን በዕውቀት፣ በማስረጃና በትብብር ለማጠናከር ያለውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያንፀባርቅ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ዶክተር መሳይ አክለው እንዳሉት፣ ኢንስቲትዩቱ ከ1924ዓ.ም ጀምሮ በርካታ የሕብረተሰብ ጤና ስራዎችን ሲሰራ እንደነበር አስታውሰው ኢንስቲትዩቱ የላቦራቶሪ አገልግሎቶችን በሀገር አቀፍ ደረጃ በማስፋፋት፣ በሥነ-ምግብ ጥናት፣ በሕብረተሰብ ጤና ክትትል፣ በድንገተኛ የጤና አደጋ ዝግጅትና ምላሽ ዘርፎች ጉልህ ሚና በመጫወት የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ስርዓት ዋነኛ ምሰሶ ሆኖ መቆየቱንም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም በሀገር ደረጃ አንጋፋ ተቋም በመሆን በአፍሪካ ደረጃም የልህቀት ማእከል መሆኑን ገልጸዋል። የዘንድሮው ጉባኤ ከኢንስቲትዩቱ ተልዕኮና ስትራቴጂያዊ እቅድ ጋር በቅርበት የተሳሰረ መሆኑን የገለጹት ዶክተር መሳይ፣ ኢንስቲትዩቱ ከተለያዩ ምንጮች የጤናና ከጤና ጋር ተያያዥ መረጃዎችን በመሰብሰብ ብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደርና ቅመራ ትንተና ማዕከል የማቋቋምና የማስተዳደር ኃላፊነት እንደተሰጠው አስታውሰዋል። በተጨማሪም ብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደርና ቅመራ ትንተና ማዕከሉ የጤና መረጃዎችን በመሰብሰብ ብቻ ሳይሆን በማደራጀት፣ በደህንነት በመጠበቅ በማስተዳደርና ወደ ተግባራዊ ማስረጃ በመቀየር ለውሳኔ አሰጣጥ እንደሚያገለግል ገልጸዋል። በተለይም የሰው፣ የእንስሳትና የአካባቢ ጤናን በሚያስተሳስረው የ"አንድ ጤና" አቀራረብ ውስጥ የዲጂታል ማከማቻዎች የተለያዩ ማስረጃዎች የሚገናኙባቸው ወሳኝ ስፍራዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል። የብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደርና ትንተና ማዕከል ዳይሬክተር ዶክተር ትዕግስት ሹመት በበኩላቸው፣ አውደ ጥናቱ መረጃን ለጤና ፖሊሲ ግብዓት፣ማስረጃ ተኮር ውሳኔ አሰጣጥ እንዴት መጠቀም እንደሚቻል ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ዶክተር ትዕግስት ማብራሪያ፣ ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት ከ600 በላይ የሚሆኑ የጤና እና ጤና ነክ መረጃዎችን በመሰብሰብ፣ በማደራጀትና በማከማቸት ለሀገራዊ የጤና ውሳኔዎች ግብዓት እያደረገ ይገኛል። እነዚህ መረጃዎች በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር፣ የጤና ፖሊሲዎችን ለመቅረጽ እና በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ ውሳኔዎችን ለማሳለጥ ጥቅም ላይ እየዋሉ ነው። ዶክተር ትግስት አክለውም፣ ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ጀምሮ የተደራጁ የጤና መረጃዎች የተለያዩ የጤና ስጋቶችን እና ወረርሽኞችን ለመቆጣጠር በተደረጉ ትንተናዎች እና ምላሾች ውስጥ በቀጥታ አስተዋጽኦ እንዳበረከቱ ገልጸዋል። የመረጃ ልውውጥና ትብብርን ለማጠናከር ከ195 በላይ የመንግሥት፣ የግል፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች በመረጃ አሰባሰብ ላይ እንዳሉና መረጃ ልውውጥ ዙሪያ የተቀናጀ ትብብር ማድረግ እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ተናጋሪዎቹ በጋራ ያስተላለፉት መልዕክት፣ የተጣራና የተደራጀ መረጃን ወደ ተግባራዊ ማስረጃ በመቀየር በጤና ዘርፍ የሚሰጡ ውሳኔዎች በታማኝ መረጃ ላይ እንዲመሰረቱ ማድረግ የጤና ሥርዓቱን ለማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ነው። በጉባኤው ከጤና ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI)፣ ከአርማወር ሀንሰን የምርምር ተቋም (AHRI)፣ ከጤና ሚኒስቴር ስር ካሉ ኤጀንሲዎች፣ ከፌዴራል ሆስፒታሎች፣ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከአጋር ተቋማት የተውጣጡ ተመራማሪዎች፣ ፖሊሲ አውጭዎች፣ የፕሮግራም መሪዎችና ከፍተኛ የጤና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። The 2026 Evidence-Informed Decision-Making (EIDM) Conference officially opened in Addis Ababa at the Adwa Victory Memorial Museum Hall, bringing together health leaders, policymakers, researchers, and stakeholders to strengthen the use of evidence in Ethiopia’s health system. The conference aims to promote data-driven decision-making and foster collaboration among institutions working to improve public health outcomes across the country. Opening the event, Ethiopian Public Health Institute (EPHI) Director General Dr. Mesay Hailu said the conference reflects a shared commitment to advancing health systems through knowledge, innovation, evidence, and partnership. He noted that EPHI has grown into a nationally respected institution and a continental center of excellence, making significant contributions in vaccine production, laboratory services, nutrition research, public health surveillance, and emergency preparedness. Dr. Mesay added that the conference aligns with EPHI’s mandate to manage the National Health Data Management and Analytics Center, which transforms health data into actionable evidence for policymaking and planning. National Health Data Management and Analytics Center Director Dr. Tigist Shumete said the conference focuses on leveraging data to support health policy development, knowledge management, and evidence-informed decisions. She highlighted that the Institute currently manages health-related data from more than 600 institutions and sources, helping to guide disease prevention, policy formulation, and national health planning. Dr. Tigist called for stronger collaboration among over 195 public institutions, private organizations, NGOs, and universities, while participants emphasized that converting high-quality data into actionable evidence is essential for building a more responsive and resilient health system in Ethiopia.

ለድንገተኛ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ዓመታዊ የመድኃኒት ፈላጐትና አቅርቦትን የተመለከተ ዓውደ ጥናት በመካሄድ ላይ ይገኛል ---------------- የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የቅድመ ዝግጁነትና አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ብሔራዊ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቢከሰቱ ሊኖር የሚችለውን የመድኃኒት ፍላጐትና አቅርቦት በመተንበይ (National Public Health Emergency Supply Forecasting Annual Exercise) ከኢንስቲትዩቱ፣ ከተለያዩ ተቋማት እና ከአጋር ድርጅት ባለሙያዎች ጋር በጋራ በመሆን ዓመታዊ የልምምድ አውደ ጥናት በቢሾፍቱ ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል። አዉደ ጥናቱ ጠንካራ የሆነ የግብአት አቀርቦት ከብሔራዊ እስከ ወረዳ ድረስ ማንኛውም ሊከሰቱ ለሚችሉ የተፈጥሮና ሰዉ ሰራሽ አደጋዎች (natural disaster, humanitarian crisis, infectious disease outbreak) ያልተቆራረጠ የመድኃኒት አቅርቦትና ፈጣን የሆነ ምላሽ መስጠት ለማስቻል ያለመ መሆኑን ከመድረኩ ተመላክቷል። የኢንስቲትዩቱ የቅድመ ዝግጁነትና አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ነዒማ ዘይኑ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ለመስራት ከታቀዱ ተግባራት መካከል አንዱ ይህ ዓመታዊ የግብአት ፍላጎት ትንቢያ ሲሆን ወቅቱም የሚቀጥለዉን በጀት ዓመት ዕቅድ የሚታቀድበት እንደመሆኑ በመገባደድ ላይ ያለውን እንዲሁም ወቅታዊ የበሽታዎች ወረርሽኝ ስርጭት መረጃዎችን በመጠቀም ሊከሰቱ ይችላሉ ተብለዉ ለሚገመቱ ወረርሽኞች የሚዉሉ ግብአቶችን ለማቀድ የተዘጋጀ መድረክ ነው፡፡ ወ/ሮ ነዒማ አያይዘውም የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከርና ቀጣይነት ያለዉ ምላሽ ለመስጠት የሚጠቅም በመሆኑ ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን እየተሰራ ያለ ስራ ሲሆን ይህ ስራ በየአመቱ አቅም የመጨመርና የቅድመ ዝግጁነት አቅምን ለማጎልበትም እንደሚረዳ አስረድተዋል፡፡

NDMC Conducts HDSS Report Writing Workshop The National Data Management Centre (NDMC) of the Ethiopian Public Health Institute (EPHI), in collaboration with the London School of Hygiene & Tropical Medicine (LSHTM), successfully organized a three-day Health and Demographic Surveillance System (HDSS) Report Writing Workshop from June 15 to 17, 2026. The main objective of the workshop was to support participants in finalizing high-quality annual HDSS reports using a harmonized reporting framework. This framework promotes consistency and comparability across HDSS sites and strengthens the use of evidence for health policy and planning. The workshop also emphasized the development of concise one-page briefs to effectively communicate key findings to technical experts and policymakers. Dr. Tigist Shumet, Director of NDMC encouraged participants to take full advantage of the opportunity to enhance the quality of their reports and strengthen their report-writing skills. The workshop brought together participants from seven Ethiopian universities—Jimma, Arba Minch, Addis Ababa, Mekelle, Gondar, Hawassa, and Haramaya Universities—all of which operate Health and Demographic Surveillance System (HDSS) sites in the country. The workshop was conducted as part of the Strengthening Ethiopian Surveys and Analytics (SESA) project, funded by the Gates Foundation, which aims to strengthen the generation and use of policy-relevant evidence in reproductive, maternal, neonatal, child, and adolescent health and nutrition (RMNCAH+N). Mr. Yoseph Zeru from the Ministry of Health’s Strategic Affairs Lead Executive Office attended the closing session and commended the collaborative efforts of NDMC-EPHI, LSHTM, and the seven HDSS universities under the SESA-HDSS program in strengthening HDSS data analytics and report-writing capacity. He highlighted the importance of high-quality, standardized reports in supporting evidence-informed decision-making within the health sector. Participants of the workshop  expressed strong appreciation for the workshop, noting that the harmonized reporting framework and peer-learning approach would significantly improve the quality, consisteny, and usefulness of HDSS annual reports. Many participants described the workshop as a valuable platform for strengthening collaboration and promoting standardized reporting practices across HDSS sites in Ethiopia.

የአሜሪካ ኤምባሲ ምክትል የሚሽን ኃላፊ ካትሪን ሮድሪጌዝ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን ጎበኙ የአሜሪካ ኤምባሲ ምክትል የተልዕኮ ኃላፊ ካትሪን ሮድሪጌዝ በኢትዮጵያና በአሜሪካ መካከል በሕብረተሰብ ጤና ዙሪያ የሚደረገው ትብብር የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ስጋቶች አስቀድሞ ለመከላከል እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን በኢንስቲትዩቱ በመገኘት ጎብኝተዋል:: የተከበሩ ካትሪን ሮድሪጌዝ በጉብኝታቸው ወቅትም እንደተናገሩት በአሜሪካ የበሽታ ቁጥጥር እና መከላከል ማዕከል ( US CDC) የሚደገፉ ፕሮግራሞች ኢትዮጵያውያንንና አሜሪካውያንን እንደ የኢቦላ ወረርሽኝ ካሉ አዳዲስ የጤና ስጋቶች ለመጠበቅ እየሰሩ መሄኑን ተናግረው ትብብሩ በዚህ ብቻ ሳይወሰን በዓለም አቀፍ የጤና ደህንነት፣ በኤችአይቪ/ኤድስ፣ በክትባት፣ በላቦራቶሪ ሥርዓት እና በድንገተኛ ጤና ምላሽ ዘርፎች ጭምር እንደሆነ ተናግረዋል:: የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ሀይሉ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በሕብረተሰብ ድንገተኛ የጤና አደጋዎችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ፣የብሄራዊ ላብራቶሪ የአቅም ግንባታ ላይ፣ እንዲሁም በሕብረተሰብ ጤና ምርምር ዘርፍ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረው የብሄራዊ የጤና መረጃ እና የአንድ ጤና ላይም ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣቱን አስረድተዋል:: በአሜሪካ እና በኢትዮጵያ መካከል የሚደረጉ ትብብሮች የላቦራቶሪ ምርመራ ፣ የድንገተኛ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ምላሽ ሥርዓቶችን እና የጥናትና ምርምር ስራዎችን በማጠናከር የሀገራትን አቅም በማጎልበት ረገድ ሚናቸው ከፍተኛ በመሆኑ ትብብሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል::በኢንስቱትዩቱ የተደረገው ጉብኝትም የትብብሩን ደረጃ የሚያሳይ በመሆኑ ለአሜሪካ መንግስትና ሕዝብ ምስጋናቸውን አቅርበዋል:: https://ephi.gov.et/የአሜሪካ-ኤምባሲ-ምክትል-የሚሽን-ኃላፊ-ካ/ The Ethiopian Public Health Institute (EPHI) was pleased to welcome Ms. Catherine Rodriguez, Deputy Chief of Mission of the U.S. Embassy in Ethiopia, for a visit to the Institute to observe the longstanding partnership between Ethiopia and the United States in strengthening public health and health security. During the visit, Ms. Rodriguez discussed with Dr. Mesay Hailu, the Director General of the EPHI, and witnessed the impact of collaborative efforts in disease surveillance, laboratory diagnostics, emergency preparedness and response, immunization, HIV/AIDS, and broader global health security initiatives. The discussions also highlighted the joint commitment to preventing, detecting, and responding to emerging public health threats, including Ebola, Marburg, mpox, cholera, measles, polio, malaria, tuberculosis, and HIV. The visit reaffirmed the strong partnership between EPHI, the U.S. Government, and the U.S. Centers for Disease Control and Prevention (CDC) in building resilient public health systems and enhancing national and regional capacity to protect communities from current and future health threats. EPHI values the continued collaboration with its partners and remains committed to advancing public health excellence for a healthier and safer Ethiopia. https://ephi.gov.et/የአሜሪካ-ኤምባሲ-ምክትል-የሚሽን-ኃላፊ-ካ/

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የፓንደሚክ ፈንድ የቦርድ ተባባሪ ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ __ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የፓንደሚክ ፈንድ የበላይ ቦርድ ተባባሪ ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል። የፓንደሚክ ፈንድ ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸዉ አገራትን አቅም በመገንባት ድንገተኛ የጤና አደጋ ክስተቶችን ለመከላከል፣ ለመለየትና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተቋቋመ መሊቲላተራል ፋይናንሲንግ አሰራር ሲሆን ሚኒስትሯ በአዲሱ ኃላፊነታቸው ዓለም አቀፍ አጋርነቶች እንዲጠናክር እና አገራት ወረርሽኞችን ለመከላከል ለሚያደርጉት ኢንቨስትመንት የሚሰጠውን ድጋፍ በበላይነት በመምራት ለዉጥ እንደሚያመጡ ፈንዱ ያለዉን እምነት ገልጸዋል፡፡ ዶ/ር መቅደስ ኃላፊነቱን የተረከቡት ከሩዋንዳ ጤና ሚኒስትር ከሆኑት ከዶ/ር ሳቢን ንሳንዚማና ሲሆን፣ ሚኒስትሯ ባስተላለፉት መልዕክት የህብረተሰባችንን ህይወት መታደግ የሚችልና የዓለምን የጤና ደህንነት ዋስትናን የሚያረጋግጥ ጠንካራ የጤና ስርዓት በመገንባት ለትዉልድ ማስተላለፍ አለብን ብለዋል።

3ኛው ዙር የመሰረታዊ ፊልድ ኢፒዲሞሎጂ (Frontline-FETP- VPD Track) ሰልጣኝ የጤና ባለሙያዎች ተመረቁ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ማዕከል የቅድመ ዝግጁነትና አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከተለያዩ ክልሎች ከሚገኙ የወረዳ ጤና ተቋማት የተውጣጡና ለ3 ወራት መሰረታዊ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ (Frontline-FETP-VPD Track) ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር እና የክትባት መርሃ ግብር (Expanded Program on Immunization /EPI) ባለሙያዎች ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ተመረቁ። የስልጠናው ዋና ዓላማ የጤና ባለሙያዎችን የእውቀትና የክህሎት አቅም በማሳደግ፣ በክትባት የምንከላከላቸውን በሽታዎች የቅኝት እና የልየታ ስራዎችን በማከናወን ፈጣን ምላሽ በመስጠት የሕብረተሰቡን ጤና የማስጠበቅ ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግ ነው፡፡ ዶ/ር መልካሙ አብቴ የኢንስቲትቱ ም/ዋና ዳይሬክተር በምርቃት ስነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው እንደገለጹት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እነዚህን መሰል በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተቁመው፣ በመሰረታዊ ፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ስልጠና የጤና ባለሙያዎችን አቅም ማሳደግና በማጎልበት በቀጣይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱን የልህቀት ማዕከል ከማድረግ ጎን ለጎን የባለሙያዎችን አቅም ከፍ በማድረግና የሁሉንም ቅንጅታዊ ስራዎች በማሳደግ ለሌሎች አገራት ተምሳሊት የሆነ ውጤታማ ስራ ለማስመዝገብ ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱን ገልፀዋል። ም/ዋና ዳይሬክተሩም አያይዘው ተመራቂዎች ያገኙትን እውቀት፣ ክህሎት እና ልምድ በመጠቀም በጋራና በቅንጅት ሕብረተሰቡ ዘንድ ሊደርስ የሚችል ከፍተኛ ለውጥ ማሳየት የሚችል ተግባር ማከናወን እንደሚገባቸውና፣ ለዚህም የኢንስቲትዩቱ ድጋፍ እና ቁርጠኝነት ትልቅ መሆኑን ተናግረዋል:: ወ/ሮ ነኢማ ዘይኑ የኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ማዕከል የቅድመ ዝግጁነትና አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር እና የክትባት መርሃ ግብር ባለሙዎች በቅንጅት የሰለጠኑበት የስልጠና ፕሮግራም በአይነቱ ለየት ያለና የመጀመሪያ መሆኑን እንዲሁም ባለሙያዎች ያአገኙትን እውቀትና ግንዛቤ በመጠቀም የተሰጣቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡ የኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ማዕከል ባለሙያ እና የስልጠናው አስተባባሪ አቶ ጃፋር ከዛሊ በበኩላቸው ለሶስት ወራት የአቅም ግንባታ ስልጠና የተከታተሉት የጤና ባለሙያዎች በክትባት የምንከላከላቸው በሽታዎች አስመልክቶ የቅኝት፣ የልየታ እና ፈጣን ምላሽ አሰጣጥ ላይ የተሻለ የእውቀት፣ የክሕሎትና የግንዛቤ አቅምን እንዲያጎለብቱ ስልጠናው በጥልቀት መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ አቶ ደግሰው ደርሶ ጤና ጥበቃ የክትባት አገልግሎት ተወካይና ዶ/ር ታጠቅ ቦጋለ የአፍሪካ ቀንድ አገራት የአፍኔት(AFENET) ድርጅት ሪጂናል አስተባባሪ ስልጠናውን አስመልክቶ የየራሳቸውን መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን አፍሪካ ሲዲሲ (US Centers for Disease Control and Prevention/CDC) እና አፍኔት (African Field Epidemiology Network /AFENET) የቴክኔክና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውን ከስልጠናው አስተባባሪ መረዳት ተችሏል፡፡ ሰልጣኝ ባለሙያዎቹ በበኩላቸው በስራ ቦታቸው የተሰጧቸውን የፊልድ ፕሮጀክቶች አጠናቀው በጽሁፍና በግንባር ገለጻ (Presentation) አማካኝነት መገምገማቸውን ጠቅሰው፣ ስልጠናው በተሰማሩበት የሥራ ዘርፍ ውጤታማ ሥራዎችን ለማስመዝገብና ለሕብረተሰቡ የሚሰጡትን የዕለት ከዕለት የጤና አገልግሎቶች በተሻለ መንገድ ተግባራዊ ለማድረግ ከፍተኛ አቅም እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል። በአጠቃላይ ስልጠናውን በብቃት ተከታትለው ያጠናቀቁና በአማካይ 70 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ 14 የኮርሱ ተሳታፊ የጤና ባለሙያዎች የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።