Ethiopian Educational Channel
Відкрити в Telegram
እንኳን ደና መጣችሁ በዚህ ቻናል ላይ የሚያገኙት 1. ትምህርታዊ መረጃ መስጠት 2.የሳይኮሎጂ አስተማሪ ምክሮችንና አነቃቂ ንግግሮች 3.መፃህፍቶች በpdf እና የእንግሊዝኛ ትምህርት ይለቀቃሉ! በዚህ ቻናል ሀይማኖታዊ እና ፓለቲካ ነክ አይለቀቅበትም ! የቴሌግራሙ ቻናል ሊንክ:👉https://t.me/EEC1227 Channel created by @BA1227
Показати більше6 836
Підписники
-724 години
-217 днів
-730 день
Архів дописів
የመንግስት ሠራተኞች የጡረታ መመሪያ!
**
1. ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ በተቀጠረው በ60 ቀናት ውስጥ ለጡረታ በማህበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ መመዝገብ አለበት፡፡
2. የጡረታ አበል ለቀጣይ ተቀማጭ የሚሆነው ገንዘብ ከሠራተኛ 7% ሲሆን ከመንግስት ደግሞ 11% በድምሩ 18% ሆኖ ለፖሊስና ለመከላከያ ግን ከሠራተኛ 7% እና ከመንግስት 25% በድምሩ 32% ነው፡፡
3. ጡረታ የሚያስወጡ ምክንያቶች:-
1=በእድሜ ምክንያት 60 ዓመት ሲሞላው
2=በራሱ ፈቃድ
3=በጤና ጉድለት
4=በስራ ለይ በደረሰ አካል ጉዳት
5=በሞት ናቸው፡፡
4. የጡረታ አበል በውክልና የሚከፈለው:-
1= በእርጅና
2=በህመም
3= ወደ ውጭ ሀገር በመሄድ
4= በትምህርት ወዳ ሌላ ቦታ በመሄድ
5=በእስራት ምክንያት ናቸው፡፡
5ኛ. የጡሮታ አበል በይርጋ የሚዘጋው:-
1=የጡረታ አበል ጥያቄ ሳይቀርብ ወይም የተወሰነለትን ጡረታ ሳይወስድ ከ5 ዓመት በላይ ከቆየ አይከፈለውም፡፡ በቀጣይ ከአመለከተበት ቀን ጀምሮ ይከፈለዋል፡፡
2=የዳራጎት ጡረታ ሳይጠየቅ ቀርቶ ወይም የተጠየቀውን 5 ዓመት ድረስ ሳይወስድ ከቆየ በይርጋ ይዘጋል (አይከፈልም)::
6. በእድሜ 60 ዓመት ሲሞላው ለሠራተኛው የሚሰጥ የጡረታ አበል ስሌት:-
* ከተቀጠረበት ቀን ጀምሮ እስከ 10 ዓመት ድረስ ያለው አገልግሎት በ30% ሲባዛ ከ10 ዓመት በላይ ያለው እያንደንዱ አገልግሎት ግን 1.25 ይባዛል፡:ለምሳሌ 28 አመት አገልግሎት ያለው ስሌት 10ዓመት×30% + 18ዓመት ×1.25= 30+22.5= 52.5% ነው፡፡ በዚህም መሠረት ለጡረታ የሚያዘው ደመወዝ የመጨረሻው የ36ወራት (3ዓመት) ብቻ ስለሆነ በ3ዓመቱ ሲከፈል የነበረው ደመወዝ 5,000 ቢሆን ጡረታው 52.5% ×5,000ብር = 2,625 ብር ጡረታ ያገኛል ማለት ነው፡፡
7. በጀማሪ ቅጥር ወቅት ቀንና ወር ሳይሞላ ዓ,ም ብቻ በህይወት ታሪክ ተሞልቶ ከተገኘ የጡረታ ቀንና ወር የሚያዘው በኢ/ያ አቆጣጠር ከሆነ ነሐሴ 30 ተብሎ ሲያዝ እ.ኤ.አ ከሆነ ታህሳስ 31 ቀን ተብሎ ይታሰባል፡፡
8. በረሱ ፍላጎት ጡረታ የመውጣት መብት እድሜው 55 ዓመት ሲሆንና 25 ዓመት አገልግሎት ሲኖረው ሆኖ ለፖሊስና ለመከላከያ ሠራዊት ግን ከሚወጡበት ዓመት 5ዓመት ቀድሞ መውጣት ይችላሉ ፡፡
9. የሟች ጡረታ የሚወርሱ ልጆች ከ18ዓመት በታች ወይም አካል ጉዳተኛ ልጅ ከሆነ 21ዓመት በታችና የሟች እናትና አባት ናቸው፡፡
10. ለጡረታ አበል ለማስፈፀም የሚያስፈልጉ ማስረጀዎች:-
1=በህይወት ታሪክ የተሞላው መረጃ (ጡ1እና 2)
2=የሙከራና የቋሚ ቅጥር ደብደቤ
3= የጡረታ መለያ ቁጥር
4= የ36 ወራት የደመወዝ መረጃ
5= የዝውውር፣ የደረጃ ዕድገትና የደመወዝ ለውጥ የተደረገበት ደብደቤ
6= የጋብቻ እና የልጆች ማስረጃ
7= የባለጡረታ ወይም የወራሽ ፎቶ ግራፍ ናቸው፡፡
እንዲታይላችሁ የምትፈልጉ አድሚሽን ካርድ ቁጥራችሁን እና ስማችሁን በትክክል ላኩ screenshot አድርጌ እልክላችኃለሁ
የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት መመልከቻ ሊንክ
👇👇👇👇👇👇👇
LINK
https://aa.ministry.et/#/result
መጀመሪያ መለያ ቁጥር ወይም ሬጅስትሬሽን ነምበር አስገቡ በመቀጠልም ስማችሁን ብቻ በማስገባት "check my result " የሚለውን ከታች ስትነኩ ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ::
የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይሆናል፡፡
AAE
በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና አሰጣጥ ወቅት ፈተና ለመስረቅም ይሁን ለማሰረቅ የሚሞክሩ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል። - ትምህርት ሚኒስቴር
ትምህርት ሚኒስቴር ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም በበይነ መረብ እና በወረቀት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሒዷል።
የፈተናው አጠቃላይ ሂደት ደህንነቱ የተጠበቀና ውጤታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተቀናጀ ሁኔታ መሰራት እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል፡፡
ፈተናውን ለመስረቅም ይሁን ለማሰረቅ የሚሞክሩ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል።
ብሔራዊ ፈተናውን ለመስጠት በመሠረተ ልማት፣ ደህንነት እና ሌሎች መስኮች ተገቢው ዝግጅት መደረጉ ተመላክቷል።
ፈተናውን ለመውሰድ 563,501 ተፈታኞች (306,456 የተፈጥሮ ሳይንስ እና 257,045 የማኅበራዊ ሳይንስ) ተፈታኞች መመዝገባቸው ተገልጿል፡፡ #MoE
@TwmariEthiopia
🔤በመጭው ማክሰኞ የ12ኛ ክፍል ፈተና ይጀምራል
✔️ተማሪዎች ፈተና ስትፈተኑ 🔤🔤
➖
➖የተረጋጋ መንፈስ መያዝ፣
➖ ጊዜን በአግባቡ ማስተዳደር
➖ ጥያቄዎችን በጥንቃቄ ማንበብ እና
➖እርግጠኛ ያልሆኑባቸውን ክፍሎች ማለፍ የተሻለ ውጤት ለማምጣት ይረዳል
✅ፈተናውን በአግባቡ ለመወጣት የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች ተግባራዊ ማድረግ ይገባቹሀል፡:
⭐️መመሪያዎችን በጥንቃቄ ያንብቡ፡
✅የፈተናውን ወረቀት መመሪያ እና ጥያቄዎች ከመጀመርዎ በፊት በደንብ መረዳት ስህተቶችን ይቀንሳል::
⭐️ጊዜን በአግባቡ ይመድቡ፡
✅ለእያንዳንዱ ጥያቄ የሚሆን ጊዜ በማስላት በአንድ ከባድ ጥያቄ ላይ ብዙ ጊዜ አያጥፉ። ጊዜ እንዳይባክን የሚያውቋቸውን ጥያቄዎች አስቀድመው ይስሩ::
⭐️አስቸጋሪ ጥያቄዎችን ይለፉ፡
✅መልሱን ወዲያውኑ ማግኘት ያልቻሉትን ጥያቄ ምልክት በማድረግ አቆይተው ይመለሱባቸው::
⭐️መረጋጋትን ያዳብሩ፡
በፈተና ወቅት ጭንቀት ከተሰማዎት ጥልቅ ትንፋሽ በመውሰድ አእምሮዎን ያረጋጉ::
⭐️መልሶችን ይከልሱ፡
✅ፈተናውን submit ከማድረጋቹህ በፊት የተሰሩትን መልሶች በሙሉ በስርዓቱ መፈተሽዎን ያረጋግጡ::
📌መልካም ፈተና
👌 የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ልጆችም ሆኑ ተማሪዎች ካላችሁ ያጋሩ
👌 share it
አዲሱ የሌብነት ስልት‼️
በቴክኖሎጂ የታገዘው አዲሱ የሌብነት ስልት፦ የሐሰት የዲጂታል ክፍያ ደረሰኞች ነጋዴዎችን እንዴት እያከሠሩ ነው?
ሰኔ 21 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ የዲጂታል ክፍያ ሥርዓትና የሞባይል ገንዘብ ማስተላለፊያ አማራጮች በከፍተኛ ፍጥነት መስፋፋታቸውን ተከትሎ፣ አጭበርባሪዎች የቴክኖሎጂ ክፍተቶችን በመጠቀም አዳዲስ የሌብነት ስልቶችን እየቀየሱ ይገኛሉ።
በአሁኑ ወቅት በርካታ ነጋዴዎችንና የንግድ ተቋማትን ለአሳሳቢ ኪሳራ እየዳረገ ያለው ዋነኛው መንገድ፣ የተለያዩ የባንክና የሞባይል ገንዘብ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎችን የክፍያ ማረጋገጫ ምስሎችንና የጽሑፍ መልዕክቶችን የሚመስሉ የሐሰት ሶፍትዌሮችን መጠቀም ነው።
እነዚህ መተግበሪያዎች በአጠቃላይ የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቱን ደኅንነት አደጋ ላይ የጣሉ ሲሆን፣ ኅብረተሰቡ ስለ አሠራራቸው በቂ ግንዛቤ ሊኖረው እንደሚገባ የዘርፉ ባለሙያዎች ያሳስባሉ።
እነዚህ "Fake Payment Receipt Generators" በመባል የሚታወቁ የሐሰት ሶፍትዌሮች በሁለት ዋና ዋና መንገዶች እንደሚሠሩ ይነገራል።
የመጀመሪያው ዘዴ ትክክለኛ የዲጂታል ክፍያ መተግበሪያዎችን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቅዳት የተዘጋጁ የክሎን (Clone) መተግበሪያዎች ናቸው።
አጭበርባሪዎች በእነዚህ መተግበሪያዎች ውስጥ የተከፋዩን ስም፣ የገንዘብ መጠን፣ የተከናወነበትን ቀንና የግብይት መለኪያ ቁጥር (Transaction ID) ራሳቸው በመሙላት፣ ገንዘቡ በስኬት እንደተላለፈ የሚያሳይ የተደናገረ የሐሰት ምስል በሰከንዶች ውስጥ ይፈጥራሉ።
ይህንን ምስል ለነጋዴው በማሳየትም ዕቃዎችንና አገልግሎቶችን ያለምንም ክፍያ በመውሰድ ያጭበረብራሉ።
ሁለተኛውና ይበልጥ የተራቀቀው ዘዴ ደግሞ የሐሰት የጽሑፍ መልዕክት (SMS Spoofing) የሚባለው የቴክኖሎጂ አሠራር ነው። በዚህ መንገድ አጭበርባሪዎች የፋይናንስ ተቋማትን ይፋዊ የላኪ ስም በማስመስል፣ የገንዘብ መግባት መልዕክት በቀጥታ ወደ ተጎጂው ስልክ እንዲደርስ ያደርጋሉ።
ተጎጂው ነጋዴ መልዕክቱ የመጣው ከትክክለኛው የጽሑፍ መስመር መስሎ ስለሚታየውና ላኪው ላይ የታወቁ ተቋማት ስም ተጽፎ ስለሚመለከት፣ የሂሳብ ቀሪውን ሳያረጋግጥ በሐሰተኛው መልዕክት ብቻ በመተማመን በቀላሉ ይሸወዳል።
እነዚህ መተግበሪያዎች ሙሉ በሙሉ ሕገ-ወጥ በመሆናቸው በይፋዊ መተግበሪያ መደብሮች ላይ በፍጹም አይገኙም። ይልቁንም አጭበርባሪዎች እነዚህን አደገኛ የሶፍትዌር ፋይሎች በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ ቻናሎች እና የደኅንነት ቁጥጥር በሌላቸው የድረ-ገጽ ማውረጃዎች ላይ በድብቅ እርስ በርስ እየተቀባበሉ ያሰራጯቸዋል።
ይህ ዓይነቱ አሠራር የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ሲሆን፣ መተግበሪያዎቹን መያዝም ሆነ መጠቀም ከፍተኛ የወንጀል ድርጊት ነው።
ይህንን በቴክኖሎጂ የታገዘ ማጭበርበር ለመከላከልና ራስን ከኪሳራ ለመጠበቅ፣ ነጋዴዎች ከደንበኞች የሚመጡላቸውን ስክሪንሾቶች (Screenshots) ወይም በስልካቸው ላይ የሚደርሱ የጽሑፍ መልዕክቶችን ብቻ አይቶ በፍጹም መተማመን የለባቸውም።
የፋይናንስ ተቋማትና የደኅንነት ባለሙያዎች በተደጋጋሚ እንደሚያሳስቡት፣ አስተማማኙ የመከላከያ መንገድ የራስን የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ በመክፈት ወይም በይፋዊ የአጭር ቁጥሮች (USSD Codes) አማካኝነት የሂሳብ ሒሳቡን በቀጥታና በእርግጠኝነት ማረጋገጥ ብቻ ነው።
@አዩዘሀበሻ
የሐረሪ ክልል የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል
የሚኒስትሪ ውጤት ተለቋል
💻ውጤት ለማየት
🏮ለ6ኛ ክፍል
https://harari6.ministry.et እና
🏮 ለ8ኛ ክፍል
https://harari.ministry.et ይጠቀሙ
@grade6and8
✅ የ2026 የዓለም ዋንጫ የ32ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ይጀምራሉ።
📅 ዛሬ ሰኔ 21/2018
🇿🇦ደቡብ አፍሪካ ⏰ ማታ 4:00 ካናዳ🇨🇦
📅 ሰኞ ሰኔ 22/2018
🇧🇷ብራዚል ⏰ ማታ 4:00 ጃፓን🇯🇵
🇩🇪ጀርመን ⏰ ማታ 5:30 ፓራጓይ🇵🇾
🇳🇱ኔዘርላንድ ⏰ ሌሊት 10:00 ሞሮኮ🇲🇦
📅 ማክሰኞ ሰኔ 23/2018
🇨🇮አይቬቲኮስት⏰ ማታ 2:00 ኖርወይ🇳🇴
🇫🇷ፈረንሳይ ⏰ ሌሊት 6:00 ስዊድን🇸🇪
🇲🇽ሜክሲኮ ⏰ ሌሊት 10:00 ኢኳዶር🇪🇨
📅 ረቡዕ ሰኔ 24/2018
🏴እንግሊዝ ⏰ ማታ 1:00 ዴ/ሪ/ኮንጎ🇨🇩
🇧🇪ቤልጄም ⏰ ማታ 5:00 ሴኔጋል🇸🇳
🇺🇸አሜሪካ ⏰ ሌሊት 10:00 ቦስንያ🇧🇦
📅 ሓሙስ ሰኔ 25/2018
🇪🇸ስፔን ⏰ ማታ 4:00 ኦስትሪያ🇦🇹
🇵🇹ፖርቹጋል ⏰ ሌሊት 8:00 ክሮሽያ🇭🇷
📅 ዓርብ ሰኔ 26/2018
🇨🇭ስዊዘርላንድ ⏰ ጥዋት 12:00 አልጄሪያ🇩🇿
🇦🇺አውስትራልያ ⏰ ማታ 3:00 ግብፅ🇪🇬
🇦🇷አርጀንቲና ⏰ ሌሊት 7:00 ኬፕ ቨርዴ🇨🇻
🇨🇴ኮሎምብያ ⏰ ሌሊት 10:30 ጋና🇬🇭
የ32ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች ተጠናቅቀዋል።
ከየምድቦቻቸው 1ኛ እና 2ኛ በመሆን 24 ሀገራት በቀጥታ እንዲሁም ተጨማሪ 8 ሀገራት ምርጥ 3ኛ በመሆን የ32ቱን ጥሎ ማለፍ ተቀላቅለዋል።
በዚህም መሰረት የ32ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ከምድብ 1 እና 2 ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቁት ደቡብ አፍሪካ እና አዘጋጇ ሀገር ካናዳ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀምራል።
ምድብ ሦስትን በበላይነት ያጠናቀቀችው ብራዚል ከጃፓን እንዲሁም የምድብ 5 አሸናፊዋ ጀርመን ከፓራጓይ ተደልድለዋል።
ኔዘርላንድስ ከሞሮኮ፣ ኮትዲቯር ከኖርዌይ፣ ፈረንሳይ ከስዊድን፣ ሜክሲኮ ከኢኳዶር፣ እንግሊዝ ከዲሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ እንዲሁም ቤልጂዬም ከሴኔጋል ይገናኛሉ።
አሜሪካ ከቦሲኒያ ሄርዞጎቪና፣ ስፔን ከኦስትሪያ፣ ፖርቹጋል ከክሮሺያ፣ ስዊዘርላንድ ከአልጄሪያ፣ አውስትራሊያ ከግብጽ፣ አርጀንቲና ከኬፕቨርዴ እንዲሁም ኮሎምቢያ ከጋና ተደልድለዋል።
ቀን:- 21/10/2018 ዓ.ም
ለትምህርት ቤታችን የተማሪ ወላጆች በሙሉ።
የ2018 ዓ.ም ተማሪዎች ካርድ የሚሰጠው ዕሁድ በ28/10/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ላይ ብቻ መሆኑን እየገለፅን ከተባለው ቀንና ሰዓት ውጭ ለሚመጣ ተማሪም ሆነ ወላጅ አገልግሎት የማይሰጥ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።
መረጃው:ረጲ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ነው
#ት/ቤቱ
ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶችን ሲጠቀሙ በአግባቡ ሊተገብሯቸው የሚገቡ
የጥንቃቄ እርምጃዎች፡፡
=========
ደንበኞች እንደ ሞባይል ባንኪንግ፣ ኢንተርኔት ባንኪንግ፣ ኤቲኤም፣ ፖስ፣ ሲቢኢ ብር የመሳሰሉ ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶችን በሚጠቀሙበት ጊዜ የሚከተሉትን የደህንንት መጠበቂያ ተግባራት ሊተገብሩ ይገባል፡
• የሚስጢር ቁጥርዎን በስልክዎ ውስጥ አለማስቀመጥ፣ በወረቀት ወይም በማስታወሻ ደብተር ላይ አለመፃፍ እና በአጠቃላይ ለሌላ ሰው አለማሳየት ወይም በቀላሉ በሚታይበት ቦታ ላይ አያስቀምጡ፤
• የተንቀሳቃሽ ስልክዎን በተቻለ መጠን ለሌላ ሰው አይስጡ (አያውሱ)፡፡ ነገር ግን ለሌላ ሰው የሚሰጡ ወይም የሚቀይሩ ከሆነ ግን ስልኩ ላይ ያለውን የየዲጂታል ባንክ አገልግሎት መጠቀሚያ መተግበሪያ እና ሌሎች የግል መረጃዎን የያዙ ጽሑፎችንና ኢሜሎችን ያጥፉ፤
• የካርድ ባንኪንግ አገልግሎት በሚጠቀሙበት ጊዜ በሚያደርጉት ነገር ላይ ብቻ ያተኩሩ፤ ትኩረትዎን የሚያስተጓጉሉ እንደ ሞባይል ስልክ እና መሰል ነገሮቸን አይጠቀሙ፤
• የኤቲኤም ማሽን ላይ ሲጠቀሙ የሚስጢር ቁጥርዎ እንዳይታይ፤ የኤቲኤም ቁልፍ ሰሌዳውን ሰውነትዎን ተጠቅመው በመሸፈን በቅርብ የቆሙ ሰዎች እንይመለከቱ ይከላከሉ፣ ከግብይት በኋላ ካርዱን መቀበሎን ያረጋግጡ፤
• የተንቀሳቃሽ ስልክዎ ላይ የሚጭኗቸውን መተግበሪያዎች ሲያወርዱ አፕስቶር እና ፕሌይስቶርን ብቻ ይጠቀሙ፤
• ደኅንነቱ ያልተረጋገጠ ድረ-ገጽ እና የማኅበራ ሚዲያ ገፆችን አይጠቀሙ፣ አጠራጣሪ ማስፈንጠሪያዎችን (links) አይክፈቱ፤
• ግብይትዎን በሚያካሂዱበት ጊዜ ችግር ቢያጋጥምዎ ከሚመለከታችው የባንኩ ሠራተኞች ውጪ የማንንም እገዛ አይጠይቁ፤
• የሚስጢር ቁጥርዎን በየጊዜው ይቀያይሩ፤
• ተከታታይ የሆኑ ወይም የስልክ ቁጥርዎን የመጨረሻ ዲጂቶች፣ ማንኛውም የግል መረጃ ለምሳሌ የልደት ቀን የሚስጥር ቁጥር አድርገው አይጠቀሙ፤
• በስልክ ምንም አይነት የባንክ መረጃዎን አይስጡ፣
• ሞባይል ሲጠፋብዎ ወደ ባንኩ ቅርንጫፍ በመሄድ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት እንዲቋረጥ ያስደርጉ፤
• የሚጠቀሙበት ኮምፒዩተር ሁሌም የቫይረስ መከላከያ እንዳለው ያረጋግጡ፤
• ሂሳብዎ ላይ አጠራጣሪ እንቅስቃሴ ሲኖር ለባንኩ ወዲያውኑ ያሳውቁ፤
• የባንክ አገልግሎት በሚጠቀሙባቸው ኮምፒውተሮች እና ተንቀሳቃሽ ስልኮች ላይ የማይታወቁ መተግበሪያዎችን አይጫኑ፤
• አገልግሎት ካገኙ በኋላ አስፈላጊውን ቅደም ተከተል በመከተል ዘግተው ይውጡ፡፡
ክፍል ሁለት
መብረቅ ለመታው ሰው ስለሚደረጉ እና ስለማይደረጉ ነገሮች :-
አይበለው እና ከእኛ ጋር ያለ ሰው የመብረቅ አደጋ ቢደርስበት ከአፈር ለመቅበር ወደ ጉድጓድ ቁፈራ ነው የምንሄደው ወይስ ምን እናድርግ፤ ብንነካው ቻርጁ ወደ እኛ ይተላለፋል ወይስ አይተላለፍም? የሚሉትና እና ሌሎች ጠቃሚ ሳይንሳዊ ምክሮችን እነኆ ።
፩. የባህላዊ ልማዶች ፍተሻ፦ የታሰበው እና ሳይንሳዊ እውነታው
ማንኛውም ሰው መጀመሪያ እርዳታ ከመጀመሩ በፊት የሚከተሉትን ጎጂ ልማዶች ማወቅ እና ማስወገድ አለበት፦
ሀ. መሬት ውስጥ መቅበር (እስከ አንገት/እስከ ደረት)
የሚታሰበው ፦ አፈሩ በሰውነት ውስጥ የተከማቸውን ኤሌክትሪክ ወደ መሬት ይስበዋል ተብሎ ይታመናል።
ሳይንሳዊ እውነታው፦ መብረቅ ሰውን መትቶ የሚያልፈው በሚሊሰከንዶች ውስጥ ስለሆነ ሰውነት ውስጥ የሚቀር የኤሌክትሪክ ክምችት የለም። አፈር መቆፈር እና ሰውን መቅበር ሌሎች ሕይወት አድን የሆኑ ስራወችን ለመሥራት የምንጠቀምበትን ወሳኝ የሆነውን ሰዓት (ወርቃማ ጊዜ) ያባክናል። በተጨማሪም አፈሩ ደረት ላይ የሚፈጥረው ጫና መተንፈስ ይከለክላል ፤ የሰውነት ሙቀትን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል ፤እንዲሁም በአደጋው ጊዜ በቃጠሎ ምክንያት የተፈጠሩ ቁስሎችን ለከፋ ኢንፌክሽን ያጋልጣል።
ሲጠቃለል መቅረቅ የመታውን ሰው ከአፈር መቅበር ምንም ዓይነት ጥቅም የለውም ።
ለ. ሌሎች የማይጠቅሙ እና ጎጂ ልማዶች :-
🎆ውሃ፣ ወተት ወይም ባህላዊ መድኃኒት በአፍ ማጠጣት፦ ራሱን የሳተ ሰው የመዋጥ አቅም ስለሌለው ፈሳሹ በቀጥታ ወደ ሳንባ በመሄድ ወዲያውኑ ሊያንቀው ወይም ሊገድለው ይችላል። ስለዚህ በማንኛውም ሁኔታ ንቁ ያልሆነ ሰው (ራሱን የሳተ) ምንም አይነት ፈሳሽ ለማጠጣት መሞከር አይመከርም።
🎆በቃጠሎ የተፈጠ ቁስል ላይ ቅቤ፣ ዘይት ወይም ሌላ ነገር መቀባት፦ የመብረቅ ቃጠሎ ከፍተኛ ውስጣዊ ሙቀት አለው። ቅቤ ወይም ዘይት መቀባት ሙቀቱ ወደ ውጭ እንዳይወጣ አፍኖ በመያዝ ቃጠሎውን ያባብሰዋል፤ ከባድ ባክቴሪያም ወደ ውስጥ ያስገባል።
🎆 አደጋው በደረሰበት ቦታ ላይ መቆየት፦ መብረቅ በአንድ በዝናብ ማዕበል ወቅት በአንድ ቦታ ላይ ከአንድ ጊዜ በላይ የመምታት ዕድሉ ከፍተኛ በመሆኑ፣ እዚያው ቦታ ላይ እርዳታ ለመስጠት መሞከር ረዳቱንም ጭምር ለአደጋ ያጋልጣል።
፪. መደረግ ያለባቸው የመጀመሪያ እርዳታዎች :-
የመጀመሪያ እርዳታ ሰጪው ሕክምና ባለሙያ ባይሆንም የሚከተሉትን እርምጃዎች ደረጃ በደረጃ መተግበር አለበት፦
ደረጃ 1 ፦ የቦታውን ደህንነት ማረጋገጥ
መብረቅ የደረሰበትን ሰው ወዲያውኑ በእጅ መንካት ምንም አይነት ችግር አያመጣም።
ነገር ግን ከላይ እንደጠቀስነው መብረቅ በአንድ በዝናብ ማዕበል ወቅት በአንድ ቦታ ላይ ከአንድ ጊዜ በላይ የመምታት ዕድሉ ከፍተኛ ነው። ስለሆነም ተጎጂውን በአስቸኳይ ይዞ ደህንነቱ የተጠበቀ ቦታ ለምሳሌ ቤት ውስጥ ካልተቻለም በአካባቢው ካለው አንጻራዊ ዝቅተኛ ቦታ ላይ መውሰድ ያስፈልጋል።
ደረጃ 2፦ ተጎጂውን ሁኔታ መገምገም እና እንደ ሁኔታው እርዳታ መስጠት
እዚህ ጋር ተጎጂው ያለበትን ሁኔታ አይቶ እርዳታውን እንደሚከተለው ማድረግ ተገቢ ነው ።
ሁኔታ ሀ፦ ራሱን ለሳተ እና መተንፈስ ለማይችል ሰው
ይህ ሁኔታ ተጎጂው የልብ ምት መቆም አጋጥሞታል ማለት ስለሆነ እጅግ አስቸኳይ እርዳታ ይፈልጋል።
ለእርዳታ ሌላ ሰው መጥራት ከተቻለ አምቡላስ መጥራት ጎን ለጎን የሚሰሩ ሆነው አብሮ ያለ ሰው ወዲያውኑ ተጎጅውን በጀርባው በማስተኛት በሁለቱ ጡቶች መካከል ላይ የእጅዎን መዳፍ በማድረግ፤ ሁለተኛውን እጅ በላዩ ላይ በማጣመር ክንድዎን ሳያጥፉ፣ የሰውነትዎን ክብደት በመጠቀም ደረቱን ወደ ታች ከ5-6 ሳንቲም ሜትር ጥልቀት በፍጥነት እና በኃይል መጫን ነው ።
ፍጥነት፦ በደቂቃ ከ100 እስከ 120 ጊዜ መጫን ። ይኼንንም እየተጋገዙ የሰውየው መተንፈስ እስኪመለስ ድረስ ወይም እስከ 30 ደቂቃ ድረስ መደጋገም ያስፈልጋል።
ይህን በትክክል ካደረግን ከ100 ሃያ ሰዎችን ወይም ከዚያ በላይ ማትረፍ ይቻላል።
እንደ አጋጣሚ ከመካከል ስልጠና የወሰደ ካለ ግን ደረትን ከመጫን በተጨማሪ ትንፋሽም መስጠት ያስፈልጋል (ለሰለጠኑ) ።
ሁኔታ ለ፦ ራሱን ለሳተ ነገር ግን በትክክል ለሚተነፍስ ሰው
ሰውየው ልቡ እየመታ እና እየተነፈሰ ከሆነ ነገር ግን ካልነቃ የሚከተሉትን ያድርጉ፦
A. ተጎጂውን በግራ ጎኑ ማስተኛት፣ የላይኛውን እግሩን አጥፎ ወደ ፊት ማድረግ እና እጁን ከጉንጩ ስር ማስደገፍ። ይህ አቀማመጥ ምላሱ ጉሮሮውን እንዳይዘጋው እና ቢተፋ እንኳ ትውከቱ ወደ ሳንባው ሳይሄድ ወደ ውጭ እንዲፈስ ያደርጋል።
B. የአየር መተላለፊያውን መከታተል፦ አፉ ውስጥ አፈር፣ ሳር ወይም ትውከት ካለ በንጹህ ጨርቅ በጥንቃቄ ማጽዳት::
C. ትንፋሹን መቆጣጠር፦ በየደቂቃው ደረቱ መነሳቱንና መውረዱን ማየት። ትንፋሹ ከቆመ ወዲያውኑ ከላይ ያየነውን ሁኔታ 'ሀ' ማድረግ ።
ሁኔታ ሐ :- የቃጠሎ ቁስሎችን በአደጋው የተፈጠረ የአጥንት ስብራት ካለ የሚደረጉ እርዳታወችን የሚተነትን ነው ይታወቃሉ።
የመጨረሻ ማሳሰቢያው መብረቅ የደረሰበት ሰው ምንም ጉዳት የሌለበት ቢመስልም፣ አልፎ ተርፎም ተነጋግሮ በገዛ እግሩ ቢሄድም እንኳ፣ በግዴታ ወደ ሆስፒታል መወሰድ አለበት።
ምንጪ: -
የአሜሪካ ቀይ መስቀል (American Red Cross) ፣
የአሜሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል (CDC) እና
የአሜሪካ የልብ ማኅበር (AHA - American Heart Association) ንን
ተጠቅመናል።
ሰዎች በአፈር ሲቀበሩ የሚያሳየው ፎቶ iloveafrica.com በሰራው ጥናታው ጽሑፍ ላይ የተገኘ ነው።
ክፍል አንድ
ስለመብረቅ እና ነጎድጓድ ልንወስዳቸው የሚገቡ እውነተኛ ጥንቃቄዎች! ⛈️
''በር ላይ አትቁም ወደ ውስጥ ግባ !'' ትለኝ ነበር እናቴ
እንደዛሬው ሳይንስ ገና ሳይራቀቅ እናቶቻችን ያውቁት የነበረውን እውነት ሳይንስ አስፍቶ እና አብራርቶ እንዲህ ይተነትነዋል ።
የአሁኑ ወቅት የክረምት ወቅት በመሆኑ የነጎድጓድና የመብረቅ አደጋዎች በብዛት የሚሰሙበት ጊዜ ነው። በተለይ የክረምት መግቢያ እና መውጫ በሆኑት ሰኔ እና መስከረም ላይ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ከሌሎች በተለየ ያዘዎትራል።
መብረቅ ተፈጥሯዊና በጣም ከፍተኛ ኃይል ያለው የኤሌክትሪክ ፍሳሽ በመሆኑ ራሳችንንና ቤተሰባችንን ለመጠበቅ ትክክለኛውን መረጃ ማወቅ ወሳኝ ነው።
በተለይ በገጠር አካባቢ የምንኖር ሰፊ ሜዳ ላይና ለእርሻ ሥራ ስለምንወጣ ለአደጋው የመጋለጥ ዕድላችን ከፍተኛ ነው።
በዚህም ምክንያት ምንም እንኳን የእግዚአብሔር ጥበቃ የሌለበት በጥበባችን እና በብስለት ብቻ የምናመልጠው ነገር ባይኖርም በእኛ በኩል መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች ማዎቃችን ግን በጣም አስፈላጊ ነው ።
፩. መደረግ ያለባቸው እውነተኛ ጥንቃቄዎች:-
ሀ. ወዲያውኑ ወደ መጠለያ መግባት : ነጎድጓድ ሲሰሙ "ገና መብረቁ አልመጣም" ብለው ከቤት ውጭ አይቆዩ። በአቅራቢያዎ ወደ ሚገኝ ቤት ወዲያውኑ መግባት ያስፈልጋል ። የቤቱ ክዳን የቆርቆሮ ካልሆነ መብረቅን ተከላክሎ ቻርጁን ወደ መሬት የመስደድ አቅም ስለሌለው ከተቻለ የጣራው ክዳን ቆርቆሮ ሆኖ ግድግዳዎቹም በቡሉኬት የተሰራ ቢሆን ይመረጣል ። ግድግዳው የእንጨት እና የጭቃ ከሆነም ጣራው በመብረቅ ሲመታ ቆርቆሮው ላይ ያረፈው ቻርጅ በግድግዳው በኩል አድርጎ ወደ መሬት ይገባል። አንዳንድ ጊዜ ግድግዳው እርጥበት ሲይዝ ሾልኮ የመግባት እና ተጠግተው በቆሙ ሰዎች ላይ ጉዳት የማድረስ እድል ይኖረዋል ፤ እንዲሁም የግድግዳው እንጨት በጣም የሰባ ከሆነ የመቀጣጠል እድል ሊኖረው ይችላል። እንደ አጠቃላይ ግን ጣራቸው ቆርቆሮ የለበሱ ቤቶች ውስጥ ወደ ግድግዳም ወደ በርም ሳይጠጉ መሃል መቀመጥ ይመከራል ።
ለ. ከረጅም ዛፎች ስር ፈጽሞ አይጠለሉ: መብረቅ ሁልጊዜም በአቅራቢያው ያለውን ረጅሙን ነገር ቀድሞ የመምታት ባህሪ አለው። በገጠርም ሆነ በከተማ ነጎድጓድ ሲኖር ረጅም ዛፍ ስር መቆም ለአደጋው በከፍተኛ ሁኔታ ያጋልጣል። ዛፍ ስር መጠለል የግድ ሆኖ ከተገኘም ብቻውን ከቆመ ዛፍ አለመጠለል ከብዙ ዛፎች መካከል ከአጭሩ ስር መሆን ይመከራል ።
ሐ. ከሜዳማ ቦታዎች መራቅ: ሰፊ የእርሻ ሜዳ ወይም ባዶ ቦታ ላይ ከሆኑ እርስዎ በአካባቢው ላይ ረጅሙ ነጥብ ስለሚሆኑ መብረቅ ሊስቡ ይችላሉ። ወዲያውኑ ወደ ዝቅተኛ ቦታ ይሂዱ ወይም ወደ መጠለያ ይሻገሩ።
መ. የውሃ አካላትን እና የብረት አጥሮችን ይራቁ:
በወንዝ፣ በኩሬ ወይም የዝናብ ውሃ በፈጠረው ጎርፍ ውስጥ ከሆኑ ወዲያውኑ ይውጡ። ውሃና ረጅም የብረት አጥሮች ኤሌክትሪክን በጣም በፍጥነት ይስባሉ።
ሠ. በቤት ውስጥ ሲሆኑ: በምግብ ማብሰያ (የኤሌክትሪክ ለምትጠቀሙ) ፣ በገላ መታጠቢያ ወይም በቧንቧ ውሃ አይጠቀሙ (መብረቅ የብረት ቧንቧዎችን ተከትሎ ሊገባ ይችላል)።
ረ. በኬብል (ገመድ) የተገናኙ ስልኮችን (የቤት ስልክ ወይም ለቻርች የተሰካ ተንቀሳቃሽ ስልክ) እና የኤሌክትሪክ ዕቃዎችን አይንኩ። ከቻሉ ከኤሌክትሪክ ጋር የተሰኩ እቃዎችን ይንቀሉ (እቃው ላይ ጉዳት እንዳይደርስ)
፪. ባያደርጓቸውም ምንም ችግር የሌላቸው ጉዳዮች
ማኅበረሰባችን ውስጥ መብረቅን ለመከላከል ተብለው የሚደረጉ ነገር ግን በሳይንሳዊ መንገድ ምንም ፋይዳ የሌላቸው፣ ባናደርጋቸውም ምንም ችግር የሌለባቸው በርካታ ልማዶች አሉ። እነሱንም ማወቅ አላስፈላጊ ጭንቀትን ይቀንሳል፡-
ሀ. መስተዋትን መሸፈን ወይም መድፋት: መስተዋት መብረቅን የመሳብ ኃይል የለውም። መስተዋት ስለተከፈተ መብረቅ አይመጣም፤ ስለተሸፈነም መብረቅ አይከላከልም። ስለዚህ መስተዋት ባይሸፍኑ ምንም ችግር የለውም።
ለ. በሞባይል ስልክ ማውራት (ገመድ አልባ): ሞባይል ስልክ ከግድግዳው ሶኬት ጋር በቻርጀር ካልተገናኘ በስተቀር፣ ዝም ብሎ በስልክ ማውራት መብረቅን አይስብም። መብረቅ የሚስበው የብረት ማማዎችን (ታወሮችን) እንጂ በእጅዎ የያዙትን ትንሽ ስልክ አይደለም።
ሐ. የሞባይ ዳታ ወይንም Wifi መጠቀም : ይኼም ምንም ችግር የለውም
በቀጣይ የመብረቅ አደጋ የደረሰበት ሰው የመጀመሪያ እርዳታ እንዴት እንሰጣለን በሚለው ዙሪያ እንወያያለን ።
በዚህ ዙሪያ ያጋጠመዎ ልምድ ካለ ወይንም ጥያቄ ካለዎ እንወያይበታለን ።
ከድንገተኛ ሞት ልዑል እግዚአብሔር ይጠብቀን።
ክፍል ሁለት
መብረቅ ለመታው ሰው ስለሚደረጉ እና ስለማይደረጉ ነገሮች :-
አይበለው እና ከእኛ ጋር ያለ ሰው የመብረቅ አደጋ ቢደርስበት ከአፈር ለመቅበር ወደ ጉድጓድ ቁፈራ ነው የምንሄደው ወይስ ምን እናድርግ፤ ብንነካው ቻርጁ ወደ እኛ ይተላለፋል ወይስ አይተላለፍም? የሚሉትና እና ሌሎች ጠቃሚ ሳይንሳዊ ምክሮችን እነኆ ።
፩. የባህላዊ ልማዶች ፍተሻ፦ የታሰበው እና ሳይንሳዊ እውነታው
ማንኛውም ሰው መጀመሪያ እርዳታ ከመጀመሩ በፊት የሚከተሉትን ጎጂ ልማዶች ማወቅ እና ማስወገድ አለበት፦
ሀ. መሬት ውስጥ መቅበር (እስከ አንገት/እስከ ደረት)
የሚታሰበው ፦ አፈሩ በሰውነት ውስጥ የተከማቸውን ኤሌክትሪክ ወደ መሬት ይስበዋል ተብሎ ይታመናል።
ሳይንሳዊ እውነታው፦ መብረቅ ሰውን መትቶ የሚያልፈው በሚሊሰከንዶች ውስጥ ስለሆነ ሰውነት ውስጥ የሚቀር የኤሌክትሪክ ክምችት የለም። አፈር መቆፈር እና ሰውን መቅበር ሌሎች ሕይወት አድን የሆኑ ስራወችን ለመሥራት የምንጠቀምበትን ወሳኝ የሆነውን ሰዓት (ወርቃማ ጊዜ) ያባክናል። በተጨማሪም አፈሩ ደረት ላይ የሚፈጥረው ጫና መተንፈስ ይከለክላል ፤ የሰውነት ሙቀትን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል ፤እንዲሁም በአደጋው ጊዜ በቃጠሎ ምክንያት የተፈጠሩ ቁስሎችን ለከፋ ኢንፌክሽን ያጋልጣል።
ሲጠቃለል መቅረቅ የመታውን ሰው ከአፈር መቅበር ምንም ዓይነት ጥቅም የለውም ።
ለ. ሌሎች የማይጠቅሙ እና ጎጂ ልማዶች :-
🎆ውሃ፣ ወተት ወይም ባህላዊ መድኃኒት በአፍ ማጠጣት፦ ራሱን የሳተ ሰው የመዋጥ አቅም ስለሌለው ፈሳሹ በቀጥታ ወደ ሳንባ በመሄድ ወዲያውኑ ሊያንቀው ወይም ሊገድለው ይችላል። ስለዚህ በማንኛውም ሁኔታ ንቁ ያልሆነ ሰው (ራሱን የሳተ) ምንም አይነት ፈሳሽ ለማጠጣት መሞከር አይመከርም።
🎆በቃጠሎ የተፈጠ ቁስል ላይ ቅቤ፣ ዘይት ወይም ሌላ ነገር መቀባት፦ የመብረቅ ቃጠሎ ከፍተኛ ውስጣዊ ሙቀት አለው። ቅቤ ወይም ዘይት መቀባት ሙቀቱ ወደ ውጭ እንዳይወጣ አፍኖ በመያዝ ቃጠሎውን ያባብሰዋል፤ ከባድ ባክቴሪያም ወደ ውስጥ ያስገባል።
🎆 አደጋው በደረሰበት ቦታ ላይ መቆየት፦ መብረቅ በአንድ በዝናብ ማዕበል ወቅት በአንድ ቦታ ላይ ከአንድ ጊዜ በላይ የመምታት ዕድሉ ከፍተኛ በመሆኑ፣ እዚያው ቦታ ላይ እርዳታ ለመስጠት መሞከር ረዳቱንም ጭምር ለአደጋ ያጋልጣል።
፪. መደረግ ያለባቸው የመጀመሪያ እርዳታዎች :-
የመጀመሪያ እርዳታ ሰጪው ሕክምና ባለሙያ ባይሆንም የሚከተሉትን እርምጃዎች ደረጃ በደረጃ መተግበር አለበት፦
ደረጃ 1 ፦ የቦታውን ደህንነት ማረጋገጥ
መብረቅ የደረሰበትን ሰው ወዲያውኑ በእጅ መንካት ምንም አይነት ችግር አያመጣም።
ነገር ግን ከላይ እንደጠቀስነው መብረቅ በአንድ በዝናብ ማዕበል ወቅት በአንድ ቦታ ላይ ከአንድ ጊዜ በላይ የመምታት ዕድሉ ከፍተኛ ነው። ስለሆነም ተጎጂውን በአስቸኳይ ይዞ ደህንነቱ የተጠበቀ ቦታ ለምሳሌ ቤት ውስጥ ካልተቻለም በአካባቢው ካለው አንጻራዊ ዝቅተኛ ቦታ ላይ መውሰድ ያስፈልጋል።
ደረጃ 2፦ ተጎጂውን ሁኔታ መገምገም እና እንደ ሁኔታው እርዳታ መስጠት
እዚህ ጋር ተጎጂው ያለበትን ሁኔታ አይቶ እርዳታውን እንደሚከተለው ማድረግ ተገቢ ነው ።
ሁኔታ ሀ፦ ራሱን ለሳተ እና መተንፈስ ለማይችል ሰው
ይህ ሁኔታ ተጎጂው የልብ ምት መቆም አጋጥሞታል ማለት ስለሆነ እጅግ አስቸኳይ እርዳታ ይፈልጋል።
ለእርዳታ ሌላ ሰው መጥራት ከተቻለ አምቡላስ መጥራት ጎን ለጎን የሚሰሩ ሆነው አብሮ ያለ ሰው ወዲያውኑ ተጎጅውን በጀርባው በማስተኛት በሁለቱ ጡቶች መካከል ላይ የእጅዎን መዳፍ በማድረግ፤ ሁለተኛውን እጅ በላዩ ላይ በማጣመር ክንድዎን ሳያጥፉ፣ የሰውነትዎን ክብደት በመጠቀም ደረቱን ወደ ታች ከ5-6 ሳንቲም ሜትር ጥልቀት በፍጥነት እና በኃይል መጫን ነው ።
ፍጥነት፦ በደቂቃ ከ100 እስከ 120 ጊዜ መጫን ። ይኼንንም እየተጋገዙ የሰውየው መተንፈስ እስኪመለስ ድረስ ወይም እስከ 30 ደቂቃ ድረስ መደጋገም ያስፈልጋል።
ይህን በትክክል ካደረግን ከ100 ሃያ ሰዎችን ወይም ከዚያ በላይ ማትረፍ ይቻላል።
እንደ አጋጣሚ ከመካከል ስልጠና የወሰደ ካለ ግን ደረትን ከመጫን በተጨማሪ ትንፋሽም መስጠት ያስፈልጋል (ለሰለጠኑ) ።
ሁኔታ ለ፦ ራሱን ለሳተ ነገር ግን በትክክል ለሚተነፍስ ሰው
ሰውየው ልቡ እየመታ እና እየተነፈሰ ከሆነ ነገር ግን ካልነቃ የሚከተሉትን ያድርጉ፦
A. ተጎጂውን በግራ ጎኑ ማስተኛት፣ የላይኛውን እግሩን አጥፎ ወደ ፊት ማድረግ እና እጁን ከጉንጩ ስር ማስደገፍ። ይህ አቀማመጥ ምላሱ ጉሮሮውን እንዳይዘጋው እና ቢተፋ እንኳ ትውከቱ ወደ ሳንባው ሳይሄድ ወደ ውጭ እንዲፈስ ያደርጋል።
B. የአየር መተላለፊያውን መከታተል፦ አፉ ውስጥ አፈር፣ ሳር ወይም ትውከት ካለ በንጹህ ጨርቅ በጥንቃቄ ማጽዳት::
C. ትንፋሹን መቆጣጠር፦ በየደቂቃው ደረቱ መነሳቱንና መውረዱን ማየት። ትንፋሹ ከቆመ ወዲያውኑ ከላይ ያየነውን ሁኔታ 'ሀ' ማድረግ ።
ሁኔታ ሐ :- የቃጠሎ ቁስሎችን በአደጋው የተፈጠረ የአጥንት ስብራት ካለ የሚደረጉ እርዳታወችን የሚተነትን ነው ይታወቃሉ።
የመጨረሻ ማሳሰቢያው መብረቅ የደረሰበት ሰው ምንም ጉዳት የሌለበት ቢመስልም፣ አልፎ ተርፎም ተነጋግሮ በገዛ እግሩ ቢሄድም እንኳ፣ በግዴታ ወደ ሆስፒታል መወሰድ አለበት።
ምንጪ: -
የአሜሪካ ቀይ መስቀል (American Red Cross) ፣
የአሜሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል (CDC) እና
የአሜሪካ የልብ ማኅበር (AHA - American Heart Association) ንን
ተጠቅመናል።
ሰዎች በአፈር ሲቀበሩ የሚያሳየው ፎቶ iloveafrica.com በሰራው ጥናታው ጽሑፍ ላይ የተገኘ ነው።
ማስታወቂያ ለግል የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች በሙሉ:-
ቀን 20/10/2018 ዓ.ም
የ2018 ዓ. ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የምትወስዱ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የግል(private)ተፈታኞች የፈተና መርሃግብራችሁ እንደሚከተለው ይሆናል።
#የአየርጤና እና የቀራንዮ መድኃኔዓለም አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህህርት ቤት የግል ተፈታኝ ተማሪወዎች
👉የመጀመሪያ ዙር
👉መፈተኛ ጣቢያ አብርሆት ቤተ-መጽሔት
#የሰጲ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የግል ተፈታኝ ተማሪዎች ደግሞ
👉ሁለተኛ ዙር
👉የመፈተኛ ጣቢያ አድዋ መታሰቢያ መሆኑን እናሳውቃለን።
ማሳሰቢያ:-
ለተፈታኞች የተከለከሉ
❌ ስልክ ይዞ መግባት አይቻልም
❌ ካልኩሌተር
❌ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን
❌ ሰዓት
❌ በሀኪም ከታዘዘ ውጪ የሆኑ መነጽሮች
❌ የሚነበቡ ጽሁፎች በሙሉ
