KOLFE SECONDARY SCHOOL(Comprehensive)
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
5 835
Obunachilar
+624 soatlar
+377 kunlar
+6030 kunlar
Postlar arxiv
ቀን 06/10/2018
የወተመህ ምክር ቤት አባላት ጋር በሰላማዊ የመማር ማስተማር እንቅስቃሴ ፣ በተማሪዎች ውጤትና ስነምግባር እንዲሁም በፈተና ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ውይይት ከክ/ከተማ ከተገኙ የፀጥታ አካል ጋር በጋራ በመሆን አካሂደናል።
👉የስነምግባር ችግር ያለባቸው ተማሪዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ ምክር ቤቱ ወስኗል።
**ት/ቤቱ
Repost from N/a
Physics 2016 Pilot Exam - Booklet 011 with solution.pdf4.93 KB
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከዚህ በታች የተለቀቀውን የመለማመጃ ቪዲዮ በማየት አድሚሽን ላይ ያለውን ዩዘር በመጠቀም ጥያቄ በመስራት እንድትለማሙዱ እናሳስባለን።
ማሳሰቢያ
- ወደ ሲስተሙ ለመግባት ይሄንን ሊንክ ተጠቀሙ
https://mock3.ethernet.gov.et
- አድሚሽን ካርድ ያለወሰዳችሁ ዛሬውኑ እንድትወስዱ እናሳስባለን
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም.
አስቸኳይ
X-Eን ይመለከታል
የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ሆነው የሚከተሉትን ተግባራት እስካሁን ያላከናወኑ ተማሪዎች ስም ዝርዝር ከየትምህርት ቤቶቹ በክፍለ ከተማ ጽ/ቤት አስተባባሪዎች ተሰብስቦ ይለአክ
1ኛ. ከብቃት ባላደራ አስተማሪዎቻቸው ጋር ቢያንስ አምስት (7) ጊዜ ያልተገናኙ ተፈታኞች
2ኛ. ከ12ኛ ክፍል ፈተና በባለቤትነት የተሰጣቸውን ጥያቄ ቁጥሮች የማያውቁ ፤ ያልተነተኑ ፣ በመጽሐፍት ቤት ያላስቀመጡ እና ለክፍል
ጓደኞቻቸው እስካሁን ያላቀረቡ ተፈታኞች
3ኛ. እስካሁን ከተፈተኗቸው ፈተናዎች መካከል በየትምህርት ዓይነቱ ቢያንስ ከሦስት ጥያቄዎች በላይ ስሕተታቸውን ተንትነው በአስተማሪዎቻቸው
ያላሳረሙ ተማሪዎች
4ኛ. ለክፍላቸው የደረሰውን ሙሉ ፈተና በስድስቱም የትምህርት አይነቶች እስከ አሁን ቢያንስ ከአምስት ጊዜ በላይ ያልተለማመዱ
5ኛ. በብቃት ቡድናቸው ውስጥ በሚገኙ የ9ኛ፣ የ10ኛ እና የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች ከሚማሩት ትምህርት በ12ኛ ክፍል ፈተና ላይ የመጡ ጥያቄዎችን አብረው የመሥራት እድል ያላገኙ ተፈታኞች
6ኛ. ከመማሪያ መጽሐፍቶቻቸው የተሰጥቸውን የዓመት የቤት ሥራ እስካሁን ተንትነው መጽሐፍት ቤት ያላስቀመጡና በክፍል ያላቀረቡ ተፈታኞች
7ኛ. ከመማሪያ መጽሐፍቶታቸው ውጪ የሚያነቧቸውን አሥራ ሁለት (12) የመጽሐፍ አርዕስቶች ያልመረጡና ዝርዝራቸውን ያላቀረቡ ተፈታኞች
መረጃ እንዲላክ
ቀን 28/09/2018 ዓ.ም 📅
ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ 👨🎓👩🎓
Top-25 የሚሊንየም ክላስተር የማጠናከሪያ ትምህርት የምትማሩ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች አድሚሽን ካርድ (Admission Card) እዛው ነገ ቅዳሜ 📝🗓️
ሰኔ 29/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እንገልጻለን 📢
ት/ቤቱ 🏫
ቀን 26/09/2018
ለሁሉም የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች በሙሉ።
ከነገ ሐሙስ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ መደበኛ መማር ማስተማር የሚቀጥል መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን።
ቀሪ የትምህርት ቀናት አጭር በመሆኑ ተከታታይ ምዘና በተገቢው መልኩ ይደራጃል ፣ ስም ቁጥጥር ይካሄዳል ፣ የባከኑ ክፍለ ጊዜያት እና የትምህርት ይዘት ሽፋን ይደረጋል።
በመሆኑም ማንኛውም ተማሪ ከትምህርት ገበታው ቀርቶ ለሚወሰደው እርምጃ ኋላፊነቱን ወላጅና ተማሪ እንደሚወስድ ከወዲሁ እናሳውቃለን።
***ት/ቤቱ
ለ3 ቀናት ቀን ትምህርት አይኖርም ተብሏል‼
ከ7ኛው ሐገራዊ ምርጫ ጋር በተገናኘ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በመጭው ነገ ሰኞ ግንቦት 24-ግንቦት26/2018ዓ.ም ድረስ የትምህርት ተቋማት ዝግ ይሆናሉ ብሏል።
ይህ የምርጫ ቦርድ መግለጫ እንደተጠበቀ ሆኖ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘ ት/ቤቶች ለ3 ቀናት(ሰኞ: ማክሰኞና ረቡዕ) ትምህርት አለመኖሩን ለተማሪዎቻቸው አሳውቀዋል።
ዋና ምክንያቱ መምህራን በሚኖሩበት አካባቢ የምርጫ ታዛቢ ሆነው ቢሰየሙ በተማሪዎች ዘንድ እንግልት እንዳይፈጠር በማሰብ የተደረገ ነው ተብሏል።
የቅዳሜ የውጤት ማላቂያ የማጠናከሪያ ትምህርት (ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል) ተማሪዎች ነገ በ22/9/2018 ዓ.ም የሚቀጥል በመሆኑ የትምህርት ሰዓታችሁን ጠብቃችሁ እንድትገኙ እያሳወቅን ወላጆች ልጆቻችሁ ወደ ት/ቤት በመላክና መማራቸውን እንድትከታተሉ በጥብቅ እናሳስባለን ፡፡
ት/ቤቱ
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
