uz
Feedback
​🌹قَـــنَـــاةُ بِـــنـــتْ مُـــحَـــمَّـــد 🌹

​🌹قَـــنَـــاةُ بِـــنـــتْ مُـــحَـــمَّـــد 🌹

Yopiq kanal

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
546
Obunachilar
-224 soatlar
+177 kunlar
+5730 kunlar
Postlar arxiv
“ልቦችን የምታናውጥና አእምሮን የምትማርክ ምርጥ ቲላዋ” 🎙“በወንድማችን አንዋር ከራያ” t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

➲በነገራችን ላይ..በሐራም የተጀመረ ጉዞ ፍጻሜው በረካ የለውም።የዛሬው ዘመን ወጣቶች ትዳር መፍረስ ትልቁና የመጀመሪያው ሰንሰለት የሚቀጠለው ከትዳር በፊት በሚደረጉ ስህተቶች ነው። ምክኒያቱም ጅማሮው በሐራም የፍቅር ግንኙነት ላይ የቆየ፣ በድብቅና በኃጢአት የተገነባ ግንኙነት ፍጻሜው ያምራል ተብሎ አይታሰብም። ጌታችን አላህ በከለከለው መንገድ የተቃረቡ ልቦች፣ በትዳር ጥላ ስር ዘላቂ ሰላምና በረካን ሊያገኙ አይችሉም። በሐራም ግንኙነት ውስጥ ያለው ውበትና መሳሳብ የሰይጣን አሸብራቂ ስራ በመሆኑ፣ ያ ግንኙነት ወደ ሐላል ትዳር ሲቀየር ያ የውሸት መጋረጃ ይቀደዳል። በሐራም ውስጥ የነበረው የውሸት ናፍቆት በትዳር ውስጥ ወደ መሰላቸትና እርስ በርስ መናናቅ ይለወጣል። ጅማሮው አላህን በማስቆጣት የሆነ ነገር፣ ፍጻሜው ውድመት መሆኑ የማይቀር የእውነት ህግ ነው። አላህን በመፍራት ላይ ያልተመሰረተ ትዳር አሸዋ ላይ እንደተሰራ ቤት ነው። መሠረቱ የላላ ቤት አውሎ ንፋስ ሲመጣ ፍርክስክሱ እንደሚወጣው ሁሉ፣ ተቅዋ የሌለውም ትዳር በትናንሽ ፈተናዎች ይናዳል።በትዳር ውስጥ አላህን መፍራት ሲኖር እያንዳንዱ አካል የሌላኛውን ሐቅ ያከብራል፤ ባል የሚስቱን ደካማ ጎን በትዕግስት ያልፋል፤ ሚስትም የባሏን ልፋትና ደረጃ ትጠብቃለች። አላህን መፍራት በሌለበት ቤት ውስጥ ግን ኩራት፣ እራስ ወዳድነት፣ አለመቻቻልና ምላሰኝነት ይነግሳሉ። አንደኛው ወገን ለሌላኛው ክብርና እውቅና አይሰጥም። አላህ የሌለበት ቤት የጨለማ ቤት ነው፤ ጭቅጭቅና ሰላም ማጣት አይለየውም። አላህ ላላገቡት በሐላል ጎዳና የልብ እርካታ የሚሆን መልካም የትዳር አጋርን ይለግሳቸው፤ ያገቡትንም ትዳራቸውን በፍቅር፣ በረካና በተቅዋ አጅቦ እስከ ጀነት የሚያዘልቅ ያድርግላቸው። ~ t.me/Sle_qelbachn1 t.me/Sle_qelbachn1

📚የሠለፍያ ጎዳና ከጥመት ለመዳን ዋና ዋስትና ነው 🎙️ ውዱ ኡስታዛችን፦ ኡስታዝ ኸድር አህመድ አላህ ይጠብቀውና t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

✍️ኢብኑ ሙነወር ሆይ ያለ ድንበር ማለፍ በክብር እንወድሀለን። በእያንዳንዱ አቋምህ አብረን ስንሰለፍ፡ በመሀይማኖች ምንም ብንዘለፍ፡ #እናከብርሀለን_ያለ_ድንበር_ማለፍ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

#እራስሽን እራስሽ እምታክሚባቸው ዘዴዎች #ስሜትሽ አዛዥሽ አይሁን ህመም ይሰማሻል እንጂ አንቺ ህመሙ አይደለሽም፡፡ #ባዶነትሽን ሙዪው በሰዎች የተተወውን ክፍተት በእውቀትና በስራ ሙይው፡፡ #ትውስታሽ
#እራስሽን እራስሽ እምታክሚባቸው ዘዴዎች #ስሜትሽ አዛዥሽ አይሁን ህመም ይሰማሻል እንጂ አንቺ ህመሙ አይደለሽም፡፡ #ባዶነትሽን ሙዪው በሰዎች የተተወውን ክፍተት በእውቀትና በስራ ሙይው፡፡ #ትውስታሽን ቆልፊ ወደ ኋላ የሚጎትቱሽን ፎቶዎችና መልእክቶች ያለ ርህራሄ አጥፊ፡፡ #ብቸኝነትሽን ውደጂው ብቻሽን መሆን መጎዳት ሳይሆን ራስን የማግኘት እድል ነው፡፡ #አዲስ ራዕይ ፅንሺ *የተሰበረውን ልብሽን አዲስ ህልም እንዲያልም አስገድጂው።*

አድስ ሙሐደራ ደሴ አረብ ገንዳ መስጅድ 💉ስለ ተውሒድና ሽርክ ምረጥ ምክር 🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር (ሀፊዘሁሏህ) t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

አጠር መጠን ያለች ኮርስ በኡስታዝ ኢብን ሙነወር ሀፊዘሁሏሁ ወረዓ ወደ ቻናሉ ለመቀላቀል 👇👇👇👇👇👇 https://t.me/yedaewachannel https://t.me/yedaewachannel

👉ወሎ ምድር ኮንቦልቻ  ዛሬ ልዩ ፕሮግራም   ⭕️«ወሎ በልጆቿ»⭕️ --------------------- የዑለሞች ምድር የብርሀን ማማ፡ የእዝነት የደግነት ውብ የፍቅር ካስማ፡ ደምቃ በልጆቿ ኮንቦልቻ ከተማ፡ በሁሉም አቅጣጫ ደዕዋ እየተሰማ፡ ወጣቱ ከየትም ተጠራርቶ ቀርቧል፡ ወሎ ምድር ዛሬ ልዩ ዝናብ ዘንቧል፡ ዳግም እንደገና ይህ ትውልድ አብቧል፡ ትውልዱ ለእውነት እጁን እየሰጠ፡ ህዝባችን በተውሒድ እየተለወጠ፡ ጠላት እየሟሟ እንደ ጨው ቀለጠ፡ አብሽር የኔ ህዝብ የታሪክ ሰገነት የሞላበት ምድር፡ የፅናት ተምሳሌት የውብ ጀግኖች ስድር፡ የሸጋዎች ሀገር የውበት አውድማ፡ የአሊሞች መፍለቂያ የደጎች ባድማ፡ የፍቅር ተምሳሌት የመውደድ ውብ አርማ፡ የእስልምና ታሪክ የታላቆች ፊርማ፡ ከትናንት እስካሁን ጀግና እማይጠፋብሽ፡ አሊም የሐቅ ሰው ሰው እሚበቅልብሽ፡ የፍቅር የሰላም ፅናት ነው መረብሽ፡ ተውሒድና ሱናን የሚያስተምሩልሽ፡ ከውስጥሽ ተፈጥረው የሚዘምሩልሽ፡ ሐቅን እየሰሙ የማያቃልሉ፡ ሽርክን ለመፋለም ሁሌ እሚታገሉ፡ እውነተኛ አፍቃሪ ምርጥ ልጆች አሉ፡ ከፊሎቹ ዛሬ ደዕዋ ታድመዋል፡ ስለ እውነት ሊሰሙ ኮንቦልቻ ተመዋል፡ የኔ ቢጤ ደግሞ ሔዷል ባህር ማዶ፡ ከሚወዳት ምድር #ከወሎ ተሰዶ፡ ....ተመኘሁ አቦ...!! ምነው ትንሽ ቅፅበት በሆንኩ አብሬያችሁ!? ምነው በተገኘሁ ከመካከላችሁ!? በደስታ ሰክሬ ምነው  ባቀፍኳችሁ!? ወንጀል ይሆን እንደ ከናንተ የለየኝ፡ ባህር ማዶ ወስዶ ናፍቆት ያሰቃየኝ፡ ለነፍሴ እንደዛ ነው ለኔ የሚታየኝ፡ ....እውነት ነው!! እርግጥ ቀንቻለሁ አልቅሻለሁ ዛሬ፡ ግን ደግሞ ለእናንተ የ'እውነት ነው ፍቅሬ፡ ንግግሬን ቆጠብኩ እናንተን አክብሬ፡ 👉ለማንኛውም!! ሰለፍያ አ'ቅ'ፋው በውብ አክናፎቿ፡ ለሐቅ አናብስቶች ተከፍተው ቀሮቿ፡ ሒዝብያን አባረው ተፈፅሞ ፍቿ፡ በደዕዋ ደምቃለች ወሎ በልጆቿ፡ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

የጥፋት መንደር ብዙ እህቶች ተምረው እዳልተማሩ የሆኑበት ሰፈር ኮመንት በመፃፍ ለፃፈላቸው ሁሉ መልስ በመመለስ ውድ ግዜያቸውን የሚጨርሱበት የሚራቆቱበት ሰፈር የኢብሊስ መንደር። አላህ ሆይ ከጥፋት ግ
የጥፋት መንደር ብዙ እህቶች ተምረው እዳልተማሩ የሆኑበት ሰፈር ኮመንት በመፃፍ ለፃፈላቸው ሁሉ መልስ በመመለስ ውድ ግዜያቸውን የሚጨርሱበት የሚራቆቱበት ሰፈር የኢብሊስ መንደር። አላህ ሆይ ከጥፋት ግዜን በከንቱ ከመጨረስ አንተ ጠብቀን!!

✍አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪ አሰላምአለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ ዉድ ሙስሊም እህቶቸ ይህ በምስሉላይ የምትመለከቱት ወንድም ይማም ሁሴን አህመድ ይባላል በባጃጅ ስራ የሚተዳደር ወንድማችን ነበር ነገርግን የኢድ ለት ጧት ሰዉ አድርሰን ብለዉት ለሶላት እንድደርስ ብሎ ሊያደርስ ሲሄድ መንገድ ላይ ድንገት ላም ትገባበትና ባጃጁ ይገለበጣል ። እንደምታዩት ከባድ ጉዳት ደርሶበታል ለህክምና የተጠየቁት ገንዘብ 900 ሺብር ሲሆን ከአቅማቸዉ በላይ ሲሆንባቸዉ ወደኛ ብቅ አድርገዉታል ። ሰበብ እንሁን እራሱ ስለተመታ አልተሰፋም በቅርቡ ታልተሰፋ ለሌላ ህመም የመጋለጥ አቅሙ ሰፊ እንደሆነ ተነግሯቸዋል እባካችሁ ተባበሩን ስንል በአሏህ ስም እንጠይቃችሁዋለን አካዉንት  👇1000088439086 ኑሩ ሁሴን 1000331303748 "አህመድ ሁሴን የግሩብ ሊንክ 👇 https://t.me/+Vp1lW-dOfOkwZjVk ሁላችንም በገንዘብም በዱአም አድ በማድረግም ሌሎቺን በማስተባበርም እንተባበር

خرج علينا النبي ﷺ فقلنا: يا رسول الله، قد عَلِمْنا الله كيف نُسَلِّمُ عليك؛ فكَيف نُصَلِّي عليك؟ فقال: قولوا: اللَّهُمَّ صَلِّ على محمد وعلى آل محمد؛ كما صَلَّيْتَ على إبراهيم، إنَّك حميد مجيد، وبَارِكْ على محمد وعلى آل محمد؛ كما باركت على إبراهيم، إنَّك حميد مجيد».

ንግግሩ ውብነው ልብን የሚያረጥብ ላስተነተነው ሰው የነፍስያምግብ ከላይ የተሰጠን ከሀያሉ ጌታ፡፡ ምስጋናይደባው በጧትም በማታ፡፡ ያአሏህ ቁርአንን እንኳን ትንርጉሙን አውቀን እያስተነተንን ስንቀራው ዝም ብለን ስንሰማው ልብን የሚያረጥብ ነፍስያን የሚያረጋጋ ውብ ቃልኮነው

« እራሳችሁን ተቀበሉ! ለወሬ ማድመቅያነት በዘለለ እውነታን እየካዱ ለራስ አጓጉል ነገር መንገር አያበረታም። ተስብርያለሁ፣ ደክምያለሁ፣ ጠንካራ ይደለሁም፣ ተስፋ ቆርጫለሁ ለማለት ሳይሆን ማፈር ያለባ
« እራሳችሁን ተቀበሉ! ለወሬ ማድመቅያነት በዘለለ እውነታን እየካዱ ለራስ አጓጉል ነገር መንገር አያበረታም። ተስብርያለሁ፣ ደክምያለሁ፣ ጠንካራ ይደለሁም፣ ተስፋ ቆርጫለሁ ለማለት ሳይሆን ማፈር ያለባችሁ በእነዚህ ስሜቶች ውስጥ ስትሰነብቱ ነው። በቅጡ ካላለቀስሽ በደንብ መሳቅ እንዴት እንደሆነ ማወቅ ይጠፋሻል። ልክ ሞትን ብንክድ እንኳ መሞታችን እንደማይቀረው ሁሉ ስብራታችሁን ስለካዳችሁ የምትጎናፀፉት ጥንካሬ የለም። ይገባኛል ይህ መራር እውነት ነው። ነገር ግን ወደዳችሁም ጠላችሁ የምትክዱት እውነታ እያላችሁ ልትበረቱ አይቻላችሁም። ይህን ለመረዳት ረጅም እድሜ መኖር፣ መሸበት አይጠበቅባችሁም ጥቂትን በጥልቀት ለማስተዋል ሞክሩ። ሁሉንም ነገር ዋጋ ከፍላችሁ ለመማር እራሳችሁን አታስገድዱት! ህመማችሁን በዘላቂነት ሊፈውስላችሁ የሚችልን ነገር ምረጡ እንጂ ህመማችሁን የሚያስታግስላችሁ ማስታገሻ አታሳድዱ! »

ሱረ ቱል- ካህፍ 🌹تلاوة القرآن الكريم🌹

የአሏህ መልእክተኛ ሰለላሁአለይሂ ወሰላም እንድህ አሉ *ሳቅን አታብዙ ብዙ ሳቅ ልብን ይገላል* _ኢብኑ ማጅህ ዘግበውታል አልባኒ ሶሂህ ብለውታል_
የአሏህ መልእክተኛ ሰለላሁአለይሂ ወሰላም እንድህ አሉ *ሳቅን አታብዙ ብዙ ሳቅ ልብን ይገላል* _ኢብኑ ማጅህ ዘግበውታል አልባኒ ሶሂህ ብለውታል_

አንድ እናት ለልጇ እንድህ ስትል መከረች እየውልህ ልጀ ከባድ የሆኑ ነገሮችን ፊትለፊት ተጋፈጣቸው ብዙተማሪወች የቀለላቸውንና የሚያውቁትን ነገር ደጋግመው ማንበብ ይመርጣሉ ምክናየቱም ያንን ሲያነቡ ብዙ ያወቁ ይመስላቸውና እኔኮ ሁሉንም አውቀዋለሁ የሚል በራስ የመተማመን የውሸት ስሜት ይሰጣቸዋል ነገር ግን ከባድ የሆነውን እና የማይረዱትን ትምህርት ሲያው ስለሚጨንቃቸው ይሸሹታል እናማ ልጀ የሚከብድህን ነገር ደጋግመህ አድርገው ምክናየቱም እድገትህ የተሸሸገው እዛ እከበደህ ነገር ውስጥ ነው፡፡ ምነኛ ድንቅ የሆነ ምክር ነው ቁርአን ከበደን ብለን ስንቶቻችን ነን ሸሽተን የተውነው ኪታብ ጀምረን ስንቶቻችንን ነን አይገባኝም ብለን በመንገድ የቀረነው ስንቶቻችን ነን ሙሲባ ሲደርስብን የሙሲባችን አጅር በሶብር ውስጥ ሆኖ ሳለ ሶብርን አተን ከአሏህ ጋር የተጣላነው መልሱን ከራሳችን ለራሳችን ፡፡

_ተደዋውለን ለረጅም ስአት ስላላወሩን! በየሥቶሪያቸው በየፕሮፋይላቸው ማሬ ውደ የኔልዩ ጓደኛ ስላላሉን! ተመቻችቶላቸው ስጦታስላልሰጡን! ስለኛአይጨነቁም አያስቡም ማለትአይደለም ስንቶች አሉ በአፍደልለ
_ተደዋውለን ለረጅም ስአት ስላላወሩን! በየሥቶሪያቸው በየፕሮፋይላቸው ማሬ ውደ የኔልዩ ጓደኛ ስላላሉን! ተመቻችቶላቸው ስጦታስላልሰጡን! ስለኛአይጨነቁም አያስቡም ማለትአይደለም ስንቶች አሉ በአፍደልለው በተግባር *ዜሮየሆኑ* ስንቶችስ ናቸው ሲያሽቃብጡልን በስቶሪ በፕሮፋይል እንዳ እንዳልሰቀሉን እንደዛ እንዳላመገሱን በአንድ ስህተታችን ገደል የሰደዱን *ደግሞስ* በተቃራኒው ስንቶች አሉ ማሰባቸውን መጨነቃቸውን በልባቸው ደብቀው ለችግራችን ቀድመው የሚደርሱ ከወደቅንበት የሚያነሱን፡፡ አሏህ ሆይ የአፍ ከልባቸው ተዋደው ውደታቸውን በተግባር ከሚያሳዩ ባሮችህ አድርገን ስናደርግም ያደርጉልናል ብለን ሳይሆን ከአንተ ዘንድ የማያልቀውን አጅር ፈልገን የምናደርግ አድርገን ```መልካም መሆን ለራስነውና ለምናውቀውም ለማናውቀውም በቻልነው መልካም እንሁን መልካምነት ይከፍለናልጅ አንከፍልበትም፡፡```_

📚በኮበልቻው ኮርስ ላይ የሚቀሩ ኪታቦች🌿📚 ይህ ደውራ በሐበሻ ምድር ለምትገኙ የእውቀት ፈላጊዎችና የሱና ወዳጆች የቀረበ ታላቅ የምስራችና መለኮታዊ ስጦታ ነው! የጥንቁቅ ሰለፎችን ፈለግ የተከተሉ የዒልምና የዚክር መድረኮችን ለሚናፍቁ፣ በሱና ጥማት ለደረቁ ልቦች እነሆ የዒልም ብርሃን በሀገራችሁ መጥቶላችኋል። በኮንቦልቻ ከተማ የሚካሄደውን ታላቅና የተባረከ የዒልም ዑደት (ደውራ) ስናበስር በታላቅ ደስታ ነው፦ 🏛️ ቦታ– ኮምቦልቻ ከተማ – መስጂደል አንሷር ነው ይሄን ኮርስ የሚሰጡት ታዋቂው የሐዲስ ሊቅ፣ አስተማሪና መካሪው ሸይኽ አል-ሙሐዲስ አቡል ሐሰን ዐሊ ቢን አሕመድ አል-ራዚሒ (አላህ ይጠብቃቸው) ናቸው። ሸይኹ በሐዲስ፣ በዐቂዳና በመንሐጅ ዙሪያ ጠቃሚ የሆኑ እውቀቶችንና መሠረታዊ ግንዛቤዎችን በሚከተሉት ኪታቦች ማብራሪያ አማካኝነት ለተማሪዎች ያካፍላሉ፦ 📚በኮርሱ ላይ የሚቀሩ የኮርሱ ኪታቦች 1️⃣ «ኑኽበቱል ፊከር» «نخبة الفكر في مصطلح أهل الأثر» (በሐዲስ የቃላት መፍቻ/መስፈርት ዙሪያ) – በታላቁ የሐዲስ ሊቅ ኢብኑ ሐጀር አል-ዐስቀላኒ። 2️⃣ «አል-ቀዋዒዱል ሙስላ» «القواعد المثلى في صفات الله وأسمائه الحسنى» (ስለ አላህ ውብ ስሞችና ባህሪያት) – በታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሙሐመድ ቢን ሷሊሕ አል-ዑሠይሚን። 3️⃣ «መታ የኩኑ አር-ረጁሉ ሚን አህሊስ-ሱና» متى يكون الرجل من أهل السنة وبمَ يخرج منها»: (አንድ ሰው መቼ ከሱና ሰዎች ይመደባል? በምንስ ይወጣል?) – በታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሙሐመድ ቢን ዐብዲላህ አል-ኢማም ተፅፎ፣ በሸይኽ ዐሊ አል-ራዚሒ ሸርህ የተደረገው። ⚠️ እነዚህ ኪታቦች በቤታችሁ  ያሏችሁ ይዛችሁ ኑቶሎ ለሌላችሁ ደግሞ  ኪታቦችን ስላዘጋጄን እኛ እንሰጣችኋለን ምንም ክፍያ የለውም 🎙️ በተጨማሪም በመድረኩ ላይ የተለያዩ ታላላቅ መሻይኾችና የእውቀት ተማሪዎች የሚሳተፉባቸው ወቅታዊ ምክሮችና የዒልም ውይይቶች ይካሄዳሉ። 🌱 የዒልም ፈላጊ ሆይ! ና ተቀላቀል። 🌱 የሐዲስና የአሠር ተማሪ ሆይ! ዕድሉን ተጠቀም። 🌱 የሱና ወዳጅ ሆይ! ለመገኘትና ለመቅሰም ትጉ። የሸይኽ አል-ሙሐዲስ ዐሊ ቢን አሕመድ አል-ራዚሒ በእነዚህ ቀናት በሀገራችን መገኘት እጅግ ውድ አጋጣሚ ነው። እርሳቸው ለነቢዩ (ﷺ) ሐዲሶች ባላቸው ጥንቃቄ፣ ለሱና ባላቸው ጽናትና ትክክለኛውን የሰለፊያ ደዕዋ በማሰራጨት የሚታወቁ በመሆናቸው፤ ማንኛውም ተማሪ ይህንን ታላቅ ዕድል ሊያመልጠው አይገባም። 📅 የደውራው ጊዜ፦ ከቅዳሜ ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም  ጀምሮ ለተከታታይ 4 ቀን የሚቆይ ይሆናል። 🕌 ይሄ ጥሪ፦ ለሁሉም ሙስሊሞች ክፍት ነው። ለሴቶችም በቂ ቦታ አለን አላህ ይህንን የዒልም መድረክ የተባረከ እንዲያደርግልን፣ ሸይኻችንንም በጤናና በስኬት እንዲጠብቅልን እንለምነዋለን። ይህ ደውራ ጠቃሚ እውቀት የሚሰራጭበት፣ ሱና ሕያው የሚሆንበት፣ ቢድዓና መከፋፈል የሚከሽፍበት ሰበብ እንዲሆን ምኞታችን ነው። ለዚህ ስራ አስተዋጽኦ ላደረጉ፣ ላገዙና ለጠቆሙትም አላህ ታላቅ ምንዳን ይክፈላቸው። ይሄን ፕሮግራም በLIVE መካታተል ለምትፈልጉ በዚህ በሌሎችም ቻናሎች ይተላለፋል🌹t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy 🌹t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

📣 ታላቅ ብስራት የደውራ ፕሮግራም ጥሪ! ✅ በኮምቦልቻ ከተማ የሚገኘው የአንሷር መስጂድ ለ 4 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ እጅግ ደማቅ እና ታላቅ የኮርስ ፕሮግራም አዘጋጅቶ ለመላው ሙስሊም ወንድሞች እ
📣 ታላቅ ብስራት የደውራ ፕሮግራም ጥሪ! ✅ በኮምቦልቻ ከተማ የሚገኘው የአንሷር መስጂድ ለ 4 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ እጅግ ደማቅ እና ታላቅ የኮርስ ፕሮግራም አዘጋጅቶ ለመላው ሙስሊም ወንድሞች እና እህቶች ጥሪውን ያቀርባል። 📚 የፕሮግራሙ ልዩ እንግዳ፦ ታላቁ የ-የመን ሙሓዲስ ፈደይለቱ ሸይኽ ዐሊ አል-ራዚሒ (ሀፊዘሁላህ) —(በየመን የሚገኘውና በርካታ ተማሪዎችን ያፈራው የታዋቂው የመዕበር መርከዝ አስተማሪ) ◈እንድሁም ትልቁ አባታችን ፈደይለቱ ሸይኽ ሙሳ አል-ቀጧን (ሀፊዘሁላህ) ይገኛሉ። 🎙️ በፕሮግራሙ ላይ የሚታደሙ መሻይኾች እና ኡስታዞች፦ ▪️ ሸይኽ ሙሐመድ መኪን   ከደሴ ▪️ ሸይኽ ጀማል ዘሀቢ         ከደሴ ▪️ ሸይኽ ሙሐመድ ሰዒድ    ከደሴ ▪️ ሸይኽ ይማም ሰዒድ        ከደሴ ▪️ ሸይኽ አሕመድ አወቀ       ከደሴ ▪️ ሸይኽ በድሩ ዩሱፍ           ከደሴ ▪️ ሸይኽ ሙሐመድ ሁሴን     ከቢስቲማ ▪️ ሸይኽ ዐብዱል ዐዚዝ        ከደሴ ▪️ ሸይኽ ሙሐመድ አሚን       ከደሴ ▪️ ሸይኽ ሐሰን አሊ ቃዲ          ከደሴ ▪️ ሸይኽ ሁሰይን አቡ ሶላሑዲን ከደሴ ▪️ ሸይኽ አወል አሕመድ መነዮ  ከመረሳ ▪️ ሸይኽ አወል አህመድ          ከከሚሴ ▪️ሸይኽ ዒሳ አደም                 ከደሴ 🔸 ዶክተር /ኡ ሁሴን አሊ         ከከላላ 🔸 ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር       ከአ.አበባ 🔸 ዶክተር/ኡ ሰዒድ ሙሳ         ከአ.አበባ 🔸 ኡስታዝ ኸድር አሕመድ     ከከሚሴ 🔸 ኡስታዝ አቡ ሒዛም          ከአዳማ 🔸 ኡስታዝ  ዐብደሽኩር          ከአሶሳ 🔸ኡስታዝ ዐብዱሰላም ሐሰን   ከአዳማ 🔸 ኡስታዝ አቡ ዒምራን   ከሀርቡ 🔸 ኡስታዝ አቡ አዩብ      ከኮቦልቻ 🔸 ኡስታዝ ሙርሰል        ከደሴ 🔸 ኡስታዝ አቡ ሻኪር      ከኮንቦልቻ 🔸 ኡስታዝ አቡ ረያን        ከመርሳ 🔸ኡስታዝ መሀመድ አያሌው ከወልዲያ 🔸ኡስታዝ አቡ ዓብዱ ረዛቅ ጅረሳ ከመርሳ 🔸 ኡስታዝ አቡ ዑበይዳ    ከኬሚሴ 🔸 ኡስታዝ ዐብዱልመሊክ ከኬሚሴ 🔸 ኡስታዝ አቡ ሐሳን        ከኮቦልቻ 🔸 ኡስታዝ አቡ ሃኒፋ         ከኬሚሴ 🔸 ኡስታዝ መ/ሲራጁ       ከኬሚሴ 🔸 ኡስታዝ ዐሊይ ሰይድ     ከደሴ 🔸 ኡስታዝ አንሷር መሀመድ ከደሴ 🔸 ኡስታዝ አቡ ሐፍሷ         ከደሴ 🔸ኡስታዝ ጀውሀር  ክፍሌ    ከደሴ 🔸 ኡስታዝ አቡ ዐብዲረሕማን ከመርሳ 🔸 ኡስታዝ አቡል መዓሊ      ከመርሳ 🔸 ኡስታዝ አቡ ሹራ            ከደሴ 🔸 ኡስታዝ አቡ ማሂ            ከኮንቦልቻ 🔸 ወንድም አቡ ሂበቲላህ       ከደሴ 👥 የአንሷር መስጅድ ኢማምና ጀመዓዎቹ ባጠቃላይ... 👤እንዲሁም ሌሎች ከተለያየ ሀገር  በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው መሻይኾችና ኡስታዞችም በቦታው ይገኛሉ! 📆 የፕሮግራሙ ቀናት፦ የመጀመሪያ ቀን፦ ሰኔ 6/2018 (ከፊታችን ቅዳሜ ጧት 3:00) ጀምሮ ለ 4 ተከታታይ ቀናት ይቆያል። 🏘 ማሳሰቢያ፦ ለታዳሚዎች በቂ የምግብ እና የመኝታ ቦታ ተዘጋጅቷል።—የሌሊት ብርድ ልብስ ይዛችሁ ብትመጡ መልካም ነው።— 🤩በእነዚህ የቴሌ ግራም አድራሻ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር በመላክ ይመዝገቡ፦ 📝ኡስታዝ አቡ ሻኪራ አህመድኑር @Abuhureirehonline    0923467646 📝 ኡስታዝ አቡ ዐዩብ   092 588 7118 @Attewhid11 📝 ወንድም አቡ ሂበቲላህ ሁሰይን @Abu_Hibetillah_Al_aseriy 0942819970 💙የቦታው አቅጣጫ ካስቸገራችሁ በነዚህ የእንግዳ ተቀባይ ወንድሞች ስልክ ቁጥሮች ላይ ይደውሉ፡ 📞 ወንድም አንዋር 0916582567 📞 ወንድም አቡ አማር 0913803997 📞 ወንድም ሰኢድ 0935568513