የአካባቢ ወጣቶች መዝሙራት
Ir al canal en Telegram
የተመረጡ የማህበራት እና የካሴት መዝሙራትን የሚያገኙበት፣ ወቅታዊና አሁናዊ መረጃዎችን የሚጋሩበት እንዲሁም የተለያዩ መፅሀፍትንና ትረካዎችንና የመሳሰሉትን የሚያገኙበት ድንቅ ቻናል ተቀላቀሉን ብዙ ያተርፉበታል። ለአስተየትዎ @Natnael1201
Mostrar más2 012
Suscriptores
+224 horas
-37 días
-330 días
Archivo de publicaciones
2 012
❝ወደ ተቀደሰችው የቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ስፍራ ይገቡ ዘንድ አሕዛብን ዝም አላላቸውም፡፡ በሕንፃዋ ላይ ቢሆን በሠራዊቱ ላይም ቢሆን ጻድቅና የዋህ በሆነ በንጉሥ አኖሬዎስ ሕዝብ ላይም ምንም ምን ክፉ ነገር ሳያደርጉ መለሳቸው እንጂ❞እንዳለ ድርሳነ ሩፋኤል ዘታኅሣሥ፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል የተጨነቁትን ከጭንቀት የሚያድን መልአክ ነው፡፡ በነሐሴ የሚነበበው የድርሳነ ሩፋኤል ተአምር ላይ ቴዎፍሎስ ለሚባል ሊቀ ጳጳስ ከጭንቀቱ እንደደረስለት ያስረዳናል፦ ይህ ቴዎፍሎስ የሚባል ደግ ጳጳስ እውነትን ስላስተማረ በሮም ሀገር የንጉሡ የወታደር አለቃ ጕድጓድ ቆፈረና በዕንጨት ሳጥን አድርጎ ከጕድጓዱ ውስጥ ጣለው፡፡ ጳጳሱም ምንም ሳይሆን ከሦስት ቀን በኋላ በአራተኛ ቀኑ ቅዱስ ሩፋኤል በአደረገለት ተአምር ከተጣለበት ጕድጓድ በሰላም ወጥቷል፡፡
❝አስተርእየኒ ሩፋኤል መልአከ ጥዒና ወፈውስ በራብዕት ዕለት ለአሕይዎ እምአመ ኀተሞ ንጉሥ በንፍቀ ዚአሁ አስተርአይኮ ለብእሲ ቀሲስ — ንጉሥ በራሱ ሳጥን ቆልፎ ከጣለው በኋላ በአራተኛ ቀኑ ልታድነው ለቀሲሱ የተገለጥክለት ፈጣን የማዳንና የሕይወት መልአክ ሩፋኤል ሆይ ለኔም ተገለጥልኝ❞እንዳለ ደራሲ። የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ የበዓሉ መታሰቢያ የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ የመታሰቢያው ዕለት ጳጕሜን ሦስት ቀንና ታኅሣሥ ዐሥራ ሦስት ቀን ነው ፤ ታኅሣሥ ዐሥራ ሦስት ቀን አንደኛ በዓለ ሢመቱ ነው:: ሁለተኛ በቴዎዶስዮስ ልጅ በንጉሥ አኖሬዎስ ትእዛዝ ንጉሡ አኖሬዎስ ራሱም ከሠራተኞች ጋር አብሮ እየሠራ በቊስጥንጥንያ ሀገር ቤተ ክርስቲያኗን ከፈጸመ በኋላ ቅዳሴ ቤቱ ታኅሣሥ ፲፫ ቀን ተከብሯል። ስለ ሁለቱም የመታሰቢያው በዓላት የጥር ድርሳነ ሩፋኤል እንዲህ ይላል፡-
❝ታላቅ በዓሉንም በወርኃ ታኅሣሥ ዐሥራ ሦስት ቀን አክብሩ!❞በዚች ዕለት የሰውንና የእንስሳቱን ማኅፀን በመፍታት ይጠብቅ ዘንድ ተሹሟል። በዚህ ታላቅ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ስም የታነፀች ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤቷም በዚሁ ዕለት ነው፡፡
❝ዛቲ ዕለት ቅዳሴ ቤትከ ነያ፣ ዘኒ ዘኮነ በብሔረ ፅርዕ ወሮምያ ሩፋኤል መልአኩ ለአምላከ ሰማይ ኬንያ: ቀድስ ሕዝበከ ዘተጋብኡ በአርአያ ከዊን ኒቅያ: በዐውደ ምሕረትከ እንዘ ይብሉ ሃሌ ሉያ — የፈጣሪ የሰማይ አምላክ አገልጋይ መልአክ ሩፋኤል ሆይ! ይች ዕለት በስምህ የታነፀች ቤተክርስቲያንህ የከበረችበት ነው፤ ይኸም የተደረገ በሮምና በፅር አገርነው፤ ምሕረትህ በሚነገርበት አደባባይ ሃሌ ሉያ እያሉ የተሰበሰቡ ሕዝብህንም ባርክ❞— እንዳለ አርኬ፡፡ ይልቁንም በወርኃ ጳጕሜን ሦስት ቀን በፍጹም ደስታ ታላቅ በዓል አድርጉ፡፡ ይች ዕለት ሊቀ-መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል የቤተ ክርስቲያን መሠረትን በዓሣ ዐንበሪው ላይ ያፀናባት:: ብፁዕ አባ ቴዎፍሎስንም ከእሥር ያዳነባት፤ ዳግመኛም ሰማያት ተከፍተው የቅዱሳንን ጸሎት ሁሉ ወደ አምላኩ እግዚአብሔር በእጁ የሚሳርግበት ዕለት ናትና፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ በቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል በጳጉሜን ሦስት ሰማያት የሚከፈቱበት (ርኅዎተ ሰማይ) በመሆኑ በዚህች በተከበረችው ዕለት ምእመናን ጸሎታቸው ያርግላቸው ዘንድ ከምን ጊዜውም በበለጠ ተግተው ይጸልያሉ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን የእኛንም ጸሎታችንን በምልጃቸው የሚያሳርጉልን ቅዱሳን መላእክትም መሥዋዕቱን የሚያሳርጉበትና የአምላካችንን ምሕረት ቸርነት ለሰው ልጆች የሚያወርዱበት ዕለት ነው፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል አማላጅነት ሁላችንንም ይጠብቀን። እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን ምእመናን። የቅዱስ ሩፋኤል ቀን ጸሎታችሁን ስታደርሱ ስለ ቅዱስ ሩፋኤል ብላችሁ አንድ አቡነ ዘበሰማያት ❝ኃጥእ ባርያህን ኃይለራጉኤልንም አስበው❞ ብላችሁ በጸሎታችሁ አስቡኝ፤ አደራ! ዲ/ን ኃይለራጉኤል
2 012
ዻጉሜንና ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ-መላእክት
ቅዱስ ሩፋኤል ከሰባቱ ሊቃነ-መላእክት አንዱ ነው። ሊቀ-መላእክትነቱም ❝መናብርት❞ በሚባሉ መላእክት ላይ ነው፡፡ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊትም ለማማለድና ትእዛዝ ለመቀበል ከሚቆሙት ሰባቱ መላእክት ሦስተኛው መልአክ ሩፋኤል ነው፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ለሰውና ለእንስሳት ርኅሩኅ መልአክ ነው፡፡ በርኅራኄውም የሰው ልጆች ምሕረትን፣ ብዕልና ክብርን ያገኙ ዘንድ ይልቁንም የመካኖችን ማኅፀናቸውን ይፈታ ዘንድ ወላጆችም ያለ ጽኑ ምጥ ይወልዱ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ቀርቦ እንደሚለምን በቅዱሳን ዘንድ በስፋት የታወቀ መልአክ ነው፡፡
በዕብራይስጥ ቋንቋ ❝ሩፋ❞ ማለት ጤና፣ ፈውስ፣ መድኃኒት፣ መስተፍሥሒ፣ ድንቅ ማለት ነው፡፡ ❝ኤል❞ ማለትም አምላክ ማለት ስለ ሆነ ሁለቱ ቃላት ሲጣመሩ ሩፋኤል የሚል ይሆናል፡፡ ይህም ከአምላክ የተሰጠ ድንቅ ፈውስ ማለት ነው፡፡
❝ስሙሂ ብሂለ ሩፋኤል መስተፍሥሒ ወመድምም ብሂል ወትርጓሜሁ ፈውሰ አምላክ ውእቱ — ሩፋኤል የተባለ ስሙ ደስ የሚያሰኝ ትርጓሜውም ድንቅ የአምላክ ፈውስ❞— እንዳለ (ድርሳነ ሩፋኤል ዘጥር) እርሱም የሰዎች ነፍሳትን በምልጃው ለማዳን የተሾመ የዋህ መልአክ እንደ ሆነ ነቢዩ ሄኖክ:-
❝ሩፋኤል ፩ዱ እመላእክት ቅዱሳን ዘመናፍስተ ሰብእ — ከቅዱሳን መላእክት አንዱ ሩፋኤል በሰዎች ነፍሳት ላይ የተሾመ ነው❞— (ሄኖ፮÷፫) ካለ በኋላ በሌላ አንቀጽ ሁለተኛውም በበሽታው ሁሉ ላይና በሰው ልጆች ቊስል ላይ የተሾመ ❝ቅዱስ ሩፋኤል ነው❞ በማለት ያስረዳናል (ሄኖ፲፥፲፫)። የነፍሳት ጠባቂ ለመሆኑ መጽሐፈ ሜላድ ነፍሳትን ለመጠበቅ በሰዎች ነፍሳት ላይ ከተሾሙ ቅዱሳን መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው ይላል (መጽሐፈ ሜላድ ዘጥቅምት)
❝የነፍስ ጠባቂ ለሆነ ሩፋኤል ሰላምታ ይገባል❞— (ተአምኆ ቅዱሳን ዘሰሉስ) ቅዱስ ሩፋኤል ለሄኖክ መካነ ነፍሳትን እንዴት እንደ ሆነ ተርጕሞ አስረድቶታል። ዳግመኛም ❝ሩፋኤል❞ ማለት ልቡናን ደስ የሚያሰኝ፤ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፤ መፈውስ፣ የዋህ፣ ይቅር ባይ ማለት ነው፡፡
❝ወአንሰ ስምየ ሩፋኤል መስተፍሥሔ አልባብ የዋህ ወኄር ወመሐሪ ላዕለ ኀጥአን — የመላእክት አለቃ ሩፋኤልም ለሐዋርያት ስሜ ሩፋኤል ነው፤ ትርጓሜውም የዋህና ሰውን አስደሳች፤ ቸር ለኃጥአን ይቅር ባይ ማለት ነው፤ ኃጥአንን ስለበደላቸው ወደ እግዚአብሔር አላሳጣቸውምና፥ ነገርግን ስለ የዋህነቴና ስለ ማዳኔ የሰውንም ልጅ እጅግ ስለ መውደዴ ከኃጢአታቸው ተመልስው ንስሓ ይገቡ ዘንድ በዘመን ላይ ዘመንን እጨምርላቸዋለሁ አስፈጻሚ መላእክትንም እልክላቸዋለሁ❞— እንዳለ ድርሳነ ሩፋኤል ዘጳጕሜን። የሰማያትን መክፈቻ ስለያዘ ሕፃናትን ገና በናታቸው ማኅፀን ጀምሮ ይጠብቃቸዋል። ኃጢአተኞችን ለንስሓ እያበቃ በንስሐ የተመለሱ የቅዱሳን ነፍሳትን ወደ ገነት፤ ወደ መንግሥተ ሰማያት እንዲገቡም ያደርጋል፡፡ በወርኃ ጥር የሚነበብ ድርሳኑ እንዲህ ይላል:-
❝አዳም ሚስቱ ሔዋንን ዐወቃት፡፡ ያን ጊዜም የዲያብሎስ ሠራዊት ከሚስቱ ሔዋን ማኅፀን የአዳምን ዘር ያጠፉ ዘንድ በፅንስ በሽታ ተመስለው ተነሡ:: ስለዚህም እግዚአብሔር ሊቀ-መላእክት ቅዱስ ሩፋኤልን መርጦ ከሌሎች ይልቅ የሰውና የእንስሳን ማኅፀን ይፈታ ዘንድ ሥልጣንን ሰጠው:: ለደካሞች የሚያዝን፤ የሚራራ፤ የተበደሉትንም የሚበቀልላቸው ልዑል እግዚአብሔር ይኸን ሥልጣን ባይሰጥ ኑሮ ከዲያብሎስ ሠራዊት የተነሣ አጋንንት ሾተላይ፣ የሐኬት ቊራኝነት የተነሣ ይህ ዓለም ያለ ፍጥረት ምድረ በዳ ሆኖ በቀረ ነበር። ርጉም ዲያብሎስ ከኃጥአን ማኅፀን ከሚገኙ ልጆች በቀር ደጋግ ጻድቃን እንዲፈጠሩ አይሻምና።❞ሊቀ-መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል እስራኤል ለአርባ ዘመን በፍልስጥኤም እጅ ተይዘው ሳሉ ለብዙ ዓመታት ያለ ልጅ መካኖች ሆነው ለኖሩት ለማኑሄና ለሚስቱ በአምሳለ ነቢይ ተገልጦ ወንድ ልጅ እንደሚወልዱ አብሥሯቸዋል። ለማኑሄም መካን የነበረችው ሚስቱ ወንድ ልጅ ስትፀንስ፤ የረከሰ ነገር እንዳትመገብ፤ የሚያሰክርም እንዳትጠጣ፤ ልጁም ሲወለድ ፀጕሩን የሚያሳድግ ናዝራዊ እንዲሆን እንጂ እንዳይላጭ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ከነገራት በኋላ ማኑሄም የእግዚአብሔርን መልአክ፥
❝ነገርህ በደረሰ ጊዜ እንድና ከብርህ ስምህ ማነው?❞ብሎ ጠየቀው፤ ከእግዚአብሔር የታዘዘውም መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል፥
❝ለምንት ዝንቱ ዘትሴአል ስምየ መድምም ውእቱ — ይህ የምትጠይቀው ስሜ ድንቅ ነው፥ ለምን ትጠይቃለህ?❞አለው (መሳ ፲፫÷፩-፳) የማኑሄ ሚስት ማኅፀንም እንደ ቅዱስ ሩፋኤል ቃል ተፈታ:: ሴቲቱም ወንድ ልጅ ወለደች ስሙንም ሶምሶን ብላ ጠራችው፤ እግዚአብሔርም ሕፃኑን ባረከው፤ ልጁም አደገ፤ የእግዚአብሔር መንፈስ በሶምሶን ላይ ነበረ (እንዳለ መሳ. ፲፫÷፳፬ ፤ ድርሳነ ሩፋኤል ዘጥር) ስለ የዋህነቱም ከጦቢት ልጅ ከጦብያ ጋር ❝ስሜ አዛርያ እባላለሁ❞ ብሎ እንደ ታዛዥ ወዳጅ ሆኖ ብዙ ሳምንታትን በወንድምነት በምድር ላይ ተገልጾ አገልግሎታል፡፡ ማንኛውም መልአክ ሕሙማንን ለመፈወስ የሚላክ ቢሆንም የቅዱስ ሩፋኤል ግን የጐላ ነው:: አስማንድዮስ የሚባል ጋኔን በጭኗ አድሮ ሰባት ባል የገደለባት የራጉኤል ልጅ ሣራንም ፈውሶ ጋኔኑን እንዳይመለስ አስሮታል፡፡ ሣራም ለጦብያ ሚስት ሁናለች:: የጦቢት ዓይነ ሥጋው በወፎች ኵስ ስለታወረ በባለመድኃኒቶች ቢደክምም ሳይድን ቀርቶ ነበር፤ የሕሙማን አኪም ቅዱስ ሩፋኤል ግን ባለመድኃኒቶች ሊያድኑት ያልቻሉትን የታወረ ዐይኑን አብርቶለታል። በመጨረሻም ቅዱስ ሩፋኤል ለጦቢት:-
❝እነሆ፥ አንተና ምራትህ ሣራ በጸለያችሁ ጊዜ የልመናችሁን መታሰቢያ እኔ በቅዱሱ ፊት አቀረብሁ❞በማለት በየቦታው በንጹሕ ሁነን የምንጸልየውን ጸሎት እንደ ሚያሳርግልን አስረድቶቷል፡፡ ጦቢት ምንም ዓይኑ ቢጠፋም እንኳ መልአኩ እንዳልተለየው እንዲህ ሲል ይገልጣል፦ አንተም
❝ሬሳ በቀበርህ ጊዜ ያን ጊዜ እኔ ካንተ ጋር ነበርሁ፤ ቸል ባላልህ ጊዜ፥ ምሳህንም ትተህ በተነሣህ ጊዜ፥ ሬሳንም ትቀብር ዘንድ በሄድህ ጊዜ፥ በጎ ሥራህንም ባልዘነጋህ ጊዜ እኔ ከአንተ ጋር ነበርሁ፡፡ አሁንም፦ ጌታ እግዚአብሔር አንተን አድንህ ዘንድ፥ ምራትህ ሣራንም ከኀዘኗ አረጋጋት ዘንድ ላከኝ፡፡ የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ+ በገናናውና በቅዱሱ ጌትነት ፊት ከሚያቀርቡ ሰባቱ ቅዱሳን መላእክት አንዱ መልአክ እኔ ሩፋኤል ነኝ❞— (መጽሐፈ ጦቢት ፲፪÷፲፩)። መልአኩ ❝አዛርያ እባላለሁ❞ ብሎ ለተወሰነ ጊዜ አብሮ ይቆይ እንጂ የሚበላ እንዳልበላና የሚጠጣ እንዳልጠጣ:-
❝እኔም ተገለጥሁላችሁ፤ ነገር ግን እይታን አያችሁ እንጂ ከእናንተ ጋር አልበላሁም፤ አልጠጣሁምም፤ እኔ ወደ ላከኝ ወደ ላይ እወጣለሁና በመጽሐፍ ጻፉት❞ብሏቸው ተሰውሯል። (መጽሐፈ ጦቢት ፲፪፥፲፱) ደጋጎች ቴዎዶስዮስንና ዲዮናስዮስን ከሕፃንነታቸው ጀምሮ ሰይጣን በጨካኞች ነገሥታት እያደረ ልዩ ልዩ መከራ በሚያመጣባቸው ጊዜ ከሥዕሉ እየተማፀኑ ስለ ሚለምኑት እግዚአብሔርን በማያምኑ ነገሥታት የሚፈተኑበት ችግራቸውን እየጊዜው እያስወገደ የዚህ ዓለም ደሀ የነበሩትን በሰው ዘንድ መወደድን፣ ብዕልን፣ ክብርንና ሥልጣንን ስጥቶ ከፍ ከፍ አድርጓቸዋል፡፡ ከደግነታቸው የተነሣም ለታላቅ ሹመት ቴዎዶስዮስን ለንጉሥነት፣ ዲዮናስዮስን ለጳጳስነት አብቅቷቸዋል፡፡ በተሾሙ ጊዜ ጠላት ቢነሣባቸውም በሰማይ ሁኖ ሰይፍን በማሳየት ብቻ የጠላት ሠራዊት ወደ ሀገራቸው ሳይመጣ በመንገድ ተመልሷል፡፡ ሊቀ-መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል (፩/፪) ⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️
2 012
ሥርዐተ ቅዱስ ወንጌል
ካህናት ወንጌልና ኪዳን ሲያነብቡ ጥምጥማቸውን ያወልቃሉ፤ አክሊላቸውንም ያወርዳሉ ይኸውም ለአክብሮተ ወንጌል ነው:: ወንጌል በሚነበብበት ጊዜ መቆም እንጂ መቀመጥ ፈጽሞ ክልክል ነው። ካህኑ አንብቦ ሲጨርስ ራሱ ተሳልሞ ከንፍቅ ካህን ጀምሮ እንደ የማዕረጋቸው ያሳልማቸዋል ካህናቱ ከተሳለሙ በኋላ ምዕመናን ይሳለማሉ ኾኖም በሚሳለሙበት ጊዜ ሴቶች ክንብንባቸውን ከራሳቸው ላይ አውርደው መሳለም ይገባቸዋል፤ ንጉሥም ቢሆን እንኳ ዘውዱን ማውረድ አለበት::
❝ነአምን በቃለ ወንጌል ቅዱስ — ቅዱስ በሆነው በወንጌልህ ቃል እናምናለን❞— እያሉ እጅ እየነሡ ክንብንባቸውን እያወረዱ ይሳለማሉ በቃለ ወንጌል ማመናቸውን ይመሰክራሉ:: ክብረ ወንጌል በቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ቅዱስ ወንጌል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ቅድሚያ የሚሰጠው ከፍ ያለ ክብር ያለው እንደሆነ የታወቀ ነው:: ስለ ክብረ ወንጌል የማይነገርበት ሥርዐት እና አምልኮ ቤተክርስቲያን የላትም:: በቅድስት ቤተክርስቲያን ቅዱስ ወንጌልን የማያሳትፍ ጸሎት፣ ቁርባን፣ መሥዋዕትና አገልግሎት የለም:: ማኅሌትና ሰዓታት ሲቆም፤ ጸሎተ ፍትሕት ሲደረስና ጸሎተ ተክሊል ሲከናወን በእነዚህ ሁሉ መስቀል ተይዞ ወንጌል ይነበባል:: በአጠቃላይ ቅዱስ ወንጌል የማይነበብበት የአገልግሎት ዘርፍም ሆነ የጸሎት ክፍል ቤተክርስቲያን የላትም። ይህም ለቅዱስ ወንጌሉ ያላትን ክብር ከፍ አድርጎ ያሳያል:: ቅዱስ ወንጌል ለሥርዐት፣ ለአምልኮት፣ ለሕግጋትና ለአገልግሎት መሠረት በመኾኑ ከሌሎቹ ሥርዓቶች የበለጠ ክብር ይሰጠዋል። ለምሳሌ:- በቅዳሴ ጊዜ ወንጌል ሲነበብ የደከመ/የታመመ እንኳን ቢሆን በዚያች በንባብ ቅጽበት ውስጥ ድካሙንም ሕመሙንም እንደምንም ችሎም ቢሆን ቆሞ እንዲያደምጥ ይታወጃል:: አዋጁን የሚያውጀው ገባሬ ሠናዩ ዲያቆን:-
❝ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን ቅዱስ ወንጌል ቆማችሁ አድምጡ!❞— የሚለው አዋጅ ከታወጀ በኋላ የተቀመጠ ካለ ቀጥ ብሎ ሕሊናውን ሰብስቦ ይቆማል:: (እዚህ ጋር ዲያቆኑ ወንጌሉን «አድምጡ» እንጂ «ስሙ» አይልም። በሁለቱ ቃላት መካከል ያለውን ልዩነት ልብ በሉ!) ዲያቆኑ ቁሙ ወአጽምዑ ማለቱ የንፍሐተ ቀርን፤ ካህኑ ወንጌል ማንበቡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፍርድ ቀን «ንዑ ኀቤየ፥ ሑሩ እምኔየ» ብሎ ፍርድ የማስተላለፉ ምሳሌ ነው:: በዚህ ጊዜ የሚደወለው ደወል የግርማ መዓቱ፤ ወንጌል ከተነበበ በኋላ መጋረጃ መዘጋቱ ሑሩ እምኔየ ብሎ ኀጥአንን የማሰናበቱ ምሳሌ ነው። (የቅዳሴ አንድምታ) ወንጌል ከተነበበም በኋላ ንፍቅ ካህን ወንጌል መስማት ክብሩ ምን ያህል እንደሆነ ሲናገር እንዲህ ይላል:-
❝ክቡር የሚሆን የወንጌልህን ቃል እንሰማ ዘንድ እንሳለመውም ዘንድ ደስ ይለን ዘንድ ለዚህ የበቃን ያደረግኸን ሁሉን የያዝህ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ላንተ ምስጋና ይገባሃል! ዳግመኛም ክቡር የሚሆን የወንጌልህን ቃል በልቡናችን ትጽፍ ዘንድ እንለምናለን እንማልድሃለን❞— ብሎ ይማጸናል:: የቅዱስ ወንጌል ክብሩ የሚጀምረው መጽሐፉን ከማክበር ሲሆን ይኸውም አቅም ያለው ደብር የመጽሐፉን ገበታ (የውጭውን ሽፋን) በወርቅ እና በብር ያስጌጡታል አቅም የሌለው ደብር ደግሞ በወርቃማ ሱቲ (በከበረ ልብስ) ያለብሱታል:: ይህ ሁሉ ታዲያ ክብሩን ለመግለጥ ነው:: ምእመናን ቅዱስ ወንጌልን እንዴት ባለ ሁኔታ መስማት እንደሚገባቸው ሥርዓተ ቅዳሴው ሲናገር:-
❝የሰማያዊውን ንጉሥ የከበረ የወንጌሉን ቃል ለመስማት ከመጀመሪያቸው እስከ መጨረሻቸው ድረስ ከማመስገን ከመቀደስ በቀር ማድነቅና ጸጥታ ሊሆን ይገባል:: የምድራዊ ንጉሥ ደብዳቤ ሲነበብ አንድ ሰው እንኳን ለመናገር የማይደፍር ከሆነ፤ ቢናገርም ቅጣትና ግርፋት የሚያገኘው ከሆነ የሰማያዊው ንጉሥ ደብዳቤ የምትሆን ወንጌል ሲነበብ የሚናገር ምን ያህል ቅጣት ያገኘው ይሆን?❞— በማለት ወንጌል ሲነበብ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ እንደሚገባው ሥርዐተ በቅዳሴያችን ያስጠነቅቃል:: ጸሎተ ወንጌል ከተፈጸመ በኋላ ንፍቅ ዲያቆን መብራት ይዞ በፊት፥ ንፍቅ ካህን ማዕጠንት ይዞ በኋላ ሆኖ ሁለቱም በቅድስት በቀኝ በኩል ዞረው በሰሜን የመቅደሱ በር ይገባሉ:: ሠራዒ ዲያቆን በቅድስቱ ላይ ሆኖ ፊቱን ወደ ምዕራብ መልሶ ቃጭል እየመታ:- «ጻዑ ንዑሰ ክርስቲያን» ይላል። ይህንንም የሚያውጅበት ምክንያት «ንዑሰ ክርስቲያን» የሚባሉት የክርስትና ሃይማኖትን በማጥናትና ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በመከታተል ላይ ያሉት ገና ያልተጠመቁ አዲስ ክርስቲያኖች ሲሆኑ እንዲወጡ መታዘዛቸው ለመቊረብ ስለማይችሉ ነው። የጥንቱ ትምህርተ ወንጌል ሰዓት ወንጌል ከተነበበ በኋላ ኤጲስ ቆጶስ ካለ ወንጌሉን በእጁ ይዞ በክፍሎቹ የተነበበውን ለሕዝቡ ተርጉሞ ማስተማር ይገባዋል። ኤጲስ ቆጶስ ከሌለ ትርጓሜን የሚችል የተማረ ካህን እንዲያስተምር ታዝዟል (ፍትሐ ነገሥት ፲፪)። ትምህርቱ ግን ሳይበዛ ከዐሥራ ዐምስት ደቂቃ ባልበለጠ ወንጌሉንና ምስባኩን እንዲሁም የተነበቡትን መልእክታት በማቆራኘት ምስጢረ ቁርባንን ማዕከል በማድረግ አጭር ትምህርተ ወንጌል መስጠት ይገባል:: በዘመናችን ግን ወንጌል ከተነበበ በኋላ «ፃዑ ንዑሰ ክርስቲያን» ከመባሉ በፊት ትምህርተ ወንጌል መስጠት ከቆመ ዓመታት ተቆጥረዋል:: ለዚህ ብዙ ምክንያቶች መጠቀስ የሚችሉ እንደሆነ ቢገባኝም ሆኖም ግን የጥንቱን (የቀደመውን) የአባቶቻችንን ሥርዓት መሸራረፍም ሆነ ማዛነፍ ተገቢ አይደለም። እዚህ ጋር ቤተክርስቲያን የተመሠረተችው ለሁለት ዐቢይ ተልእኮ መሆኑ መታወቅ አለበት፤ ይኸውም ለቅዳሴና ለወንጌል ነው:: እነዚህ ሁለቱ የማይነጣጠሉ ሰምና ወርቅ፤ ድር እና ማግ፤ ጥርስ እና ከንፈር ሆነው የሚኖሩ የድኅነታችን ወሳኝ ጸጋዎች ናቸው:: ይልቁንም ወንጌል ደግሞ የጸጋዎች ሁሉ መግቢያ በር ነው። ሰው ሳይማር አይጠመቅም፤ ሳይጠመቅ አይቆርብም፤ ስለዚህ ጥምቀትም ቁርባንም የሚገኙት ከወንጌል ትምህርት የተነሣ ነው:: «ፃዑ» ከመባሉ በፊት ትምህርት የሚሰጥበት ምክንያት ለሁለት ዓላማ ነው። አንዱ ከሌላ ቤተ እምነት ወይም ከአምልኮተ ጣዖት የመጡ ለምሥጢረ ጥምቀት ደጅ የሚጠኑ ንዑሳነ ክርስቲያንን አስተምሮ ለመሸኘት ሲሆን፥ ለቍርባን የተዘጋጁ ምእመናን ደግሞ ፈሪሃ እግዚአብሔር ባልተለየው ልቡና፣ ትሕትና በተዋሐደው ስብእና ቀሪውን ሥርዐት እንዲከታተሉና በፍርሃትና በረዓድ ሆነው ወደ ቅዱስ ቁርባን እንዲቀርቡ ለማነቃቃት እንዲሁም ለማስጠንቀቅ ነው:: ይልቁንም እዚህ ላይ ትምህርት መስጠቱ ልዩ ጥቅም አለው። ይኸውም አንደኛ ምእመኑ በቁመት ብዛት ሰውነቱ ሳይዳከም ልቡናው ሳይደክም በትኩስ ተመስጦ በሞቀ መንፈሳዊ ኀይል ትምህርቱን በሚገባ ነቅቶ ተግቶ ይሰማል:: ሁለተኛው «ወንጌል መስማት» የከበረ የቅዳሴው አካል የድኅነት ማዕከል እንደሆነ በሚገባ እንዲገነዘብ ስለሚረዳ። እናስተውል! ዲ/ን ኃይለራጉኤል
2 012
❝ቅድመ ሥዕልኪ እሰግድ ወአስተበርክ ክሡተ ቅድመ ማኅበራንኪ እሉ እንዘ እቀውም ድርገተ ፈጻሚተ መፍቅድ ማርያም እስእለኪ ስእለተ ጸግውኒ እግዝእትየ ለዓለመ ዓለም ሕይወተ እምእደ እኩያን አጽራርየ አድኅንኒ ሊተ❞... .. . [በእነዚህ የአንቺ ማኅበር በሚሆኑ ጉባኤያተኞችሽ መካከል በአንድነት እየቆምኩ በሥዕልሽ ፊት እሰግዳለሁ፤ በግልጽም እንበረከካለሁ፡፡ የልቤን መሻት የምትፈጽሚልኝ ማርያም ሆይ እለምንሻለሁ፤ እመቤቴ ሆይ፥ ለዘለዓለሙ ሕይወትን ስጪኝ፥ ከክፉ ጠላቶቼ እጅም አድኚኝ።]
2 012
♡ የልቤ ዜማ ♡
የልቤ ዜማ ነሽና
ሰላም ነው ያንቺ ምስጋና
ሞገሴ ነው ስምሽ ለኔ
ስላለሽ ማርያም ከጎኔ
በመገፍት ብኖር እምነቴን አፀናለሁ
በጣቶችሽ ተይዤ አዲሱ ቀን አያለሁ [፪]
ስማፀን ደጅሽ መጥቼ
ተመለሰኩ ተረጋግቼ
እንደምን አንቺን እረሳለሁ
በምልጃሽ ተፈውሻለሁ
የጠላቶቼን አራስ የሚቀጠቅጠው
የአብራክሽን ፍሬ ተስፍዬን አበራው [፪]
የድኅነት ምክንያት አርጎሻል
ለአዳም ዘር ትምክህት ሆነሻል
የልቤ ብርሃን ፍና
አዛኝት ባንቺ ልፅናና
የአፌን እንጉርጉሮ ምስጋናዬ ወርሶታል
እግሬ ከእረግረግ ወጥቶ በሰገነት ተተክሏል [፪]
ሐዜኔን የምሻገረው
ስምሽን እየጠራሁ ነው
አገኘው ደስታ ሰላም
ጠርቼ ብዬ ማርያም
በአብረቅራቂው ፍቅር በዓለሙ ውስጥ ስኖር
ለሙውጣት ዳክራለሁ ማርያም ማርያም እላለሁ [፪]
ሰምተሻል ልመናዬን
ወጣሁኝ ያኑን ጥልቁን
እሳቱን ባንቺ አልፌአለሁ
በምልጃሽ ደግፌ አለ
ዘማሪ ዲያቆን እንዳለ ደረጀ
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
2 012
የበዓሉ መጠሪያ ስሞች
1. ደብረ ታቦር የተባለው ጌታ ክብሩን የገለጠበት ስፍራ ደብረ ታቦር ስለሆነ በዚሁ በዓሉ ስያሜውን አግኝቷል።
2. ቡሔ ይባላል ፦ ቡሄ ብርሃን ማለት ነው በደብረታቦር ቧ ብሎ የተገለጠውንየጌታችንን የፊቱን ብርሃን ጸዳል፤ የልብሱንም እንደ ነጭ በረዶ ጸዓዳ መሆን ያስረዳል፡፡
3. ቡሔ ማለት መላጣ (ገላጣ) ማለት ነው፡፡ይኸውም በበዓሉ ዋዜማ ልጆች ‹‹ ቡሔ በሉ፤ ቡሔ መጣ ፣ ያ መላጣ፣ ቅቤ ቀቡት እንዳይነጣ›› ይላሉ እዚህ ላይ ቡሄ ያለው ዳቦውን ነው፡፡
4. "ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት›" እንደሚባል ወቅቱበሃገራችን የጸዓተ ክረምት ዋዜማ ስለሆነ የክረምቱ አፈናው ተወግዶ /ተጋምሶ/ የብርሃን ወገግታ የሚታይበት ፤ በዶፉና በጎርፉ ተሸፍና የነበረች መሬት የምትገለጥበት በመሆኑ ነው፡፡
5. ቡሔ (ቡሔእየ) ተብሎ ይተረጎማል ይኸውም የደብረታቦር እለት እርሾ ሳይገባበት ተቦክቶ የሚጋገረውን ኅብስት ያሳያል፡፡
6. ችቦ የመብራቱ ፣ የሙልሙል ዳቦ የመጋገሩና የጅራፍ ማጮኽ ምክንያት
መብራት የሚበራው 12 ለ13 ዋዜማ ሌሊት በ3 ሰዓት ነው
የጌታችን ክብሩ በተገለጠበት ጊዜ ብርሃኑ የሌሊቱን ጨለማ ገፍቶት እስከ አርሞንዔም ደርሶ ነበርና በዚያ አካባቢ የነበሩ እረኞች በሁኔታው ተገርመው ቀንም መስሎኣቸው ሌሊቱም ተዘንግቷቸው በዚያው ቆይተው ነበርና ቤተሰቦቻቸው ምን አግኝቷቸው ይሆን በማለት መብራት አብርተው (ችቦ ይዘው)፣ የሚመገቡትን ይዘው/ሙልሙል/ልጆቻቸውን ፍለጋ ወጥተዋል እረኞችም ያሉበትን ቦታ ለቤተሰቦቻቸው ጅራፍን በማጮኸ አመልክተዋቸዋልና ይህን ለማሰብ ነው፡፡
ዋናው ምሥጢሩ ግን፡- የችቦው ብርሃን የጌታ ክብር መገለጡን፣ የጅራፋ ጩኸት ሐዋርያትን ያስደነገጣቸው የአብ የምስክርነቱ ቃል ምሳሌ ሲሆን፣ ኅብስቱ ጌታችን በመስቀል ላይ መሥዋዕት የመሆኑ (የሥጋወደሙ) ምሳሌ ነው፡፡
• ከላይ እናዳየነው ጅራፋ መጮኹ የአብ የምስክርነቱ ቃል ምሳሌ ነው ይኸውም በታቦር ተራራ ላይ እንደሆነም ተገልጧል ስለዚህ ዛሬም ምሳሌነቱን ለማጉላት ጅራፍ የማጮኹን ሥርዓት በተራራ ማድረግ የተሻለ ነው፡፡ ከዚህ በተረፈ ግን ሥርዓቱን ባልጠበቀ መልኩ ማክበሩ ሃይማኖታዊ ትውፊት የለውም ይልቁንም ሰውን ለማስደንገጥ ተብሎ በአስደንጋጭ ነገሮች ሰውን ማስደንገጥ የበዓሉን ሥርዓት ማሳደፍም ከመሆኑም በላይ ከሃይማኖተኛ ሰው የማይጠበቅ የሰውን መብትና ክብር መንካት ነው
ጌታችን በብርሃን ንስሓ እንመላለስ ዘንድ ዓይነ ልቡናችንን ብሩህ ያድርግልን፡፡
✔️መ/ር ነቢዩ ኤልያስ
2 012
ዘክረምት☘️
እግዚአብሔር፦ የበልግ ዝናምን ይሰጣችሁ ዘንድ እግዚአብሔርን ለምኑት። በረከትን ለእናንተ ያዘንባል። ክረምትን በየዓመቱ የምታስገባ አቤቱ ዕውቀትን ስጠን። ሰማይን በደመና የሚጋርድ ለሥጋ ሁሉ ምግብን የሚሰጥ ነው። በምድር ሁሉ ዝናምን ያወርዱ ዘንድ ደመናትን የሚያዝዛቸው ነው። ለቸሮች ቸር ለይቅር ባዮች ይቅር ባይ የሆነ [እግዚአብሔር] በምድር ላይ ዝናምን ያወርዳል። [አቤቱ አንተ] ለነገሥታት ሰላምን ትሰጣለህ ለአብያተ ክርስቲያናትም ጸጥታን ትሰጣለህ። በኖኅ ጸሎት ይቅር በለን። አንተ ሕይወትን የፈጠርክ በረከትን የምትሰጥ ነህ። አንተ የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ ነህ። ከፍጥረት ሁሉ ሰውን ከፍ ከፍ ያደረግህ ከዕለታት ሁሉ ሰንበትን ያከበርክ አንተ ነህ። ወደ ምድረ በዳ ብሄድም ኀይሌ እግዚአብሔር ነው። ብወድቅና ብፍገመገም በመስቀልህ እነሣለሁ። (#በግእዝ፦ ሰአልዎ ለእግዚአብሔር የሀብክሙ ዝናመ ጸደይ። ያዝንም ለክሙ በረከተ። ዘአንተ ታርኁ ክረምተ በበዓመት ሀበነ እግዚኦ አእምሮ። ዘይገለብቦ ለሰማይ በደመና ዘይሁብ ሲሳየ ለኵሉ ዘሥጋ። ዘይኤዝዞሙ ለደመናት ያውርዱ ዝናመ ውስተ ኵሉ ምድር። ኄር ለኄራን መሓሪ ለመሓርያን ያወርድ ዝናመ በዲበ ምድር። ትሁብ ሰላመ ለነገሥት ወኅድዐተ ለአብያተ ክርስቲያናት። በጸሎቱ ለኖኅ ተሣሀለነ። አንተ ውእቱ ገባሬ ሕይወት ወሃቤ በረከት። አንተ ኬንያሁ ለኵሉ ፍጥረት። እምኵሉ ፍጥረት ሰብአ ዘአዕበይከ ወእምኵሉ ዕለት ሰንበተ ዘአክበርከ። እመኒ ሖርኩ ውስተ በድው ኀይልየ እግዚአብሔር እመኒ ወደቁ ወተንተንኩ እትነሣእ በመስቀልከ)።
ክረምት፦ የዝናም ኮቴው ተሰማ። ዝናም በሚዘንብ ጊዜ የተራቡት ይጠግባሉ። ዝናም በሚዘንብ ጊዜ ችግረኞች ደስ ይላቸዋል። (#በግእዝ፦ ደምፀ እገሪሁ ለዝናም። ሶበ ይዘንም ዝናም ይጸግቡ ርኁባን። ሶበ ይዘንም ዝናም ይትፌሥሑ ነዳያን)።
ምጽአት፦ ወልድ ከሰማይ ኀይላት ጋር በሚያስደነግጥ ግርማ በመጣ ጊዜ። የዕለታት ሁሉ በኵር የሆነች እሑድ ትሰለጥናለች። ያን ጊዜ ጨረቃ የለም፣ ፀሐይም የለም፣ ክረምት የለም በጋም የለም። (#በግእዝ፦ አመ ይመጽእ ወልድ በግርማ መደንግፅ ምስለ ኀይለ ሰማያት ትሰፍን እሑድ ርእሰ ኵሎን ዕለታት። አሜሃ አልቦ ወርኅ ኢ ፀሐይ ኢ ክረምት ወኢ ሐጋይ)።
🍏ዘዘወትር🍏
እግዚአብሔር፦ ክረምትን ለምድር ያዘጋጃል። በተራሮች ላይም ሣርን ያበቅላል። ደመናትም ቃሉን ይሰማሉ። [አቤቱ] አንተ ነዳያንንና ባዕለ ጸጎችን ትመግባቸዋለህ። ለሙት ልጆች አባት ነህ። ስለችግረኞች ሕዝብ ብለህ የምድርን ፍሬን ባርክ ለዘርና ለመከር አድርስ። የክርስቶስ ጥበቡ ድንቅ፣ ነገሩ መልካም፣ ቃሉ ያማረ ነው። ውሃን በደመና ሲያቁር ደመናው አይቀደድም። እግዚአብሔር ምክሬ እንደ ምክራችሁ ሐሳቤ እንደ ሐሳባችሁ አይደለም አለ። በምድር ላይ ዝናምን የማዘንብ በተራሮች ላይ ሣርን የማበቅል እኔ ነኝ። ለእንስሳት ምግባቸውን እሰጣቸዋለሁ። ይህንን ሁሉ እጄ ፈጥሮታልና። ከአብ በስተቀር የወልድን ሐሳብ የሚያውቅ የለም። ከወልድ በቀርም የአብን ሐሳብ የሚያውቅ የለም። አቤቱ አንተ የማትጎድል መዝገብ ነህ። አንተ ክብራችንና ጌጣችን ነህ። አንተ የመድኀኒታችን አክሊል ነህ። (#በግእዝ፦ ያስተዴሉ ክረምተ ለምድር ወያበቍል ሣዕረ ውስተ አድባር። እስመ ደመናትኒ ይሰምዑ ቃሎ። አንተ ትሴስዮሙ ለነዳይ ወለባዕላይ ለዕጓለ ማውታ አብ። ባርክ ፍሬሃ ለምድር አብጽሕ ለዘርዕ ወለማዕረር በእንተ ነዳያን ሕዝብከ። ጥዑም ቃሉ ወሠናይ ነገሩ መንክር ጥበቢሁ ለክርስቶስ። ዘየዐቍሮ ለማይ በደመና ወኢይሰጠጥ ደመናሁ። ይቤ እግዚአብሔር ኢኮነ ምክርየ ከመ ምክርክሙ ወኢኮነ ኅሊናየ ከመ ኅሊናክሙ። አነ ውእቱ ዘአወርድ ዝናመ ዲበ ምድር ወአበቍል ሣዕረ ውስተ አድባር እሁቦሙ ሲሳዮሙ ለእንስሳ እስመ እደውየ ገብሮ ለዝንቱ ኵሉ። አልቦ ዘየአምር ኅሊናሁ ለወልድ ዘእንበለ አብ ወአልቦ ዘየአምር ኅሊናሁ ለአብ ዘእንበለ ወልድ። አንተ ውእቱ ዘኢይቀብል መዝገብ። አንተ ውእቱ ክብርነ ወትርሲትነ። አንተ ውእቱ አክሊለ መድኀኒትነ)።
ምስጋና፦ በየዘመኑ እንዴት እንደሠራ አይቼ እግዚአብሔርን እያመሰገንሁ ከገዳም ወጣሁ። (#በግእዝ፦ ወፃእኩ ውስተ ገዳም እንዘ እሴብሖ ለእግዚአብሔር ርእይየ ኵሎ ዘከመ ገብረ በበመዋዕሊሁ)።
ተፈጥሮ፦ ደመናት በእውነት በአቅማቸው ውሃዎችን ያካፋሉ። (#በግእዝ፦ ይነፈንፋ ጽድቀ ደመናት ማያተ በአቅሞሙ)።
🍒ዘተረስዐ ዘልደት ሰንበት🍒
ነገረ ማርያም፦ እግዚአብሔር ማርያምን ዘመንሽ ዘመኔ ነው መጠንሽ መጠኔ ነው አላት። (#በግእዝ፦ ወይቤላ እግዚአብሔር ለማርያም አዝማንየ አዝማንኪ አምጣንየ አምጣንኪ)።
© በትረ ማርያም አበባው ካሣ
2 012
▽▽▽መሐረነ አብ = አብ ሆይ ማረን▽▽▽
➧፩➧መሐረነ አብ ➝ሃሌ ሉያ ➝ተሣሃለነ ወልድ
➝ሃሌ ሉያ ➝መንፈስ ቅዱስ መሓሪ ተዘከረነ በሣህልከ (፫ ጊዜ በል)
➧፪➧ለከ ንፌኑ ስብሐተ ወለከ ናዐርግ አኰቴተ።
➧፫➧መሐረነ መሓሪ ኀጢአተነ አስተሥሪ።
➧፬➧ወአድኅነነ ➝ወተማኅጸን ነፍሰነ ወሥጋነ ➝ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር።
➧፭➧አምላክነ ➝ወመድኀኒነ ➝ኢየሱስ ክርስቶስ ተሣሃለነ።
➧፮➧በብዝኀ ምሕረትከ ➝ደምስስ አበሳነ ➝ወፈኑ ሣህለከ ላዕሌነ።
➧፯➧እስመ እም ኀቤከ ➝ውእቱ ሣህል ➝ሃሌ ሉያ መሐረነ አብ መሓሪ።
➧፰➧ወተሣሃለነ ➝ሀብ ሣህለከ መሓሪ ➝ኢታጥፋነ ተዘኪረከ ዘትካት።
➧፱➧በምሕረትከ ➝እስመ መሓሪ አንተ
➝ወብዙኅ ሣህልከ ለኵሎሙ እለ ይጼውዑከ።
➧፲➧ይጼውዑከ በጽድቅ ➝ሰማዒ ወትረ ➝ከሃሊ ዘውስተ አድኅኖ።
➧፲፩➧ከሃሊ ➝ዘውስተ አድኅኖ ➝ለአምላክነ ጻድቅ እስመ ጽድቅ ቃሉ።
➧፲፪➧ንስአሎ ለአብ ➝ይፈኑ ለነ ሣህሎ ➝እስመ አብ የአክል ለዘሰአሎ።
➧፲፫➧ሃሌ ሉያ ➝ስብሐት ሎቱ ይደሉ ➝ሃሌ ሉያ አኰቴት ሎቱ ይደሉ።
➧፲፬➧ሃሌ ሉያ ➝ለክርስቶስ ለእግዚአ ኵሉ ➝ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ።
➧፲፭➧ወይዕዜኒ ➝መኑ ተስፋየ ➝አኮኑ ➝እግዚአብሔር ➝ውስተ እዴከ እግዚኦ አመኀፅን ነፍስየ።
➧፲፮➧ኀበ አምላከ ምሕረት ➝አመኀፅን ነፍስየ ➝ኀበ ንጉሠ ስብሐት ➝አመኀፅን ነፍስየ ➝በእግዚእየ ወአምላኪየ ➝አመኀፅን ነፍሰየ ➝እም ኵሉ ምግባረ እኩይ አድኅና ለነፍስየ።
➧፲፯➧ሀቡ ➝ንስአሎ ➝ናስተምሕሮ ➝ለአምላክነ ጻድቅ እስመ ጽድቅ ቃሉ።
➧፲፰➧ዘይክል ኵሎ ወአልቦ ዘይሰአኖ ➝አምላከ ነዳያን ረዳኤ ምንዱባን ➝ንሕነ ኀቤከ ተማኅፀነ።
➧፲፱➧ዘይክል ኵሎ ወአልቦ ዘይሰአኖ ➝አምላከ ነዳያን ናዛዜ ኅዙናን ➝ንሕነ ኀቤከ ተማኅፀነ።
➧፳➧ዘይክል ኵሎ ወአልቦ ዘይሰአኖ ➝አምላከ ነዳያን ወተስፋ ቅቡጻን ➝ንሕነ ኀቤከ ተማኅፀነ።
➧፳፩➧ወበከመ ዐቀብከነ እም ነግህ እስከ ሠርክ ዕቀበነ እግዚኦ እም ሠርክ እስከ ነግህ። (፫ ጊዜ በል)
➧፳፪➧አይቴ ውእቱ አምላኮሙ ከመ ኢይበሉነ አሕዛብ ምህላነ ስማዕ ቃለ አብ።
➧፳፫➧አይቴ ይእቲ ትምክሕቶሙ ከመ ኢይበሉነ አሕዛብ ምህላነ ስምዒ ማርያም።
➧፳፬➧ኤሎሄ ኤሎሄ ዘአመ ትቤ በጽራሕከ ተማኅፀነ ምህላነ ስማዕ አምላክነ።
➧፳፭➧ተሣሃልከ እግዚኦ ምድረከ ሃሌ ሉያ ፤ ስማዕ ጸሎተነ ወስእለተነ ፤ ወስረይ ኵሎ ኀጢአተነ ፤ ስማዕ ፤ ጸሎተነ ወስእለተነ ፤ ዘሰማዕኮ ጸሎቶ ወስእለቶ ለዕዝራ ፤ ተወከፍ ምህላነ ሰላመከ ሀበነ፤ እማዕከሌነ ኢትርኀቅ።
➧፳፮➧ወሚጥ መዐተከ እምኔነ ፤ ሃሌ ሉያ ንዒ ኀቤየ እንቲኣየ ፤ ሠናይት ርግብየ መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል ወኵሉ ነገራ በሰላም።
➧፳፯➧አርእየነ እግዚኦ ሣህለከ ሃሌ ሉያ ፤ ሰአል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲኣነ ሐረድዎ ወገመድዎ ፤ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኀበ ሰብአ ነገሥት ፤ ረገጸ ምድረ ፤ አንሥአ ሙታነ አባ ጊዮርጊስ ፤ በሰላም ዐደወ ፤ መንግሥተ ክብር ወረሰ
➧፳፰➧መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ሰአል ወጸሊ በእንቲኣነ አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩ ለንጉሥ ዐቢይ።
➧፳፱➧ገብርኤል አብሠራ ለማርያም ወይቤላ ትወልዲ ወልደ ወይነግሥ ለቤተ ያዕቆብ ለዓለም ወአልቦ ማኅለቅት ለሰላሙ።
➧፴➧ ባርከኒ አባ እንሣእ በረከተከ በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ገብረ-መንፈስ-ቅዱስ አባ ባርከኒ እንሣእ በረከተከ።
(ብፁዕ አባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘዔለ ገዳማተ እም ኀበ እግዚኡ ይንሣእ ዕሴተ ቦአ ሀገረ ደብረ ሊባኖስ በፍሥሓ ወበሰላም።)
➧፴፩➧ማኅደረ ሰላምነ ቅድስት ደብተራ እሞሙ ለሰማእት ወእኅቶሙ ለመላእክት ንዑ ንስግድ ኵልነ ኀበ ማርያም እምነ።
(መስቀል ብርሃን ለኵሉ ዓለም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን መድኀኔ ዓለም ወሀቤ ሰላም ሰላመከ ሀበነ።)
➧፴፪➧ለዓለም ወለዓለመ ዓለም ሃሌ ሉያ ሰላመ አብ ወሰላመ ወልድ ወሰላመ መንፈስቅዱስ የሀሉ ማዕከሌክሙ።
►►►►እግዚኦታ ይቀጥላል . . .►►►
➥➥መ/ር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ (ከድሬዳዋ)
2 012
◦•●◉ በታማኝነቱ የተመሰገነ ◉●•◦
በታማኝነቱ የተመሰገነ
ለእመቤታችን ጠባቂ የሆነ
ዮሴፍ አረጋዊ ይባርከን ፀሎትህ
ምሳሌ ሆኖናል ብርሃን ህይወትህ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ማዕረግ ቅድስና ታላቅ ስለሆነ
ከእስራኤል አባቶች እጣው ለአንተ ሆነ
ጌታን ለማሳደግ በቅተሀል በፀጋ
በአተረፍከው መክሊት በተሰጠህ ዋጋ/2/
◦•●◉።።።።።።።አዝ።።።።።።።◉●•◦
በረሃብ በስደት ልብህ አልተፈታ
ለፈጠረ ሕፃን ታምነሃል ለጌታ
ተጋድሎህን አልገታ ድካም ሽምግልና
በረታ ጉልበትህ በአምላክ እንደገና/2/
◦•●◉።።።።።።።አዝ።።።።።።።◉●•◦
የዳዊት ልጅ ዮሴፍ እጅግ አስተማርከን
ጠባቂ እና አባት ሆነህ በሌት በቀን
የድንግልን ሀዘን ሰቆቃ ስደት
ተካፍለህ ወስደሃል ታላቅ በረከት/2/
◦•●◉።።።።።።።አዝ።።።።።።።◉●•◦
የሰማዩን ኪዳን የአብን አደራ
በትንሿ ቤትህ ጠበክም ሳትፈራ
በዓለም ስደተኛ የሆነው ሕፃን
አደገ በቤትህ ታላቁ መድህን/2/
2 012
🍀🍀🍀🍀🍀🍀
መዝሙር ዘሰንበት
🍁🍁🍁🍁🍁🍁
ከሐምሌ ፳፬ እስከ ሐምሌ ፴
(በ፫/ሙ) ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ
በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ፤ምህሮሙ ወይቤሎሙ አክብሩ ሰንበትየ፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ፤ በሰንበት አጋንንተ አውጽአ ወበቃሉ እለ ለምፅ አንጽሐ ፤በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ በሰንበት ወረቀ ምድረ ወገብረ ፅቡረ ወበምራቁ አሕየወ ዕውረ፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ዘይኤዝዞሙ ለደመናት ያውርዱ ዝናመ ውስተ ኵሉ ምድር፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ያውርዱ ዝናመ ውስተ ኵሉ ምድር ውስተ ፍና ኀበ ይትፈቀድ መካን፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ውስተ ፍና ኀበ ይትፈቀድ መካን ከመ ኅቡረ ይትፈሣሕ ዘይዘርዕ ወየዓርር ፤በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ማ፦ምድር ርእየቶ ወአእኰተቶ ፤ባሕርኒ ሰገደት ሎቱ።
አመላለስ፦
ምድርኒ ርእየቶ ወአእኮተቶ/2/
ባሕርኒ ሰገደት ሎቱ/4/
ትርጉም፦
በሰንበት ወደአይሁድ ምኲራብ ገባ ሰንበቴን አክብሩ ብሎ አስተማራቸው በሰንበት አጋንንትን አወጣ በቃሉ ለምፃሞችን አነጻ በሰንበት ምራቁን ወደምድር እንትፍ አለ ጭቃም አደረገ በምራቁ ዕውሩን አዳነ በምድር ሁሉ ላይ ዝናምን ያወርዱ ዘንድ ደመናዎችን የሚያዛቸው እሱ ነው በሚያስፈልግበት ስፍራ ሁሉ። የሚዘራም የሚያጭድም አንድ ላይ ይደሰቱ ዘንድ። ምድር አየችው አመሰገነችው ባሕርም ሰገደችለት።
https://t.me/maheberat
2 012
👆የቀጠለ
እኒኽም ቅዱሳን ይኽንን በሚነጋገሩበት ጊዜ በውስጡ አንገትን የሚቆለምም ልብንም የሚያቀልጥ ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርን የሚበጣጥስ መሳሪያ ካለበት የብረት ጋን ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና የብረቱን ጋን እሳት አጠፋው፡፡ ከቅዱሳኑም አንዳቸውንም ሳያቃጥላቸው የብረቱ ጋር ማቃጠሉና መፍላቱ ጸጥ አለ፡፡
ወንድሞቻችን ሆይ እንግዲህ በጭንቃቸው ጊዜ ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ይህ መልአክ ከሰማእታትና ከጻድቃን ጐን እንደማይለይ እወቁ ለኃጥአንም ኃጢአታቸውን ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይላቸዋል፡፡ እኛም የዚህ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓሉን እያከበርን አማላጅና ወዳጅ እናድርገው። በዚህም በሚመጣውም ዓለም ሊረዳን ይችላልና፡፡
ዳግመኛም መስፍኑ ሐሳቡ ሳይሳካለት ስለቀረ 14 የሾሉና የጋሉ የብረት ችንካሮች አምጥተው ሰባቱን በእናቱ በኢየሉጣ አካል ሰባቱን በራሱ በቂርቆስ አካል ማለት ሁለቱን በጆሮዎቹ ሁለቱን በዐይኖቹ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ አንዱን በልቡ ይቸነክራቸው ዘንድ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የህፃኑን የእራስ ቆዳ ገፈው እሳት ውስጥ ይጨምሩ ዘንድ አዘዘ፡፡
አሁንም መልአኩ መጥቶ ይህንን መከራ ከእርሱ አራቀለት፡፡ ቀጥሎም በመቃን ውስጥ ጨምረው በገመድ እንዲጎትቱት አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ መልአኩ አዳነው፡፡ ሕዝቡም ይህንን ሁሉ ተአምር ባዩ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቅዱስ ገብርኤልንም አከበሩት፡፡ ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት እየሉጣ ብዙ መከራ ከተቀበሉ በኋላ ጥር 15 በሰይፍ ተመትተው ስማትነትን ተቀብለዋል።
የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት እየሉጣ ተራዳኢነት ጸሎት አይለየን። ከዚህ በኋላ ሕፃኑን አስፈልገው ቢጠይቁት ነቢዩ ዳዊት የተናገረው ኃይለ ቃል መንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት፤ ‹‹የአሕዛብ ጣዖታት የወርቅና የብር የሰው እጅ ሥራዎች ናቸው፡፡ የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ›› መዝ. ፻፴ በማለት ሲዘልፏቸው አገር ገዥው ሰምቶ ተቆጣና የብረት ጋን አስመጥቶ ውኃ ሞልቶ ከዕቶን እሳት ላይ ጥዶ ልዩ ልዩ ማገዶዎች በመጨመር ነበልባሉ ከመጠን በላይ ሆነ፡፡ የብረት ጋኑም ድምፅ እንደ ክረምት መብረቅና ነጎድጓድ እስኪያስፈራ ድረስ አስነድዶ ሕፃኑን ከነእናቱ ወስዳችሁ ጨምሩአቸው ብሎ አዘዘ፡፡
በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ በጣም ፈራች፡፡ የእግዚአብሔር ሥራ እፁብ ድንቅ ግሩም ረቂቅ ነው፡፡ ገና አፉን ያልፈታ የሦስት ዓመት ሕፃን ‹‹እናቴ ሆይ! ገድላችን እንፈጽም ዘንድ ጨክኝ በርቺ›› አላት፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም ‹‹ልጄ የነፍስ አባት ሁነኝ›› አለችው፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ከዘመናቸው ሳይደርስ፣ ታሪካቸውን ሳይማር የሠለስቱ ደቂቅን ታሪክ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ‹‹አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል›› ቢላት ፍርሃቱ ሊለቃት ባለመቻሉ፣ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ጸለየ፡፡
‹‹ጌታ ሆይ! የወይኑን ፍሬ ስትሻ ግንዱን ታጠፋለህን? እንደዚህስ ሁሉ እኔን አድነህ እናቴን ታጠፋታለህን?›› ብሎ በጸለየጊዜ መንፈስ ቅዱስ አደረባትና መንግሥተ ሰማያትን በዓይነ ሥጋ እንድታይ አደረጋት፡፡ ከዚህ በኋላ ፍርሃቱ ለቀቃትና ‹‹ልጄ ሆይ! ከዛሬ ጀምሮ መምህሬ፣ አባቴ፣ መካሪዬ እልሃለሁ እንጂ ልጄ አልልህም›› ብላ በጭካኔ ከልጅዋ ጋር ወደ ፈላው የብረት ጋን ገባችበት፡፡
በዚህ ጊዜ ሕፃኑ ቂርቆስ አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል ያለውን ቃል ለመፈጻም እግዚአብሔር አምላክ መልአኩ
ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው፡፡ መልአኩም በትእምርተ መስቀል እሳቱን ቢባርከው እንደ በረዶ ቀዝቅዞላቸዋል፡፡ በመልካቸውም እንደ ፀሐይ አበራ፡፡ ከእግር ጥፍራቸው እስከ ራስ ጠሩራቸው አንድም ሳይጎዳቸው በደህና ወጡ፡፡
በመጨረሻም ሕፃኑ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ እንዲህ አለ፡፡ ይህን ያህል ገድል ተጋድዬ ምን ዋጋ ትሰጠኛለህ ቢለው፣ ጌታ በልብህ ያለውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው፡፡ ዳግመኛም ሥጋህ በምድር ላይ እንዳይፈርስ እንዳይበሰብስ በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርሃለሁ አለው፡፡
ስለሆነም በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያናችን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለእናታችን ለቅድስት ኢየሉጣ እና ለሕፃኑ ለቅዱስ ቂርቆስ ያደረገውን ይህን ታላቅ ተአምር ድንቅ ሥራ በማሰብ ከዋዜማው ጀምራ እግዚአብሔርን ስታመሰግን ትውላለች ታድራለች፡፡
የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል በረከት ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይኑር አሜን፡፡
2 012
ሐምሌ 19
ቅዱስ ገብርኤል
እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!
በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት የሚታሰብበት ዕለት ነው። የሐምሌ 19 ስንክሳርና የሐምሌ ወር ድርሳነ ገብርኤል እንዲህ ተርከውታል፡፡
በዘመነ ሰማእታት ከሐድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቲያኖች ላይ መከራ አጽንተውባቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች ሰማእትነትን ሲቀበሉ የተቀሩት አገር ጥለው ተሰደዱ። እየሉጣም የሦስት ዓመት ህፃን የነበረውን ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኮንን አገኘችው ሰዎችም ነገር አሰሩባት ወደእርሱ አስቀረባት እና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኮንን ሆይ ዕድሜው ሦስት አመት የሆነው ህፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እሱን ጠይቅ አለችው፡፡
ህፃኑም ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደእርሱ አስመጣው ህፃኑም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ህፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው፡፡ ህፃኑም መልሶ አዎ ለኔ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ሐዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፡፡ መጻሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏል እና አለው፡፡ እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስካስደነገጣቸው ድረስ ንጉሱን መኳንንቱንና ጣኦታቱን ረገማቸው፡፡ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ፡፡
መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በያይነቱ በሆነ ስቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው እናቱንም ከእርሱ ጋር አሰቃያት፡፡ እግዚአብሔርም ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር፡፡ ብዙዎች አህዛብም ይኸንን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማእትነት አረፉ፡፡ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ፡፡ በህፃኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት፡፡ ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው፡፡
መስፍኑም በውስጡ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል ጨምራችሁ ታላቅ የብረት ጋን አንጡልኝ ብሎ ጭፍሮቹን አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም እንዳዘዛቸው ካአደረጉ በኋላ ያዘዝከንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፡፡ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮኸል ወላፈኑም እንደጸሐይ ነጸብራቅ በሩቁ ይጋረፋል፡፡ የፍላቱም ኃይል በ14 ክንድ ያኽል ከፍታ ወደ ላይ ይዘላል፡፡ እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት በዚህ ጊዜ ህፃን ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አስረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእስር ቤት አወጧቸው፡፡
በዚያም ፍላቱ ወደላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው፡፡ በዚህን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተዘጋጅቶላት ከነበረው ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ ድንጋጼም አይደርብሽ አናንያንና አዛርያን ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከእቶነ እሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ፡፡
እናት ሆ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለመዳን ስትይ በማያልፈው ዘላለማዊ እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሽን ይኽስ አይሆንም ይቅርብሽ፡፡ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናት ሆይ ሶስናን ከእደ ረበናት /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ እርሱ እኛንም ከጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን ልጆቹንና ሚስቱን በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባሳጣው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ እግዚአብሐር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ እግዚአብሔርም እንደወደደ አደረገ ከማለት በስተቀር ምንም የተናገረው ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም የሱን ዓላማ በመከተል ይኽንን መከራ ልንታገስ ይገባናል፡፡
ነገር ግን እናቱ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዐይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ አምላክ ሆይ ይችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይኽን እንዳታደር ግን ቸርነትህ ትከለክልኸለች አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት ቅጠሉን ግን ጠብቁት ብለኽ ልታዝ መለኮታዊ ባሕሪህ አይደለም፡፡ ነገር ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም በአንድ ጠብቁት ብለኽ ታዝዛለኽ እንጂ፡፡ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይኽንን ያየ ሁሉ ማዳን የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከእሳት ባልሸሹም ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡
አቤቱ ዲያብሎስም ከባለስልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ ቅዱሳኖቹንም ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማው በማለት እንዳይደነፋ ለእናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ስጣት ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከእየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታኽ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ እነሆ በብረት ጋን ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቸዋለሁና አለችው፡፡
2 012
በዘባነ ኪሩብ
በዘባነ ኪሩብ ለሚቀመጠው
በእሳት ድንጋዮች ቅጥሩን ላጠራው
ዘምሩ ለእግዚአብሔር ለጌታ ዘምሩ
የተከበረ ነው በሰማይ በምድሩ /2×/
/አዝ/
ኢሳይያስ ሲያየው በእጅግ አፈረ
የተፈራ ነው የተከበረ
የሰማይ ደጆች ተንቀጠቀጡ
ለቅዱስ ስሙ ክብርን ሲሰጡ
/አዝ/
ያልተቀደሰ ለምጽ ያነደደው
እንዴት ይችላል ሊያመሰግነው
በል ፍቀድልኝ ፍቅር ነህና
ልግባ መቅደስህ ላቅርብ ምስጋና
/አዝ/
ዙፋንህ ታየኝ ትምክህቴ ሆይ
ስትመሰገን በሰማይ ላይ
ሲያመሰግንህ ያልተደሰተ
ባይተዋር አልሁን አልወጣ ከአንተ
/አዝ/
ቅኔ የሞላበት ያንን ሰገነት
ልቀላቀለው ተመኘሁ በእውነት
ልዘምርልህ ባይገባኝም
ዝም የሚል ልሳን አልሰጠኸኝም
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
2 012
አጎንብሼ ሄጄ
አጎንብሼ ሄጄ ቀና ብዬ መጣው
በዮሐንስ ጠበል ጤናዬን አገኘው
ጌታን ያጠመቁ ክቡራን እጆቹ
ተዓምር ይሰራሉ ዛሬም ለልጆቹ
አዝአልጋዬን አዝዬ በደስታ ዘለልኩኝ በመጥምቁ ጠበል በእጁ ተዳሰስኩኝ የመራኝን በትር ከእጄ ላይ ጥያለሁ በሰባኪው ጸሎት በምልጃው ድኛለሁ
አዝለዓለም ያልተቻላት በእምነቱ ለቆኛል አበቃልህ ያሉኝ እጅግ ተደንቀዋል በለምጽ የነደድኩት ታደስኩ እንደገና አዲስ አካል ይዤ ቆምኩኝ ለምስጋና
አዝያለፍኩባት ሰፈር በእምባ ተሞልቼ እልልታዬን ሰማች ድኜ ተደስቼ የንዕማን ቁስል ተራግፏል ከላዬ መሞቴን የማይወድ አሰበኝ ጌታዬ
አዝአባናና ፋርፋን አስንቁአል ጠበል ዮርዳኖስ በእምነት ለወረዱ ሁሉ ዮሐንስ በመንፈስ ሲያጠምቅ አይቻለሁ በእጁ ተፈውሼ ምስክር ሆኛለሁ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
2 012
በማህፀን ቅኔ
በማህፀን ቅኔ ለማርያም ተሰማ
በተራራማ አገር በኤፍሬም ከተማ
ዮሐንስ ይናገር በረሃ ያደገው
ድንግል ስትናገር ምን እንዳዘለለው
የእናቱ ማህፀን የቅኔ እርስት ሆነች
ድንግል የአምላክ እናት ፊቱ ስለቆመች
በሀሴት ዘለለ ዘመረ በደስታ
ከድንግል ሲወጣ ታላቁ ሰላምታ
አዝ።።።።።።
በድንግል ማህፀን ስላየ ጌታውን
ከመወለድ ቀድሞ ሰማነው መዝሙሩን
ትንቢቱ ሲፈፀም በሆዷ ሲነግስ
ሰገደ ለአምላኩ የስድስት ወር ፅንስ
አዝ።።።።።።
ጀመረ ስብከቱን ገና ሳይወለድ
ተፈጥሮ መች ቻለ ነብዩን ለማገድ
አፉ ተከፈተ በታላቅ ምስጋና
በእናቱ ማህፀን ድምፅን አሰማና
አዝ።።።።።።
የዮሐንስ እናት ኤልሳቤጥ ገረማት
ልጇ በማህፀን ቅኔን ሲቀኝባት
ድምጿን ከፍ አረገች አለም እንዲሰማ
ሞላት መንፈስ ቅዱስ በመዝሙር በዜማ
አዝ።።።።።።
የዮሐንስ እናት ኤልሳቤጥ ገረማት
ልጇ በማህፀን ቅኔን ሲቀኝባት
ድምጿን ከፍ አረገች አለም እንዲሰማ
ሞላት መንፈስ ቅዱስ በመዝሙር በዜማ
2 012
Repost from ያሬዳውያን
እግዚአብሔርን አመስግኑ
ስራው ግሩምድንቅ ነው በሉ
እግዚአብሔርን አመስግኑት
እግዚአብሔርን አመስግኑት
ሥራ ግሩም ድንቅ ነው በሉት
እግዚአብሔርን እመስግኑት
ስራህ ግሩም ድንቅ ነው በሉት
❴አዝ❵
ሠማይን ያለ ምሰሶ
ምድርንም ያለ መሰረት
ያጸናው እርሱ ነው
ሥራህ ድንቅ ነው በሉት
❴አዝ❵
የባህርንም ጥልቀት የመጠነ
ዳርቻዋን የወሰነ
እግዚአብሔርን አመስግኑ
ሥራ ግሩም ድንቅ ነው በሉት
❴አዝ❵
ማእበል ንፋሱን የሚገስጽ
ፍጥረቱ ለስሙ የሚታዘዝ
ትጉህ እረኛ ድካም የሌለበት
እግዚአብሔርን ሥራህ ድንቅ ነው በሉት
❴አዝ❵
ንጹሐ ባህርይ ነው ሁሉን የሚገዛ
የነገስታት ንጉስ አልፋና ኦሜጋ
ዘለዓለም እርሱ ነው የማይለወጥ
እግዚአብሔር ስራህ ድንቅ ነው በሉት
❴አዝ❵
ጥበብን የሚሰጥ ጥበበኛ
ፍርድ የማያጎድል እውነተኛ ዳኛ
እንደ እርሱ ያለ ከቶ አይገኝም
እግዚአብሔር ግሩም ነው ለዘልዓለም
2 012
ኪዳነምሕረት እናቴ
ኪዳነምህረት እናቴ
ሚስጥረኛየ ጓዳዬ
የጎደለኝን ታውቂያለሽ
ካፌ ሳይወጣ ሳልነግርሽ/2/
አዝአልፏል መናኛው ኑሮ ምልጃሽ ውሀውን ቀይሮ መልካሙ ወይን ደረሰ እንባዬ ባንቺ ታበሰ /2/
አዝልዘምር ልቁም ከፊትሽ ልምጣ ልንበርከክ ለክብርሽ ብርቅ ከሀገር ከቤቴ ከቶ አረሳሽም እናቴ/2/
አዝአልልም መቼ ነው ቀኑ የኔ መጎብኛ ዘመኑ እንደሚፈፀም አምናለሁ ሁሉን በጊዜው አያለሁ /2/
አዝየልቤን ችግር ላዋይሽ ከስእልሽ ፊት ቆሜ እንባዬ ቀድሞኝ ዝም አልኩኝ ሳልነግርሽ ስለምታውቂ /2/ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ
2 012
ሰኔ ፲፪ የቅዱስ_ሚካኤል ዓመታዊ በዓል!
እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለእናታችን ቅድስት አፎሚያ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል እናታችን ቅድስት አፎሚያን ከጠላት ዲያብሎስ እጅ ያዳነበት ፣ እናታችን ቅድስት አፎሚያ እረፍቷ ነው ።እግዚአብሔር ከቅዱሱ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ፣ ከእናታችን ቅድስት አፎሚያ በረከት ተካፋይ ያድርገን ። 👉 በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡ ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ ባያት ጊዜ ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ፣ ሌላ ባል አግብታ፣ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ፤ እነሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ፤ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ በሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡ ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና “የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?” በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው “በኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም” ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን “ድረስልኝ” እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሠኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ ይህች የታመነች ቅድስት አፎምያ በሰላም እስክታርፍ ጊዜ ድረስ የተጓዘችበትን መንፈሳዊ ጎዳና አስተውለን ይሆን? አስቀድማ ከባሏ ጋር አንድ ሆና በታማኝነት ፈጣሪዋን አገለገለችው፡፡ በኋላም የባሏን ኑዛዜ አክብራ ምንም እንኳን ኃጢአት ባይሆንባትም በሁለተኛ ትዳር ራስዋን ማጠላለፍ አልፈለገችም፡፡ በጎ ሥራ አብልጣ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ተፋጠነች እንጂ፡፡ ሰይጣን ልጅ አለመውለዷን ተጠቅሞ ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ “መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ መናፍስት ከእግዚአብሔር እንደሆኑ መርምሩ” ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘውን መመሪያ ተጠቅማ ሰይጣንን በተወክሎ እግዚአብሔር ተቃውማ አሸነፈችው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን ርዳታ ያገኘችውና በሰላም ዐርፋ ወዳገለገለችው እግዚአብሔር በክብር የሔደችው በጽናት ተጋድላ ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጸሎቷ ይማረን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኃይል ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
