fa
Feedback
Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

رفتن به کانال در Telegram

EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

کانال Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (@ethphi) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 912 مشترک است و جایگاه 1 519 را در دسته پزشکی و رتبه 2 151 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 912 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 14 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 241 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 21 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 13.20% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.79% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 2 101 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 240 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 15 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته پزشکی تبدیل کرده‌اند.

15 912
مشترکین
+2124 ساعت
+867 روز
+24130 روز
آرشیو پست ها
Ethiopia achieves historic WHO verification of national Emergency Medical Team, becoming first civilian EMT in Africa to attain international classification https://www.afro.who.int/countries/ethiopia/news/ethiopia-achieves-historic-who-verification-national-emergency-medical-team-becoming-first-civilian

የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ግብዓቶች አቅርቦት ሰንሰለትን ለማጠናከር ሀገር አቀፍ ዕቅድ በመዘጋጀት ላይ ነው -------------------------------------- የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከዩኤስ አስፐር (US ASPR)፣ ከአሜሪካው የበሽታዎች ቁጥጥርና መከላከያ ማዕከል (US CDC) እና ከግሎባል ዋን ሄልዝ ጋር በመተባበር በድንገተኛ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ወቅት አስፈላጊዎቹን የቁጥጥር አቅርቦቶችን በወቅቱና በተቀናጀ መልኩ ለማድረስ የሚያስችል ብሔራዊ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች አቅርቦት ሰንሰለት ዕቅድ (National PHE MCM Plan) እያዘጋጀ ነው። ዕቅዱ በአደጋ ጊዜ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች አቅርቦት በትክክለኛው ጊዜ፣ በተገቢው መጠንና በሚያስፈልገው ቦታ እንዲደርሱ የሚያስችል የተቀናጀ ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችል ነው። በዕቅድ ዝግጅት አዉዳ ጥናቱ ላይ የተገኙት የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መልካሙ አብቴ፣ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች መኖራቸው ብቻ የሚሰጠውን ምላሽ ውጤታማ አያደርጉትም። የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች አቅርቦት በተገቢው ሁኔታ መለየት፣ ማሰራጨት፣ በአግባቡ አገልግሎት ላይ ኢንድዉልና የሰለጠኑ ባለሙያዎች እንዲኖሩ መደረጉ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል። ዶ/ር መልካሙ፣ ኢንስቲትዩቱ በሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ የልህቀት ማዕከል ለመሆን በሚያደርገው ጥረት፣ የበሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች አቅርቦትና የሎጂስቲክስ አስተዳደርን ማጠናከር ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑን ጠቁመው፣ ከማዕከላዊ የአቅርቦት ሥርዓት እስከ ክልሎች፣ የጤና ተቋማትና ታችኛው የማሕበረሰብ ክፍል ድረስ ያለውን የማከማቻ፣ የማሰራጨትና ምላሽ መስጫ ቦታ ድረስ (Last mile) የማድረስ ሂደት በተቀናጀ መልኩ ማስተዳደር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የኢንስቲትዩቱ የበሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ዝግጁነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ነኢማ ዘይኑ በበኩላቸው፣ ዕቅዱ በሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ ሁኔታዎች ወቅት ሕይወት አድን የሆኑ ግብዓቶች አቅርቦት በተፈለገው ጊዜና ቦታ እንዲደርሱ በማስቻል የሀገሪቱን የአደጋ ምላሽ አቅም እንደሚያጠናክር ገልጸው ዕቅዱ ተቋማት በቅንጅት እንዲሰሩ፣ የግብዓት ፍላጎትን በቅድሚያ መተንበይ ከማስቻሉም በላይ የክምችትና የስርጭት ሥርዓቶች እንዲጠናከሩ ጠንካራ መሠረት እንደሚፈጥርም አመላክተዋል። በአሜሪካው አስፐር ስር ያለው የስትራቴጂክ ናሽናል ስቶክፓይል (SNS) ከፍተኛ አማካሪ ማይክል አየርስ፣ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነት በማውሳት፣ በተቀናጀ መልኩ መሥራት በአደጋ ጊዜ አስፈላጊ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች በፍጥነት ለሚያስፈልጋቸው ሕብረተሰቦች እንዲደርሱ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ከኢንስቲትዩቱ ጋር ያለውን ቀጣይ ትብብር ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነትም አረጋግጠዋል። በአዉደ ጥናቱ የአቅርቦት ሰንሰለቱን ከመነሻ እስከ መድረሻ ያሉ የባለድርሻ አካላት ሚናና ኃላፊነትን መለየት፣ ማከማቸት፣ ማሰራጨት እና ከመነሻ እስከ መድረሻ ድረስ ያሉ ሂደቶች ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን መለየት፣ የአደጋ ምላሽ የቅንጅት ሥርዓትን ማጠናከር እንዲሁም የዝግጁነትና የምላሽ ዕቅድ ማዘጋጀት ላይ ውይይቶች ይካሄዳሉ። ዕቅዱ ተግባራዊ ሲሆን፣ በሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ወቅት የድንገተኛ አደጋ ግብዓቶች አቅርቦቶች በፍጥነት፣ በተቀናጀና በውጤታማ ሁኔታ እንዲደርሱ በማስቻል የኢትዮጵያን የሕብረተሰብ ጤና ደህንነትና የአደጋ ምላሽ አቅምን ለማጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለሀገራችን ብሔራዊ የጤና ደህንነት የሚጠበቅበትን ኃላ
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለሀገራችን ብሔራዊ የጤና ደህንነት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በብቃት በመወጣት ላይ ይገኛል። ኢንስቲትዩቱ የጤና ላብራቶሪ አቅም ግንባታ ሥራዎችን በማጠናከር፣ የላቁ የሪፈራል እና ሪፈረንስ ላብራቶሪ ምርመራዎችን በማስፋፋት፣ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝት፣ ዝግጁነትና ምላሽ ሥራዎችን በማጠናከር፣ የጤናና ጤና ነክ መረጃዎችን በማደራጀትና በመተንተን፣ እንዲሁም የሕብረተሰብ ጤና ምርምሮችን በማካሄድ ተአማኒነት ያለው መረጃ በማመንጨት ለጤና ፕሮግራሞች እና ለፖሊሲ ግብዓትነት እንዲውል እያደረገ ይገኛል። ባለፈው ዓመት የጤና ሥጋቶችን በመከላከል፣ በምርምር፣ በላቦራቶሪ አቅም ግንባታ እና በጤና ደህንነት ሥራዎች አፈጻጸም ረገድ በርካታ ስኬታማ ተግባራትን አከናውነናል፡፡ በ2019 ዓ.ም. የሕብረተሰብ ጤናን ለመጠበቅ፣ የጤና ሥጋቶችን ቀድሞ በመለየትና በመከላከል፣ እንዲሁም ለችግሮች ፈጣን ምላሽ በመስጠት የጤና ደህንነት አቅማችንን ይበልጥ ለማጠናከር ከሁሉም አጋር ተቋማትና ከሕብረተሰባችን ጋር በላቀ ቅንጅትና ቁርጠኝነት የምናገለግል መሆኑን እንገልጻለን፡፡ እንኳን ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን!! አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የጤና እና የስኬት ዓመት ይሁንልን! ዶ /ር መሳይ ኃይሉ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር

አረንጓዴ አሻራን ከጤና ጋር በማጣመር የአየር ንብረት ስጋትን ቀድሞ ለመከላከል እየተሰራ ነው -------------- ኢትዮጵያ፦ የአየር ንብረት ሳይንስን ከሕብረተሰብ ጤናና ከሥነ-ምግብ ሳይንስ ጋር በማቀናጀት የቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ የትንበያና የዝግጁነት ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ። “A Centennial Legacy and Beyond: Transforming Risk Forecast into Health and Nutrition Action in Climate Impact Ethiopia” በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደው መድረክ፣ የአየር ንብረት መረጃና ትንበያን ከጤናና ከሥነ-ምግብ ውሳኔዎች ጋር በማገናኘት የሚከሰቱ የጤና ስጋቶችን ቀድሞ ለመለየት፣ ለመከላከልና ለመመለስ የተሰሩ ሥራዎች፣ የተገኙ ውጤቶችና የወደፊት አቅጣጫዎች ተመልክተዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ ኢንስቲትዩቱ ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ ያካበተውን የጤናና የሥነ-ምግብ ምርምር ልምድ በመጠቀም የአየር ንብረት ስጋቶችን ቀድሞ ለመለየት፣ ለመተንበይና ለመዘጋጀት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ድርቅ፣ ጎርፍ፣ ከፍተኛ ሙቀትና የምግብ እጥረት በሕብረተሰቡ ጤና ላይ የሚያሳድሩትን ተፅዕኖ ለመቀነስ የምርምርና የትንበያ መረጃን ወደ ተጨባጭ የጤና እርምጃ መቀየር ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ዶ/ር መሳይ በንግግራቸው አረንጓዴ አሻራ የአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን የጤና ልማት አካል መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች የአየር ጥራትን ከማሻሻል፣ የከተማ ሙቀትን ከመቀነስና የተፈጥሮ ሀብትን ከመጠበቅ ባለፈ ለሕብረተሰቡ አካላዊና አእምሯዊ ደህንነት አዎንታዊ አስተዋፅኦ እንዳላቸው ገልጸዋል። “አየር ንብረትና ጤና የተለያዩ ጉዳዮች ሳይሆኑ በአንድ የሕይወት ሰንሰለት የተሳሰሩ ጉዳዮች ናቸው” ያሉት ዶ/ር መሳይ፣ የአየር ንብረት ስጋትን መቀነስ የጤና ስጋትንም ቀድሞ መቀነስ መሆኑን አመልክተዋል። በመድረኩ የቀረቡት ሳይንሳዊ ጥናቶችም በተለይ የአረንጓዴ አሻራ ሥራዎች በአካባቢ፣ በአየር ንብረትና በሕብረተሰብ ጤና ላይ ያላቸውን ተፅዕኖ ለመረዳት ላይ ያተኮሩ መሆናቸው ተገልጿል። በተለይም በከተሞች የሚከናወኑ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ለአየር ንብረት መላመድ፣ ለአካባቢ ጤናና ለጤናማ ኑሮ ያላቸውን ሚና የሚያሳዩ ማስረጃዎች ቀርበዋል። ዶ/ር መሳይ እንዳሉት፣ “አረንጓዴ አሻራ የምንተክለው ዛፍ ብቻ ሳይሆን፣ ለትውልድ የምንገነባው የጤናማ አካባቢና የተሻለ ሕይወት መሠረት ነው።” በመሆኑም የአረንጓዴ ልማትን ከጤና ልማት ጋር በማጣመር የአየር ንብረት-ተቋቋሚ የጤና ሥርዓት መገንባት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ሜትሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ፈጠነ ተሸመ በበኩላቸው፣ የአየር ንብረት ሳይንስን ወደ ጤና ትንበያና ውሳኔ ለመቀየር ተቋማዊ ቅንጅት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። እንደ ኤልኒኖ ያሉ የአየር ንብረት ክስተቶች የውሃ ወለድ በሽታዎችን፣ ወባንና ሌሎች በሽታዎችን ሊያባብሱ በመቻላቸው፣ ቅድመ ማስጠንቀቂያንና የጤና ሥርዓት ዝግጁነትን ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል። የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ የአየር ንብረት ለውጥ ከአካባቢ ጉዳይ ባለፈ ቀጥተኛ የሕብረተሰብ ጤና ስጋት መሆኑን ጠቁመዋል። የአየር ንብረት፣ የጤናና የሥነ-ምግብ መረጃዎችን በማቀናጀት በጥናት፣ በቅድመ ትንበያና በፈጣን ምላሽ ላይ መስራት እንደሚገባም አመልክተዋል። ኢንስቲትዩቱ ኮሌራ፣ ወባና ዴንጊ ትኩሳትን ጨምሮ በአየር ንብረት ሊባባሱ የሚችሉ በሽታዎችን ቀድሞ ለመተንበይና የላብራቶሪ አቅምን ለማጠናከር እየሰራ መሆኑንም ዶ/ር ጌታቸው ገልጸዋል። የሥርዓተ-ምግብ፣ አካባቢ ጤና እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ማስረሻ ተሰማ መድረኩ የአየር ንብረት ቅኝትንና ሳይንሳዊ ምርምርን በማገናኘት የጤና ስጋቶችን ቀድሞ ለመለየትና ለመከላከል የሚያስችል መፍትሄ-ተኮር መድረክ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህን የተቀናጀ ሥራ በተሳለጠ መልኩ ለማስኬድ “የአየር ንብረት፣ ጤና እና አመጋገብ የዕውቀት ማዕከል” ተቋቁሞ በኢንስቲትዩቱ መሪነት ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በጥምረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል። ማዕከሉ የአየር ንብረት፣ ጤናና ሥነ-ምግብ መረጃዎችን በማጣመር ለውሳኔ ሰጪዎችና ለጤና ሥርዓቱ ቀድሞ የሚያስጠነቅቁ ሳይንሳዊ መረጃዎችን ለማቅረብ እንዲሁም ምርምርን ወደ ተግባራዊ የጤና እርምጃ ለመቀየር የሚያግዝ መድረክ መሆኑ ተጠቁሟል። በተጨማሪም በመድረኩ የቀረቡ ጥናቶች በተለይ በአዲስ አበባ በኮሪደር ልማት የተከናወኑ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች በአካባቢ ጤናና በአየር ንብረት መላመድ ላይ ያላቸውን አዎንታዊ አስተዋፅኦ ያሳዩ መሆናቸው ተገልጿል። የአረንጓዴ አሻራን በማበረታታት የሕብረተሰብ ጤናን ለማጠናከር የተያዘውን ቁርጠኝነት በተግባር ለማሳየትም የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተርና ም/ዋና ዳይሬክተሮች በኢንስቲትዩቱ ግቢ ውስጥ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ እፅዋትን ተክለዋል። በአጠቃላይ፣ የአየር ንብረት መረጃን ወደ ተጨባጭ የጤና እርምጃ መቀየር፣ ምርምርን ማጠናከር፣ የአረንጓዴ ልማትን ማስፋፋትና ተቋማዊ ቅንጅትን ማሳደግ አየር ንብረት-ተቋቋሚ የጤና ሥርዓት ለመገንባት ቁልፍ መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በወረርሽኝና በሌሎች የሕብረተሰብ ድንገተኛ የጤና አደጋዎች ወቅት የሚያገለግሉ የለይቶ ማከሚያና ማቆያ ማዕከላትን አቅም ለማጠናከር የሚያስችል በክልል ሆስፒታሎች ለሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ። ——————————————- ስልጠናው በተለይም በድንበርና በድንበር አካባቢ ያሉ የጤና ተቋማት የበሽታ ስርጭት ስጋትን በመቀነስ፣ ወረርሽኝ ሲከሰት የተጠረጠሩና የተረጋገጡ ታካሚዎችን በተገቢው አለማቀፍ መመዘኛን ባሟላ መልኩ ለይቶ ለማከምና ለማቆየት የሚያስችል አቅምን በማጠናከር ላይ አተኩሯል። በዚህም በለይቶ ማከሚያና ማቆያ ማዕከላት የኢንፌክሽን መከላከልና ቁጥጥር (IPC)፣ የግል መከላከያ መሳሪያዎች (PPE) እና ውሃ፣ ንጽህናና ንጽህና አጠባበቅ (WASH) ዝግጁነትን በማጠናከር የበሽታ ስርጭትን በተለይም በድንበር አካባቢ ለመቆጣጠር የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ትኩረት የሰጠ ነበር። የ አንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ምላሽና መልሶ ማገገም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መድሀንዬ ተክለጺዮን፣ በስልጠናው እንደተናገሩት ኢንስቲትዩቱ በድንገተኛ የጤና አደጋም ሆነ በወረርሽኝ ወቅት ትክክለኛና ውጤታማ ምላሽ ለመስጠት የለይቶ ማከሚያ ማዕከላትን ማጠናከርና ባለሙያዎችን በማብቃት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ መድሀንዬ፣ የኢንፌክሽን መከላከልና ቁጥጥር ሥርዓትን ማጠናከር የጤና ባለሙያዎችን ወረርሽኝ ሲከሰት የሕክምና አገልግሎት ሲሰጡ ከኢንፌክሽን ለመጠበቅ፣ በጤና ተቋማት የሚከሰትን የኢንፌክሽን ስርጭት ለመቀነስና በተለይም በድንበር አካባቢ የበሽታ ስርጭት ስጋትን ለመቆጣጠር ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። የውኃ፣ የንፅህና እና የንጽህና አጠባበቅ አገልግሎት (WASH) ዲቪዥን ኃላፊ ወ/ሮ ሀና መኮንን በበኩላቸው፣ ስልጠናው ከWHO/ከአለም ጤና ድርጅት እና ሌሎች አጋሬች በትብብር የተሰጠ መሆኑን ተናግረው በወረርሽኝና በሌሎች የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ወቅት በይበልጥም የለይቶ ማከሚያ ማእከላት እንዲጠናከሩ በተጨማሩም በማቆያ የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ለኢንፌክሽን እንዳይጋለጡ ፣ ተገቢውን PPE መጠቀምና የIPC መርሆችን በትክክል መተግበር ራሳቸውን፣ ባልደረቦቻቸውን፣ ታካሚዎችንና ማኅበረሰቡን ለመጠበቅ ስልጠናው እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል። ስልጠናው በጤና ተቋማት በተለይም ደግሞ በለይቶ ማከሚያ ወይም ማቆያ ማዕከላት ሊከሰቱ የሚችሉ የኢንፌክሽን ስጋቶችን በተሻለ ለመረዳትና ተግባራዊ የመከላከያ እርምጃዎችን ለመውሰድ የሚረዳ ሲሆን፣ በተለይም ደግሞ PPEን በትክክል የመልበስና የማውለቅ ልምምድ ተግባራዊ እውቀት እንዳስጨበጣቸው ሰልጣኞች ተናግረዋል።

IOM Donates Thermal Imaging Cameras to EPHI to Strengthen Health Surveillance ----------------------- The International Organization for Migration (IOM) has donated and officially handed over 14 thermal imaging cameras to the Ethiopian Public Health Institute (EPHI) to strengthen health surveillance and early detection of public health threats at Ethiopia’s Points of Entry (PoEs) with emphasis at Bole International Airport (BIA). The equipment will enhance the capacity of health authorities to conduct efficient, non-contact temperature screening and support the early identification of travelers who may require further health assessment, particularly during outbreaks and other public health emergencies. Dr. Mesay Hailu, Director General of EPHI, and Dr. Melkamu Abte, Deputy Director General, received the equipment on behalf of EPHI. The handover reflects the continued collaboration between IOM and EPHI in strengthening health security, disease surveillance, preparedness, and response capacities at Ethiopia’s borders. IOM’s current Ethiopia response plan specifically highlights support for disease surveillance and outbreak preparedness at Points of Entry. The donated equipment is expected to contribute to stronger, technology-enabled surveillance systems and improved preparedness to detect and respond to emerging public health threats.

የእብድ ውሻ በሽታ የላቦራቶሪ ምርመራን (Rabies Testing) ለማጠናከር የሚያግዝ አውደ ጥናት ተካሄደ ------------------------- የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የላቦራቶ
+3
የእብድ ውሻ በሽታ የላቦራቶሪ ምርመራን (Rabies Testing) ለማጠናከር የሚያግዝ አውደ ጥናት ተካሄደ ------------------------- የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የላቦራቶሪ አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ከUK Health Security Agency (UKHSA) ጋር በመተባበር በቢሾፍቱ ከተማ ያዘጋጀው የእብድ ውሻ በሽታ የላቦራቶሪ ምርመራን ለማጠናከር የሚያግዝ አውደ ጥናት ተካሄደ። በአውደ ጥናቱ ላይ የክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች፣ የእንስሳት ጤና እና ሌሎች የባለድርሻ አካላት ተወካዮች ተሳትፈዋል። በአውደ ጥናቱ ላይ የተገኙት የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሳሮ አብደላ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከጤና ሚኒስቴር፣ ከክልሎች እና ከዩኤስ-ሲዲሲ (US-CDC) ጋር በመተባበር በሽታውን ለመመርመር የሚያስችል አቅም በኢንስቲትዩቱ እና በተወሰኑ ክልሎች ማደራጀት በመቻሉ በላቦራቶሪ ምርመራ በኩል በርካታ ሥራዎች ተከናውነዋል። ይሁን እንጂ ይህ አገልግሎት የብዙ-ዘርፎችን (Multi-sectoral) ትብብር የሚጠይቅ በመሆኑ ክፍተቶችን ለማሻሻል በቀጣይ በቅንጅት መሥራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በተለይም የእብድ ውሻ በሽታ የላቦራቶሪ ምርመራ አገልግሎትን ለማጠናከር ከማህበረሰብ ግንዛቤ ጀምሮ ሊሠሩ የሚገባቸው ዘርፈ ብዙ ሥራዎች እንዳሉ አንስተው፤ በእንስሳት ጤና ዘርፍ በሽታውን የመከላከል እንዲሁም በላቦራቶሪ ፈጥኖ የመመርመር አቅምን ለማሳደግ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በየደረጃው ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። በንግግራቸው ማጠቃለያም ይህንን አገልግሎት ለበርካታ ዓመታት በከፍተኛ ኃላፊነት ያስቀጠሉ የኢንስቲትዩቱን እና የክልል ከፍተኛ ባለሙያዎችን፣ እንዲሁም በሀገራችን ከፍተኛ ዝግጅት የሚፈልጉ ላቦራቶሪዎችን በማደራጀት ዘርፍ ቁልፍ አጋ