uk
Feedback
የአካባቢ ወጣቶች መዝሙራት

የአካባቢ ወጣቶች መዝሙራት

Відкрити в Telegram

የተመረጡ የማህበራት እና የካሴት መዝሙራትን የሚያገኙበት፣ ወቅታዊና አሁናዊ መረጃዎችን የሚጋሩበት እንዲሁም የተለያዩ መፅሀፍትንና ትረካዎችንና የመሳሰሉትን የሚያገኙበት ድንቅ ቻናል ተቀላቀሉን ብዙ ያተርፉበታል። ለአስተየትዎ @Natnael1201

Показати більше
2 023
Підписники
-224 години
-97 днів
-1530 день
Архів дописів
​​​​ሰኔ ፲፪ የቅዱስ_ሚካኤል ዓመታዊ በዓል!
እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለእናታችን ቅድስት አፎሚያ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።
ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል እናታችን ቅድስት አፎሚያን ከጠላት ዲያብሎስ እጅ ያዳነበት ፣ እናታችን ቅድስት አፎሚያ እረፍቷ ነው ።እግዚአብሔር ከቅዱሱ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ፣ ከእናታችን ቅድስት አፎሚያ በረከት ተካፋይ ያድርገን ። 👉 በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡ ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ ባያት ጊዜ ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ፣ ሌላ ባል አግብታ፣ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ፤ እነሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ፤ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ በሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡ ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና “የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?” በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው “በኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም” ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን “ድረስልኝ” እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሠኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ ይህች የታመነች ቅድስት አፎምያ በሰላም እስክታርፍ ጊዜ ድረስ የተጓዘችበትን መንፈሳዊ ጎዳና አስተውለን ይሆን? አስቀድማ ከባሏ ጋር አንድ ሆና በታማኝነት ፈጣሪዋን አገለገለችው፡፡ በኋላም የባሏን ኑዛዜ አክብራ ምንም እንኳን ኃጢአት ባይሆንባትም በሁለተኛ ትዳር ራስዋን ማጠላለፍ አልፈለገችም፡፡ በጎ ሥራ አብልጣ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ተፋጠነች እንጂ፡፡ ሰይጣን ልጅ አለመውለዷን ተጠቅሞ ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ “መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ መናፍስት ከእግዚአብሔር እንደሆኑ መርምሩ” ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘውን መመሪያ ተጠቅማ ሰይጣንን በተወክሎ እግዚአብሔር ተቃውማ አሸነፈችው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን ርዳታ ያገኘችውና በሰላም ዐርፋ ወዳገለገለችው እግዚአብሔር በክብር የሔደችው በጽናት ተጋድላ ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጸሎቷ ይማረን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኃይል ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️ የሰኔ 12 የሀያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ማኅሌት አማርኛ ትርጉም(ክፍል ፪) 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 መልክዓ ሚካኤል ለእስትፋስከ ከተባለ በኃላ ዚቅ ወከሢቶ ረከበ ኀበ ይብል እዜንዎሙ ለነዳያን ፈነወኒ: ወእከስት ሎሙ ግዕዛነ ለጼውዋን: ወእፈውስ ሎሙ ለቁሱላነ ልብ: ወእሰምዮ ለባሕራን ኅሩየ: ዝኬ ዘተነግረ በመዋዕለ ትካት: ለ፳ኤል ኅብስተ መና ዘአውረደ በገዳም: ወርእየቱ ከመ ተቅዳ ወከመ አያያተ መዓር ጥዑም ፈድፋደ።  የዐማርኛ ትርጕም ደብዳቤውን ገልጦም ”ለችግረኞች እረዳቸው ዘንድ ላከኝ” የሚል ጽሑፍ አገኘ። ለምርኮኞችምነጻነትን እሰጣቸው ዘንድ።የልብ ቁስለኞችንም አድን ዘንድ፤ባሕራን የተመረጠ ብዬ እሰይመዋለኹ።ይኽ በጥንት ዘምን የተነገረ ነው።ለእስራኤል መና ከደመና በምድረ በዳ ያወረደ ርሱ ነው።መልኩም እንደ ድንብላልና እጅግ እንደሚጣፍጥ የማር ወለላ ነበር። ወረብ "ወከሢቶ ረከበ"/፪/ ኀበ ይብል እዜንዎሙ ለነዳያን ፈነወኒ/፪/ ወእስብክ ሎሙ ግዕዛነ ለጼውዋን ወእስምዮ ለባሕራን ኅሩየ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም ደብዳቤውን ገልጦም ”ለችግረኞች እረዳቸው ዘንድ ላከኝ” የሚል ጽሑፍ አገኘ።ለምርኮኞችም ነጻነትን እሰጣቸው ዘንድ።ባሕራን የተመረጠ ብዬ እሰይመዋለኹ። መልክዐ ሚካኤል፦ ሰላም ለአጻብኢከ መጽሐፈ እለ ለክዑ፤ዕጒለ አባግዕ እምኖሎት በጊዜ ተመልዑ፤ሚካኤል አንተ ለንጉሠ ነገሥት ካህነ ምሥዋኡ፤አሣዕነ መድኃኒት ለእገርየ አጻብኢከ ይቅጽዑ፤ከመ በፍናውየ የኀዝ ለሰላም ቅብዑ።  የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል ሆይ በትጉሃን እረኞች ትጋት የተነሣ ደቂቀ አባግዕ በበረከቱ ጊዜ መጻሕፍትን ላዘጋጁ ጣቶችህ ሰላም እላለሁ። ጠባቂው መልአክ ሆይ የነገሥታት ንጉሥ የሚሆን የእግዚአብሔርየመሥዋቱ ካህን ነህና።በምሄድበት ጎዳና በሰላም እራመድ ዘንድ።በጥበብ የበለጸጉ ጣቶች ለእግሮቼ የሕይወት ጫማን ያዘጋጁልኝ። ዚቅ ቅዱሳት አጻብኢከ ለጽሒፈ መጽሐፍ እለ ተቀንያ: ወብጹዓት አዕይንቲከ ምስጢረ መለኮትዘርእያ: ሚካኤል መልአክ ወሐዋርያ።  የዐማርኛ ትርጕም መልአክና አስተማሪ የኾንክ ሚካኤል መጽሐፍን ለመጽሐፍ የቀኑ/የለዘቡ እጣቶችኽ የተለዩ ናቸው፤የመለኮት ምስጢርን ያዩ ዐይኖችኽም ምስጉኖች ናቸው። ወረብ ምስጢረ መለኮት ዘርእያ አዕይንቲከ/፪/ ሚካኤል መልአክ መልአክ ወሐዋርያ ሚካኤል መልአክ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል መልአክ ኾይ መልአክ ነኽ፤ ዳግመኛም ሚካኤል መልአክም ሐዋርያ ነኽ መልክዐ ሚካኤል፦ አምኃ ሰላም አቅረብኩ ለመልክዕከ ኲሉ:ለለአሐዱ አሐዱ ዘበበክፍሉ: ሚካኤል ክቡር ለልዑል መልአከ ኃይሉ:  ተወኪፈከ አምኃየ እምኑኃ ሰማያት ዘላዕሉ:  ዕሴተ ጸሎትየ ፈኑ ወአስብየ ድሉ።  የዐማርኛ ትርጕም  ሚካኤል ሆይ ለእያንዳንዱ በየክፍሉ ለተነገሩ መልኮችህ ሁሉ የምስጋና እጅ መንሻ አቀርባለሁ።ልዑሉ መልአክ ሆይ እግዚአብሔር ኃይሉን የሚገልጽብህ ኃያል መልአክ ነህና የምስጋናዬን እጅ መንሻ ተቀብለህ።ከላይ ከኢየሩሳሌም ሰማያዊት የጸሎቴን ዋጋ እጥፍ ድርብ አድርገህ ላክልኝ። ዚቅ  መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ሚካኤል: ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ: አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩለንጉሥ ዓቢይ።  የዐማርኛ ትርጕም  የሰላማችን አለቃ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ስለ እኛ ለምንልን፤ ልመናችንን ወደ ገናናው ንጉሥ ዙፋን አሳርግ ወረብ  መልአከ ሰላምነ/፬/ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ሰአል በእንቲአነ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም  የሰላማችን አለቃ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ስለ እኛ ለምንልን አንገርጋሪ  አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእነ: ሚካኤል አርመመ ወገብርኤል ተደመ: ፀሐይ ጸልመ ወወርኅደመ ኮነ: ወሪዶ እመስቀሉ አብርሃ ለኲሉ።  የዐማርኛ ትርጕም  ጌታችንን አይሁድ በሰቀሉት ጊዜ ሚካኤል ዝም አለ፤ገብርኤል ግን ተቆጣ፤ፀሓይ ጨለመ፤ጨረቃም ደምን ኾነ ከመስቀሉ ወርዶ ለኹሉ አበራ። አመላለስ  ወሪዶ እመስቀሉ/፪/ እመስቀሉ አብርሃ ለኲሉ/፬/  የዐማርኛ ትርጕም  ከመስቀሉ ወርዶ ለኹሉ አበራ። ወረብ  አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእነ/፪/ ሚካኤል አርመመ ወገብርኤል ተደመ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም  ጌታችንን አይሁድ በሰቀሉት ጊዜ ሚካኤል ዝም አለ፤ገብርኤል ግን ተቆጣ። እስመ ለዓለም፦ ይቤሎሙ ኢየሱስ ለአርዳኢሁ: አዓርግ ሰማየ አቡየ ወአቡክሙ: ኀበ አምላኪየ ወአምላክክሙ: ዘንተ ይቤሎሙ ዓርገ ውስተ ሰማያት: ካዕበ ይመጽእ በዘዚአሁ ስብሐት: ሠርጎሙ ለሐዋርያት ብርሃኖሙ ለእለ ውስተ ጽልመት: መድኃኔነገሥት ክብሮሙ ለመላእክት ኖላዊሆሙ ለአሕዛብ ለከ ስብሐት  የዐማርኛ ትርጕም  ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን “ወደ አባቴና አባታችኹ ሰማይ እኼዳለኹ” አላቸው። ይኽን ብሏቸው ወደ ሰማያት ወጣ።ዳግመኛም በራሱ ምስጋና ይመጣል።የደቀ መዛሙርቱ ሽልማታቸው ነው፤በጨለማ ውስጥ ላሉትም ብርሃናቸው ነው፤የነገሥት አዳኝ የመላእክት ክብራቸው፣ጠባቂያቸው ነው። ዓዲ እስመ ለዓለም-  እምድኅረ ተንሥአ እሙታን ዓርገ ውስተ ሰማያት በስብሐት አምላከ ምሕረት: ወተቀብልዎ አዕላፋ አዕላፋት: ወሚካኤል ሊቀ መላእክት በንፍሐተ ቀርን እምኀበ እግዚአብሔር: ስብኩ ትንሣኤ ውስተ ኲሉ ምድር።  የዐማርኛ ትርጕም  የይቅርታ አምላክ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ በክብር ወደ ሰማያት አረገ፤የአእላፍ መላእክትም ተቀበሉት፤ሚካኤልም በመለኸት ድምፅ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፤በዓለም ኹሉ መነሣቱን አስተምሩ። https://t.me/maheberat

❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️ የሰኔ 12 የሀያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ማኅሌት አማርኛ ትርጉም(ክፍል ፩) 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 ሥርዓተ ነግሥ:-  ስምዐኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ 👉አቤቱ ጸሎቴን ስማኝ ምስጋና አቀርባለኹ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ 👉ጩኸቴም በፊትኽ ይድረስ ምስጋና አቀርባለኹ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ 👉ፊትኽን ከእኔ አትመልስ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ 👉በችግሬ ጊዜ ጆሮኽን ወደ እኔ አድምጥ ምስጋና አቀርባለኹ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ 👉በምጠራኽ ጊዜም ፈጥነኽ ስማኝ ምስጋና አቀርባለኹ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ንወድሶ ለዘሀሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል። 👉 ለዘለዓለሙ ምስጋና አቀርባለኹ። ያ ማለት ያለ ልዑል እግዚአብሔርን እናመስግነው ማለት ነው። በአንዲት ቃል ዓለምን ኹሉ የፈጠረ አምላክ ፈጽሞ የተመሰገነ ነው።    መልክዐ ሥላሴ፦ ሰላም ለጒርኤክሙ ስቴ አንብዐ ሰብእ ዘኀሠሠ፤ብዑላነ ሞገስ ሥላሴ ኢታንድዩኒ ሞገሰ፤እመ ትትኃየዩኒሰ ኢትኅድጉኒ ጽኑሰ፤ሚካኤልኑ ለአውጽኦ ስጋየ ጌሠ፤ወእመ አኮ ገብርኤል ወሀበኒ ነፍሰ።  የዐማርኛ ትርጕም  የሰውን እንባ መጠጥ ለፈለገ ጉሮሯችኹ ሰላም ይገባል።ባለሟል ባዕለጸጎች ሥላሴ ከበሟልነት አታሳጡኝ፤ቸል ቸል ብትሉኝ ስንኳ ችግረኛ እንደኾንኩ አትተውኝ፤ሚካኤል ሥጋዬን ለማውጣት ገሠገሠን?ያም ባይኾን ገብርኤል ነፍስን ሰጠኝ። ዚቅ  ኢይጽሕቅ ዘይመክሮ ወኢየኀሥሥ ዘይመክሮ:አልቦቱ ጥንት ወኢተፍጻሜት: ኢየኀልቅመንግሥቱ ወአልቦ ዘይክል መዊዐ ኀይሉ:ወአልቦ ኁልቊ ለሠራዊተ መላእክት እለ ይትለአክዎ: አንተ ውእቱ አቡሃ ለጥበብ: ገባሬ ኲሉፍጥረት ወገባሪሃ ለሕግ።  የዐማርኛ ትርጕም  የሚመክረው አይለምንም፤የሚመክረውም አይፈልግም።መጀመሪያና መጨረሻ የለውም።መንግሥቱም አያልቅም።ኀይሉን ማሸነፍ የሚችልም የለም።ለሚላኩት የመላእክት አለቆችም ስፍር ቁጥር የላቸውም።የጥበብ አባቷ አንተ ነኽ፤የፍጥረት ኹሉ ሠሪ አንተ ነኽ፤የሕግ ሠሪዋም አንተ ነኽ።    ነግሥ  ሰላም ለልሳንከ መዝሙረ ቅዳሴ ዘነበልባል፤ ወለድምፀ ቃልከ ሐዋዝ ቀርነ መንግሥቱ ለቃል፤ሞገሰ ክብሩ ሚካኤል ለተላፊኖስ ባዕል፤አልቦ ዘይትማሰለከ በልማደ ምሕረት ወሣህል፤እንበለ ባሕቲታ እኅትከ ማርያም ድንግል። የዐማርኛ ትርጕም  ነበልባላዊ የኾነ የምስጋና መዝሙር ለሚሰጥ አንደበትኽ ሰላም ይገባል።የቃል የመንግሥቱ መለኸት ያማረ ለቃልኽ ድምፅም ሰላም ይገባል።የተላፊኖስ ሀብታም የክብሩ ሞገስ ሚካኤል ኾይ በምሕረትና ይቅርታ ልምድ የሚመሳሰልኽ የለም።ብቸኛዋ እኅትኽ ማርያም ድንግል ናት እንጅ ዚቅ  አመ ይነፍህ ሚካኤል ቀርነ በደብረ መቅደስየ: አሜሃ ይትነሥኡ ሙታን: ይትፌሥሁ መላእክት በዕርገቱ: በፍሥሃ ወበሰላም አዕኮትዎ ለንጉሠ ስብሐት።  የዐማርኛ ትርጕም  ሚካኤል በመቅደሴ ተራራ መለኸትን በነፋ ጊዜ ያን ጊዜ ሙታኖች ይነሣሉ፤ወደ ሰማይ በማረጉም መላእክት ይደሰታሉ፤የምስጋና ንጉሥን በደስታና በፍቅር አመሰገኑት።    መልክዐ ሚካኤል፦ ሰላም ለዝክረ ስምከ ምስለ ስመ ልዑል ዘተሳተፈ፤ወልደ ያሬድ ሄኖክ በከመ ጸሐፈ፤ ሶበ እጼውእ ስመከ ከሢትየ አፈ፤ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል በከመ ታለምድ ዘልፈ፤ለረዲኦትየ ነዓ ሠፊሐከ ክንፈ።  የዐማርኛ ትርጕም  ሚካኤል ኾይ የያሬድ ልጅ ሄኖክ እንደጻፈው።ከልዑል ስም አጠራር ጋር ለተባበረ ስም አጠራርኽ ሰላም እላለኹ።የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ኾይ የተቸገሩትን የተጨነቁትን ዘወትር እንደምትረዳቸው ኹሉ እኔንም ለመርዳት ክንፍኽን ዘርግተኽ ፈጥነኽ ድረስልኝ። ዚቅ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ አቢተነ በመድኃኒትከ: ጸግወነ ንጸውዕ ስመከ: ኖላዊነ ኄር ትጉሕ ዘኢትነውም ሰላመከ ሀበነ።  የዐማርኛ ትርጕም ምስጋና ምስጋና በመድኀኒትኽ አሳድረን፤ስምኽን እንጠራ ዘንድ ስጠን፤የማታንቀላፋ ትጉ ቸር እረኛ ሰላምኽን ስጠን። ወረብ ሀበነ ሰላመከ ንጸውዕ ስመከ/፪/ ዘኢትነውም ትጉሕ "ኖላዊነ ኄር"/፪//፪/  የዐማርኛ ትርጕም የማታንቀላፋ ትጉ ቸር እረኛ፤ ስምኽን እንጠራ ዘንድ ሰላምኽን ስጠን።    መልክዐ ሚካኤል፦ ሰላም ለልሳንከ በነቢበ ጽርፈት ዘኢተሀበለ፤በእንተ ሥጋሁ ለሙሴ አመ ምስለ ሰይጣን ተበሀለ፤ሚካኤል ክብርከ እምክብረ መላእክት ተልዕለ፤ቀዊምየ ቅድመ ስዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ፤በብሂለ ኦሆ ፍጡነ አስምዐኒ ቃለ።  የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል ኾይ ስለ ሙሴ ሥጋ ከዲያብሎስ ጋር ክርክር በተደረገ ጊዜ የዘለፋ ቃል ላልተናገረ አንደበትኽ ሰላም እላለሁ።ክቡሩ መልአክ ኾይ ክብርኽ ከመላእክት ኹሉ ክብር ከፍ ያለ ነውና። በሥነ ሥዕልኽ ፊት ቁሜ ልመናዬን በማቀርብበት ጊዜ ኹሉ። “አይዞኽ አለኹልኽ” በማለት ፈጥነኽ ድምፅኽን አሰማኝ። ወረብ ቀዊምየ ቅድመ ስዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ/፪/ "በብሂለ ኦሆ"/፪/ ፍጡነ አስምአኒ ቃለ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም በሥነ ሥዕልኽ ፊት ቁሜ ልመናዬን በማቀርብበት ጊዜ ኹሉ። “አይዞኽ አለኹልኽ” በማለት ፈጥነኽ ድምፅኽን አሰማኝ። ዚቅ አመ ይነፍሕ ሚካኤል ቀርነ በደብረ መቅደስየ: አሜሃ ይትነሥኡ ሙታን: ይትፌሥሁ መላእክት በዕርገቱ: በፍሥሃ ወበሰላም አዕኮትዎ ለንጉሠ ስብሐት።  የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል በመቅደሴ ተራራ መለኸትን በነፋ ጊዜ ያን ጊዜ ሙታኖች ይነሣሉ፤ወደ ሰማይ በማረጉም መላእክት ይደሰታሉ፤የምስጋና ንጉሥን በደስታና በፍቅር አመሰገኑት።    መልክዐ ሚካኤል፦ ሰላም ዕብል ለአስናኒከ ዘመንፈስ፤ ዘኢይረክቦን ጥረስ፤ሚካኤል ረዳኢ ለእለ ውስተ ባሕር ወየብስ፤እስመ ረሰይከ ካህነ ምሥዋኡ ክርስቶስ፤መፍትው ሊተ ትተንብል ቀሲስ። የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል ኾይ መሰበር ማፋጨት ለማያገኛቸው ረቂቃን አስናኖችኽ ሰላም ይገባል።ረዳቴ መልአክ ኾይ በባሕር ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ በየብስ ላይ ለሚመላለሱ ፍጥረታት ኹሉ ረዳታቸው አንተ ነኽ።ስለዚኽም ኢየሱስ ክርስቶስ በመሠዊያው ላይ ካህን አድርጎ ሾሞኻልና። አንተ ቀሲሱ ሚካኤል ለኔ ለአገልጋይኽ ምሕረትን ትለምን ዘንድ ተገቢ ነው። ዚቅ ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕረ ምስሌሁ: ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ: ዮም ሰማያዊ በምድር አስተርአየ።  የዐማርኛ ትርጕም ባሕራንም ከርሱ ጋራ ወደ ባሕር የኼደ ሚካኤልን አየኹት መረዳቱን ግን አልቻልኩም፤ ሰማያዊ ዛሬ በምድር ታየ። ወረብ ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕረ/፪/ ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ ስዕንኩ/፪/ ባሕራንም ከርሱ ጋራ ወደ ባሕር የኼደ ሚካኤልን አየኹት፤ መረዳቱን ግን አልቻልኩም፤ሰማያዊ ዛሬ በምድር ታየ።    መልክዐ ሚካኤል ሰላም ለእስትንፋስከ ቁሱላነ ነፍስ ለአጥዕዮ፤ ዘይነፍሕ ፄና አንህዮ፤ሚካኤል ነዓ ኲናተከ በተረስዮ፤ለገቢር ከመ ቀዳሚ ለአርዌ አመፃ ደርብዮ፤እስመ ኢኃደገ እንከ ዘትካት እከዮ። የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል ኾይ የነፍስ ቁስለኞችን ለማዳን መድኃኒተ ፈውስን እፍ ለሚለው እስትንፋስህ ሰላም እላለሁ።ድል አድራጊው መልአክ ሆይ ያ የቀድሞው አመፀኛው አውሬ (ዲያብሎስ) የጥንት ተንኮሉን ሊተው አልቻለምና።የጦር መሣሪያህን ታጥቀህ።መጥተህ ድምጥማጡን አጥፋው።

ቅድስት ሥላሴ ሥላሴን ቅድስት ሥላሴ እያልን የመጥራታችን ምስጢር ምንድን ነው? ◉ አንዲት ሴት ወይም እናት ልጆቿን አልወለደችም ተብላ አትጠረጠርም ፤ ሥላሴም ይህንን ዓለም ፈጥረዋል እናም አልፈጠሩም
ቅድስት ሥላሴ ሥላሴን ቅድስት ሥላሴ እያልን የመጥራታችን ምስጢር ምንድን ነው? ◉ አንዲት ሴት ወይም እናት ልጆቿን አልወለደችም ተብላ አትጠረጠርም ፤ ሥላሴም ይህንን ዓለም ፈጥረዋል እናም አልፈጠሩም ተብለው አይጠራጠሩም። ◉ አንዲት ሴት በባሕሪይዋ ልጅን ታስገኛለች ፤ ሥላሴም ይህንን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥተው ስለፈጠሩት በሴት አንጻር ቅድስት ተብለው ይጠራሉ ። ◉ አንድም ሴት አዛኝ ናት ፤ ለታናሹም ይሁን ለታላቁ ትራራለች ሥላሴም እንደዚሁ ለፍጥረት ሁሉ ያዝናሉ ፥ ይራራሉ ፥ ምህረት ይሰጣሉ። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንዲህ ይላል ። ምህረታችሁ ከልክም በላይ የበዛ በሴት አንቀጽ ቅድስት ተብላችሁ የተጠራችሁ ሥላሴ በማለት ያመሰጥራል። ስለዚህ ቅድስት ለምን ተባሉ ቢባል በረከታቸው ፥ ርህራሄያቸውና፥ ይቅር ባይነታቸው መሆኑን ማወቅ አለብን። ◉ አንድም ሴት ልጇ ቢታመምባት አትወድም ፤ ሥላሴም አንድም ልጅ በዲያብሎስ እጅ ተይዞ በኃጢአት እንዲታመሙ አይወዱም ፥ አይፈቅዱም በመሆኑም ቅድስት ይባላሉ። ◎ አንድም ሴት ልጅ የልጇን ነውር አትጠየፍም ልጄ ቆሽሿል ፥ ተበላሽቷል ብላ ፊቷን አታዞርም። ሥላሴም የሰውን በኃጢአት መቆሸሽ ሳይፀየፉ በቸርነታቸው ጎቦኝተው ለንስሐ ያደርሱታል ። ◎ ይህንን የፅድቅ አየር የምንምገው ያማረውንም ብርሃን የለበስነው ስለ ፅድቃችን ሳይሆን በሥላሴ ቸርነት ነውና ስለዚህም ሥላሴን በሴት አንቀፅ ቅድስት እንላቸዋለን። ◉ አንድም ሴት ልጆቿን ፈጭታና ጋግራ ትመግባቸዋለች ሥላሴም እንደዛው ናቸው ። በዝናብ አብቅለው በፀሐይ አብሥልው ፍጥረታትን ሁሉ ይመግባሉ። ስለዚህ ሥላሴ እንደ እናት ሁሉንም ይመግባሉና በሴት አንቀጽ ቅድስት ይባላሉ ።

ምስጋና በመቅደስህ ምስጋና በመቅደስህ ዝማሬ በማደርያህ ልሰዊ ጠዋት ማታ ክብሬነህ የኔ ጌታ ሰገነት አይመቸኝ ካባዬ ክብር አይሆነኝ ሁሉንም ንቄዋለው ያንተን ቤት መርጫለው/2/ አዝ ====== ያረጃል ያለም ዝና ጥበብም ሆኖ መና አንተ ግን ያው አንተነህ በሁሉ ትፀናለህ/2/ አዝ ====== ከሰማይ ባይንህ ታየው በፍቅረሸህ ተጎበኘው በባህሪህ ባለጸጋ ፈወስከኝ በደም ዋጋ/2/ አዝ ====== ቃልህን ነብሴ ሰምታ ተዋበች በእልልታ ወደ ግርህ መረገጫ መስገዴ አለው ብልጫ /2/

Repost from Janderebaw Media
"አሕዛብ፦ አምላካቸው ወዴት ነው? ለምን ይላሉ? የፈሰሰውን የባሪያዎችህን ደም በቀል ዓይኖቻችን እያዩ አሕዛብ ይወቁት።" መዝሙር 79:10

ዘምር ዘምር አለኝ ዘምር ዘምር አለኝ ልቤ ተነሳሳ(2) የአምላኬን ቸርነት እንዴት ብየ ልርሳ ያደረገልኝን እንዴት ብየ ልርሳ አዝ.............. የሚቃጠለው ስም በፊትህ ምንድን ነው ሰማይና ምድር ሁሉም ገንዘብህ ነው ያለኝን ሰብስቤ ባኖረው በፊትህ ዋጋ አይሆንም ጌታ ስለቸርነትህ አዝ.............. ይበዛል ይሰፋል የእግዚአብሔር ምስጋና አይቆምም በዘመን ማዕበል ነውና እንኳን ድንጋይ ቀርቶ ጣራው ቢናድብኝ የከንፈሬን ፍሬ ማንም አይወስድብኝ አዝ............... የጳውሎስ የሲላስ መከራ ቢፀና አልተውም ቅኔውን የአምላኬን ምስጋና ሊያስጥለኝ አይችልም እስር ሰንሰለቴ አለብኝ ውለታ የሰማይ አባቴ አዝ............... የተደረገለት ብዙ የተቀበለ ይኖራል በፍቅሩ እየተቃጠለ ክብሬን ሁሉ ትቼ ልዘምርልህ ይህ ነው ችሎታዬ ላንተ ምሰጥህ

#Update ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ " በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት 13 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን፣ ከ280 በላይ ምእመናን መፈናቀላቸውንና
+1
#Update ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ " በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት 13 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን፣ ከ280 በላይ ምእመናን መፈናቀላቸውንና የ101 ዓመት ቤተ ክርስቲያን መቃጠሉን " አሳወቁ። ብፁዕነታቸው በደረሰው ጥቃት ሐዘናቸውን ገልጸዋል። ብፁዕነታቸው " ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ:ም ጀምሮ በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ ወረዳ፣ በሺርካ ወረዳና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 13 ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ የ101 ዓመት እድሜ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል " ብለዋል። " የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል " ሲሉ ገልጸዋል። የተገደሉ ሰዎች ስም ዝርዝርም እንደሚከተለው ነው ፦ 1. አቶ ደምረው አበራ የ70 ዓመት 2. ከፈለኝ ልክየለው የ56ዓመት 3. ሐይሉ ንጉሴ የ70 ዓመት 4. እሸቴ ዳመና የ42 ዓመት 5. አበባየሁ ዳኜ የ42 ዓመት 6. ሰሙ አባይነህ የ70 ዓመት 7. 1 ሚሊሻ 8. አማረ በላይነህ የ80 ዓመት 9. ተሬ ደሴ የ25 ዓመት 10. ወጣት ገነነ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ 11. ሙርቴሳ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ 12. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 13. አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ በተጨማሪ በአሰኮ ወረዳ ከ280 ሰው በላይ መፈናቀሉን ብፁዕነታቸው ጠቁመዋል። " በመሆኑም ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በሃይማኖታቸው ብቻ ቤታቸው እየተለየ ተቃጥሏል፤ ንብረታቸውና ከብቶቻቸው ተዘርፈዋል። ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎችም ይዘውት የሸሹት እምነታቸውንና ማንነታቸውን ብቻ በመሆኑ አሁን ላይ ሜዳ ላይ ወድቀው ይገኛሉ " ብለዋል። " በተፈጸመው ጥቃት የተሰማነን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን የሞቱትን ወገኖቻችን (ልጆቻችን) እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን ይማርልን (በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን) ያዘኑትን እና የተፈናቀሉትን ወገኖቻችን (ልጆቻችን) እግዚአብሔር ያጽናናልን " ሲሉ ሀዘናቸውን ገልጸዋል። መረጃው የአርሲ ሀገረ ስብከት ሚድያ ነው። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ከ10 በላይ ምዕመናን መገደላቸውን ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል። በአሰኮ ወረዳ፣ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ
ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ከ10 በላይ ምዕመናን መገደላቸውን ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል። በአሰኮ ወረዳ፣ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ እና ካራ ኩፍቴና በሚባሉ አካባቢዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጥሯል የተባለው ጥቃት " አሰቃቂ እንደነበር " የአይን እማኞች ለቴሌቪዥን ጣቢያው ገልጸዋል። " በአሰኮ ወረዳ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ ብቻ በታጣቂ  ኃይሎች ጥቃት ከ10 በላይ ንጹሃን ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል " ብለዋል። በአካባቢው 101 ዓመታትን ዕድሜ ያስቆጠረው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወውደሙን እማኞች አመልክተዋል። በካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይ ጥቃት የተሰነዘረ ሲሆን የቤተክርስቲያኑ ንብረት የሆኑ ቤቶች በመቃጠላቸው ምእመናን የመድኃኔዓለምን ቅዱስ ጽላት ይዘው በእግራቸው ወደሌላ አካባቢ መሻቸውን የአይን እማኞቹ አሳውቀዋል። ቤቶችን የማቃጠል፣ ንብረት ከብቶችን የመዝረፍ ድርጊት እንደነበረም ተመላክቷል። በሌላ በኩል ፥ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሺርካ ወረዳ ሁለት ወጣት ኦርቶዶክሳውያን ላይ ግድያ መፈጸሙ ተገልጿል። ድርጊቱ የተፈጸመው ሚታና ዋጂ በተባለ ቀበሌ ሲሆን ታጣቂዎች ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ወጣቶቹ መኖሪያ ቤት በመግባት ከያዟቸው በኋላ ወደ ሚታና ጋዶ ቀበሌ በመውሰድ አንደኛውን በስለት ሁለተኛውን ደግሞ በጥይት በመምታት በጭካኔ ሕይወታቸውን እንዳጠፉት የቤተክርስቲያኗ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ሕይወታቸውን ያጡት ወጣቶች ሥርዓተ ቀብር ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በጋዶ ማሕደረ ስብሐት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን  ተፈጽሟል። በአርሲ ሀገረስብከት ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ ጥቃቶች ተፈጽመው የሰዎች ህይወት ማለፉ፣ ጉዳት መድረሱ የሚታወቅ ሲሆን ከጥቂት ወራት በፊት መሰል ጥቃቶች ሪፖርት መደረጋቸው የሚዘነጋ አይደለም። (ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአካባቢው ነዋሪዎችን እያነጋገረ ሲሆን ቤተክርስቲያኗ እና የሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ከሰጡበት ተካቶ ይቅረባል) ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

አበረታኝ ፍቅርህ ጌታዬ አበረታኝ ፍቅርህ ጌታዬ አበረታኝ ክንድህ አምላኬ በስምህ ድኛለሁ በፀጋህ በማደሪያህ ሆኜ ስጠራህ አዝ--- ሰዶም ስትቃጠል መርገሟ ሲበዛ ሊተወኝ አይሻም ልጁን እንደዋዛ ህጉን በማሰቤ አምላክ ፈረደልኝ ጎትቶ የሚያወጣ መልአክ ሰደደልኝ አዝ--- በገናን መደርደር አያቆምም ጣቴ የወንጭፌ ድንጋይ አንተነህ ጉልበቴ የሳኦልን ካባ አውልቀህ ጣልክልኝ የፍልስጤሙን ሰው ክንድህ ሰበረልኝ አዝ--- ሶስት ጌዜ ስክድህ አላውቅህም ብዬ ዶሮ ስለጮኸ ትዝ አልከኝ ጌታዬ ወጣሁኝ በዕንባ ከአይሁድ እሳት ሥር ከሐዲ ሳትለኝ አኖርኝ በፍቅር አዝ--- ሳምራዊ ናት ሳትል ክብርን የጠኽኝ እንደ አንተ ከአይሁድ ፍቅርን ማን አሳየኝ ምስጢሬን በሙሉ ነገርከኝ ጌታዬ የፍቅር ውሃ ቀዳሁ እንሥራዬን ጥዬ

✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹 እንኳን አምላክን ለወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል
✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹 እንኳን አምላክን ለወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ለታየበት ፤ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም ታላቅ በዓልን ላደረጉበት ለተወደደች ዕለት በሰላም አደረሳችሁ🙏 🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀 "አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኀምሰ ዕለታተ። ትእምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ። ሚ መጠነ ማርያም ታሥተፌሥሒ ትፍሥሕተ። ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሑ መዓልተ። ብፁዕ ዘርእየኪ በሕልሙ ሌሊተ"። ትርጉም፦ ✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹 የፊትሽን መልክ ያይ ዘንድ የሞተ ሰው እስኪነሣ ድረስ በደብረ ምጥማቅ ለአምስት ቀናት ያኽል በተገለጽሽ ጊዜ ማርያም ምን ያኽል ደስ ታሰኚ ኖሯል! በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ምስጉን ነው። አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም በማኅሌተ ጽጌ። ✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹

❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️ የግንቦት ደብረ ምጥማቅ ማርያም ስርዓተ ማኅሌት አማርኛ ትርጓሜ ክፍል ፪ ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨  ዚቅ ክበበ ገጻ ከመ ወርኅ፤ወአዕይንቲሃ ከመ ኮከበ ጽባሕ፤ወቆማ ከመ በቀልት ለማርያም ድንግል፤ወላህያ ከመ ጽጌረዳ፤ ከመ ፍህም ቀይሕ ከናፍሪሃ፤እስመ ወለደት ለነ መና ኅቡዐ፤ ዘውእቱ ኅብስተ ሕይወት፤ መፍትሔ ሕማማት።  የዐማርኛ ትርጕም የፊቷ ቅርጽ እንደ ጨረቃ ነው፤ዐይኖቿም እንደ ማለዳ ኮከብ ናቸው፤የድንግል ማርያም ቁመቷም እንደ ዘንባባ ነው፤ደም ግባቷም እንደ ጽጌረዳ አበባ ነው፤ከናፍሮቿ እንደ ቀይ ፍም ናቸው፤ የተሸሸገ መናን ወልዳልናለችና። ርሱም የችግሮች ፈቺ የሕይወት ምግብ ነው።  ወረብ ክበበ ገጻ ከመ ወርኅ ወአዕይንቲሃ ከመ ኮከበ ጽባሕ/፪/ ወቆማ ከመ በቀልት ለማርያም ድንግል/፪/  የዐማርኛ ትርጕም የፊቷ ቅርጽ እንደ ጨረቃ ነው፤ዐይኖቿም እንደ ማለዳ ኮከብ ናቸው፤የድንግል ማርያም ቁመቷም እንደ ዘንባባ ነው።  መልክዐ ማርያም ሰላም ለጒርዔኪ ሠናይ እምወይን፤በከመ ይቤ ሰሎሞን፤ማርያም ድንግል ለባሲተ ዐቢይ ብርሃን፤ክድንኒ ገርዜነ ጸጋ ኢያዕጽበኒ ዕርቃን፤ዘኢአነምዎ ጠቢባን በኪን።  የዐማርኛ ትርጕም ሰሎሞን እንዳለ ከወይን ለሚያምር ጉሮሮሽ ሰላም ይገባል።ትልቅ ብርሃንን የተጎናጸፍሽ ድንግል ማርያም ኾይ መራቆት እንዳያስጨንቀኝ ጥበበኞችና ብልኻተኛ ያልሰሩትን የጸጋ ግምጃ አልብሽኝ። ዚቅ በከመ ይቤ ሰሎሞን በእንተ ማርያም፤ ንዑ ንትፈጋዕ ወኢይኅልፈነ ጽጌ ደመና መስቀል ዘዮም አብርሀ በሥነ ማርያም፤ጴጥሮስኒ ሰመያ እመ ብርሃን፤ጳውሎስኒ ይቤላ ደብተራ ግዕዛን፤አጽገዩ ሕዝብ ወመሐይምናን፤በቤተ መርዓ ተመልዑ ክርስቲያን።  የዐማርኛ ትርጕም ሰሎሞን ስለ ማርያም እንዳለ እንደሰት ዘንድ ኑ በማርያም ደም ግባትም ዛሬ ያበራ የመስቀል ደመና አበባ አይለፈን፤ጴጥሮስ የብርሃን እናት አላት፤ጳውሎስም የነጻነት ድንኳን አላት።ሕዝብና አማኞች አሸበረቁ፤ በጫጉላ ቤት ክርስቲያኖች ሞሉ።  ወረብ በከመ ይቤ "ሰሎሞን"/፪/ በእንተ ማርያም/፪/ ንዑ ንትፈጋዕ ወኢይኅልፈነ "ጽጌ"/፪/ ደመና አብርሀ በሥነ ማርያም/፪/ ትርጉም፦ ሰሎሞን ስለ ማርያም እንዳለ እንደሰት ዘንድ ኑ። በማርያም ደም ግባት ደመና አበራ።  መልክዐ ማርያም ሰላም ለመልክዕኪ ዘተሠርገወ አሚረ፤ ዘያበርህ ወትረ፤ፍቅርትየ አንቲ እንተ ታበድሪ ፍቅረ፤አርእይኒ ገጸ ዚአኪ ማርያም ምዕረ፤ዘኢይሰምዖ ካልዕ እንግርኪ ነገረ።  የዐማርኛ ትርጕም ዘወትር የሚያበራ የፀሓይ ጮራን ለተሸለመ መልክሽ ሰላም ይገባል።ፍቅርን የምትሰጪ ወዳጄ አንቺ ኾይ ሌላ የማይሰማው ነነገርን እነግርሽ ዘንድ ያንቺን ፊት ማርያም አንድ ጊዜ አሳይኝ።  ዚቅ ትበርህ እምኮከበ ጽባሕ፤ወታስተርኢ እምአርእስተ አድባር፤አዳም ወሠናይት፤ ጽዕዱት ወብርህት ከመ ፀሐይ። የዐማርኛ ትርጕም ከጠዋት ኮከብ ይልቅ ትበራለች፤ ከተራሮች ራሶችም ትታያለች፤ፈጽማ ያማረች ናት፤ነጭና እንደ ፀሓይ የምታበራ ናት።  ወረብ ትበርህ እምኮከበ ጽባሕ ወታስተርኢ እምአርእስተ አድባር/፪/ አዳም ወሠናይት ጽዕዱት ወብርህት ከመ ፀሐይ ብርህት/፪/  የዐማርኛ ትርጕም ከጠዋት ኮከብ ይልቅ ትበራለች፤ከተራሮች ራሶችም ትታያለች፤ፈጽማ ያማረች ናት፤ ነጭና እንደምታበራ ፀሓይ የምታበራ ናት።  መልክዐ ማርያም በዝንቱ ቃለ ማሕሌት ወበዝንቱ ይባቤ፤ለዘይስእለኪ ብእሲ ጊዜ ረከቦ ምንዳቤ፤ብጽሒ ፍጡነ ትሰጠዊዮ ዘይቤ፤ማርያም ዕንቊየ ክርስቲሎቤ ወምዕዝተ ምግባር እምከርቤ፤ዘጸገየ ማሕጸንኪ አፈወ ነባቤ።  የዐማርኛ ትርጕም ችግር ባገኘው ጊዜ በዚኽ የምስጋና ቃል እና በዚኽ እልልታ ለሚለምንሽ ሰው የሚለውን ትሰጭው ዘንድ ፈጥነሽ ድረሺ፤ዕንቊዬ የኾንሽ ዕንቊ ማርያም ከሽቱ ይልቅ በምግባር የምትሸቺ ማሕጸንሽ ያበበውን ተናጋሪ አፍን ስጪው።  ዚቅ ኢይትዐፀዉ አናቅጽኪ: ክቡራት ዕንቊ መሠረትኪ ሠናይት ሰላማዊት እንተ ናፈቅራ በጽድቅ: መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል።  የዐማርኛ ትርጕም ደጆችን አይዘጉ፤መሠረትሽ የከበረ ዕንቊ ነው፤ያማረች ሰላማዊት በእውነት የምንወዳት የአፏ ሽታ እንደ እንኮይ ነው ወረብ ኢይትዐፀዉ አናቅጽኪ ክቡራት ዕንቊ መሠረትኪ/፪/ ሠናይት ሰላማዊት "እንተ ናፈቅራ"/፪/ በጽድቅ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም ደጆችን አይዘጉ፤መሠረትሽ የከበረ ዕንቊ ነው፤ያማረች ሰላማዊት በእውነት የምንወዳት ናት  ማኅሌተ ጽጌ ኦ ሰላመ ሰጣዊት እንተ ትሔውጺ እምርኁቅ፤ ወትትረአዪ ለኲሉ በደብረ ምጥማቅ፤ተፈሥሒ ድንግል ዘገዳመ ጽጌ ማዕነቅ፤እስመ ተሰምዐ በምድርነ ቃለ ተአምርኪ ጽድቅ፤ ለአድኅኖ ኀጥእ ዘይበቊዕ እምብሩር ወወርቅ።  የዐማርኛ ትርጕም ሰላምን የምሰጪ ከሩቅ ይምታበሪ ምጥማቅ በተባለ ተራራ ለኹሉ የምትታዪ የአበባ ጫካ ሽመላ ድንግል ደስ ይበልሽ።ከብርና ከወርቅ ይልቅ ኀጢአተኛን ለማዳን የሚጠቅም የተኣምርሽ ቃል እውነት በምድራችን ተሰርቷልና።  ዚቅ እንተ ታስተርኢ እምአርእስተ አድባር ርኁቅ: ጻድቃን ኪያሃ አብደሩ እምወርቅ: ሀገረ ክርስቶስ ሐዳስ ንድቅ: ወበውስቴታ የሐድር ጽድቅ።  የዐማርኛ ትርጕም ከተራሮች ራሶች በርቀት የምትታይ ጻድቃን ከወርቅ ይልቅ ርሷን መረጡ፤ የክርስቶስ አገር ዐዲስ ሕንፃ ናት። በውስጧም እውነት ያድራል።  ምልጣን አይ ይእቲ ዛቲ እንተ ታስተርኢ እምርኁቅ ከመ ማኅቶት: ብርህት ከመ ፀሐይ: ሙሴኒ ርእያ ሀገር ቅድስት: ዕዝራኒ ተናገራ: ዳዊት ዘመራ።  የዐማርኛ ትርጕም እንደ ፀሓይ የምታበራ ፤እንደ መብራት ከሩቅ የምትታይ ይኽች ማን ናት? ሙሴ ያያት አገር ናት፤ዕዝራም ተናገራት፤ዳዊትም አመሰገናት። አመላለስ ዕዝራኒ ተናገራ/፪/ ተናገራ ዳዊት ዘመራ ተናገራ ዘመራ ዳዊት/፪/  የዐማርኛ ትርጕም ዕዝራም ተናገራት ተናገራት፤ ዳዊት አመሰገናት ዳዊት አመሰገናት  እስመ ለዓለም አይ ይእቲ ዛቲ እንተ ትሔውጽ ከመ ጎህ:አዳም ከመ ወርኅ: ሠናይት ከመ ሥርዓት:ብርህት ከመ ፀሐይ: እምሊባኖስ ትወጽእ መርዓት: እምነ ጽዮን አግዓዚት: ታቦተ ፍሥሓ ምስሌሃ: ወአሕዛብኒ ቅድመ ገጻ: ወትረ ተሀሉ ምስሌነ።  የዐማርኛ ትርጕም እንደ ፀሓይ የምታበራ፣እንደ ድርጭት ወፍ የምታምር፣እንደ ጨረቃ የምታምር፣ እንደ ማለዳ ጮራ የምታበራ ይኽች ማን ናት? ከሊባኖስ ተራራ ሙሽራ ትወጣለች፤ነጻ ከምታወጣ ከጽዮን፣የደስታ ታቦት/ማደሪያ ከርሷ ጋራ አለ፤አሕዛብም ከፊቷ አሉ፤ዘወትር ከእኛ ጋራ ትኑር። 🔆 መልካም በዓል 🔆

❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️ የግንቦት ደብረ ምጥማቅ ማርያም ስርዓተ ማኅሌት አማርኛ ትርጓሜ ክፍል ፩ ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ሥርዓተ ነግሥ:- 👉ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፣ በአሐቲ ቃል። ትርጉም፦ 👉አቤቱ ጸሎቴን ስማኝ ምስጋና አቀርባለኹ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ 👉ጩኸቴም በፊትኽ ይድረስ ምስጋና አቀርባለኹ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ 👉ፊትኽን ከእኔ አትመልስ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ 👉በችግሬ ጊዜ ጆሮኽን ወደ እኔ አድምጥ ምስጋና አቀርባለኹ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ 👉በምጠራኽ ጊዜም ፈጥነኽ ስማኝ ምስጋና አቀርባለኹ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ንወድሶ ለዘሀሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል። 👉 ለዘለዓለሙ ምስጋና አቀርባለኹ። ያ ማለት ያለ ልዑል እግዚአብሔርን እናመስግነው ማለት ነው። በአንዲት ቃል ዓለምን ኹሉ የፈጠረ አምላክ ፈጽሞ የተመሰገነ ነው። መልክዐ ሥላሴ፦ ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ ለሣሕል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል። የዐማርኛ ትርጕም በአካል እኩል ለኾኑ ኩላሊቶቻችኹ ሰላም ይገባል።ሥላሴ ከእናንተ አንዱ እግዚአብሔር ቃል ዓለማችኹን በይቅርታ በጎበኘ ጊዜ የአበው ተስፋ በድንግል ማርያም ተፈጸመ። በቀራንዮም መድኀኒት የኾነ መስቀል ተተከለ።  ዚቅ ወሀለወት አሐቲ ድንግል ብርህት ከመ ፀሐይ: እንተ ታስተርኢ እምአርእስተ አድባር: ወትትመረጐዝ በትእምርተ መስቀል።  የዐማርኛ ትርጕም በመስቀል ምልክት ተደግፋ ከተራሮች ራሶች የምትታይ እንደ ፀሓይ የምታበራ አንዲት ድንግልም አለች።  ነግሥ ሰላም ለልሣንከ መዝሙረ ቅዳሴ ዘነበልባል፤ወለድምፀ ቃልከ ሐዋዝ ቀርነ መንግሥቱ ለቃል፤ሞገሰ ክብሩ ሚካኤል ለተላፊኖስ ባዕል፤አልቦ ዘይትማሰለከ በልማደ ምሕረት ወሣሕል፤እንበለ ባሕቲታ እኅትከ ማርያም_ድንግል።  የዐማርኛ ትርጕም ለመምስጋና መዝሙር ነበልባል ለኾነ አንደበትኽ ሰላም ይገባል። የቃል የመንግሥቱ መለኸት የኾነ ሚያምር የቃል ድምፅም ሰላም ይገባል።የተላፊኖስ የክብሩ ሞገስ ሚካኤል ኾይ በምሕረትና ይቅርታ ያለ ብቸኝዋ እኅትኽ ድንግል ማርያም የሚመስልኽ የለም።  ዚቅ መላእክት በልሳነ እሳት ይሴብሑኪ፤መላእክት በአክናፈ ብርሃን ይኬልሉኪ፤ማርያም እምነ ወእሙ ለእግዚእነ፤መላእክት በቀለመ ወርቅ ይጽሕፉ ውዳሴኪ፤እስከ ዳግም ምጽአቱ ለበኲርኪ። የዐማርኛ ትርጕም መላእክት በእሳት አንደበት ያመሰግኑሻል፤መላእክት በብርሃን ክንፎች ይጋርዱሻል፤የጌታችን እናት የኾንሽ እናታችን ማርያም ኾይ መላእክት እስከ የኸር ልጅሽ ዳግም ምጽአት ድረስ በቀለመ ወርቅ ምስጋናሽን ይጽፋሉ።  ዘጣዕሙ ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኀኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኰት ስሙ።  የዐማርኛ ትርጕም እንደልጅሽ የደሙ አምሳል ጣምናው ድንቅ የኾነ ለስምሽ መታሰቢያ ሰላም ይገባል። ማርያም የሕይወት መሠረት ነሽ፤ ከጥንት ከተገኘው ለመድኀኒትም መጀመሪያ ነሽ። ለዓለሙ ቤዛ አድርጎ አንችን መልካሟን የፈጠረ እግዚአብሔር ይባረክ፤ ስሙም ይመስገን። ዚቅ እግዚአብሔር ውእቱ ብርሃንኪ ለዓለም: ወመሠረትኪ ለትውልደ ትውልድ: ኢየኀልቅ ብዝኀ ሰላምኪ: ወነገሥት ይትቀነዩ ለኪ: ያመጽኡ አምኃኪ እምርኁቅ ብሔር።  የዐማርኛ ትርጕም ለዓለም ብርሃንሽ እግዚአብሔር ነው። ለልጅ ልጅም መሠረትሽ ነው። የሰላምሽ ብዛት አያልቅም፤ነገሥት ይገዙልሻል፤ከሩቅ አገር እጅ መንሻሽን ያመጣሉ።  መልክአ ማርያም ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ፤እምነ ከልበኔ ወቊስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ፤ማርያም ድንግል ለባሲተ ዐቢይ ትእዛዝ፤ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ ዐዚዝ፤ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ።  የዐማርኛ ትርጕም ከሽቱ፣ከነጭ ዕጣንና ከሚሸት ዕጣን የሚያምር የስምሽ መታሰቢያ ሰላም ሰላም ይገባል።ትልቅ ትእዛዝን የተጎናጸፍሽ ድንግል ማርያም ኾይ ፈሳሽ ውኃ መልካም ዝግባን እንደሚያጠጣው ጽኑዕ የኾነ የፍቅርሽ ወይን ዘወትር /ጠዋት ጠዋት/ ያጠጣኝ።  ዚቅ በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኁብርት: እኅትየ መርዓት ርግብየ ሠናይት: ርቱዕ አፍቅሮትኪ እምወይን: መዓዛ ዕፍረትኪ እምኲሉ አፈው: እትፌሣሕ ወእትኃሠይ ብኪ: ናፍቅር አጥባተኪ እምወይን: ኲለንታኪ ሠናይት እንተ እምኀቤየ: አልብኪ ነውር ወኢምንትኒ ላዕሌኪ: ፃዒ እምሊባኖስ እኅትየ መርዓት።  የዐማርኛ ትርጕም በወርቅ ልብሶች የተሸለመችና የተጎናጸፈች ናት፤እኅቴ ሙሽራ ርግቤ ቆንጆ ናት፤ከወይን መውደድሽ የቀና ነው፤የሽቶሽ ሽታ ከሽቶዎች ኹሉ ያምራል፤ፈጽሜ በአንቺ እደሰታለኹ፤ከወይን ይልቅ ጡቶችሽን እንውደድ፤በእኔ ዘንድ ኹለመናሽ መልካም ናት፤ ነውር የለብሽም፤በላይሽ ላይም ምንም ነገር የለብሽም፤እኅቴ ሙሽራዬ ኾይ ወደ ሊባኖስ ተራራ ውጪ።  ወረብ "በአልባሰ ወርቅ"/፪/ ዑጽፍት ወኁብርት/፪/ እኅትየ መርዓት ርግብየ ሠናይት እኅትየ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም በወርቅ ልብስ የተሸለመችና የተጎናጸፈች እኅቴ ሙሽራ ርግቤ ቆንጆ እኅቴ  መልክዐ ማርያም ሰላም ለገጽኪ ዘጥቀ ይልሂ፤እምሥነ ከዋክብት ወወርኅ ወእምሥነ ፀሐይ መብርሒ፤ማርያም ድንግል ፍንዋትየ ሠርሂ፤በመዓልት ወበሌሊት ኢይርከበኒ ጸናሂ፤መሥገርተ አበሳ ዘይጠፍር ወግበ ይድሂ።  የዐማርኛ ትርጕም  ከከዋክብትና ጨረቃ ደም ግባት እና ከሚያበራ የፀሓይ ደም ግባት እጅግ ለሚያምር ፊትሽ ሰላም ይገባል፤ድንግል ማርያም ኾይ የበደል ወጥመድን የሚታታ እና ጉድጓድን የሚቆፍር ጠላት በቀንና በሌሊት እንዳያገኘኝ መንገዶቼን አቅኚ። 🔆 መልካም በዓል 🔆

✞ አቡነ አቢብ (አባ ቡላ) ✞ ✝️ ልዩ ስሟ አምዓዳ በምትባል ሀገር በሉፊ አውራጃ በሮም አገር አንድ ጽኑ ክርስቲያን ነበር፡፡ ✝️ ይህ ክርስቲያን ስሙ አብርሃም ይሰኛል፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከአንዱ አገር ወደ ሌላ አገር ሲሰደድ የኖረ እግዚአብሔርን የሚፈራ ለሰው ሁሉ በጎን የሚያደርግ ለነዳይና ለምስኪን ባልቴቶች እናት አባት ለሞቱባቸዉ ልጆች ምጽዋትን የሚሰጥ ነበር፡፡ ✝️ እንዲሁም እንደርሱ ደግ የሆነች ስሟ ሐሪክ የምትባል ደግ ሚስት ነበረችው የስሟ ትርጉምም  በክርስቶስ የታመነች ማለት ነው፡፡  ✝️ እነዚህ ሁለት ደግ ክርስቲያኖች ታዲያ ልጅ አልነበራቸውም ነገር ግን ልጅ ባይኖራቸውም እለት እለት እግዚአብሔርን ከማመስገን በቀር አማረው አያውቁም ነገር ግን ለቤተ እግዚአብሔር  አገልጋይ የሚሆን አንድ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ በአንቃዕድዎ ወደ እግዚአብሔር ይለምኑ ነበር፡፡ ✝️ አንድ ቀን መልዐከ እግዚአብሔር ለዚህ   ደግ ሰው ተገልፆ ይኽ ፍሬ የአንተ ነው እርሱም ወደ እኔ የሚቀርብ እግዚአብሔርን የሚያስደስት ፈቃዱንም የሚፈፅም ያማረ መባዕ ነው ብሎ እጅግ መልካም ፍሬን በእጁ ሰጠው፡፡ ✝️ ይኽ ደግ ሰው አብርሃምም ከእንቅልፉ ተነስቶ ይህንን  በህልሙ የሰማውንና የአየውን ነገር ኹሉ ለሚስቱ ሐሪክ ነገራት እርሷም ታላቅ ደስታ ተደሰተች ልዑል እግዚአብሔርን በአንድነት አመሰገኑ፡፡ሚስቱ ሐሪክም ፀነሰች፡፡ ✝️ ይኽቺ ሚስቱ ሐሪክ በፀነሰች ጊዜም በቤታቸው መካከል ሁለንተናው መልካምና ታላቅ ዛፍ በቀለ በቅጠሉ ላይ በዕብራይስጥ ቋንቋ የተጻፈ ጽሕፈትን አዩ ጽሕፈቱም በጽዮን አድሮ የሚኖር የያዕቆብ ፈጣሪ ቅዱስ የእግዚአብሔር አገልጋይ ቡላ የሚል ነው፡፡ ✝️ ከዚህም በኀላ ሐሪክ መልከ መልካምና ከብርሃናት ይልቅ ፊቱ የሚያበራ ወንድ ልጅን ወለዱ፡፡እናቱና አባቱ ይህንን በአዩ ጊዜ ታላቅ ደስታ ተደስተው ለነዳያን ምጽዋትን ለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን በወርቅና በብር ያጌጡ የነዋየ ቅድሳት አልባሳትን ሰጡ ስሙንም ቡላ ብለው ሰየሙት፡፡ትርጓሜውም ለእግዚአብሔር የተለየ ማለት ነው፡፡ ✝️ እናትና አባቱም በመልካም አስተዳደግ አሳደጉት አሥር አመት በሆነው ጊዜም በመጀመሪያ አባቱ አብርሃም አረፈ ከትንሽ ቀናት በኀላ እናቱ ሐሪክ አረፈች፡፡ ✝️ በዚያን ዘመን ታዲያ ንጉሡ ቤተ ክርስቲያንን እንዲዘጉ እና ቤተ ጣዖት እንዲከፍቱ ክርስቲያን ሁላቸው የምስጋና ባለቤት ጌታችንና መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን (ሎቱ ስብሐት) እንዲክዱ የሚል ወደዚያች አገር ደረሰ፡፡ ✝️ ይህ የተባረከ ብላቴና ቡላም ይህንን በሰማ ደጋጎች ክርስቲያንም ሲሰቃዩ ባየ ጊዜ ስለ ክርስቶስ በሰማዕትነት ይሞት ዘንድ ጨክኖ ሕዝብን ሰማዕትነት ለመቀበል በወዲህም በወዲያም ያሉትን ሕዝቡን እየገፋ ሄዶ ንጉሥ አቅሮጵስ ካለበት ቀርቦ ያፈርክና የተዋረድክ የረከስክ የጽድቅ ሁሉ ጠላት የዲያቢሎስ መልእክተኛ አንተና ንጉስክ የተነቀፋችሁ የምታመልኳቸው ጣዖታትም የተዋረዱና በምድር የረከሱ ናቸው አለው፡፡ ✝️ ንጉሡም ሰምቶ ይህንን ወጣቱ ቡላን አስረው ከፊቱ ያቆሙት ዘንድ አዝዞ ተመልከቱ የእሊክ ክርስቲያን ልቦናቸው የጸና ነው ትንሽ ብላቴና ሆኖ ሳለ ምንም አልፈራም ይልቁኑም እንድቀጣው ይቃወመኛል እንጂ አለ፡፡ ✝️ ይህንንም ብሎ በሚቆራርጥ ብረት ሠንሰለት አሰሩት ጀርባውን በአለንጋ እንዲገርፉት ሰውነቱም እየለያዩ እየቆራረጡ የውስጥ አንጀቱን በተቆለፈ ብረትና በስለታማ መጋዝ እጆቹንና እግሮቹን ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ፡፡ ✝️ በእንዲህ ባለ መከራ ቢያሰቃዩትም ተመልሶ በእግሩ ይቆማል እንጂ አልሞተም ንጉሡ እሊህ ክርስቲያን መተታቸውን ተመልከቱ አለ፡፡ ✝️ እንዲሁም አባ ቡላ በአሥራ አምስት አመቱ ከሌላ ንጉሥ ጋር እንደ ቀድሞ ለረከሱ ጣዖቶች አልሰግድም በማለቱ ብዙ ስቃይ አሰቃየው በመጨረሻም አንገቱን ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ብጹዕ ጻድቅ ቡላም ራሱን ከመቁረጣቸው አስቀድሞ ከመዝሙረ ዳዊት ሳምኬት ዐማፅያንን ጠልቼ ሕግህን ተከተልኩ ረዳቴና መጠጊያዬ አንተ ነህ በቃልህም አመንኩ የአምላኬን ትዕዛዝ እፈፅም ዘንድ  ዐማፅያን ከእኔ ራቁ በሕይወት እኖር ዘንድ እንደ ቃልህ ተቀበለኝ ተስፋዬንም አታስቀርብኝ ርዳኝ አድነኝ ሁል ጊዜ ሕግህን እናገራለሁ ከትእዛዝህ የሚርቁ ሁሉ ምኞታቸው አመፃ ነውና አዋረድኻቸው እሊኽ በምድር ያሉ ኃጥአን ከዳተኞች ናቸው፡፡ ስለዚህም አምልኮተ ሕግህን ወደድኹ፡፡ከሕግህ የተነሣ ፈርቻለሁና በአንተ መታመንን ከሰውነቴ ጋራ አስማማ፡፡ የሚለውን ጸሎት ጸለየ፡፡ ✝️ የእግዚአብሔር አገልጋይ ቡላም በዚህች ቀን በሚያዝያ 18 አንገቱን ተቆረጠ በዚህን ጊዜ መልአከ እግዚአብሔር ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ወርዶ ራሱን ወስዶ ከሥጋው ቢያገናኘው እንደነበረ ሆኖ ተነሣ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም አይዞህ አትፍራ እመን ጽና እግዚአብሔር ይረዳሃል ፡፡በሃገሪቱ ዳረቻ ወደ አለዉ ገዳም ሂድ እኔ የምሰጥህ በእጄ ያለች ልብስህ ሁል ጊዜ ይህች ናት ጌታችን ከወዳጆቹ ቅዱሳን መነኮሳት ጋራ ተሳታፊ እንድትሆን አዝዞኻል ብሎ የብርሃን መስቀል ምልክት ያላት አስኬማንም ሰጥቶት ከእርሱ ዘንድ ተሰወረ፡፡ ✝️ ጻድቁ አባታችን አቡነ አቢብ(ቡላ) ጌታችንና መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ መፍቅሬ ሰብእ (ሰውን ወዳጅ) አምላካቸውን አርአያ ያደረጉ ለሰው ያላቸውን ፍቅር አድንቆ ከማዕድ በኀላ ስብሐት ተብሎ የተረፈውን በእንተ አቡነ አቢብ ብሎ ሦስት ጊዜ የተመገበውን ሰው ሁሉ እስከ አሥር ትውልድ እምርልሃለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ✝️ የንዑድ ክቡር ጻድቁ አባታችን አቡነ አቢብ (ቡላ) ጸሎታቸዉና በረከታቸው ከእኛ ጋር ይኹን ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ ✞ (በዮሐንስ ዘሐረር - ዝክረ ቅዱሳን) ምንጭ፡ ገድለ አቡነ አቢብ

✨           ''ስለ ማይነገር ስጦታዉ''            ✨ ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን ቸል ያላለን አምላክ ስንጓዝ ማይበሉን አቋርጠን ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመሰገን 🤍🙏 የህይወት እስትንፋስ ዘራብን ሕያው እንድንሆን ይህን ያደረገ አምላካችን እግዚአብሔር ይመስገን ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን🙏 ነፋስን ገስጾ ማዕበል አቁሞ የሚያሻግር ❤️‍🩹 የአለም ፈተና ቢበዛ እሱ መጠጊያችን ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን ዳግም እንዳንሞት በሞቱ ሞትን የረታልን የምንመካበት ትንሳኤ ሰላምን ለሰጠን ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመሰገን ከሲኦል እስራት ተፈተን ነፃ የወጣንበት መስቀሉን ለሰጠን ለአምላካችን እንዘምር በእውነት ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን💞                   ዘማሪ ቸርነት ሰናይ 🤩            

ኪዳነምሕረት እናቴ ኪዳነምህረት እናቴ ሚስጥረኛየ ጓዳዬ የጎደለኝን ታውቂያለሽ ካፌ ሳይወጣ ሳልነግርሽ/2/
አዝ
አልፏል መናኛው ኑሮ ምልጃሽ ውሀውን ቀይሮ መልካሙ ወይን ደረሰ እንባዬ ባንቺ ታበሰ /2/
አዝ
ልዘምር ልቁም ከፊትሽ ልምጣ ልንበርከክ ለክብርሽ ብርቅ ከሀገር ከቤቴ ከቶ አረሳሽም እናቴ/2/
አዝ
አልልም መቼ ነው ቀኑ የኔ መጎብኛ ዘመኑ እንደሚፈፀም አምናለሁ ሁሉን በጊዜው አያለሁ /2/
አዝ
የልቤን ችግር  ላዋይሽ ከስእልሽ ፊት ቆሜ እንባዬ ቀድሞኝ ዝም አልኩኝ ሳልነግርሽ ስለምታውቂ /2/ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮ

✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿 ሰባኬ ወንጌል መጋቤ ሃይማኖት ለቤተ ክርስቲያን ዘይደምፅ ቀርን ነባቤ ለቤተ ክርስቲያን፡፡ ያሬድ ፀሐያ ለኢትዮዽያ ዓምደ ብርሃን ለቤተ ክርስቲያን መልአክ ዘበምድር፡፡ ✨
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿
ሰባኬ ወንጌል መጋቤ ሃይማኖት ለቤተ ክርስቲያን ዘይደምፅ ቀርን ነባቤ ለቤተ ክርስቲያን፡፡ ያሬድ ፀሐያ ለኢትዮዽያ ዓምደ ብርሃን ለቤተ ክርስቲያን መልአክ ዘበምድር፡፡
✨🌿ትርጉም ቅዱስ ያሬድ ሰባኬ ወንጌል መጋቤ ሃይማኖት ለቤተ ክርስቲያንም የሚመሰክር መለከት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ፀሐይ የብርሃንም ምሰሶ በምድር ላይ ያለ መልአክ ነው፡፡ ✨🌿✨🌿 እንኳን ለኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ ! ✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨

ስድቤን አርቀሽ ስድቤን አርቀሽ ነውሬን ሸፈንሽው እመ አምላክ በአንቺ መቼም አላፍር ስምሽን ጠርቼ እጽናናለሁኝ ሀዘኔን በአንቺ እረሳለሁኝ ነውር አለብኝ ብዙ ስድብ አንጀት የሚልጥ ልብ የሚያቆስል ስሜን ለውጠው ቢያንቋሽሹኝ በሀዘን በለቅሶ ድንግል መጣሁኝ እንደ ሃና ሆኜ ከቤተ መቅደስ በመረረ ሐዘን ነው የማለቅስ ፍረጅልኝና ልመለስ ከቤቴ ሐዘኔን በደስታ ለውጪው እናቴ በግራም በቀኝም ጠላት ቢከበኝ አብዝቼ እጮሃለው እናቴ ስሚኝ አዝ መከራው በዝቶ ግራ ገብቶኛል  ድምፅሽን ልስማ ያረጋጋኛል  የሰው ህይወቱ ብርቱ ሰልፍ ነው       ደስታና ሐዘን የማይለየው በእጃችን ወድቋል ሲሉ ጠላቶቼ አመለጥኳቸው ስምሽን ጠርቼ ሰው የዘራውን ያንኑ ያጭዳል በቆፈረው ጉድጓድ ራሱ ይገባል እናቴ እመቤቴ ብዬ ስጠራሽ ከመከራ ሁሉ ታወጪኛለሽ አዝ በምርኮ ሳለሁ በሰው ሀገር      ግፍ ውለውብኝ ስኖር በእስር       ምልጃሽ ደርሶልኝ ተፈትቻለሁ       በታምራትሽ እኔ ድኛለሁ ቃልሽን ሰምቶ ጽንሱ ሰገደ ብላለች ኤልሳቤጥ ነውሬ ተወገደ የጌታዬ እናት እኔን አሰበችኝ ታሪኬን ቀይራ ይኽው ባረከችኝ የእመቤቴ ከሆንኩ ማን ይቃወመኛል ወጀቡም ማእበሉም ይታዘዝልኛል አዝ ወይን እኮ አልቋል የዶኪማስ ቤት       ድንግል አማልጅው ነይ የእኛ እመቤት       ስምሽ ሲጠራ በየቦታው       ይሞላልና የጎደለው            ግራ የገባው የቸገረው             ድንግልን ይጥራት እንድትረዳው             ሳዝን ስተክዝ የምታጽናና             እናት አለችኝ እርህርህይተ ልቦና እናቴ እመቤቴ ብዬ ስጠራሽ ከመከራ ሁሉ ታወጪኛለሽ ዘማሪ ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ

በቸርነት በይቅርታው አሰበን በፍቅሩና በምሕረቱ ጎበኘን አምላካችን በሞቱ ወደደን አምላካችን በሞቱ ወደደን /2/ አዝ ተነጥቆ ሰላም እረፍታችን ላያድን ላይፈውስ ጽድቃችን ተጥለን ስንኖር በሞት በደምህ ወጣን አርነት በደምህ ወጣን ነጻነት አዝ የጭንቀት የመከራ አመት ተረሳ በኢየሱስ ሞት በፍፁም ፍቅሩ ወደደን በሞቱም ከሞት አዳነን በሞቱም ከሞት አዳነን አዝ ሕዝቡን ሲያስጨንቅ የነበረ የጠላት ቅጥሩ ተሰበረ ማልቀስ ቀረልን መቅበዝበዝ ገነት ገብተናል በእርሱ ወዝ ገነትን ወረስን በእርሱ ወዝ አዝ ሰማይና ምድር ተስማሙ ታጥበዋልና በደሙ ነፃነት አዋጅ ተሰማ አዜምን የጽድቁን ዜማ ዘመርን የጽድቁን ዜማ

♡ ሥላሴን አመስግኑ ♡ ሥላሴን አመስግኑ /2/ የምድር ፍጥረታት ዘምሩ እልል በሉ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል ከምንም በፊት ዓለማትን ሁሉ ለፈጠረ ጌታ ምስጋና ይድረሰው ከጠዋት እስከማታ አዝ........ ኪሩቤል ሱራፌል የሚያመሰግኑት መላእክት በሰማይ ሥሉስ ቅዱስ ያሉት እኛም የአዳም ልጆች እንዘምራለን በሰማይ በምድር እንጠራሃለን አዝ.......... ብራብ በሥላሴ እጠግባለሁኝ ብጠማም በአምላኬ እረካለሁኝ ሥላሴ አምባዬ ክብሬ ናቸውና ሁሌም ይመሩኛል በሕይወት ጎዳና                        ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ