የአካባቢ ወጣቶች መዝሙራት
Kanalga Telegram’da o‘tish
የተመረጡ የማህበራት እና የካሴት መዝሙራትን የሚያገኙበት፣ ወቅታዊና አሁናዊ መረጃዎችን የሚጋሩበት እንዲሁም የተለያዩ መፅሀፍትንና ትረካዎችንና የመሳሰሉትን የሚያገኙበት ድንቅ ቻናል ተቀላቀሉን ብዙ ያተርፉበታል። ለአስተየትዎ @Natnael1201
Ko'proq ko'rsatish2 013
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+47 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
Postlar arxiv
2 013
◦•●◉ በታማኝነቱ የተመሰገነ ◉●•◦
በታማኝነቱ የተመሰገነ
ለእመቤታችን ጠባቂ የሆነ
ዮሴፍ አረጋዊ ይባርከን ፀሎትህ
ምሳሌ ሆኖናል ብርሃን ህይወትህ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ማዕረግ ቅድስና ታላቅ ስለሆነ
ከእስራኤል አባቶች እጣው ለአንተ ሆነ
ጌታን ለማሳደግ በቅተሀል በፀጋ
በአተረፍከው መክሊት በተሰጠህ ዋጋ/2/
◦•●◉።።።።።።።አዝ።።።።።።።◉●•◦
በረሃብ በስደት ልብህ አልተፈታ
ለፈጠረ ሕፃን ታምነሃል ለጌታ
ተጋድሎህን አልገታ ድካም ሽምግልና
በረታ ጉልበትህ በአምላክ እንደገና/2/
◦•●◉።።።።።።።አዝ።።።።።።።◉●•◦
የዳዊት ልጅ ዮሴፍ እጅግ አስተማርከን
ጠባቂ እና አባት ሆነህ በሌት በቀን
የድንግልን ሀዘን ሰቆቃ ስደት
ተካፍለህ ወስደሃል ታላቅ በረከት/2/
◦•●◉።።።።።።።አዝ።።።።።።።◉●•◦
የሰማዩን ኪዳን የአብን አደራ
በትንሿ ቤትህ ጠበክም ሳትፈራ
በዓለም ስደተኛ የሆነው ሕፃን
አደገ በቤትህ ታላቁ መድህን/2/
2 013
🍀🍀🍀🍀🍀🍀
መዝሙር ዘሰንበት
🍁🍁🍁🍁🍁🍁
ከሐምሌ ፳፬ እስከ ሐምሌ ፴
(በ፫/ሙ) ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ
በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ፤ምህሮሙ ወይቤሎሙ አክብሩ ሰንበትየ፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ፤ በሰንበት አጋንንተ አውጽአ ወበቃሉ እለ ለምፅ አንጽሐ ፤በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ በሰንበት ወረቀ ምድረ ወገብረ ፅቡረ ወበምራቁ አሕየወ ዕውረ፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ዘይኤዝዞሙ ለደመናት ያውርዱ ዝናመ ውስተ ኵሉ ምድር፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ያውርዱ ዝናመ ውስተ ኵሉ ምድር ውስተ ፍና ኀበ ይትፈቀድ መካን፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ውስተ ፍና ኀበ ይትፈቀድ መካን ከመ ኅቡረ ይትፈሣሕ ዘይዘርዕ ወየዓርር ፤በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ማ፦ምድር ርእየቶ ወአእኰተቶ ፤ባሕርኒ ሰገደት ሎቱ።
አመላለስ፦
ምድርኒ ርእየቶ ወአእኮተቶ/2/
ባሕርኒ ሰገደት ሎቱ/4/
ትርጉም፦
በሰንበት ወደአይሁድ ምኲራብ ገባ ሰንበቴን አክብሩ ብሎ አስተማራቸው በሰንበት አጋንንትን አወጣ በቃሉ ለምፃሞችን አነጻ በሰንበት ምራቁን ወደምድር እንትፍ አለ ጭቃም አደረገ በምራቁ ዕውሩን አዳነ በምድር ሁሉ ላይ ዝናምን ያወርዱ ዘንድ ደመናዎችን የሚያዛቸው እሱ ነው በሚያስፈልግበት ስፍራ ሁሉ። የሚዘራም የሚያጭድም አንድ ላይ ይደሰቱ ዘንድ። ምድር አየችው አመሰገነችው ባሕርም ሰገደችለት።
https://t.me/maheberat
2 013
👆የቀጠለ
እኒኽም ቅዱሳን ይኽንን በሚነጋገሩበት ጊዜ በውስጡ አንገትን የሚቆለምም ልብንም የሚያቀልጥ ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርን የሚበጣጥስ መሳሪያ ካለበት የብረት ጋን ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና የብረቱን ጋን እሳት አጠፋው፡፡ ከቅዱሳኑም አንዳቸውንም ሳያቃጥላቸው የብረቱ ጋር ማቃጠሉና መፍላቱ ጸጥ አለ፡፡
ወንድሞቻችን ሆይ እንግዲህ በጭንቃቸው ጊዜ ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ይህ መልአክ ከሰማእታትና ከጻድቃን ጐን እንደማይለይ እወቁ ለኃጥአንም ኃጢአታቸውን ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይላቸዋል፡፡ እኛም የዚህ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓሉን እያከበርን አማላጅና ወዳጅ እናድርገው። በዚህም በሚመጣውም ዓለም ሊረዳን ይችላልና፡፡
ዳግመኛም መስፍኑ ሐሳቡ ሳይሳካለት ስለቀረ 14 የሾሉና የጋሉ የብረት ችንካሮች አምጥተው ሰባቱን በእናቱ በኢየሉጣ አካል ሰባቱን በራሱ በቂርቆስ አካል ማለት ሁለቱን በጆሮዎቹ ሁለቱን በዐይኖቹ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ አንዱን በልቡ ይቸነክራቸው ዘንድ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የህፃኑን የእራስ ቆዳ ገፈው እሳት ውስጥ ይጨምሩ ዘንድ አዘዘ፡፡
አሁንም መልአኩ መጥቶ ይህንን መከራ ከእርሱ አራቀለት፡፡ ቀጥሎም በመቃን ውስጥ ጨምረው በገመድ እንዲጎትቱት አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ መልአኩ አዳነው፡፡ ሕዝቡም ይህንን ሁሉ ተአምር ባዩ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቅዱስ ገብርኤልንም አከበሩት፡፡ ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት እየሉጣ ብዙ መከራ ከተቀበሉ በኋላ ጥር 15 በሰይፍ ተመትተው ስማትነትን ተቀብለዋል።
የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት እየሉጣ ተራዳኢነት ጸሎት አይለየን። ከዚህ በኋላ ሕፃኑን አስፈልገው ቢጠይቁት ነቢዩ ዳዊት የተናገረው ኃይለ ቃል መንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት፤ ‹‹የአሕዛብ ጣዖታት የወርቅና የብር የሰው እጅ ሥራዎች ናቸው፡፡ የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ›› መዝ. ፻፴ በማለት ሲዘልፏቸው አገር ገዥው ሰምቶ ተቆጣና የብረት ጋን አስመጥቶ ውኃ ሞልቶ ከዕቶን እሳት ላይ ጥዶ ልዩ ልዩ ማገዶዎች በመጨመር ነበልባሉ ከመጠን በላይ ሆነ፡፡ የብረት ጋኑም ድምፅ እንደ ክረምት መብረቅና ነጎድጓድ እስኪያስፈራ ድረስ አስነድዶ ሕፃኑን ከነእናቱ ወስዳችሁ ጨምሩአቸው ብሎ አዘዘ፡፡
በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ በጣም ፈራች፡፡ የእግዚአብሔር ሥራ እፁብ ድንቅ ግሩም ረቂቅ ነው፡፡ ገና አፉን ያልፈታ የሦስት ዓመት ሕፃን ‹‹እናቴ ሆይ! ገድላችን እንፈጽም ዘንድ ጨክኝ በርቺ›› አላት፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም ‹‹ልጄ የነፍስ አባት ሁነኝ›› አለችው፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ከዘመናቸው ሳይደርስ፣ ታሪካቸውን ሳይማር የሠለስቱ ደቂቅን ታሪክ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ‹‹አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል›› ቢላት ፍርሃቱ ሊለቃት ባለመቻሉ፣ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ጸለየ፡፡
‹‹ጌታ ሆይ! የወይኑን ፍሬ ስትሻ ግንዱን ታጠፋለህን? እንደዚህስ ሁሉ እኔን አድነህ እናቴን ታጠፋታለህን?›› ብሎ በጸለየጊዜ መንፈስ ቅዱስ አደረባትና መንግሥተ ሰማያትን በዓይነ ሥጋ እንድታይ አደረጋት፡፡ ከዚህ በኋላ ፍርሃቱ ለቀቃትና ‹‹ልጄ ሆይ! ከዛሬ ጀምሮ መምህሬ፣ አባቴ፣ መካሪዬ እልሃለሁ እንጂ ልጄ አልልህም›› ብላ በጭካኔ ከልጅዋ ጋር ወደ ፈላው የብረት ጋን ገባችበት፡፡
በዚህ ጊዜ ሕፃኑ ቂርቆስ አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል ያለውን ቃል ለመፈጻም እግዚአብሔር አምላክ መልአኩ
ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው፡፡ መልአኩም በትእምርተ መስቀል እሳቱን ቢባርከው እንደ በረዶ ቀዝቅዞላቸዋል፡፡ በመልካቸውም እንደ ፀሐይ አበራ፡፡ ከእግር ጥፍራቸው እስከ ራስ ጠሩራቸው አንድም ሳይጎዳቸው በደህና ወጡ፡፡
በመጨረሻም ሕፃኑ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ እንዲህ አለ፡፡ ይህን ያህል ገድል ተጋድዬ ምን ዋጋ ትሰጠኛለህ ቢለው፣ ጌታ በልብህ ያለውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው፡፡ ዳግመኛም ሥጋህ በምድር ላይ እንዳይፈርስ እንዳይበሰብስ በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርሃለሁ አለው፡፡
ስለሆነም በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያናችን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለእናታችን ለቅድስት ኢየሉጣ እና ለሕፃኑ ለቅዱስ ቂርቆስ ያደረገውን ይህን ታላቅ ተአምር ድንቅ ሥራ በማሰብ ከዋዜማው ጀምራ እግዚአብሔርን ስታመሰግን ትውላለች ታድራለች፡፡
የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል በረከት ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይኑር አሜን፡፡
2 013
ሐምሌ 19
ቅዱስ ገብርኤል
እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!
በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት የሚታሰብበት ዕለት ነው። የሐምሌ 19 ስንክሳርና የሐምሌ ወር ድርሳነ ገብርኤል እንዲህ ተርከውታል፡፡
በዘመነ ሰማእታት ከሐድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቲያኖች ላይ መከራ አጽንተውባቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች ሰማእትነትን ሲቀበሉ የተቀሩት አገር ጥለው ተሰደዱ። እየሉጣም የሦስት ዓመት ህፃን የነበረውን ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኮንን አገኘችው ሰዎችም ነገር አሰሩባት ወደእርሱ አስቀረባት እና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኮንን ሆይ ዕድሜው ሦስት አመት የሆነው ህፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እሱን ጠይቅ አለችው፡፡
ህፃኑም ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደእርሱ አስመጣው ህፃኑም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ህፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው፡፡ ህፃኑም መልሶ አዎ ለኔ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ሐዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፡፡ መጻሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏል እና አለው፡፡ እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስካስደነገጣቸው ድረስ ንጉሱን መኳንንቱንና ጣኦታቱን ረገማቸው፡፡ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ፡፡
መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በያይነቱ በሆነ ስቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው እናቱንም ከእርሱ ጋር አሰቃያት፡፡ እግዚአብሔርም ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር፡፡ ብዙዎች አህዛብም ይኸንን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማእትነት አረፉ፡፡ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ፡፡ በህፃኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት፡፡ ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው፡፡
መስፍኑም በውስጡ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል ጨምራችሁ ታላቅ የብረት ጋን አንጡልኝ ብሎ ጭፍሮቹን አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም እንዳዘዛቸው ካአደረጉ በኋላ ያዘዝከንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፡፡ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮኸል ወላፈኑም እንደጸሐይ ነጸብራቅ በሩቁ ይጋረፋል፡፡ የፍላቱም ኃይል በ14 ክንድ ያኽል ከፍታ ወደ ላይ ይዘላል፡፡ እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት በዚህ ጊዜ ህፃን ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አስረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእስር ቤት አወጧቸው፡፡
በዚያም ፍላቱ ወደላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው፡፡ በዚህን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተዘጋጅቶላት ከነበረው ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ ድንጋጼም አይደርብሽ አናንያንና አዛርያን ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከእቶነ እሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ፡፡
እናት ሆ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለመዳን ስትይ በማያልፈው ዘላለማዊ እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሽን ይኽስ አይሆንም ይቅርብሽ፡፡ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናት ሆይ ሶስናን ከእደ ረበናት /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ እርሱ እኛንም ከጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን ልጆቹንና ሚስቱን በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባሳጣው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ እግዚአብሐር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ እግዚአብሔርም እንደወደደ አደረገ ከማለት በስተቀር ምንም የተናገረው ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም የሱን ዓላማ በመከተል ይኽንን መከራ ልንታገስ ይገባናል፡፡
ነገር ግን እናቱ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዐይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ አምላክ ሆይ ይችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይኽን እንዳታደር ግን ቸርነትህ ትከለክልኸለች አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት ቅጠሉን ግን ጠብቁት ብለኽ ልታዝ መለኮታዊ ባሕሪህ አይደለም፡፡ ነገር ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም በአንድ ጠብቁት ብለኽ ታዝዛለኽ እንጂ፡፡ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይኽንን ያየ ሁሉ ማዳን የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከእሳት ባልሸሹም ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡
አቤቱ ዲያብሎስም ከባለስልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ ቅዱሳኖቹንም ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማው በማለት እንዳይደነፋ ለእናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ስጣት ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከእየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታኽ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ እነሆ በብረት ጋን ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቸዋለሁና አለችው፡፡
2 013
በዘባነ ኪሩብ
በዘባነ ኪሩብ ለሚቀመጠው
በእሳት ድንጋዮች ቅጥሩን ላጠራው
ዘምሩ ለእግዚአብሔር ለጌታ ዘምሩ
የተከበረ ነው በሰማይ በምድሩ /2×/
/አዝ/
ኢሳይያስ ሲያየው በእጅግ አፈረ
የተፈራ ነው የተከበረ
የሰማይ ደጆች ተንቀጠቀጡ
ለቅዱስ ስሙ ክብርን ሲሰጡ
/አዝ/
ያልተቀደሰ ለምጽ ያነደደው
እንዴት ይችላል ሊያመሰግነው
በል ፍቀድልኝ ፍቅር ነህና
ልግባ መቅደስህ ላቅርብ ምስጋና
/አዝ/
ዙፋንህ ታየኝ ትምክህቴ ሆይ
ስትመሰገን በሰማይ ላይ
ሲያመሰግንህ ያልተደሰተ
ባይተዋር አልሁን አልወጣ ከአንተ
/አዝ/
ቅኔ የሞላበት ያንን ሰገነት
ልቀላቀለው ተመኘሁ በእውነት
ልዘምርልህ ባይገባኝም
ዝም የሚል ልሳን አልሰጠኸኝም
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
2 013
አጎንብሼ ሄጄ
አጎንብሼ ሄጄ ቀና ብዬ መጣው
በዮሐንስ ጠበል ጤናዬን አገኘው
ጌታን ያጠመቁ ክቡራን እጆቹ
ተዓምር ይሰራሉ ዛሬም ለልጆቹ
አዝአልጋዬን አዝዬ በደስታ ዘለልኩኝ በመጥምቁ ጠበል በእጁ ተዳሰስኩኝ የመራኝን በትር ከእጄ ላይ ጥያለሁ በሰባኪው ጸሎት በምልጃው ድኛለሁ
አዝለዓለም ያልተቻላት በእምነቱ ለቆኛል አበቃልህ ያሉኝ እጅግ ተደንቀዋል በለምጽ የነደድኩት ታደስኩ እንደገና አዲስ አካል ይዤ ቆምኩኝ ለምስጋና
አዝያለፍኩባት ሰፈር በእምባ ተሞልቼ እልልታዬን ሰማች ድኜ ተደስቼ የንዕማን ቁስል ተራግፏል ከላዬ መሞቴን የማይወድ አሰበኝ ጌታዬ
አዝአባናና ፋርፋን አስንቁአል ጠበል ዮርዳኖስ በእምነት ለወረዱ ሁሉ ዮሐንስ በመንፈስ ሲያጠምቅ አይቻለሁ በእጁ ተፈውሼ ምስክር ሆኛለሁ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
2 013
በማህፀን ቅኔ
በማህፀን ቅኔ ለማርያም ተሰማ
በተራራማ አገር በኤፍሬም ከተማ
ዮሐንስ ይናገር በረሃ ያደገው
ድንግል ስትናገር ምን እንዳዘለለው
የእናቱ ማህፀን የቅኔ እርስት ሆነች
ድንግል የአምላክ እናት ፊቱ ስለቆመች
በሀሴት ዘለለ ዘመረ በደስታ
ከድንግል ሲወጣ ታላቁ ሰላምታ
አዝ።።።።።።
በድንግል ማህፀን ስላየ ጌታውን
ከመወለድ ቀድሞ ሰማነው መዝሙሩን
ትንቢቱ ሲፈፀም በሆዷ ሲነግስ
ሰገደ ለአምላኩ የስድስት ወር ፅንስ
አዝ።።።።።።
ጀመረ ስብከቱን ገና ሳይወለድ
ተፈጥሮ መች ቻለ ነብዩን ለማገድ
አፉ ተከፈተ በታላቅ ምስጋና
በእናቱ ማህፀን ድምፅን አሰማና
አዝ።።።።።።
የዮሐንስ እናት ኤልሳቤጥ ገረማት
ልጇ በማህፀን ቅኔን ሲቀኝባት
ድምጿን ከፍ አረገች አለም እንዲሰማ
ሞላት መንፈስ ቅዱስ በመዝሙር በዜማ
አዝ።።።።።።
የዮሐንስ እናት ኤልሳቤጥ ገረማት
ልጇ በማህፀን ቅኔን ሲቀኝባት
ድምጿን ከፍ አረገች አለም እንዲሰማ
ሞላት መንፈስ ቅዱስ በመዝሙር በዜማ
2 013
Repost from ያሬዳውያን
እግዚአብሔርን አመስግኑ
ስራው ግሩምድንቅ ነው በሉ
እግዚአብሔርን አመስግኑት
እግዚአብሔርን አመስግኑት
ሥራ ግሩም ድንቅ ነው በሉት
እግዚአብሔርን እመስግኑት
ስራህ ግሩም ድንቅ ነው በሉት
❴አዝ❵
ሠማይን ያለ ምሰሶ
ምድርንም ያለ መሰረት
ያጸናው እርሱ ነው
ሥራህ ድንቅ ነው በሉት
❴አዝ❵
የባህርንም ጥልቀት የመጠነ
ዳርቻዋን የወሰነ
እግዚአብሔርን አመስግኑ
ሥራ ግሩም ድንቅ ነው በሉት
❴አዝ❵
ማእበል ንፋሱን የሚገስጽ
ፍጥረቱ ለስሙ የሚታዘዝ
ትጉህ እረኛ ድካም የሌለበት
እግዚአብሔርን ሥራህ ድንቅ ነው በሉት
❴አዝ❵
ንጹሐ ባህርይ ነው ሁሉን የሚገዛ
የነገስታት ንጉስ አልፋና ኦሜጋ
ዘለዓለም እርሱ ነው የማይለወጥ
እግዚአብሔር ስራህ ድንቅ ነው በሉት
❴አዝ❵
ጥበብን የሚሰጥ ጥበበኛ
ፍርድ የማያጎድል እውነተኛ ዳኛ
እንደ እርሱ ያለ ከቶ አይገኝም
እግዚአብሔር ግሩም ነው ለዘልዓለም
2 013
ኪዳነምሕረት እናቴ
ኪዳነምህረት እናቴ
ሚስጥረኛየ ጓዳዬ
የጎደለኝን ታውቂያለሽ
ካፌ ሳይወጣ ሳልነግርሽ/2/
አዝአልፏል መናኛው ኑሮ ምልጃሽ ውሀውን ቀይሮ መልካሙ ወይን ደረሰ እንባዬ ባንቺ ታበሰ /2/
አዝልዘምር ልቁም ከፊትሽ ልምጣ ልንበርከክ ለክብርሽ ብርቅ ከሀገር ከቤቴ ከቶ አረሳሽም እናቴ/2/
አዝአልልም መቼ ነው ቀኑ የኔ መጎብኛ ዘመኑ እንደሚፈፀም አምናለሁ ሁሉን በጊዜው አያለሁ /2/
አዝየልቤን ችግር ላዋይሽ ከስእልሽ ፊት ቆሜ እንባዬ ቀድሞኝ ዝም አልኩኝ ሳልነግርሽ ስለምታውቂ /2/ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ
2 013
ሰኔ ፲፪ የቅዱስ_ሚካኤል ዓመታዊ በዓል!
እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለእናታችን ቅድስት አፎሚያ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል እናታችን ቅድስት አፎሚያን ከጠላት ዲያብሎስ እጅ ያዳነበት ፣ እናታችን ቅድስት አፎሚያ እረፍቷ ነው ።እግዚአብሔር ከቅዱሱ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ፣ ከእናታችን ቅድስት አፎሚያ በረከት ተካፋይ ያድርገን ። 👉 በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡ ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ ባያት ጊዜ ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ፣ ሌላ ባል አግብታ፣ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ፤ እነሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ፤ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ በሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡ ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና “የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?” በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው “በኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም” ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን “ድረስልኝ” እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሠኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ ይህች የታመነች ቅድስት አፎምያ በሰላም እስክታርፍ ጊዜ ድረስ የተጓዘችበትን መንፈሳዊ ጎዳና አስተውለን ይሆን? አስቀድማ ከባሏ ጋር አንድ ሆና በታማኝነት ፈጣሪዋን አገለገለችው፡፡ በኋላም የባሏን ኑዛዜ አክብራ ምንም እንኳን ኃጢአት ባይሆንባትም በሁለተኛ ትዳር ራስዋን ማጠላለፍ አልፈለገችም፡፡ በጎ ሥራ አብልጣ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ተፋጠነች እንጂ፡፡ ሰይጣን ልጅ አለመውለዷን ተጠቅሞ ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ “መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ መናፍስት ከእግዚአብሔር እንደሆኑ መርምሩ” ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘውን መመሪያ ተጠቅማ ሰይጣንን በተወክሎ እግዚአብሔር ተቃውማ አሸነፈችው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን ርዳታ ያገኘችውና በሰላም ዐርፋ ወዳገለገለችው እግዚአብሔር በክብር የሔደችው በጽናት ተጋድላ ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጸሎቷ ይማረን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኃይል ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
2 013
❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️
የሰኔ 12 የሀያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ማኅሌት አማርኛ ትርጉም(ክፍል ፪)
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
መልክዓ ሚካኤል ለእስትፋስከ ከተባለ በኃላ
ዚቅ
ወከሢቶ ረከበ ኀበ ይብል እዜንዎሙ ለነዳያን ፈነወኒ: ወእከስት ሎሙ ግዕዛነ ለጼውዋን: ወእፈውስ ሎሙ ለቁሱላነ ልብ: ወእሰምዮ ለባሕራን ኅሩየ: ዝኬ ዘተነግረ በመዋዕለ ትካት: ለ፳ኤል ኅብስተ መና ዘአውረደ በገዳም: ወርእየቱ ከመ ተቅዳ ወከመ አያያተ መዓር ጥዑም ፈድፋደ።
የዐማርኛ ትርጕም
ደብዳቤውን ገልጦም ”ለችግረኞች እረዳቸው ዘንድ ላከኝ” የሚል ጽሑፍ አገኘ።
ለምርኮኞችምነጻነትን እሰጣቸው ዘንድ።የልብ ቁስለኞችንም አድን ዘንድ፤ባሕራን የተመረጠ ብዬ እሰይመዋለኹ።ይኽ በጥንት ዘምን የተነገረ ነው።ለእስራኤል መና ከደመና በምድረ በዳ ያወረደ ርሱ ነው።መልኩም እንደ ድንብላልና እጅግ እንደሚጣፍጥ የማር ወለላ ነበር።
ወረብ
"ወከሢቶ ረከበ"/፪/ ኀበ ይብል እዜንዎሙ ለነዳያን ፈነወኒ/፪/
ወእስብክ ሎሙ ግዕዛነ ለጼውዋን ወእስምዮ ለባሕራን ኅሩየ/፪/
የዐማርኛ ትርጕም
ደብዳቤውን ገልጦም ”ለችግረኞች እረዳቸው ዘንድ ላከኝ” የሚል ጽሑፍ አገኘ።ለምርኮኞችም ነጻነትን እሰጣቸው ዘንድ።ባሕራን የተመረጠ ብዬ እሰይመዋለኹ።
መልክዐ ሚካኤል፦
ሰላም ለአጻብኢከ መጽሐፈ እለ ለክዑ፤ዕጒለ አባግዕ እምኖሎት በጊዜ ተመልዑ፤ሚካኤል አንተ ለንጉሠ ነገሥት ካህነ ምሥዋኡ፤አሣዕነ መድኃኒት ለእገርየ አጻብኢከ ይቅጽዑ፤ከመ በፍናውየ የኀዝ ለሰላም ቅብዑ።
የዐማርኛ ትርጕም
ሚካኤል ሆይ በትጉሃን እረኞች ትጋት የተነሣ ደቂቀ አባግዕ በበረከቱ ጊዜ መጻሕፍትን ላዘጋጁ ጣቶችህ ሰላም እላለሁ። ጠባቂው መልአክ ሆይ የነገሥታት ንጉሥ የሚሆን የእግዚአብሔርየመሥዋቱ ካህን ነህና።በምሄድበት ጎዳና በሰላም እራመድ ዘንድ።በጥበብ የበለጸጉ ጣቶች ለእግሮቼ የሕይወት ጫማን ያዘጋጁልኝ።
ዚቅ
ቅዱሳት አጻብኢከ ለጽሒፈ መጽሐፍ እለ ተቀንያ: ወብጹዓት አዕይንቲከ ምስጢረ መለኮትዘርእያ: ሚካኤል መልአክ ወሐዋርያ።
የዐማርኛ ትርጕም
መልአክና አስተማሪ የኾንክ ሚካኤል መጽሐፍን ለመጽሐፍ የቀኑ/የለዘቡ እጣቶችኽ የተለዩ ናቸው፤የመለኮት ምስጢርን ያዩ ዐይኖችኽም ምስጉኖች ናቸው።
ወረብ
ምስጢረ መለኮት ዘርእያ አዕይንቲከ/፪/
ሚካኤል መልአክ መልአክ ወሐዋርያ ሚካኤል መልአክ/፪/
የዐማርኛ ትርጕም
ሚካኤል መልአክ ኾይ መልአክ ነኽ፤
ዳግመኛም ሚካኤል መልአክም ሐዋርያ ነኽ
መልክዐ ሚካኤል፦
አምኃ ሰላም አቅረብኩ ለመልክዕከ ኲሉ:ለለአሐዱ አሐዱ ዘበበክፍሉ:
ሚካኤል ክቡር ለልዑል መልአከ ኃይሉ: ተወኪፈከ አምኃየ እምኑኃ ሰማያት ዘላዕሉ: ዕሴተ ጸሎትየ ፈኑ ወአስብየ ድሉ።
የዐማርኛ ትርጕም
ሚካኤል ሆይ ለእያንዳንዱ በየክፍሉ ለተነገሩ መልኮችህ ሁሉ የምስጋና እጅ መንሻ አቀርባለሁ።ልዑሉ መልአክ ሆይ እግዚአብሔር ኃይሉን የሚገልጽብህ ኃያል መልአክ ነህና የምስጋናዬን እጅ መንሻ ተቀብለህ።ከላይ ከኢየሩሳሌም ሰማያዊት የጸሎቴን ዋጋ እጥፍ ድርብ አድርገህ ላክልኝ።
ዚቅ
መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ሚካኤል: ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ: አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩለንጉሥ ዓቢይ።
የዐማርኛ ትርጕም
የሰላማችን አለቃ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ስለ እኛ ለምንልን፤ ልመናችንን ወደ ገናናው ንጉሥ ዙፋን አሳርግ
ወረብ
መልአከ ሰላምነ/፬/
ሊቀ መላእክት ሚካኤል ሰአል በእንቲአነ/፪/
የዐማርኛ ትርጕም
የሰላማችን አለቃ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ስለ እኛ ለምንልን
አንገርጋሪ
አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእነ: ሚካኤል አርመመ ወገብርኤል ተደመ: ፀሐይ ጸልመ ወወርኅደመ ኮነ: ወሪዶ እመስቀሉ አብርሃ ለኲሉ።
የዐማርኛ ትርጕም
ጌታችንን አይሁድ በሰቀሉት ጊዜ ሚካኤል ዝም አለ፤ገብርኤል ግን ተቆጣ፤ፀሓይ ጨለመ፤ጨረቃም ደምን ኾነ ከመስቀሉ ወርዶ ለኹሉ አበራ።
አመላለስ
ወሪዶ እመስቀሉ/፪/
እመስቀሉ አብርሃ ለኲሉ/፬/
የዐማርኛ ትርጕም
ከመስቀሉ ወርዶ ለኹሉ አበራ።
ወረብ
አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእነ/፪/
ሚካኤል አርመመ ወገብርኤል ተደመ/፪/
የዐማርኛ ትርጕም
ጌታችንን አይሁድ በሰቀሉት ጊዜ ሚካኤል ዝም አለ፤ገብርኤል ግን ተቆጣ።
እስመ ለዓለም፦
ይቤሎሙ ኢየሱስ ለአርዳኢሁ: አዓርግ ሰማየ አቡየ ወአቡክሙ: ኀበ አምላኪየ ወአምላክክሙ: ዘንተ ይቤሎሙ ዓርገ ውስተ ሰማያት: ካዕበ ይመጽእ በዘዚአሁ ስብሐት: ሠርጎሙ ለሐዋርያት ብርሃኖሙ ለእለ ውስተ ጽልመት: መድኃኔነገሥት ክብሮሙ ለመላእክት ኖላዊሆሙ ለአሕዛብ ለከ ስብሐት
የዐማርኛ ትርጕም
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን “ወደ አባቴና አባታችኹ ሰማይ እኼዳለኹ” አላቸው።
ይኽን ብሏቸው ወደ ሰማያት ወጣ።ዳግመኛም በራሱ ምስጋና ይመጣል።የደቀ መዛሙርቱ ሽልማታቸው ነው፤በጨለማ ውስጥ ላሉትም ብርሃናቸው ነው፤የነገሥት አዳኝ የመላእክት ክብራቸው፣ጠባቂያቸው ነው።
ዓዲ እስመ ለዓለም-
እምድኅረ ተንሥአ እሙታን ዓርገ ውስተ ሰማያት በስብሐት አምላከ ምሕረት: ወተቀብልዎ አዕላፋ አዕላፋት: ወሚካኤል ሊቀ መላእክት በንፍሐተ ቀርን እምኀበ እግዚአብሔር: ስብኩ ትንሣኤ
ውስተ ኲሉ ምድር።
የዐማርኛ ትርጕም
የይቅርታ አምላክ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ በክብር ወደ ሰማያት አረገ፤የአእላፍ መላእክትም ተቀበሉት፤ሚካኤልም በመለኸት ድምፅ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፤በዓለም ኹሉ መነሣቱን አስተምሩ።
https://t.me/maheberat
2 013
❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️
የሰኔ 12 የሀያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ማኅሌት አማርኛ ትርጉም(ክፍል ፩)
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
ሥርዓተ ነግሥ:-
ስምዐኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡
👉አቤቱ ጸሎቴን ስማኝ ምስጋና አቀርባለኹ
ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡
👉ጩኸቴም በፊትኽ ይድረስ ምስጋና አቀርባለኹ
ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡
👉ፊትኽን ከእኔ አትመልስ
በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡
👉በችግሬ ጊዜ ጆሮኽን ወደ እኔ አድምጥ ምስጋና አቀርባለኹ
አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡
👉በምጠራኽ ጊዜም ፈጥነኽ ስማኝ ምስጋና አቀርባለኹ
ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ንወድሶ ለዘሀሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
👉 ለዘለዓለሙ ምስጋና አቀርባለኹ። ያ ማለት ያለ ልዑል እግዚአብሔርን እናመስግነው ማለት ነው። በአንዲት ቃል ዓለምን ኹሉ የፈጠረ አምላክ ፈጽሞ የተመሰገነ ነው።
መልክዐ ሥላሴ፦
ሰላም ለጒርኤክሙ ስቴ አንብዐ ሰብእ ዘኀሠሠ፤ብዑላነ ሞገስ ሥላሴ ኢታንድዩኒ ሞገሰ፤እመ ትትኃየዩኒሰ ኢትኅድጉኒ ጽኑሰ፤ሚካኤልኑ ለአውጽኦ ስጋየ ጌሠ፤ወእመ አኮ ገብርኤል ወሀበኒ ነፍሰ።
የዐማርኛ ትርጕም
የሰውን እንባ መጠጥ ለፈለገ ጉሮሯችኹ ሰላም ይገባል።ባለሟል ባዕለጸጎች ሥላሴ ከበሟልነት አታሳጡኝ፤ቸል ቸል ብትሉኝ ስንኳ ችግረኛ እንደኾንኩ አትተውኝ፤ሚካኤል ሥጋዬን ለማውጣት ገሠገሠን?ያም ባይኾን ገብርኤል ነፍስን ሰጠኝ።
ዚቅ
ኢይጽሕቅ ዘይመክሮ ወኢየኀሥሥ ዘይመክሮ:አልቦቱ ጥንት ወኢተፍጻሜት: ኢየኀልቅመንግሥቱ ወአልቦ ዘይክል መዊዐ ኀይሉ:ወአልቦ ኁልቊ ለሠራዊተ መላእክት እለ ይትለአክዎ: አንተ ውእቱ አቡሃ ለጥበብ: ገባሬ ኲሉፍጥረት ወገባሪሃ ለሕግ።
የዐማርኛ ትርጕም
የሚመክረው አይለምንም፤የሚመክረውም አይፈልግም።መጀመሪያና መጨረሻ የለውም።መንግሥቱም አያልቅም።ኀይሉን ማሸነፍ የሚችልም የለም።ለሚላኩት የመላእክት አለቆችም ስፍር ቁጥር የላቸውም።የጥበብ አባቷ አንተ ነኽ፤የፍጥረት ኹሉ ሠሪ አንተ ነኽ፤የሕግ ሠሪዋም አንተ ነኽ።
ነግሥ
ሰላም ለልሳንከ መዝሙረ ቅዳሴ ዘነበልባል፤ ወለድምፀ ቃልከ ሐዋዝ ቀርነ መንግሥቱ ለቃል፤ሞገሰ ክብሩ ሚካኤል ለተላፊኖስ ባዕል፤አልቦ ዘይትማሰለከ በልማደ ምሕረት ወሣህል፤እንበለ ባሕቲታ እኅትከ ማርያም ድንግል።
የዐማርኛ ትርጕም
ነበልባላዊ የኾነ የምስጋና መዝሙር ለሚሰጥ አንደበትኽ ሰላም ይገባል።የቃል የመንግሥቱ መለኸት ያማረ ለቃልኽ ድምፅም ሰላም ይገባል።የተላፊኖስ ሀብታም የክብሩ ሞገስ ሚካኤል ኾይ በምሕረትና ይቅርታ ልምድ የሚመሳሰልኽ የለም።ብቸኛዋ እኅትኽ ማርያም ድንግል ናት እንጅ
ዚቅ
አመ ይነፍህ ሚካኤል ቀርነ በደብረ መቅደስየ: አሜሃ ይትነሥኡ ሙታን: ይትፌሥሁ መላእክት
በዕርገቱ: በፍሥሃ ወበሰላም አዕኮትዎ ለንጉሠ ስብሐት።
የዐማርኛ ትርጕም
ሚካኤል በመቅደሴ ተራራ መለኸትን በነፋ ጊዜ ያን ጊዜ ሙታኖች ይነሣሉ፤ወደ ሰማይ በማረጉም መላእክት ይደሰታሉ፤የምስጋና ንጉሥን በደስታና በፍቅር አመሰገኑት።
መልክዐ ሚካኤል፦
ሰላም ለዝክረ ስምከ ምስለ ስመ ልዑል ዘተሳተፈ፤ወልደ ያሬድ ሄኖክ በከመ ጸሐፈ፤ ሶበ እጼውእ ስመከ ከሢትየ አፈ፤ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል በከመ ታለምድ ዘልፈ፤ለረዲኦትየ ነዓ ሠፊሐከ ክንፈ።
የዐማርኛ ትርጕም
ሚካኤል ኾይ የያሬድ ልጅ ሄኖክ እንደጻፈው።ከልዑል ስም አጠራር ጋር ለተባበረ ስም አጠራርኽ ሰላም እላለኹ።የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ኾይ የተቸገሩትን የተጨነቁትን ዘወትር እንደምትረዳቸው ኹሉ እኔንም ለመርዳት ክንፍኽን ዘርግተኽ ፈጥነኽ ድረስልኝ።
ዚቅ
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ አቢተነ በመድኃኒትከ: ጸግወነ ንጸውዕ ስመከ: ኖላዊነ ኄር ትጉሕ ዘኢትነውም
ሰላመከ ሀበነ።
የዐማርኛ ትርጕም
ምስጋና ምስጋና በመድኀኒትኽ አሳድረን፤ስምኽን እንጠራ ዘንድ ስጠን፤የማታንቀላፋ ትጉ ቸር እረኛ ሰላምኽን ስጠን።
ወረብ
ሀበነ ሰላመከ ንጸውዕ ስመከ/፪/
ዘኢትነውም ትጉሕ "ኖላዊነ ኄር"/፪//፪/
የዐማርኛ ትርጕም
የማታንቀላፋ ትጉ ቸር እረኛ፤
ስምኽን እንጠራ ዘንድ ሰላምኽን ስጠን።
መልክዐ ሚካኤል፦
ሰላም ለልሳንከ በነቢበ ጽርፈት ዘኢተሀበለ፤በእንተ ሥጋሁ ለሙሴ አመ ምስለ ሰይጣን ተበሀለ፤ሚካኤል ክብርከ እምክብረ መላእክት ተልዕለ፤ቀዊምየ ቅድመ ስዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ፤በብሂለ ኦሆ ፍጡነ አስምዐኒ ቃለ።
የዐማርኛ ትርጕም
ሚካኤል ኾይ ስለ ሙሴ ሥጋ ከዲያብሎስ ጋር ክርክር በተደረገ ጊዜ የዘለፋ ቃል ላልተናገረ
አንደበትኽ ሰላም እላለሁ።ክቡሩ መልአክ ኾይ ክብርኽ ከመላእክት ኹሉ ክብር ከፍ ያለ ነውና።
በሥነ ሥዕልኽ ፊት ቁሜ ልመናዬን በማቀርብበት ጊዜ ኹሉ። “አይዞኽ አለኹልኽ” በማለት ፈጥነኽ ድምፅኽን አሰማኝ።
ወረብ
ቀዊምየ ቅድመ ስዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ/፪/
"በብሂለ ኦሆ"/፪/ ፍጡነ አስምአኒ ቃለ/፪/
የዐማርኛ ትርጕም
በሥነ ሥዕልኽ ፊት ቁሜ ልመናዬን በማቀርብበት ጊዜ ኹሉ።
“አይዞኽ አለኹልኽ” በማለት
ፈጥነኽ ድምፅኽን አሰማኝ።
ዚቅ
አመ ይነፍሕ ሚካኤል ቀርነ በደብረ መቅደስየ: አሜሃ ይትነሥኡ ሙታን: ይትፌሥሁ መላእክት
በዕርገቱ: በፍሥሃ ወበሰላም አዕኮትዎ ለንጉሠ ስብሐት።
የዐማርኛ ትርጕም
ሚካኤል በመቅደሴ ተራራ መለኸትን በነፋ ጊዜ ያን ጊዜ ሙታኖች ይነሣሉ፤ወደ ሰማይ በማረጉም መላእክት ይደሰታሉ፤የምስጋና ንጉሥን በደስታና በፍቅር አመሰገኑት።
መልክዐ ሚካኤል፦
ሰላም ዕብል ለአስናኒከ ዘመንፈስ፤
ዘኢይረክቦን ጥረስ፤ሚካኤል ረዳኢ ለእለ ውስተ ባሕር ወየብስ፤እስመ ረሰይከ ካህነ ምሥዋኡ ክርስቶስ፤መፍትው ሊተ ትተንብል ቀሲስ።
የዐማርኛ ትርጕም
ሚካኤል ኾይ መሰበር ማፋጨት ለማያገኛቸው ረቂቃን አስናኖችኽ ሰላም ይገባል።ረዳቴ መልአክ ኾይ በባሕር ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ በየብስ ላይ ለሚመላለሱ ፍጥረታት ኹሉ ረዳታቸው አንተ ነኽ።ስለዚኽም ኢየሱስ ክርስቶስ በመሠዊያው ላይ ካህን አድርጎ ሾሞኻልና። አንተ ቀሲሱ ሚካኤል ለኔ ለአገልጋይኽ ምሕረትን ትለምን ዘንድ ተገቢ ነው።
ዚቅ
ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕረ ምስሌሁ: ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ: ዮም ሰማያዊ በምድር አስተርአየ።
የዐማርኛ ትርጕም
ባሕራንም ከርሱ ጋራ ወደ ባሕር የኼደ ሚካኤልን አየኹት መረዳቱን ግን አልቻልኩም፤ ሰማያዊ ዛሬ በምድር ታየ።
ወረብ
ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕረ/፪/
ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ ስዕንኩ/፪/
ባሕራንም ከርሱ ጋራ ወደ ባሕር የኼደ ሚካኤልን አየኹት፤
መረዳቱን ግን አልቻልኩም፤ሰማያዊ ዛሬ በምድር ታየ።
መልክዐ ሚካኤል
ሰላም ለእስትንፋስከ ቁሱላነ ነፍስ ለአጥዕዮ፤
ዘይነፍሕ ፄና አንህዮ፤ሚካኤል ነዓ ኲናተከ በተረስዮ፤ለገቢር ከመ ቀዳሚ ለአርዌ አመፃ ደርብዮ፤እስመ ኢኃደገ እንከ ዘትካት እከዮ።
የዐማርኛ ትርጕም
ሚካኤል ኾይ የነፍስ ቁስለኞችን ለማዳን መድኃኒተ ፈውስን እፍ ለሚለው እስትንፋስህ ሰላም እላለሁ።ድል አድራጊው መልአክ ሆይ ያ የቀድሞው አመፀኛው አውሬ (ዲያብሎስ) የጥንት ተንኮሉን ሊተው አልቻለምና።የጦር መሣሪያህን ታጥቀህ።መጥተህ ድምጥማጡን አጥፋው።
2 013
ቅድስት ሥላሴ
ሥላሴን ቅድስት ሥላሴ እያልን የመጥራታችን ምስጢር ምንድን ነው?
◉ አንዲት ሴት ወይም እናት ልጆቿን አልወለደችም ተብላ አትጠረጠርም ፤ ሥላሴም ይህንን ዓለም ፈጥረዋል እናም አልፈጠሩም ተብለው አይጠራጠሩም።
◉ አንዲት ሴት በባሕሪይዋ ልጅን ታስገኛለች ፤ ሥላሴም ይህንን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥተው ስለፈጠሩት በሴት አንጻር ቅድስት ተብለው ይጠራሉ ።
◉ አንድም ሴት አዛኝ ናት ፤ ለታናሹም ይሁን ለታላቁ ትራራለች ሥላሴም እንደዚሁ ለፍጥረት ሁሉ ያዝናሉ ፥ ይራራሉ ፥ ምህረት ይሰጣሉ። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንዲህ ይላል ።
ምህረታችሁ ከልክም በላይ የበዛ በሴት አንቀጽ ቅድስት ተብላችሁ የተጠራችሁ ሥላሴ በማለት ያመሰጥራል። ስለዚህ ቅድስት ለምን ተባሉ ቢባል በረከታቸው ፥ ርህራሄያቸውና፥ ይቅር ባይነታቸው መሆኑን ማወቅ አለብን።
◉ አንድም ሴት ልጇ ቢታመምባት አትወድም ፤ ሥላሴም አንድም ልጅ በዲያብሎስ እጅ ተይዞ በኃጢአት እንዲታመሙ አይወዱም ፥ አይፈቅዱም በመሆኑም ቅድስት ይባላሉ።
◎ አንድም ሴት ልጅ የልጇን ነውር አትጠየፍም ልጄ ቆሽሿል ፥ ተበላሽቷል ብላ ፊቷን አታዞርም። ሥላሴም የሰውን በኃጢአት መቆሸሽ ሳይፀየፉ በቸርነታቸው ጎቦኝተው ለንስሐ ያደርሱታል ።
◎ ይህንን የፅድቅ አየር የምንምገው ያማረውንም ብርሃን የለበስነው ስለ ፅድቃችን ሳይሆን በሥላሴ ቸርነት ነውና ስለዚህም ሥላሴን በሴት አንቀፅ ቅድስት እንላቸዋለን።
◉ አንድም ሴት ልጆቿን ፈጭታና ጋግራ ትመግባቸዋለች ሥላሴም እንደዛው ናቸው ። በዝናብ አብቅለው በፀሐይ አብሥልው ፍጥረታትን ሁሉ ይመግባሉ። ስለዚህ ሥላሴ እንደ እናት ሁሉንም ይመግባሉና በሴት አንቀጽ ቅድስት ይባላሉ ።
2 013
ምስጋና በመቅደስህ
ምስጋና በመቅደስህ ዝማሬ በማደርያህ
ልሰዊ ጠዋት ማታ ክብሬነህ የኔ ጌታ
ሰገነት አይመቸኝ ካባዬ ክብር አይሆነኝ
ሁሉንም ንቄዋለው ያንተን
ቤት መርጫለው/2/
አዝ ======
ያረጃል ያለም ዝና ጥበብም ሆኖ መና
አንተ ግን ያው አንተነህ
በሁሉ ትፀናለህ/2/
አዝ ======
ከሰማይ ባይንህ ታየው በፍቅረሸህ ተጎበኘው በባህሪህ ባለጸጋ
ፈወስከኝ በደም ዋጋ/2/
አዝ ======
ቃልህን ነብሴ ሰምታ ተዋበች በእልልታ
ወደ ግርህ መረገጫ መስገዴ
አለው ብልጫ /2/
2 013
Repost from Janderebaw Media
"አሕዛብ፦ አምላካቸው ወዴት ነው? ለምን ይላሉ? የፈሰሰውን የባሪያዎችህን ደም በቀል ዓይኖቻችን እያዩ አሕዛብ ይወቁት።"
መዝሙር 79:10
2 013
ዘምር ዘምር አለኝ
ዘምር ዘምር አለኝ ልቤ ተነሳሳ(2)
የአምላኬን ቸርነት እንዴት ብየ ልርሳ
ያደረገልኝን እንዴት ብየ ልርሳ
አዝ..............
የሚቃጠለው ስም በፊትህ ምንድን ነው
ሰማይና ምድር ሁሉም ገንዘብህ ነው
ያለኝን ሰብስቤ ባኖረው በፊትህ
ዋጋ አይሆንም ጌታ ስለቸርነትህ
አዝ..............
ይበዛል ይሰፋል የእግዚአብሔር ምስጋና
አይቆምም በዘመን ማዕበል ነውና
እንኳን ድንጋይ ቀርቶ ጣራው ቢናድብኝ
የከንፈሬን ፍሬ ማንም አይወስድብኝ
አዝ...............
የጳውሎስ የሲላስ መከራ ቢፀና
አልተውም ቅኔውን የአምላኬን ምስጋና
ሊያስጥለኝ አይችልም እስር ሰንሰለቴ
አለብኝ ውለታ የሰማይ አባቴ
አዝ...............
የተደረገለት ብዙ የተቀበለ
ይኖራል በፍቅሩ እየተቃጠለ
ክብሬን ሁሉ ትቼ ልዘምርልህ
ይህ ነው ችሎታዬ ላንተ ምሰጥህ
2 013
+1
#Update
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ " በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት 13 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን፣ ከ280 በላይ ምእመናን መፈናቀላቸውንና የ101 ዓመት ቤተ ክርስቲያን መቃጠሉን " አሳወቁ።
ብፁዕነታቸው በደረሰው ጥቃት ሐዘናቸውን ገልጸዋል።
ብፁዕነታቸው " ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ:ም ጀምሮ በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ ወረዳ፣ በሺርካ ወረዳና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 13 ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ የ101 ዓመት እድሜ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል " ብለዋል።
" የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል " ሲሉ ገልጸዋል።
የተገደሉ ሰዎች ስም ዝርዝርም እንደሚከተለው ነው ፦
1. አቶ ደምረው አበራ የ70 ዓመት
2. ከፈለኝ ልክየለው የ56ዓመት
3. ሐይሉ ንጉሴ የ70 ዓመት
4. እሸቴ ዳመና የ42 ዓመት
5. አበባየሁ ዳኜ የ42 ዓመት
6. ሰሙ አባይነህ የ70 ዓመት
7. 1 ሚሊሻ
8. አማረ በላይነህ የ80 ዓመት
9. ተሬ ደሴ የ25 ዓመት
10. ወጣት ገነነ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ
11. ሙርቴሳ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ
12. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ
13. አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ
በተጨማሪ በአሰኮ ወረዳ ከ280 ሰው በላይ መፈናቀሉን ብፁዕነታቸው ጠቁመዋል።
" በመሆኑም ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በሃይማኖታቸው ብቻ ቤታቸው እየተለየ ተቃጥሏል፤ ንብረታቸውና ከብቶቻቸው ተዘርፈዋል። ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎችም ይዘውት የሸሹት እምነታቸውንና ማንነታቸውን ብቻ በመሆኑ አሁን ላይ ሜዳ ላይ ወድቀው ይገኛሉ " ብለዋል።
" በተፈጸመው ጥቃት የተሰማነን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን የሞቱትን ወገኖቻችን (ልጆቻችን) እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን ይማርልን (በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን) ያዘኑትን እና የተፈናቀሉትን ወገኖቻችን (ልጆቻችን)
እግዚአብሔር ያጽናናልን " ሲሉ ሀዘናቸውን ገልጸዋል።
መረጃው የአርሲ ሀገረ ስብከት ሚድያ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
2 013
ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ከ10 በላይ ምዕመናን መገደላቸውን ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።
በአሰኮ ወረዳ፣ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ እና ካራ ኩፍቴና በሚባሉ አካባቢዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጥሯል የተባለው ጥቃት " አሰቃቂ እንደነበር " የአይን እማኞች ለቴሌቪዥን ጣቢያው ገልጸዋል።
" በአሰኮ ወረዳ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ ብቻ በታጣቂ ኃይሎች ጥቃት ከ10 በላይ ንጹሃን ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል " ብለዋል።
በአካባቢው 101 ዓመታትን ዕድሜ ያስቆጠረው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወውደሙን እማኞች አመልክተዋል።
በካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይ ጥቃት የተሰነዘረ ሲሆን የቤተክርስቲያኑ ንብረት የሆኑ ቤቶች በመቃጠላቸው ምእመናን የመድኃኔዓለምን ቅዱስ ጽላት ይዘው በእግራቸው ወደሌላ አካባቢ መሻቸውን የአይን እማኞቹ አሳውቀዋል።
ቤቶችን የማቃጠል፣ ንብረት ከብቶችን የመዝረፍ ድርጊት እንደነበረም ተመላክቷል።
በሌላ በኩል ፥ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሺርካ ወረዳ ሁለት ወጣት ኦርቶዶክሳውያን ላይ ግድያ መፈጸሙ ተገልጿል።
ድርጊቱ የተፈጸመው ሚታና ዋጂ በተባለ ቀበሌ ሲሆን ታጣቂዎች ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ወጣቶቹ መኖሪያ ቤት በመግባት ከያዟቸው በኋላ ወደ ሚታና ጋዶ ቀበሌ በመውሰድ አንደኛውን በስለት ሁለተኛውን ደግሞ በጥይት በመምታት በጭካኔ ሕይወታቸውን እንዳጠፉት የቤተክርስቲያኗ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
ሕይወታቸውን ያጡት ወጣቶች ሥርዓተ ቀብር ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በጋዶ ማሕደረ ስብሐት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
በአርሲ ሀገረስብከት ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ ጥቃቶች ተፈጽመው የሰዎች ህይወት ማለፉ፣ ጉዳት መድረሱ የሚታወቅ ሲሆን ከጥቂት ወራት በፊት መሰል ጥቃቶች ሪፖርት መደረጋቸው የሚዘነጋ አይደለም።
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአካባቢው ነዋሪዎችን እያነጋገረ ሲሆን ቤተክርስቲያኗ እና የሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ከሰጡበት ተካቶ ይቅረባል)
ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
2 013
አበረታኝ ፍቅርህ ጌታዬ
አበረታኝ ፍቅርህ ጌታዬ
አበረታኝ ክንድህ አምላኬ
በስምህ ድኛለሁ በፀጋህ
በማደሪያህ ሆኜ ስጠራህ
አዝ---
ሰዶም ስትቃጠል መርገሟ ሲበዛ
ሊተወኝ አይሻም ልጁን እንደዋዛ
ህጉን በማሰቤ አምላክ ፈረደልኝ
ጎትቶ የሚያወጣ መልአክ ሰደደልኝ
አዝ---
በገናን መደርደር አያቆምም ጣቴ
የወንጭፌ ድንጋይ አንተነህ ጉልበቴ
የሳኦልን ካባ አውልቀህ ጣልክልኝ
የፍልስጤሙን ሰው ክንድህ ሰበረልኝ
አዝ---
ሶስት ጌዜ ስክድህ አላውቅህም ብዬ
ዶሮ ስለጮኸ ትዝ አልከኝ ጌታዬ
ወጣሁኝ በዕንባ ከአይሁድ እሳት ሥር
ከሐዲ ሳትለኝ አኖርኝ በፍቅር
አዝ---
ሳምራዊ ናት ሳትል ክብርን የጠኽኝ
እንደ አንተ ከአይሁድ ፍቅርን ማን አሳየኝ
ምስጢሬን በሙሉ ነገርከኝ ጌታዬ
የፍቅር ውሃ ቀዳሁ እንሥራዬን ጥዬ
