uk
Feedback
KOLFE SECONDARY SCHOOL(Comprehensive)

KOLFE SECONDARY SCHOOL(Comprehensive)

Відкрити в Telegram

Показати більше
6 124
Підписники
+424 години
+767 днів
+33530 день
Архів дописів
ጥብቅ መልዕክት ለ12ኛ ክፍል 2ኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንሰ(Natural Science) ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ ነገ አርብ ሰኔ 26/2018 በመፈተኛ ጣቢያችሁ ሜክሲኮ ኮሜርስ ኮሌጅ ስለሆነ  ጠዋት 12:00  ት/ቤት መድረስ  አለባችሁ ስለዚህ  ጠዋት 12:30 ላይ ተነስተን ጉዞ እንጀምራለን ስለሆነም ቀድማችሁ እንድትገኙ እናሳስባለን ። ማሳሰቢያ 1. ማንኛውንም ኤሌክትሮኒክስ ነገሮች(ስልክ ፣ ፍላሽ ፣ ሰዓት ወ.ዘ.ተ) መያዝ አይቻልም። 2. ከዮኒፎርም በላይ የሚደረብ ልብስ አይፈቀድም። 3. የፀጉር እና የጆሮ ጌጣጌጥ ማድረግ አይፈቀድም። 4. ከጋብቻ ቀለበት በስተቀር ሌላ ቀለበት ማድረግ አይፈቀድም። 7.ስትመጡ መታወቂያ ፣ አድሚሽን ካርድ መያዝ እና ዮኒፎርም መልበስ ግዴታ ነው። 8. አርፍዶ የሚመጣን ተማሪ ስለማንጠብቅ በሰዓቱ ተገኙ።

ቀን 23/10/2018 ዓ.ም ከዛሬ ጀምሮ የ2018 ዓ.ም የብሔራዊ ፈተና ለምትወስዱ የትምህርት ቤታችን ተማሪዎች በሙሉ! 🤗 ፈተናው ጥሩ ውጤት የምታመጡበት: ያሰባችሁት ደረጃ የምትደርሱበት: የደከማችሁበትና የለፋችሁለትን የምታጭዱበት ምርጥ ጊዜ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!  🙏🏽 በርቱልን፣ ውጤታችሁን በጉጉት እንጠብቃለን! ፈጣሪ ከሁላችሁም ጋር ይሁን🙏 ❤️💪🏼❗️

ቀን 23/10/2018 ዓ.ም ከዛሬ ጀምሮ የ2018 ዓ.ም የብሔራዊ ፈተና ለምትወስዱ የትምህርት ቤታችን ተማሪዎች በሙሉ! 🤗 ፈተናው ጥሩ ውጤት የምታመጡበት: ያሰባችሁት ደረጃ የምትደርሱበት: የደከማችሁበትና የለፋችሁለትን የምታጭዱበት ምርጥ ጊዜ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!  🙏🏽 በርቱልን፣ ውጤታችሁን በጉጉት እንጠብቃለን! ፈጣሪ ከሁላችሁም ጋር ይሁን🙏 ❤️💪🏼❗️

22/10/18 ሰዓት ይከበር - የነገው የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች መነሻ ሠዓት ጠዋት 12 ሰዓት መሆኑን እናሳውቃለን። በሰዓቱ የደረሱ ተማሪዎችን ይዘን የምንሄድ ይሆናል። በሰዓቱ ተገኙ።

22/10/2018ዓ.ም ትኩረት ለ1ኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ አገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ነገ 23/10/2018ዓ.ም አገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል፤በመሆኑም ዛሬ ለኦረንቴሽን የመጣችሁ ተማሪዎች  እንዲሁም ያልተገኛችሁ  ትኩረት ማድረግ ያለባችሁ ነጥቦች በስዓት ከመድረስ አንፃር  -------ጠዋት 12፡00  ት/ቤት መድረስ ይኖርባችኋል፤ዘግይቶ መምጣት በራሳችሁ ላይ ጫና የሚፈጥር ይሆናል ሞባይልም ሆነ ማንኛውንም ኤሌክትሮኒክስ ነገሮችን መያዝ በፍጽም የተከለከለ ነው ዩኒፎርም መልበስ ይኖርባችኋል በአጠቃላይ ነገ በተባለው ስዓት  ት/ቤት ደርሳችሁ  ወደ መፈተኛ ጣቢያችሁ ለመሄድ ወላጆች እገዛ እንዲያደርጉላችሁ በጋራ ውይየት ማድረግ ይጠበቅባችኋል፡፡ ሁላችሁም  የላቀ ውጤት እንድታመጡና መልካም ፈተና እንዲሆንላችሁ  ተመኝተናል!! አዲስ ከተማ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት

📢 ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የተዘጋጀ ወሳኝ መልዕክት! 📢 📅 በመጪው ማክሰኞ ለሚጀምረው የ12ኛ ክፍል ፈተና ከፍተኛ ውጤት ለማምጣትና ራሳችሁን ዝግጁ ለማድረግ እነዚህን 5 የወርቅ ህጎች ተግባራዊ አድርጉ፡ 📝 1. መመሪያዎችን በጥንቃቄ ማንበብ ፈተናውን ከመጀመርዎ በፊት መመሪያውን እና ጥያቄዎቹን በደንብ መረዳት አላስፈላጊ ስህተቶችን በግማሽ ይቀንሳል። ⏱ 2. ጊዜን በአግባቡ ማስተዳደር በአንድ አስቸጋሪ ጥያቄ ላይ ሙጥኝ ብላችሁ ጊዜ አታባክኑ፤ መጀመሪያ የምታውቋቸውን ጥያቄዎች ፈጥናችሁ ስሩ። ⏭ 3. አስቸጋሪ ጥያቄዎችን ማለፍ ወዲያውኑ መልሱ ያልመጣላችሁን ጥያቄ ምልክት አድርጋችሁ እለፉት፤ ጊዜ ሲኖራችሁ በኋላ ትመለሱበታላችሁ። 🧘‍♂️ 4. መረጋጋትን ማዳበር በፈተና ወቅት ጭንቀት ከተሰማችሁ ለአፍታ ቆም በሉ፣ ጥልቅ ትንፋሽ ውሰዱና አእምሮአችሁን አረጋጉ። ✅ 5. መልሶችን በድጋሚ መከለስ ፈተናውን ሙሉ በሙሉ *Submit* ከማድረጋችሁ በፊት ሁሉንም የተሰሩ መልሶች በድጋሚ በጥንቃቄ መፈተሽዎን ያረጋግጡ። 🎯 ፈተናውን በስኬት ተወጥታችሁ ለትልቅ ውጤት እንድትበቁ ምኞታችን ነው! መልካም ፈተና!

=>በፈተና ጊዜ የሚፈጠርን ጭንቀት ወይም ቴንሽንን ልንቆጣጠር የምንችልባቸው ዘዴዎች! ======================== ፈተና የመፈተኛ ጊዜ ሲቃረብ ሁላችንም በመጠኑ መጨነቅ እና ከወትሮው ከፍ ባለ መጠን ውጥረት ውስጥ መግባታችን የተለመደ ነገር ነው:: => ከፈተና በፊት ይህን አይነቱን ከፍተኛ ውጥረት መቆጣጠር የምንችለበት መንገድ:- ------------------------------------------------ ፈተና ሲመጣ መጠነኛ ውጥረት እና ጭንቀት ተፈጥሮአዊ እና ሁሉም ተፈታኝ ተማሪ እንደሚያጋጥመው መረዳት። ለፈተና ስንዘጋጅ አዎንታዊ እና በጎ ሀሳቦችን ማሰብ፡፡ ፈተና ማለት ከዚህ ቀደም ከተማርነው ነገር የተረዳነውን እና የቀሰምነውን እውቀት የምንለካበት መመዘኛ እንጂ የኛ የህይወት ምዕራፍ ማብቂያ ወይም አጠቃላይ ችሎታችንን የሚያመላክት አይደለም ።  ማወቅ ያለብን አንድ ነገር ቢኖር መሳሳትን አለመፍራት እና ሁሌም ለማወቅ እና ራስን ለማሻሻል ዝግጅ መሆንን ነው ። እንዲሁም አሁን የምንፈተነው ፈተና እንዳሰብነው እንኳን ውጤቱ ባያስደስት ለቀጣይ ማስተካከል እና ማሻሻል እንደሚቻል ማመን። ከጓደኞቻችን ጋር ያጠናነውን ነገር በጋራ ሆነን መጠያየቅ እና እርስ በርስ ያወቅነውን ነገር መለዋወጥ፡፡ ይህ ዘዴ ይበልጥ የማስታወስ ብቃታችንን እንደሚጨምር እና የተጠያየቅነው ነገር እንዳይረሳን ያረጋል ። ከዚህም በተጨማሪ የተሳሳትነውን ነገር ድጋሚ እንድንከልስ እና እርማት እንድናረግ ያግዘናል። የፈተና ቀን ሲቃረብ እንደ ወትሮው ዘና ማለት እና በቂ እረፍትና በቂ እንቅልፍ  መተኛት ። ይህም ጭንቀትን ይቀንስልናል፣ እንዲሁም ተረጋግተን ያጠናነውን ነገር አስበን እንድንሰራ ይረዳናል። 

SOCIAL ROUND FOUR (R4).xlsx0.36 KB

+1
NATURAL ROUND 1.xlsx0.36 KB

የሰዓት ማስተካከያ - የነገው የኦረንቴሽን ፕሮግራም መንገድ ሊዘጋጋ ስለሚችል ጠዋት 12:30 ከት/ቤት የምንነሳበት ሰዓት መሆኑን እናሳውቃለን። በሰዓቱ የደረሱ ተማሪዎችን ይዘን የምንሄድ በመሆኑና በመፈተኛ ቦታ አቴንዳንስ ስለሚወሰድ እንዳንወቀስ አደራ በሰዓቱ ተገኙ።

ትራንስፖርት በት/ቤት ተዘጋጅቷል

ጥብቅ መልዕክት ለ12ኛ ክፋል የተፈጥሮ ሳይንሰ(Natural Science) ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎቻችን በሙሉ። ✍የፊታችን ሰኞ ሰኔ 22/2018 በመፈተኛ ጣቢያችሁ ኮሚርስ ዩንቨርስቲ  ኦረንቴሽን የሚሰጥ ስለሆነ  ጠዋት 1:30 በመፈተኛ ጣቢያ መድረስ ስላለብን ከት/ቤት ቤት ጠዋት 1:00 ላይ ተነስተን ጉዞ እንጀምራለን። ስለሆነም ቀድማችሁ እንድትገኙ እናሳስባለን ። 📌 ዮኒፎርም መልበስ ፣ አድሚሽን ካርድ እና መታወቂያ መያዝ እንዳትረሱ ያልያዘ ተማሪ ወደ መፈተኛ አዳራሽ እንዲገባ አይፈቀድለትም ፣ መገኘት ግዴታ ነው የስም ቁጥጥር  ይደረጋል ፣ የመፈተኛ ወንበራችሁን የምታዩበት በመሆኑ በጣም  አስፈላጊ ኦረንቴሽ ነዉ። 📌 ሌሎች የሚከለከሉ ነገሮችንም እንዳትይዙ። 📌 የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎቻችንን በተመለከተ ወደፊት ኦረንቴሽን የሚሰጥበትን ቀንና ሁኔታ የምናሳውቃችሁ ይሆናል። ት/ቤቱ

👉ጥብቅ መልዕክት👈 🗣📄ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች:- 👉1ኛ:- የፊታችን ሰኞ ጠዋት 1:30 የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural) 1st Round ላይ የተመደባችሁ ሁሉ ተማሪዎች በየመፈተኛ ጣቢያ እንድትገኙና የፈተና ኦረንቴሽን እንድትወስዱ። 👉2ኛ:- ሰኞ ከሰዓት 6:30 የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural) 2nd Round የተመደባችሁ ሁላችሁም ተማሪዎች የፈተና ኦረንቴሽን እንድትወስዱ በጥብቅ እናሳስባለን። 👉3ኛ:- ተማሪዎች ኦረንቴሽን የሚወስዱት በኮሜርስ ዩንቨርስቲ ጣቢያ መሆኑን አውቃችሁ በሰአቱ ተገኙ። ✍ማሳሰቢያ:- 1ኛ:- ተማሪዎች የጠዋቱም ሆነ የከሰዓቱም ላይ መታወቂያና አድሚሽን ካርድ ይዘው መምጣት ግዴታ ነው። 2ኛ:- ተማሪዎች ኦረንቴሽ ላይ መገኘት ግዴታ ነው። 3ኛ:- የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ኦረንቴሽን በሌላ ቀን የምናሳውቃችሁ ይሆናል::

ለኮልፌ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ወላጆች ከ9-11ኛ ክፍል የተማሪዎች የውጤት ካርድ እሁድ ሠኔ 21/2018 ስለሚሠጥ ጠዋት 3ሠአት ትምሀርት ቤት በመገኘት መውሰድ ትችላላችሁ። ት/ቤቱ

19/10/2018ዓ.ም 🛜💻Mock Exam⌨️🖱 ✅የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በዛሬው እለትም mock exam ልምምድ በማድረግ ላይ ናቸው። ።።።***ት/ቤቱ

photo content
+1

photo content
+3

NATIONAL EXAM DATE AND ROUND

ቀን 18/10/2018 🗣📄ማስታወቂያ ➡️ ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ➡️ የ Mock Examል ልምምዱ ግን አርብ ይቀጥላል‼️🖱⌨️💻 ✅ ዛሬ በ Mock Exam  ልምምድ እግሊዘኛ መለማመዳችሁ ይታወቃል። ✅ በተለይ የ1ኛ  ዙር ተፈታኝ እና የ 4ኛ ዙር ተፈታኝ  ተማሪዎች ዛሬ በእግሊዘኛ የትምህርት አይነት ተለማምዳችኋል ። ✅ ነገ አርብ በ19/10/2018 ጠዋት 1:30 የ2ኛ ዙር ተፈተኝ ባዮሎጅ የት/ት ዓይነት እና ከሰዓት 6:30 የ5ኛ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎች ኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ትለማመዳለችሁ። ➡️ ሰዓት ይከበር‼️ ➡️ መቅረት አይቻልም‼️ ➡️ አቴንዳስ ይያዛል‼️ ✅ ወላጆች ልጆቻችሁን ልካችሁ የሙከራ ፈተናውን ይፈተኑ‼️ ለልምምድ  ስትመጡ መሟላት ያለባቸው ግዴታዎች 1. መፈተኛ ካርድ መያዝ 2. መታወቂያ መያዝ 3. ዩኒፎርም መልበስ 4. ወንድ ተማሪዎች ፀጉር መቆረጥ ማሳሰቢያ:- ✅ ከላይ የተዘርዘሩትን ያላሟላ ተማሪ ወደ ግቢ መግባትም  ሆነ መለማመድ አይችልም። ✅ በማንኛውም ምክንያት ያልተለማመደ  ተማሪ ለሚገጥመው ችግር ት/ቤቱ ሀላፊነት አይወስድም። 🟰🟰🟰🟰 ት/ቤቱ 🟰🟰🟰🟰