Ethiopian Educational Channel
Ir al canal en Telegram
እንኳን ደና መጣችሁ በዚህ ቻናል ላይ የሚያገኙት 1. ትምህርታዊ መረጃ መስጠት 2.የሳይኮሎጂ አስተማሪ ምክሮችንና አነቃቂ ንግግሮች 3.መፃህፍቶች በpdf እና የእንግሊዝኛ ትምህርት ይለቀቃሉ! በዚህ ቻናል ሀይማኖታዊ እና ፓለቲካ ነክ አይለቀቅበትም ! የቴሌግራሙ ቻናል ሊንክ:👉https://t.me/EEC1227 Channel created by @BA1227
Mostrar más6 808
Suscriptores
-324 horas
-187 días
-4330 días
Archivo de publicaciones
ማስታወቂያ ለግል የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች በሙሉ:-
ቀን 20/10/2018 ዓ.ም
የ2018 ዓ. ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የምትወስዱ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የግል(private)ተፈታኞች የፈተና መርሃግብራችሁ እንደሚከተለው ይሆናል።
#የአየርጤና እና የቀራንዮ መድኃኔዓለም አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህህርት ቤት የግል ተፈታኝ ተማሪወዎች
👉የመጀመሪያ ዙር
👉መፈተኛ ጣቢያ አብርሆት ቤተ-መጽሔት
#የሰጲ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የግል ተፈታኝ ተማሪዎች ደግሞ
👉ሁለተኛ ዙር
👉የመፈተኛ ጣቢያ አድዋ መታሰቢያ መሆኑን እናሳውቃለን።
ማሳሰቢያ:-
ለተፈታኞች የተከለከሉ
❌ ስልክ ይዞ መግባት አይቻልም
❌ ካልኩሌተር
❌ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን
❌ ሰዓት
❌ በሀኪም ከታዘዘ ውጪ የሆኑ መነጽሮች
❌ የሚነበቡ ጽሁፎች በሙሉ
Africa's Largest Countries by land area.
1. Algeria 🇩🇿
2. Democratic Republic of the Congo 🇨🇩
3. Sudan 🇸🇩
4. Libya 🇱🇾
5. Chad 🇹🇩
6. Niger 🇳🇪
7. Angola 🇦🇴
8. Mali 🇲🇱
9. South Africa 🇿🇦
10. Ethiopia 🇪🇹
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ፓስፖርት ለማሳደስ የምትፈልጉ ደንበኞቻችን የመደበኛ እና የአስቸኳይ ፓስፓርት እድሳት አገልግሎት ክፍያ ዋጋ
• መደበኛ 5,000 ብር
• አስቸኳይ የ2 ቀን 25,000 ብር
• አስቸኳይ የ5 ቀን 20,000 ብር ነዉ
ማሳሰቢያ፦
• ከዚህ ውጪ ክፍያ ከተጠየቁ በነፃ የስልክ ቁጥር 8133 በመደወል ወይም በተቋሙ የቅሬታ ማቅረቢያ "ICS Resolve" መተግበሪያ (App) ቅሬታ ማቅረብ፡ የገጠመዎትን ማንኛውንም የአገልግሎት ችግር በቀላሉ ሪፖርት ማድረግ የሚችሉ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን።
• ለየትኛዉም የፓስፖርት አገልግሎት በኦንላይን ለመመዝገብ ትክክክለኛው ዌብሳይት አድራሻችን www.immigration.gov.et መሆኑን እንገልፃለን።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
ሁሉም የሚታወቅባት ኢትዮጵያ !
የማስተርስ ትምህርት አራት አመት‼️
"የማስተርስ ትምህርት ወደ 4 ዓመት ሊያድግ ይገባል " ተባለ‼️
የአሰራር ለውጥ ካልተደረገ ወደፊት ለሚመረቁ ተማሪዎች እውቅና ለመስጠት ትልቅ ተግዳሮት ይፈጥራል ብሏል የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን
በኢትዮጵያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚሰጠው የሁለተኛ ዲግሪ (የማስተርስ) ትምህርት ፕሮግራም ከሁለት ዓመት ወደ አራት ዓመት ሊያድግ እንደሚገባ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ ይህንን ያስታወቀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት የ11 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሰጠው ሙያዊ ማብራሪያ፣ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ በሁለት ዓመት መደበኛ መርሃ ግብር እየተሰጠ ያለው የማስተርስ ትምህርት፣ አዲስ ከጸደቀው የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ደንብና ከአለም አቀፍ በተለይም ከአውሮፓ ስታንዳርድ ጋር የማይገናኝ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ ክፍተት በአስቸኳይ የማይስተካከል ከሆነ፣ ወደፊት ለሚመረቁ ተማሪዎች የትምህርት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ወይም እውቅና (Authentication) ለመስጠት ትልቅ ተግዳሮት እንደሚሆን ባለስልጣኑ አስገንዝቧል።
ከእነዚህም መካከል በሀገራችን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ሳያመጡ ወደ ውጭ ሀገር ሄደው ከተማሩ በኋላ፣ ወደ ሀገር ቤት ሲመለሱ የሚጠይቁት የብቃት ማረጋገጫ ጉዳይ ትልቅ አነጋጋሪ አጀንዳ ሆኗል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ2017 ዓ.ም ያጸደቀው የኢትዮጵያ የትምህርትና ስልጠና የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ደንብ፣ እውቅና ካላቸው የውጭ ሀገር የትምህርት ተቋማት የተገኙ የብቃት ማረጋገጫዎች በሀገሪቱ መመዘኛ መሰረት ተመዝነው እውቅና እንዲሰጣቸው ቢደነግግም፣ አሁን ያለው አሰራር ግን ይህንን ለመተግበር አስቸጋሪ አድርጎታል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እንዳመለከተው፣ ለአማራጭ የትምህርት ክሬዲት ስርአት (ECTS) በአውሮፓ (ከፍተኛ) የሆነው መስፈርት፣ በኢትዮጵያ ደንብ ውስጥ ' (ዝቅተኛ) ሆኖ ተቀምጧል። ይህንን ወደ ዓመት ሲተረጎም የማስተርስ ፕሮግራም ደንቡ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ የ4 ዓመት ፕሮግራም መሆን እንዳለበት ያስገድዳል።
ጉዳዩን በተመለከተ ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት እንዲሁም ለትምህርት ሚኒስቴር በደብዳቤ ቢገለጽም እስካሁን ምንም ምላሽ አልተገኘም ተብሏል፡፡
source:ethiofm
Xenderን ለፋይል ማስተላለፊያ ብቻ የሚጠቀሙ ከሆነ እነዚህን 4 ድብቅ ጥቅሞች አምልጠውዎታል!
ብዙዎቻችን Xenderን የምናውቀው ፎቶ እና ቪዲዮ ከስልክ ስልክ ለመላላክ ብቻ ነው። ነገር ግን ይህ መተግበሪያ ህይወታችንን የሚያቀሉ ሌሎች አስገራሚ ጥቅሞችን በአንድ ላይ ይዟል።
መተግበሪያው ውስጥ ተደብቀው የሚገኙትን 4 ዋና ዋና ጥቅሞች እነሆ👇
1️⃣ ቪዲዮን ወደ MP3 (ኦዲዮ) መቀየር
ጥቅሙ፡ የቪዲዮ ሙዚቃዎችን ወይም ንግግሮችን ወደ ኦዲዮ (Audio) ለመቀየር ሌላ ተጨማሪ መተግበሪያ መጫን አያስፈልግዎትም።
አጠቃቀም፡ Xender ውስጥ ገብተው ከታች "ToMP3" የሚለውን ይጫኑ ➡️ "Select Video" የሚለውን በመንካት ቪዲዮዎን ይምረጡ። በሰከንዶች ውስጥ ወደ MP3 ይቀየርልዎታል።
2️⃣ የማህበራዊ ሚዲያ ቪዲዮዎችን ማውረጃ (Downloader)
ጥቅሙ፡ ከፌስቡክ፣ ከኢንስታግራም ወይም ከቲክቶክ ቪዲዮዎችን በቀላሉ ማውረድ ይችላሉ።
አጠቃቀም፡ Xender ውስጥ ከታች "Social" የሚለውን ይጫኑ ➡️ ማውረድ የሚፈልጉትን የቪዲዮ ሊንክ (Link) ኮፒ አድርገው እዚህ ላይ ይለጥፉ (Paste ያድርጉ) ➡️ "Download" የሚለውን ይንኩ።
3️⃣ ያለ ኬብል ስልክን ከኮምፒውተር ጋር ማገናኘት
ጥቅሙ፡ ምንም አይነት የዩኤስቢ (USB) ኬብል ሳይጠቀሙ ፋይሎችን ከስልክ ወደ ላፕቶፕ/ኮምፒውተር በፍጥነት መጫን ያስችላል።
አጠቃቀም፡ Xender ላይ በቀኝ በኩል ያለውን ምልክት ነክተው "Connect to PC" ይምረጡ ➡️ የስልክዎን Hotspot አብርተው ኮምፒውተርዎን ያገናኙ ➡️ ኮምፒውተርዎ ብሮውዘር (Browser) ላይ ስልኩ ያሳየዎትን የድር አድራሻ (IP Address) ይተይቡ።
4️⃣ አዲስ ስልክ ሲገዙ ዳታ ማዛወሪያ (Phone Clone)
ጥቅሙ፡ አዲስ ስልክ ሲቀይሩ በድሮ ስልክዎ ላይ ያሉትን ስሞች (Contacts)፣ ፎቶዎች እና መተግበሪያዎች በአንድ ጊዜ ወደ አዲሱ ስልክ ያዛውራል።
አጠቃቀም፡ በሁለቱም ስልኮች Xender ላይ "Phone Clone" የሚለውን ይምረጡ ➡️ አንዱን "Old" ሌላኛውን "New" በማድረግ ያገናኙ እና ሁሉንም መረጃዎች በቀላሉ ያዛውሩ።
ወላጅ እናቱን የሚኒስትሪ ፈተናው ቀን በሞት ያጣው ተማሪ ኻሊድ የባንክ አካውንት ይፋ ሆኗል።
ተማሪ ኻሊድን መርዳት የምትፈልጉ የሲንቄ ባንክ እና የአዋሽ ባንክ አካውንት ተከፍቷል። ተማሪ ኻሊድ እድሜው 18 ስላልሞላውና ዘመድም ስለሌለው፤ ብቻውን ገንዘብ አውጥቶ መጠቀም ስለማይችል፣ አካውንቱ በአካባቢው መስጅድ ኡስታዝ፣ ከሀገር ሽማግሌ እና ከራሱ ጋር በጋራ በመሆን አካውንት ተከፍቶለታል።
①) ስንቄ ባንክ
11 14385901915
②) አዋሽ ባንክ
013201115433100
የምርጫ አስፈጻሚዎች ክፍያ መዘግየት ቅሬታና የቦርዱ ምላሽ !
የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ አስፈፃሚዎች የውል ክፍያቸው በወቅቱ ባለመከፈሉ ምክንያት ለከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና መዳረጋቸውን ገለጹ።
" የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በውል ስምምነቱ ላይ የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ አላከበረም " ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል።
እንደ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገለጻ፣ ከቦርዱ ጋር በተደረገው የስራ ውል መሠረት ለ54 የሥራ ቀናት በቀን 548 ብር ታስቦ በአጠቃላይ 29,592.00 ብር ሊከፈል ስምምነት ተደርጓል።
ይሁን እንጂ አጠቃላይ የምርጫ ሥራው ተጠናቆ የሥራ ማስፈጸሚያ ቁሳቁሶች በሰነድ በተረከቡ በ15 ቀናት ውስጥ መፈጸም የነበረበት የ60 በመቶ የመጨረሻ ክፍያ (17,755.20 ብር) እስካሁን ሊከፈላቸው አልቻለም።
ከዚህም በተጨማሪ የ14 ቀናት የሥራ ክፍያ 7,672 ብር እና የ4 ቀናት የስልጠና አበል 2,192 ብር በደብዳቤ ሊከፈላቸው ቃል ተገብቶ እንደነበር አስታውሰዋል።
አሁን ባለው የኑሮ ውድነት ወቅት የክፍያው መዘግየት የዕለት ተዕለት ሕይወታቸውን ከማናጋቱም በላይ፣ ለተከናወነው ከፍተኛ አገራዊ ሥራ የሚገባውን ሙያዊ ክብር የሚያሳጣ መሆኑን አስፈፃሚዎቹ ጠቁመዋል።
ስለሆነም፣ ምርጫ ቦርድ የገባውን የውል ስምምነት በማክበር፣ የተዘገየውን አጠቃላይ ክፍያ በሰነድ ላይ በተጠቀሰው የባንክ ሒሳብ ቁጥራቸው መሠረት በአስቸኳይ ገቢ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።
ምን ምላሽ ተሰጠ ?
ትላንት በነበረው መግለጫ ወቅት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህንኑ የአስፈጻሚዎች ቅሬታ ለቦርዱ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉም በጉዳዩ ላይ ምላሽ ሰጥተዋል።
ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ ምን አሉ ?
" ከምርጫ አስፈጻሚዎች ጋር በነበረው ውል መሰረት የመጀመሪያውን 40% ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ከፍሏል። ይህንን ለመክፈል ትልቅ ችግር ገጥሞን የነበረው በሶማሌ ክልል እና አፋር ክልል ነው።
አስፈጻሚዎቻችን አስፈጻሚዎቻችን የባንክ አካውንት ስላልነበራቸው የምርጫ ቦርድ ሰራተኞች በቦታው ተገኝተው ገንዘብ በካሽ አውጥተው መክፈል ነበረባቸው ይህንን አድርገዋል፤ የክፍያ ሂደቱን አጠናቀዋል።
ቀሪ 60 በመቶው የሚከፈለው የምርጫ አስፈጻሚዎች ከቦርዱ የተቀበሉትን ንብረት ለቦርዱ ሙሉ ለሙሉ አስረክበው ሲጨርሱ የሚከፈል ይሆናል። ይህንን የማጥራት ሂደት ጀምረናል።
ምንም አይነት የቦርዱ ንብረት በእጃቸው የሌለ አስፈጻሚዎች መክፈል ጀምረናል። ከእነሱ ጋር ያለው ንብረት ተጠናቆ ሲገባ ከሥር ከሥር ክፍያው ይፈጸማል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
የመጨረሻ የምርጫ ውጤት ይፋ ሆነ!!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት ብልጽግና ፓርቲ 438 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎችን በማሸነፍ በፓርላማው ውስጥ አብላጫውን ይዞ መቀጠሉ ተረጋግጧል።
ውጤቱን ይፋ ያደረጉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ ሲሆኑ፣ የምርጫ ውጤት ማሳወቂያ ሥነ-ሥርዓቱ በፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በሲቪክ ማህበራት፣ በውጭ ሀገራት አምባሳደሮች እና በመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች በተገኙበት ተካሂዷል።
ጠቅላላ ምርጫው በ1,139 የምርጫ ክልሎች የተካሄደ ሲሆን፣ 501 የፌዴራል ፓርላማ መቀመጫዎችን እና 638 የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎችን አካትቷል።
ዋና ዋና ውጤቶች
• ብልጽግና ፓርቲ – 438 መቀመጫዎች
• ተቃዋሚ ፓርቲዎች – 41 መቀመጫዎች
• የግል ዕጩዎች – 8 መቀመጫዎች
🗳️ ከምርጫው ሂደት ግምገማ እስከ ድጋሚ ቆጠራና ምርጫ ውሳኔዎች፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ መግለጫ
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ነዋይ የምርጫውን አጠቃላይ አፈፃፀም፣ የታዩ ጠንካራ ጎኖችን፣ ያጋጠሙ ፈተናዎችን እና ድጋሚ ቆጠራና ምርጫ የሚደረግባቸውን ክልሎች አስመልክቶ ዝርዝር መግለጫ ሰጥተዋል። ዋና ዋና ነጥቦቹ የሚከተሉት ናቸው፦
📊 የምርጫው ቁጥራዊ መረጃዎች በአጭሩ፦
ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች እና 80 የግል እጩዎች።
መራጭና አስፈፃሚ፦ 54 ሚሊየን 57 ሺ 861 መራጮች፣ 350 ሺ ምርጫ አስፈፃሚዎች እና 260 ሺ የፓርቲ ወኪል ታዛቢዎች።
ልዩ ተሳትፎ፦ 126 ሺ ወታደሮች፣ ከ28 ሺ በላይ ተፈናቃዮች እና ከ20 ሺ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የምርጫው አካል ነበሩ።
ሚዲያና ጋዜጠኞች፦ 73 መገናኛ ብዙሃን (1,827 የአገር ውስጥና 45 የውጪ ጋዜጠኞች) ዘግበውታል። 19 የክርክር መድረኮችም ተካሂደዋል።
🤝 የሲቪክ ማህበራትና የውጪ ታዛቢዎች ሚና፦
169 አገር በቀል ማህበራት የመራጮች ሲቪክ ትምህርት ፈቃድ ያገኙ ሲሆን፣ 114ቱ ከቦርዱ የገንዘብ ድጋፍ አግኝተዋል።
55 ማህበራት ከ64 ሺ በላይ ታዛቢዎችን በማሳተፍ ድምፅ አሰጣጡን ታዝበዋል።
ከውጪ፡ 63 ከአፍሪካ ህብረት፣ 26 ከኢጋድ፣ 21 ሚሲዮኖች እና 1 የውጪ ምርጫ አስፈፃሚ በታዛቢነት ተሳትፈዋል።
⚠️ ያጋጠሙ ዋና ዋና ፈተናዎችና የህግ እርምጃዎች፦
የቴክኖሎጂ ክፍተት፦ በፓርቲዎች ዘንድ የዲጂታል ምዝገባ ስርዓቱን የመረዳት ክፍተት የታየ ሲሆን፣ ቦርዱ አድሚኖችን በራሱ ወጪ በመቅጠር ደግፏል። በ22 ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች የመረጃ ፍሰት አስቸጋሪነትና የመሰረተ ልማት እጥረት ኦፕሬሽኑን ፈትኖታል።
የአስፈፃሚዎች ገለልተኝነትና ጣልቃ ገብነት፦ የፓርቲ ወኪሎችን መከልከል፣ በአስፈፃሚዎች ላይ መደለያ ማቅረብ እና አንዳንድ ዝቅተኛ የመንግስት አስተዳደር እርከን ላይ ያሉ አካላት በቦርዱ ስራ ውስጥ የመግባት ችግሮች ተስተውለዋል።
ህጋዊ ተጠያቂነት፦ በህግ ጥሰት የተሳተፉ የአስተዳደር አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ የህግ ሂደት ላይ ናቸው። በ129 የምርጫ ክልሎች የቀረቡ አቤቱታዎችን ምክንያት በማድረግ ቦርዱ የድጋሚ ቆጠራና ምርጫ ውሳኔ አሳልፏል።
የመራጮች ብዛት፦ በህጉ መሰረት በአንድ ጣቢያ ከ1,500 መራጭ መብለጥ ባይኖርበትም፣ ከዛ በላይ የተመዘገበባቸውና የሰልፍ መራዘም የታየባቸው ጣቢያዎች ነበሩ።
🚨 ድጋሚ ቆጠራ እና ድጋሚ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎች ይፋ ሆኑ!
🔄 የድምፅ አቆጣጠር በድጋሚ የሚካሄድባቸው የምርጫ ክልሎች፦
በደቡብ ኢትዮጵያ፦ ብርብር፣ ገረሴ እና ዳሞት ወይዴ
በሲዳማ ክልል፦ ገረሰላም እና ጨኮ
በኦሮሚያ ክልል፦ ወልመራ፣ ክብረ መንግስት እና አሊቦ
በሱማሌ ክልል፦ ቀላፎ እና ሀርሺ
በአፋር ክልል፦ አሚባራ
በሀላባ፦ የሀላባ 1 ምርጫ ክልል (ለክልል ምክር ቤት)
🗳️ ድጋሚ ምርጫ (በአዲስ መልክ) የሚካሄድባቸው የምርጫ ክልሎች፦
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፦ ሶሮ 1 እና ጠንባሮ
በሱማሌ ክልል፦ ሀርገሌ፣ ዳሮ፣ ሀዲጋላ፣ ሀዋሌ እና ዳራቶሌ
ሌሎች አካባቢዎች፦ ባቱ ዝዋይ፣ ቤጊ፣ አሮሬሳ እና ጨንቻ የምርጫ ክልሎች።
#ምርጫ2018 #NEBE #EthiopianElection
አጠቃላይ የምርጫ ውጤት (ፓርላማ)
1. አዲስ አበባ ከተማ (23 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልጽግና ፓርቲ 20 መቀመጫዎች
- ኢዜማ 2 መቀመጫዎች
- የግል ዕጩ 1 መቀመጫ
2. አፋር ክልል (8 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልጽግና ፓርቲ 7 መቀመጫዎች
- የአፋር ህዝብ ፓርቲ 1 መቀመጫ
3. አማራ ክልል (ምርጫ የተካሄደባቸው 130 የፓርላማ መቀመጫዎች )
- ብልጽግና 117 መቀመጫዎች
- አብን 6 መቀመጫዎች
- አዲህን 3 መቀመጫዎች
- አርጎባ አንድነት ጀበርቲ ፓርቲ 1 መቀመጫ
- ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 1 መቀመጫ
- ኢዜማ 1 መቀመጫ
- ነጻነትና እኩልነት 1 መቀመጫ
4. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ (9 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልጽግና ፓርቲ 8 መቀመጫዎች
- ጉሙዝ ብሔራዊ ንቅናቄ 1 መቀመጫ
5. ድሬዳዋ (2 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልጽግና ፓርቲ 2 መቀመጫዎች
6. ጋምቤላ ክልል (3 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልጽግና ፓርቲ 3 መቀመጫዎች
7. ኦሮሚያ ክልል (ምርጫ ውጤት ይፋ ከተገለጸበት 173 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልጽግና 167 መቀመጫዎች
- 5 የግል ዕጩዎች 5 መቀመጫዎች
- አዲስ ትውልድ ፓርቲ 1 መቀመጫ
8. ሐረሪ ክልል (2 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልጽግና ፓርቲ 2 መቀመጫዎች
9. ሲዳማ ክልል (ምርጫ ውጤት ይፋ ከተገለጸበት 16 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልጽግና ፓርቲ 13 መቀመጫዎች አሸንፏል
- መድረክ 3 መቀመጫዎች
10. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ (20 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልጽግና ፓርቲ 17 መቀመጫዎች
- ኢዜማ 1 መቀመጫ
- ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 1 መቀመጫ
- ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 1መቀመጫ
11. ደቡብ ኢትዮጵያ (ምርጫ ውጤት ይፋ ከተገለጸበት 45 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልጽግና ፓርቲ 35 መቀመጫዎች
- ኢዜማ 7 መቀመጫዎች
- የጌድዮ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 1 መቀመጫ
- የወላይታ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ 1 መቀመጫ
- የግል እጩ 1 መቀመጫ
12. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ (ምርጫ ውጤት ይፋ ከተገለጸበት 33 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልጽግና ፓርቲ 28 መቀመጫዎች
- ኢዜማ 2 መቀመጫዎች
- የግል ዕጩ 1 መቀመጫ
- ትብብር ለኢትዮጵያ 1 መቀመጫ
- ነጻነትና እኩልነት 1 መቀመጫ
13. ሶማሌ ክልል (22 የፓርላማ መቀመጫዎች)
- ብልፅግና ፓርቲ 19 መቀመጫዎች
- የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር 1 መቀመጫ
- ሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ 1 መቀመጫ
- ህብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት ፓርቲ 1 መቀመጫ
ማስታወሻ ፦በትግራይ ክልል በ38 የፓርላማ መቀመጫዎች ምርጫ አለመከናወኑ ይታወቃል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጉልህ የሆነ የምርጫ ሕግ ጥሰት መፈጸሙን ባረጋገጠባቸው የምርጫ ክልሎች ላይ ድጋሚ ምርጫ እንዲካሄድ ውስኗል።
በዚህም ቦርዱ በ5 ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ በሚደረግባቸውና በ8 ለክልል ምክር ቤት ምርጫ በሚደረግባቸው ምርጫ ክልሎች ድጋሜ ምርጫ ይካሄድባቸዋል ተብሏል።
ድጋሜ ምርጫ የሚካሄድባቸው ምርጫ ክልሎች የትኞቹ ናቸው ?
ሶሮ 1 — ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣
ጠምባሮ ምርጫ ክልል — ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤
ሀርገሌ ምርጫ ክልል — ሶማሌ ክልል ለክልል ምክር ቤት ምርጫ፣
ዳሎል ምርጫ ክልል — ሶማሌ ክልል ለክልል ምክር ቤት ምርጫ፣
ሀዲጋላ ምርጫ ክልል — ሶማሌ ክልል ለክልል ምክር ቤት ምርጫ፣
አዋሬ ምርጫ ክልል — ሶማሌ ክልል ለክልል ምክር ቤት ምርጫ፣
ዳራቶሌ ምርጫ ክልል — ሶማሌ ክልል ለክልል ምክር ቤት ምርጫ፣
ባቱ ዙሪያ ምርጫ ክልል — ኦሮሚያ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤት ምርጫ፣
ቤጊ ምርጫ ክልል — ኦሮሚያ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለክልል ምክር ቤት፣
አሮሬሳ ምርጫ ክልል — ሲዳማ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ፣
ጨንቻ ምርጫ ክልል — ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፥ ለክልል ምክር ቤት ምርጫ፤ ድጋሚ ምርጫ የሚካሄድባቸው የምርጫ ክልሎች ናቸው ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
#ምርጫ2018 : ብልፅግና ፓርቲ ዛሬ ይፋ በተደረገው ውጤት 438 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) መቀመጫዎችን አግኝቷል።
ፓርቲው ያሸነፈው ከፍተኛ የፓርላማ መቀመጫ ቁጥር መንግሥት መመስረት የሚያስችለው ነው።
በሌላ በኩል ፦
- የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) 👉 13 መቀመጫዎች
- የግል ዕጩዎች 👉 8 መቀመጫዎች
- አማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) 👉 6 መቀመጫዎች
- የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) 👉 3 መቀመጫዎች
- የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ 👉 3 መቀመጫዎች
- ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች
- ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ 👉 2 መቀመጫዎች
- የአፋር ህዝብ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- አርጎባ አንድነት ጀርበቲ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- ጉሙዝ ብሔራዊ ንቅናቄ 👉 1 መቀመጫ
- አዲስ ትውልድ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 👉 1 መቀመጫ
- የጌዴኦ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- የወላይታ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ 👉 1 መቀመጫ
- የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር 👉 1 መቀመጫ
- ህብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- ሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ ... አግኝተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
- ብልፅግና ፓርቲ 👉 32 መቀመጫ
- የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- የግል እጩ 1 መቀመጫ
- የሀረሪ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
#ምርጫ2018
የክልል ምክር ቤቶች ውጤት
1. አዲስ አበባ (ክልሉ ያለው መቀመጫ ብዛት - 158)
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 10
- ብልፅግና 👉 134 መቀመጫዎች
- ኢዜማ 👉 8 መቀመጫዎች
- አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 4 መቀመጫዎች
- ህዳሴ ፓርቲ 👉 2 መቀመጫዎች
- ኦነግ ፓርቲ 👉 2 መቀመጫዎች
- ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 👉 2 መቀመጫዎች
- ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 👉 2 መቀመጫዎች
- የወላይታ ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ 👉 1 መቀመጫ
- የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) 👉 1 መቀመጫ
- የወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- የግል እጩ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል።
2. አፋር (ዛሬ ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 135 መቀመጫዎች)
ምርጫ ውጤታቸው ይፋ የተደረገ የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 31
- ብልፅግና ፓርቲ 👉 124 መቀመጫ
- የአፋር ነፃ አውጪ ግንባር ፓርቲ 👉 4 መቀመጫ
- የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) 👉 3 መቀመጫዎች
- የአፋር ህዝብ ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች
- የአርጎባ አንድነት ጀበርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል።
ድጋሚ ቆጠራ የሚከናወንበት ምርጫ ክልል ብዛት - 1
3. አማራ (ዛሬ ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 277 መቀመጫዎች)
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 129
- ብልፅግና ፓርቲ 👉 257 መቀመጫዎች
- የአማራ ዲሞክራሲ ሃይል ንቅናቄ 👉 4 መቀመጫዎች
- ኢዜማ 👉 3 መቀመጫዎች
- አብን 👉 2 መቀመጫዎች
- አርጎባ አንድነት ጀበርቲ 👉 1 መቀመጫ
- የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- የቅማንት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 👉 1 መቀመጫ
- ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 👉 1 መቀመጫ
- የወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- ነጻነትና እኩልነት 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል።
#ማስታወሻ ፦ 4 መቀመጫዎች በንባብ በተሰማው ሪፓርት አልተካተተም።
ምርጫ ያልተካሄደባቸው የምርጫ ክልል ብዛት - 8
4. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 165 መቀመጫዎች)
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 20
- ብልፅግና 👉 145 መቀመጫዎች
- የጉሙዝ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ 👉 14 መቀመጫዎች
- የቤንሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ 👉 5 መቀመጫዎች
- የግል እጩ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል።
5. ድሬዳዋ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 189 መቀመጫዎች )
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 47
- ብልፅግና ፓርቲ 👉 161 መቀመጫዎች
- ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 8 መቀመጫዎች
- ኢዜማ ፓርቲ 👉 6 መቀመጫዎች
- አዲስ ትውልድ 👉 3 መቀመጫዎች አሸንፈዋል።
#ማስታወሻ ፦ 11 መቀመጫዎች በንባብ በተሰማው ሪፓርት አልተካተተም።
6. ጋምቤላ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 205 መቀመጫዎች)
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 14
- ብልፅግና 👉 176 መቀመጫዎች
- ሰላም ለኢትዮጵያ 👉 17 መቀመጫዎች
- ኢዜማ ፓርቲ 👉 6 መቀመጫዎች
- ህዳሴ ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች አሸንፈዋል።
#ማስታወሻ ፦ 3 መቀመጫዎች በንባብ በተሰማው ሪፓርት አልተካተተም።
7. ኦሮሚያ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 528 መቀመጫዎች)
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 173
- ብልፅግና 👉 523 መቀመጫዎች
- የግል እጩዎች 👉 4 መቀመጫዎች
- ኢዜማ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል።
#ማስታወሻ ፦ በኦሮሚያ ክልል ካሉ 179 የምርጫ ክልል ምርጫው የተካሄደው 173 መሆኑን በሪፓርቱ ተገልጿል።
ለክልል ምክር ቤት ድጋሚ ቆጠራ የሚካሄድበት ምርጫ ክልል ብዛት = 1
ለክልል ምክር ቤት ድጋሜ ምርጫ የተወሰነበት = 2
8. ሲዳማ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 190 መቀመጫዎች)
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 19
- ብልፅግና ፓርቲ 👉 175 መቀመጫዎች
- መድረክ 8 መቀመጫዎች
- የሲዳማ አንድነት ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች
- የሲዳማ ህዝብ አንድነት ዲሞክራሲያዊ ድርጅት 👉 1 መቀመጫ
- ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ 👉 1 መቀመጫ
- የኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ህብረት 👉 1 መቀመጫ
- የመላው ሲዳማ ህዝብ ደሚሞክራሲ አንድነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል።
9. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 171 መቀመጫዎች)
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 22
- ብልፅግና 👉 144 መቀመጫዎች
- ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 👉 12 መቀመጫዎች
- ኢዜማ ፓርቲ 10 መቀመጫዎች፤
- ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች
- ወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል።
#ማስታወሻ ፦ 1 መቀመጫ በንባብ በተሰማው ሪፓርት አልተካተተም።
10. ደቡብ ኢትዮጵያ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 224 መቀመጫዎች)
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 55
- ብልፅግና 👉 182 መቀመጫዎች
- ኢዜማ 👉 27 መቀመጫዎች
- የወላይታ ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ 👉 3 መቀመጫዎች
- ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 2 መቀመጫዎች
- የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ 👉 2 መቀመጫዎች
- ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 👉 2 መቀመጫዎች
- ጌዲዮ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት 👉 2 መቀመጫ
- የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ 👉 2 መቀመጫ
- የግል እጩ 👉 1 መቀመጫ
- የኩሽ ህዝቦች ብሔራዊ ንቅናቄ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል።
ለክልል ምክር ቤት ድጋሚ ቆጠራ የሚካሄድበት ምርጫ ክልል ብዛት = 1
11. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 170 መቀመጫዎች)
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 34
- ብልፅግና ፓርቲ 👉 143 መቀመጫዎች
- ኢዜማ ፓርቲ 👉 12 መቀመጫዎች
- ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 7 መቀመጫዎች
- ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 👉 3 መቀመጫዎች
- ጎጎት ለጉራጌ አንድነትና ፍትህ ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች
- ወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- የወለኔ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል።
12. ሶማሌ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 252 መቀመጫዎች)
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 66
- ብልፅግና ፓርቲ 👉 214 መቀመጫ
- የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር (ONLF) 👉 20 መቀመጫ
- ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 13 መቀመጫ
- የሱማሌ ፌደራሊስት ፓርቲ 👉 2 መቀመጫ
- የግል እጩ 👉 1 መቀመጫ
- የምዕራብ ሶማሌ ዲሞክራቲክ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- ህብረት ለዲሞክራሲ ለነጻነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል።
#ማስታወሻ ፦ ለክልል ምክር ቤት ድጋሚ ቆጠራ የሚካሄድበት ምርጫ ክልል ብዛት = 5
13. ሐረሪ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 36 መቀመጫዎች)
ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 3
FAQ
ስለ CGPA እና GPA አሰራር ማብራሪያ
ብዙዎች እንደሚሳሳቱት፣ Cumulative GPA (CGPA) ማለት የ-1st Semester እና የ-2nd Semester Gpaን ደምሮ ለሁለት ማካፈል ማለት አይደለም።❌
የትኛውም የGPA ስሌት የሚሰራው ተማሪው በወሰዳቸው አጠቃላይ Credit Hours ብዛት ላይ ተመስርቶ ነው።
📚 የሴሚስተር GPA አሰራር
የአንድን ተማሪ የሴሚስተር ውጤት (GPA) ለማስላት፣ እያንዳንዱ ትምህርት ያለው የ Credit Hour በዛው ትምህርት የመጣው Grade Point ይባዛል። ከዚያም የሁሉም ትምህርቶች ውጤት በአንድ ላይ ተደምሮ፣ በሴሚስተሩ ለተወሰዱት አጠቃላይ የ Credit Hour ድምር ይካፈላል።
ምሳሌ፦ አንድ ተማሪ በሴሚስተሩ 3 ትምህርቶችን ቢወስድ፡
1ኛ ትምህርት፦ Grade A (4.0) እና Credit Hour 5 ቢሆን ➔ 4.0 x 5 = 20
2ኛ ትምህርት፦ Grade A- (3.75) እና Credit Hour 5 ቢሆን ➔ 3.75 x 5 = 18.75
3ኛ ትምህርት፦ Grade B (3.0) እና Credit Hour 3 ቢሆን ➔ 3.0 x 3 = 9
የተማሪውን GPA ለማግኘት፦
የውጤቶች አጠቃላይ ድምር፦ 20 + 18.75 + 9 = 47.75
የአጠቃላይ Credit Hour ድምር፦ 5 + 5 + 3 = 13
በመጨረሻም፣ የውጤቱን ድምር ለአጠቃላይ ክሬዲት ሰዓቱ ስናካፍለው የሴሚስተሩን GPA እናገኛለን፦
47.75 ÷ 13 = 3.67
ስለዚህ፣ ይህ ተማሪ በሴሚስተሩ 3.67 GPA አመጣ ይባላል።
CGPA ሲሰላም በተመሳሳይ መንገድ የሁሉንም ሴሚስተሮች(የሁሉንም ኮርሶች) አጠቃላይ የውጤት ድምር ለአጠቃላይ የክሬዲት ሰዓት ድምር በማካፈል ነው የሚገኘው።
📌 የ CGPA አሰራር ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ፦
ለምሳሌ የአንድን ተማሪ የሁለት ሴሚስተር የCGPA ውጤት ለማስላት፦
• 1st Semester ላይ፦
የውጤት ድምር = 47.75
የ Credit Hour ድምር = 13
(GPA = 3.67)
• 2nd Semester ላይ፦
የውጤት ድምር = 52.00
የCredit Hour ድምር = 15
(GPA = 3.46)
❌ የተሳሳተው አሰራር፦
የሁለቱን ሴሚስተር GPA ደምሮ ለሁለት ማካፈል (3.67 + 3.46) ÷ 2 = 3.56 (ይህ ስህተት ነው!) የምትወስዱት ኮርስ በጨመረ ቁጥር የተሳሳተ Result ነው የምታገኙት
ትክክለኛው አሰራር (CGPA)፦
የሁለቱንም ሴሚስተር አጠቃላይ የውጤት ድምር ለአጠቃላይ የክሬዲት ሰዓት ድምር ማካፈል፦
• አጠቃላይ የውጤት ድምር፦ 47.75 + 52.00 = 99.75
• አጠቃላይ የCredit Hour ድምር፦ 13 + 15 = 28
ስለዚህ CGPA = 99.75 ÷ 28 = 3.562 (ወደ ሁለት Digit ሲጠጋ 3.56 ይሆናል።)
ውጤቱ ተመሳሳይ ሊሆን የቻለው የሁለቱ ሴሚስተሮች የክሬዲት hr በጣም ስለሚቀራረብ ብቻ ነው፤ የምትወስዷቸው ኮርሶች በበዙ ቁጥር የ ሁለቱ አሰራር ልዩነት ይፈጥራል።
share it your friends
#ልጄ_ሆይ ..... #ሰው_ሁን !
“የዚህች ዓለም ትልቁ ስኬት በሀብት መክበር፣ በዕውቀት መላቅ ወይም በሥልጣን መግነን አይደለም። ትልቁና ከባዱ ስኬት ‘ሰው መሆን’ ነው።”
መኖርና ሰው መሆን ይለያያሉ። መኖር ተፈጥሯዊ ስጦታ ነው፤ ሰው መሆን ግን በየቀኑ የሚገነባ የጥበብና የሥነ-ምግባር ማማ ነው።
ልጄ ሆይ፥ እነዚህን የሕይወት የወርቅ ምክሮች በልብህ ሰሌዳ ላይ ጻፋቸው፦
#ልብህ_ለሌሎች_ይምታ !
የሰው ልጅ እውነተኛ መለኪያው የኪሱ ስፋት ሳይሆን የልቡ ርኅራኄ ነው። ስትችል በምታገኘው አጋጣሚ ሁሉ ደግነትን ዝራ።
መርዳት ማለት ቁሳቁስ ማካፈል ብቻ አይደለም፤ ከሰዎች ጋር አብሮ ማልቀስና አብሮ መደሰትም ጭምር ነው።
#በቃልህ_ታመን !
ክብረ ወሰንህና ማንነትህ የሚለካው በምትናገረው ቃል ነው።
የምትሰጠው ተስፋ ከምድር በታች የተቀበረ ጽኑ መሠረት ይሁን። ቃልን ማክበር ለራስ የሚሰጥ ታላቅ ክብር ነው።
#በትሕትና_ከፍ_በል !
ዕውቀትህና ሀብትህ ሲጨምር ትሕትናህም አብሮ ይጨምር። በትዕቢት የምታገኘው ክብር ጊዜያዊ ነው፤ በትሕትና የምታገኘው ፍቅር ግን ዘላለማዊ ነው።
ጎንበስ ማለት መሸነፍ ሳይሆን ሰውን ማክበር ነው።
!
ሕይወት ሁልጊዜ አልጋ በአልጋ አትሆንም። ማዕበል ሲነሳ የሚወድቅ ሳይሆን፣ ሥሩ ወደ መሬት ጠልቆ የገባ ጽኑ ዛፍ ሁን።
ውድቀት የሕይወት ማቆሚያ ሳይሆን፣ ይበልጥ ጠንክሮ የመነሻ አዲስ ምዕራፍ ነው።
!
ሰዎች ክፉ ስላደረጉብህ አንተም ክፉ አትሁን፤ ያኔማ በክፋታቸው ተሸነፍክ ማለት ነው።
አንተ ግን በውስጥህ ያለውን ሰብዓዊነት ሁልጊዜ በመልካምነትህ አስመስክር።
ልጄ ሆይ! ዕድሜህ ሲጨምር ዓለም ብዙ ስሞችን፣ ማዕረጎችንና ዝናዎችን ትሰጥህ ይሆናል።
ያኔ ግን ሁሉንም ማዕረጎች አውልቀህ ስትመረመር ከውስጥህ “እውነተኛ ሰው” ይገኝ። ሰው መሆንህን ስታረጋግጥ የሕይወትን እውነተኛ ትርጉም አገኘህ ማለት ነው።
+1
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል።
ሰኔ 13/2018 ዓ.ም
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።
በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞ በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል።
ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል።
@አ/አ ት/ቢሮ
በፈተና ዋዜማ ተማሪዎች አእምሮን ለማዝናናት በቂ እንቅልፍ መተኛት፣ የተዘጋጁ ማጠቃለያዎችን ብቻ በአጭሩ መገምገም፣ የፈተና መገልገያ ቁሳቁሶችን ማዘጋጀት፣ ጤናማ ምግብ መመገብ እና አላስፈላጊ ጭንቀትን ማስወገድ አለባቸው።በፈተና ዋዜማ እና የፈተና ጊዜ ስኬትን ለማረጋገጥ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች ተግባራዊ ማድረግ ይገባል በቂ እረፍት ማድረግ፡ አእምሮን ለማነቃቃት እና ጭንቀትን ለመቀነስ ቢያንስ ከ 7 እስከ 8 ሰዓታት የሚሆን ጥልቅ እንቅልፍ መተኛት ያስፈልጋል። የፈተና ቁሳቁስ ማሟላት፡ እስክሪብቶ፣ እርሳስ፣ ማጥፊያ፣ መለያ (ID) እና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶች አስቀድመው በቦርሳ መዘጋጀት አለባቸው። አጭር ግምገማ ብቻ ማድረግ፡ አዳዲስ ርእሶችን ለማንበብ ከመሞከር ይልቅ ቀደም ሲል የተሰሩ ማጠቃለያዎችን እና ዋና ዋና ነጥቦችን ብቻ ማየት ይበጃል። ትክክለኛ አመጋገብ፡ አእምሮ በተገቢው መንገድ እንዲሠራ ቀላል፣ ሰውነትን የሚያነቃቁ እና ጤናማ ምግቦችን መመገብ ይገባል። ስሜትን መቆጣጠር፡ የፈተና ፍርሃትን እና ጭንቀትን ለመቀነስ ከመጠን በላይ ከማሰብ መቆጠብ፣ አዎንታዊ አስተሳሰብ መያዝ እና ዘና ማለት ያስፈልጋል። የፈተና ቦታን ማወቅ፡ የፈተናው ቦታ ሩቅ ከሆነ አስቀድሞ መንገድን በመለየት ሰዓት አክብሮ ለመገኘት እቅድ መያዝ ወሳኝ ጉዳይ ነው ተማሪዎች ሆይ እንወዳቹሀለን
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
