ch
Feedback
Ethiopian Educational Channel

Ethiopian Educational Channel

前往频道在 Telegram

እንኳን ደና መጣችሁ በዚህ ቻናል ላይ የሚያገኙት 1. ትምህርታዊ መረጃ መስጠት 2.የሳይኮሎጂ አስተማሪ ምክሮችንና አነቃቂ ንግግሮች 3.መፃህፍቶች በpdf እና የእንግሊዝኛ ትምህርት ይለቀቃሉ! በዚህ ቻናል ሀይማኖታዊ እና ፓለቲካ ነክ አይለቀቅበትም ! የቴሌግራሙ ቻናል ሊንክ:👉https://t.me/EEC1227 Channel created by @BA1227

显示更多
6 814
订阅者
-424 小时
-157
-3930
帖子存档
#ምርጫ2018  : ብልፅግና ፓርቲ ዛሬ ይፋ በተደረገው ውጤት 438 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) መቀመጫዎችን አግኝቷል። ፓርቲው ያሸነፈው ከፍተኛ የፓርላማ መቀመጫ ቁጥር መንግሥት መመስረት የሚያስችለው ነው። በሌላ በኩል ፦ - የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) 👉 13 መቀመጫዎች - የግል ዕጩዎች 👉 8 መቀመጫዎች - አማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) 👉 6 መቀመጫዎች - የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) 👉 3 መቀመጫዎች - የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ 👉 3 መቀመጫዎች - ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች - ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ 👉 2 መቀመጫዎች - የአፋር ህዝብ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ - አርጎባ አንድነት ጀርበቲ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ - ጉሙዝ ብሔራዊ ንቅናቄ 👉 1 መቀመጫ - አዲስ ትውልድ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ - ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 👉 1 መቀመጫ - የጌዴኦ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ - የወላይታ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ 👉 1 መቀመጫ - የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር 👉 1 መቀመጫ - ህብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ - ሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ ... አግኝተዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

- ብልፅግና ፓርቲ 👉 32 መቀመጫ  - ​የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ  - ​ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ  - የግል እጩ 1 መቀመጫ  - ​የሀረሪ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

#ምርጫ2018 የክልል ምክር ቤቶች ውጤት 1. አዲስ አበባ (ክልሉ ያለው መቀመጫ ብዛት - 158) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 10 - ብልፅግና 👉 134 መቀመጫዎች - ኢዜማ 👉 8 መቀመጫዎች - አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 4 መቀመጫዎች - ህዳሴ ፓርቲ 👉 2 መቀመጫዎች - ኦነግ ፓርቲ 👉 2 መቀመጫዎች - ትብብር ለኢትዮጵያ  አንድነት 👉 2 መቀመጫዎች - ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 👉 2 መቀመጫዎች - የወላይታ ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ 👉 1 መቀመጫ - የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) 👉 1 መቀመጫ - የወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ - የግል እጩ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል። 2. አፋር (ዛሬ ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 135 መቀመጫዎች) ምርጫ ውጤታቸው ይፋ የተደረገ የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 31 - ብልፅግና ፓርቲ 👉 124 መቀመጫ - የአፋር ነፃ አውጪ ግንባር ፓርቲ 👉 4 መቀመጫ - የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) 👉 3 መቀመጫዎች - የአፋር ህዝብ ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች - የአርጎባ አንድነት ጀበርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል። ድጋሚ ቆጠራ የሚከናወንበት ምርጫ ክልል ብዛት - 1 3. አማራ (ዛሬ ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 277 መቀመጫዎች) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 129 - ብልፅግና ፓርቲ 👉 257 መቀመጫዎች - የአማራ ዲሞክራሲ ሃይል ንቅናቄ 👉  4 መቀመጫዎች - ኢዜማ 👉 3 መቀመጫዎች - አብን 👉 2 መቀመጫዎች - አርጎባ አንድነት ጀበርቲ 👉 1 መቀመጫ - የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ - የቅማንት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ - ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 👉 1 መቀመጫ - ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 👉 1 መቀመጫ - የወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ - ነጻነትና እኩልነት 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል። #ማስታወሻ ፦ 4 መቀመጫዎች በንባብ በተሰማው ሪፓርት አልተካተተም። ምርጫ ያልተካሄደባቸው የምርጫ ክልል ብዛት - 8 4. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 165 መቀመጫዎች) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 20 - ብልፅግና 👉 145 መቀመጫዎች - የጉሙዝ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ 👉 14 መቀመጫዎች - የቤንሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ 👉 5 መቀመጫዎች - የግል እጩ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል። 5. ድሬዳዋ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 189 መቀመጫዎች ) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 47 - ብልፅግና ፓርቲ 👉 161 መቀመጫዎች - ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 8 መቀመጫዎች - ኢዜማ ፓርቲ 👉 6 መቀመጫዎች - አዲስ ትውልድ 👉 3 መቀመጫዎች አሸንፈዋል። #ማስታወሻ ፦ 11 መቀመጫዎች በንባብ በተሰማው ሪፓርት አልተካተተም። 6. ጋምቤላ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 205 መቀመጫዎች) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 14 - ብልፅግና 👉 176 መቀመጫዎች - ሰላም ለኢትዮጵያ 👉 17 መቀመጫዎች - ኢዜማ ፓርቲ 👉 6 መቀመጫዎች - ህዳሴ ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች አሸንፈዋል። #ማስታወሻ ፦ 3 መቀመጫዎች በንባብ በተሰማው ሪፓርት አልተካተተም። 7. ኦሮሚያ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 528 መቀመጫዎች) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት - 173 - ብልፅግና 👉 523 መቀመጫዎች - የግል እጩዎች 👉 4 መቀመጫዎች - ኢዜማ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል። #ማስታወሻ ፦ በኦሮሚያ ክልል ካሉ 179 የምርጫ ክልል ምርጫው የተካሄደው 173 መሆኑን በሪፓርቱ ተገልጿል። ለክልል ምክር ቤት ድጋሚ ቆጠራ የሚካሄድበት ምርጫ ክልል ብዛት = 1 ለክልል ምክር ቤት ድጋሜ ምርጫ የተወሰነበት = 2 8. ሲዳማ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 190 መቀመጫዎች) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 19 - ብልፅግና ፓርቲ 👉 175 መቀመጫዎች - መድረክ 8 መቀመጫዎች - የሲዳማ አንድነት ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች - የሲዳማ ህዝብ አንድነት ዲሞክራሲያዊ ድርጅት 👉 1 መቀመጫ - ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ 👉 1 መቀመጫ - የኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ህብረት 👉 1 መቀመጫ - የመላው ሲዳማ ህዝብ ደሚሞክራሲ አንድነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል። 9. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 171 መቀመጫዎች) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 22 - ብልፅግና 👉 144 መቀመጫዎች - ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 👉 12 መቀመጫዎች - ኢዜማ ፓርቲ 10 መቀመጫዎች፤ - ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች - ወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል። #ማስታወሻ ፦ 1 መቀመጫ በንባብ በተሰማው ሪፓርት አልተካተተም። 10. ደቡብ ኢትዮጵያ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 224 መቀመጫዎች) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 55 - ብልፅግና 👉 182 መቀመጫዎች - ኢዜማ 👉 27 መቀመጫዎች - የወላይታ ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ 👉 3 መቀመጫዎች - ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 2 መቀመጫዎች - የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ 👉 2 መቀመጫዎች - ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 👉 2 መቀመጫዎች - ጌዲዮ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት 👉 2 መቀመጫ - የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ 👉 2 መቀመጫ - የግል እጩ 👉 1 መቀመጫ - የኩሽ ህዝቦች ብሔራዊ ንቅናቄ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል። ለክልል ምክር ቤት ድጋሚ ቆጠራ የሚካሄድበት ምርጫ ክልል ብዛት = 1 11. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 170 መቀመጫዎች) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 34 - ብልፅግና ፓርቲ 👉 143 መቀመጫዎች - ኢዜማ ፓርቲ 👉 12 መቀመጫዎች - ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 7 መቀመጫዎች - ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 👉 3 መቀመጫዎች - ጎጎት ለጉራጌ አንድነትና ፍትህ ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች - ወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ - የወለኔ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል። 12. ሶማሌ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 252 መቀመጫዎች) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 66 - ብልፅግና ፓርቲ 👉 214 መቀመጫ  - ​የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር (ONLF) 👉 20 መቀመጫ  - ​ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 👉 13 መቀመጫ  - ​የሱማሌ ፌደራሊስት ፓርቲ 👉 2 መቀመጫ  - ​የግል እጩ 👉 1 መቀመጫ  - ​የምዕራብ ሶማሌ ዲሞክራቲክ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ  - ​ህብረት ለዲሞክራሲ ለነጻነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ አሸንፈዋል። #ማስታወሻ ፦ ለክልል ምክር ቤት ድጋሚ ቆጠራ የሚካሄድበት ምርጫ ክልል ብዛት = 5 13. ሐረሪ (ምርጫ ውጤታቸው ይፋ በተደረጉት 36 መቀመጫዎች) ምርጫ የተካሄደበት የክልል ም/ቤት ምርጫ ክልል ብዛት ፦ 3

FAQ ስለ CGPA እና GPA አሰራር ማብራሪያ ብዙዎች እንደሚሳሳቱት፣ Cumulative GPA (CGPA) ማለት የ-1st Semester እና የ-2nd Semester Gpaን ደምሮ ለሁለት ማካፈል ማለት አይደለም።❌ የትኛውም የGPA ስሌት የሚሰራው ተማሪው በወሰዳቸው አጠቃላይ Credit Hours ብዛት ላይ ተመስርቶ ነው። 📚 የሴሚስተር GPA አሰራር የአንድን ተማሪ የሴሚስተር ውጤት (GPA) ለማስላት፣ እያንዳንዱ ትምህርት ያለው የ Credit Hour በዛው ትምህርት የመጣው Grade Point ይባዛል። ከዚያም የሁሉም ትምህርቶች ውጤት በአንድ ላይ ተደምሮ፣ በሴሚስተሩ ለተወሰዱት አጠቃላይ የ Credit Hour ድምር ይካፈላል። ምሳሌ፦ አንድ ተማሪ በሴሚስተሩ 3 ትምህርቶችን ቢወስድ፡ 1ኛ ትምህርት፦ Grade A (4.0) እና Credit Hour 5 ቢሆን ➔ 4.0 x 5 = 20 2ኛ ትምህርት፦ Grade A- (3.75) እና Credit Hour 5 ቢሆን ➔ 3.75 x 5 = 18.75 3ኛ ትምህርት፦ Grade B (3.0) እና Credit Hour 3 ቢሆን ➔ 3.0 x 3 = 9 የተማሪውን GPA ለማግኘት፦ የውጤቶች አጠቃላይ ድምር፦ 20 + 18.75 + 9 = 47.75 የአጠቃላይ Credit Hour ድምር፦ 5 + 5 + 3 = 13 በመጨረሻም፣ የውጤቱን ድምር ለአጠቃላይ ክሬዲት ሰዓቱ ስናካፍለው የሴሚስተሩን GPA እናገኛለን፦ 47.75 ÷ 13 = 3.67 ስለዚህ፣ ይህ ተማሪ በሴሚስተሩ 3.67 GPA አመጣ ይባላል። CGPA ሲሰላም በተመሳሳይ መንገድ የሁሉንም ሴሚስተሮች(የሁሉንም ኮርሶች) አጠቃላይ የውጤት ድምር ለአጠቃላይ የክሬዲት ሰዓት ድምር በማካፈል ነው የሚገኘው። 📌 የ CGPA አሰራር ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ፦ ለምሳሌ የአንድን ተማሪ የሁለት ሴሚስተር የCGPA ውጤት ለማስላት፦ • 1st Semester ላይ፦ የውጤት ድምር = 47.75 የ Credit Hour ድምር = 13 (GPA = 3.67) • 2nd Semester ላይ፦ የውጤት ድምር = 52.00 የCredit Hour ድምር = 15 (GPA = 3.46) ❌ የተሳሳተው አሰራር፦ የሁለቱን ሴሚስተር GPA ደምሮ ለሁለት ማካፈል (3.67 + 3.46) ÷ 2 = 3.56 (ይህ ስህተት ነው!) የምትወስዱት ኮርስ በጨመረ ቁጥር የተሳሳተ Result ነው የምታገኙት ትክክለኛው አሰራር (CGPA)፦ የሁለቱንም ሴሚስተር አጠቃላይ የውጤት ድምር ለአጠቃላይ የክሬዲት ሰዓት ድምር ማካፈል፦ • አጠቃላይ የውጤት ድምር፦ 47.75 + 52.00 = 99.75 • አጠቃላይ የCredit Hour ድምር፦ 13 + 15 = 28 ስለዚህ CGPA = 99.75 ÷ 28 = 3.562 (ወደ ሁለት Digit ሲጠጋ 3.56 ይሆናል።) ውጤቱ ተመሳሳይ ሊሆን የቻለው የሁለቱ ሴሚስተሮች የክሬዲት hr በጣም ስለሚቀራረብ ብቻ ነው፤ የምትወስዷቸው ኮርሶች በበዙ ቁጥር የ ሁለቱ አሰራር ልዩነት ይፈጥራል። share it your friends

#ልጄ_ሆይ ..... #ሰው_ሁን ! “የዚህች ዓለም ትልቁ ስኬት በሀብት መክበር፣ በዕውቀት መላቅ ወይም በሥልጣን መግነን አይደለም። ትልቁና ከባዱ ስኬት ‘ሰው መሆን’ ነው።” መኖርና ሰው መሆን ይለያያሉ። መኖር ተፈጥሯዊ ስጦታ ነው፤ ሰው መሆን ግን በየቀኑ የሚገነባ የጥበብና የሥነ-ምግባር ማማ ነው። ልጄ ሆይ፥ እነዚህን የሕይወት የወርቅ ምክሮች በልብህ ሰሌዳ ላይ ጻፋቸው፦ #ልብህ_ለሌሎች_ይምታ ! የሰው ልጅ እውነተኛ መለኪያው የኪሱ ስፋት ሳይሆን የልቡ ርኅራኄ ነው። ስትችል በምታገኘው አጋጣሚ ሁሉ ደግነትን ዝራ። መርዳት ማለት ቁሳቁስ ማካፈል ብቻ አይደለም፤ ከሰዎች ጋር አብሮ ማልቀስና አብሮ መደሰትም ጭምር ነው። #በቃልህ_ታመን ! ክብረ ወሰንህና ማንነትህ የሚለካው በምትናገረው ቃል ነው። የምትሰጠው ተስፋ ከምድር በታች የተቀበረ ጽኑ መሠረት ይሁን። ቃልን ማክበር ለራስ የሚሰጥ ታላቅ ክብር ነው። #በትሕትና_ከፍ_በል ! ዕውቀትህና ሀብትህ ሲጨምር ትሕትናህም አብሮ ይጨምር። በትዕቢት የምታገኘው ክብር ጊዜያዊ ነው፤ በትሕትና የምታገኘው ፍቅር ግን ዘላለማዊ ነው። ጎንበስ ማለት መሸነፍ ሳይሆን ሰውን ማክበር ነው። ! ሕይወት ሁልጊዜ አልጋ በአልጋ አትሆንም። ማዕበል ሲነሳ የሚወድቅ ሳይሆን፣ ሥሩ ወደ መሬት ጠልቆ የገባ ጽኑ ዛፍ ሁን። ውድቀት የሕይወት ማቆሚያ ሳይሆን፣ ይበልጥ ጠንክሮ የመነሻ አዲስ ምዕራፍ ነው። ! ሰዎች ክፉ ስላደረጉብህ አንተም ክፉ አትሁን፤ ያኔማ በክፋታቸው ተሸነፍክ ማለት ነው። አንተ ግን በውስጥህ ያለውን ሰብዓዊነት ሁልጊዜ በመልካምነትህ አስመስክር። ልጄ ሆይ! ዕድሜህ ሲጨምር ዓለም ብዙ ስሞችን፣ ማዕረጎችንና ዝናዎችን ትሰጥህ ይሆናል። ያኔ ግን ሁሉንም ማዕረጎች አውልቀህ ስትመረመር ከውስጥህ “እውነተኛ ሰው” ይገኝ። ሰው መሆንህን ስታረጋግጥ የሕይወትን እውነተኛ ትርጉም አገኘህ ማለት ነው።

የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል። ሰኔ 13/2018 ዓ.ም የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግ
+1
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል። ሰኔ 13/2018 ዓ.ም የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞ በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል። ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል። @አ/አ ት/ቢሮ

በፈተና ዋዜማ ተማሪዎች አእምሮን ለማዝናናት በቂ እንቅልፍ መተኛት፣ የተዘጋጁ ማጠቃለያዎችን ብቻ በአጭሩ መገምገም፣ የፈተና መገልገያ ቁሳቁሶችን ማዘጋጀት፣ ጤናማ ምግብ መመገብ እና አላስፈላጊ ጭንቀት
በፈተና ዋዜማ ተማሪዎች አእምሮን ለማዝናናት በቂ እንቅልፍ መተኛት፣ የተዘጋጁ ማጠቃለያዎችን ብቻ በአጭሩ መገምገም፣ የፈተና መገልገያ ቁሳቁሶችን ማዘጋጀት፣ ጤናማ ምግብ መመገብ እና አላስፈላጊ ጭንቀትን ማስወገድ አለባቸው።
በፈተና ዋዜማ እና የፈተና ጊዜ ስኬትን ለማረጋገጥ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች ተግባራዊ ማድረግ ይገባል በቂ እረፍት ማድረግ፡ አእምሮን ለማነቃቃት እና ጭንቀትን ለመቀነስ ቢያንስ ከ 7 እስከ 8 ሰዓታት የሚሆን ጥልቅ እንቅልፍ መተኛት ያስፈልጋል። የፈተና ቁሳቁስ ማሟላት እስክሪብቶ፣ እርሳስ፣ ማጥፊያ፣ መለያ (ID) እና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶች አስቀድመው በቦርሳ መዘጋጀት አለባቸው። አጭር ግምገማ ብቻ ማድረግ፡ አዳዲስ ርእሶችን ለማንበብ ከመሞከር ይልቅ ቀደም ሲል የተሰሩ ማጠቃለያዎችን እና ዋና ዋና ነጥቦችን ብቻ ማየት ይበጃል። ትክክለኛ አመጋገብ፡ አእምሮ በተገቢው መንገድ እንዲሠራ ቀላል፣ ሰውነትን የሚያነቃቁ እና ጤናማ ምግቦችን መመገብ ይገባል። ስሜትን መቆጣጠር የፈተና ፍርሃትን እና ጭንቀትን ለመቀነስ ከመጠን በላይ ከማሰብ መቆጠብ፣ አዎንታዊ አስተሳሰብ መያዝ እና ዘና ማለት ያስፈልጋል። የፈተና ቦታን ማወቅ፡ የፈተናው ቦታ ሩቅ ከሆነ አስቀድሞ መንገድን በመለየት ሰዓት አክብሮ ለመገኘት እቅድ መያዝ ወሳኝ ጉዳይ ነው ተማሪዎች ሆይ እንወዳቹሀለን

ሒሳብ የ6ኛ ክፍል 2018ዓ/ም
+9
ሒሳብ የ6ኛ ክፍል 2018ዓ/ም

የእቁብ (Equb) መተዳደሪያ ደንብ ፎርም የእቁብ (Equb) መተዳደሪያ ደንብ በአጠቃላይ የተሳታፊዎች መብትና ግዴታ፣ የገንዘብ አያያዝ፣ የመውጫ እና የክስ ሂደት የሚያቀናጅ የውስጥ ህግ ነው። 1. መግቢያ (General Provisions) የእቁብ ስም ዓላማ (ለቁጠባ፣ ለመርዳት፣ ለንግድ ወዘተ) አባላት ቁጥር የእቁብ ዘመን (duration) 2. አባልነት (Membership) መግቢያ መስፈርቶች አዲስ አባል መጨመር መንገድ አባልነት ማቋረጥ (በፈቃድ / በስርዓት) 3. የክፍያ ስርዓት (Contribution Rules) የወር/ሳምንት ክፍያ መጠን የክፍያ ቀን የዘግይት ቅጣት ክፍያ ካልተፈጸመ የሚወሰድ እርምጃ 4. የዕጣ ሂደት (Lottery / Turn Allocation) የመጀመሪያ ዕጣ መወሰን (በዕጣ ወይም በስምምነት) ቀጣይ ዕጣ የሚወጣበት ሂደት ቀድሞ ዕጣ ለመውሰድ የሚፈቀድ ነገር 5. አስተዳደር (Management) አስተዳዳሪ (Chairperson) ገንዘብ ተቆጣጣሪ (Treasurer) ጸሐፊ (Secretary) የእያንዳንዱ ሀላፊነት 6. የገንዘብ አያያዝ (Financial Management) ገንዘብ የሚቀመጥበት (ባንክ/እጅ) የመዝገብ ማስተናገድ ግልጽነት (transparency) 7. የቅጣት እና የስርዓት ደንቦች የዘግይት ቅጣት ክፍያ ካልከፈለ የሚወሰድ እርምጃ ህግ ጥሰት ላይ የሚወሰድ ውሳኔ 8. የመውጫ እና ተተኪ (Exit & Replacement) አባል መውጣት ሲፈልግ ተተኪ መግባት ከወጣ በኋላ የገንዘብ መመለስ ሂደት 9. የክስ መፍትሄ (Dispute Resolution) በውስጥ መፍትሄ (internal resolution) ካልተፈታ ወደ ህግ (court/arbitration) 10. የመጨረሻ ድንጋጌዎች ደንቡ መቀየር የሁሉም አባላት ፊርማ አስፈላጊ ነው። አስፈላጊ ምክር እቁብ ደንብ በጽሑፍ መኖር አስፈላጊ ነው ሁሉም አባላት መፈረም አለባቸው ከፍተኛ ገንዘብ ካለ ሕጋዊ ማረጋገጫ (notarization) ይመከራል ✅💟🙏🏽

የኢትዮጵያ ዓመታዊ የበጀት ቁጥሮች!
የኢትዮጵያ ዓመታዊ የበጀት ቁጥሮች!

~#Survival of the fittest~ ==========/////======== ቻርለስ ዳርዊን ''Survival of the fittest'' የሚባል ቲዎሪ አለው።ወደ አማርኛ ሲተረጎም ''አሸናፊዎች ይህንን አለም ይኖራሉ፣ዘራቸውንም ያስቀጥላሉ አይነት ትርጉም አለው። በዚህ ቲዎሪ ቁልፍ ጉዳዩ አሸናፊ ማነው? የሚለው ነው።ስለዚህም አሸናፊዎች ማለት የአካባቢን ጫና የሚቋቋሙ፣ጦርነትን የሚያሸንፉ፣ታግለው የሚረቱ፣ጉልበት ያላቸው፣የተሰባሰቡና አንድነት ያላቸው.....ወዘተ አካባቢያቸው ውስጥ የመቀጠልና ዘራቸውንም የማስቀጠል እጣ ፋንታ አላቸው ይላል። በቻርለስ ዳርዊን እሳቤ ለሰው ልጅ ክፋትን ያስተማረች ተፈጥሮ ናት፣ምክንያቱም ህዳታንና አነስተኛ ጉልበት ያላቸውን አታስተናግድም ማለት ነው። ዳርዊን አያይዘውም በ1871 ባሳተመው “Descent of Man” በተሰኘ የምርምር (እና የሰው ዘር አመጣጥ ግምት) መጽሐፉ፣ የሰው ልጆች ወደ ጦርነት የሚያዘነብሉትና ከጦርነት የሚርቁት - እንደ ዘሮቻቸው ሁኔታ ይወሰናል በማለት ገለፀ፡፡ ያም ማለት አያት ቅድመ-አያቶቼ የታወቁ ጦረኞች ከነበሩ፣ እኔም ውስጥ ያ ጦረኛነት አለ፡፡ ጦርነት ያምረኛል፡፡ ወይም አያስፈራኝም፡፡ ቁጡ ነኝ፡፡ አትንኩኝ ባይ ነኝ፡፡ በደም ሥሬ የአርበኝነት ስሜት ይንቀዠቀዣል እንደማለት ነው፡፡ ቻርለስ ዳርዊን ሲገልፅልን የዚህ ዓይነት ከጥንት ጀምሮ ራሳቸውን ከሌላው ጥቃት ተከላክለው ለማትረፍ የግድ መዋጋት ከነበረባቸው ማህበረሰቦች የተገኘህ ዘር ከሆንክ፣ በደምህ ውስጥ የሆኑ ለጦርነት አመቺ የሆኑ ተፈጥሯዊ ባህርያትን ተላብሰህ ትገኛለህ፡፡ እና ቻርለስ ዳርዊን ጦርነትን የዘር ውርስ ጉዳይ ያደርገዋል ማለት ነው፡፡ ዳርዊን ብቻም ግን አይደለም፡፡ ብዙ የታወቁ ሳይንቲስት ተከታዮችን አፍርቷል፡፡ ኬንያ ተወልዶ ያደገው ዘረ-እንግሊዝ ዕውቅ የጂን-ቲዎሪስት ሪቻርድ ዳውኪንስም በ1976 ባሳተመው ‹‹The Selfish Gene›› በሚል መፅሐፉ ይህን የዳርዊንን ቲዎሪ እውነትነት ያረጋግጥልናል፡፡ የማያቋርጡ ጦርነቶች ሲፈራረቁበት በነበረ ምድር በኖሩ ህዝቦች ዘንድ፣ ከጊዜ ወደጊዜ፣ ከዘመን ዘመን፣ ደካሞቹና ፈሪዎቹ በprocess of natural selection እየተገደሉ፣ እየተገለሉ፣ ወደሌላ ሀገር እየተሰደዱ፣ መሬታቸውን ሚስታቸውን እየተቀሙ፣ ዘረ-ቢስ፣ ንብረት-አልባ ሆነው ይቀራሉ፡፡ ይሞታሉ፡፡... ሚስት ያጣሉ፡፡ ብዙ ልጅ ወልደው ማሳደግ ይሳናቸዋል፡፡ በሀይለኞች ይገደላሉ፡፡ ጥሩ ለጤና ተስማሚ ምግብ ለመመገብ አቅም አይፈቅድላቸውም፡፡ ባጭር በቅለው ባጭር ሟቾች ይሆናሉ፡፡ እና ኃይለኝነት በሚያስከብርበት ማህበረሰብ ውስጥ፣ ሁሉም ከሀይለኛና ተዋጊ ዘር የተወለደ ይሆናል፡፡ ቻርለስ ዳርዊን ስለዚህኛው በዘሩ ለጦርነት አስፈላጊ የሆኑ ባህርዮቹን ከአያት ከቅድመ-አያቶቹ ወርሶ ስለሚገኘው የሰው ልጅ ‹‹ዲሰንት ኦፍ ማን›› መጽሲያብራራልን በራሱ ቃል እንዲህ ይላል፡- ‹‹A tribe including many members who, from possessing in high degree the spirit of patriotism, fidelity, obedience, courage and sympathy, were always ready to aid one another, and to sacrifice themselves for the common good, would be victorious over most other tribes, and this would be - natural selection.›› — Charles Darwin, The Descent of Man (1871) እንግዲህ ቻርለስ ዳርዊን የሚለን - ጦርነት ልማዳቸው ከነበሩ ማህበረሰቦች የሚወለዱ ዘሮቻቸው ከሌሎች የሰው ዘሮች በበለጠ ሁኔታ በደማቸው ውስጥ የታተመ የአርበኝነት መንፈስ ይታይባቸዋል፡፡ የታማኝነት ተፈጥሮ አላቸው፡፡ የታዛዥነት፣ የአክባሪነት፣ ለቃላቸው ሟችነት አላቸው በውስጣቸው፡፡ በተፈጥሯቸው አይፈሬ ናቸው፡፡ ደፋር፣ ጀግኖች ናቸው፡፡ ... ... ለሌላው የሚቆረቆሩም ናቸው፡፡ የሰው ህመም፣ የሰው ስቃይ ውስጣቸው ዘልቆ ይሰማቸዋል፡፡ ሌላውን በችግሩ ጊዜ ለመርዳት አይሳሱም፡፡ እንዲያውም ከፍ ሲልም፣ የራሳቸውን ህይወት ለሌላው ሰው ሲሉ፣ ለአጠቃላዩ ወገናቸው ሲሉ፣ ለመሰዋት ዓይናቸውን አያሹም፡፡ እና እነዚህን ባህርያት የተላበሱ ሰዎች በብዛት ያሉት ማኅበረሰብ (ነገድ፣ ህዝብ፣ ብሔር፣ ወይም ጎሳ) ሌሎችን በጦርነት ገጥሞ እንደሚያሸንፍ ጥርጥር የለውም! - ይለናል ቻርለስ ዳርዊን፡፡ በሶስቱ በዓለም ስማቸው የታወቀ፣ እና በዓለማችን አስተሳሰብ ላይ የየራሳቸውን ጉልህ ተፅዕኖ ያሳረፉ ፈላስፎች የሰው ልጅንና የጦርነትን ግንኙነት ከሚተነትኑት ሀተታቸው በአጭሩ ስንመለከት:- አንዱ በቶማስ ሆብስ የሚቀነቀነው ፍልስፍና የሰውን ልጆች በተፈጥሯችን አውሬዎች፣ ተናካሾች፣ ስግብግቦች፣ ተጠራጣሪዎች፣ ባጭር ሟቾች፣ ክፉዎች ያደርገናል፡፡ ሁለተኛው በዣን ዣክ ሩሶ የሚቀነቀነው ፍልስፍና ደግሞ የሰውን ልጅ ክብሩን የጠበቀ፣ የዋህና ፍፁም ሠላማዊ፣ ቢበዛ ከልፊያና ከትግል የማያልፍ ‹‹ኖብል ሳቬጅ›› ያደርገዋል፡፡ ሶስተኛው በቻርለስ ዳርዊን የሚቀነቀነው የኢቮሉሽን ሳይንስን የተመረኮዘና በሪቻርድ ዳውኪንስ የጂን ሪሰርች ቲዎሪዎች የተደገፈ ፍልስፍና ደግሞ - ጦርነትም ጀግንነትም የዘር ውርስ ነው ይለናል! ማጠቃለያ ይህቺ አለም ኢ-ፍትሐዊ ነች።ትንንሾችንና ጉልበት የሌላቸውን አታስተናግድም፣ላልተሰባሰቡትና ሀይል ለሌላቸውን ቦታ የላትም፣ታጋይ ያልሆኑና አሸናፊ ያልሆኑ ዘሮቻቸውን አያስቀጥሉባትም። ስለሆነም እንደ ግለሰብም ሆነ እንደህዝብ ለመቀጠልና ዘሮቻችንን ለማስቀጠል፣ብሎም ላለመጥፋት አካባቢያችን ውስጥ መታገል፣ሀይል ማሰባሰብ፣ጉልበት መደመር፣አንድነት መፍጠር፣አሸናፊ መሆን ብቸኛው አማራቻችን ነው ማለት ነው። ስለዚህ ''ዳርዊኒዝም መዳኛችን ነው''!! ========ሰላም======= ✍️በተግባር አንዱዓለም በቀለ ሚያዝያ 30/2018 እንጅባራ!!!

ለፈታኞች የምግብ ዝርዝር በቂ ነው ማለት ያስቸግራል። ከዚህ በላይ ቢደረግላቸው ይገባቸዋል
+1
ለፈታኞች የምግብ ዝርዝር በቂ ነው ማለት ያስቸግራል። ከዚህ በላይ ቢደረግላቸው ይገባቸዋል

ፈታኞች በጣም ጥንቃቄ ማድረግ አለባችሁ የተማሪ ህይወት እንዳታበላሹ!!

[ ከሚኒስትሪ ፈታኝ መምህራን የሚጠበቁ ዋና ዋና ነገሮች ]
👉🏾 የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል። 👉🏾 ፈታኝ መምራህን የተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ። 👉🏾 በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው። 👉🏾 የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው። 👉🏾 በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ። 👉🏾 ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ተማሪ እንዳይመለከቱ እንዳይኮርጁ  መቆጣጠር አለባቸው። 👉🏾 ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ሲኮርጂ ወይንም ሲያስኮርጅ የተገኘ ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ፈተናው ከጀመረ 30 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም። 👉🏾 የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ

✔️ለ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈተኞች የትምህርት አይነትና ኮድ (ለአዲስ አበባ ተፈታኞች) ✔️የሚኒስትሪ ተፈታኞች ማድረግ የሚገባቸው 1ነገሮች ⭐️1.ለመልስ መስጫ ወረቀት እርሳስ ብቻ መ
✔️ለ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈተኞች የትምህርት አይነትና ኮድ (ለአዲስ አበባ ተፈታኞች) ✔️የሚኒስትሪ ተፈታኞች ማድረግ የሚገባቸው 1ነገሮች ⭐️1.ለመልስ መስጫ ወረቀት እርሳስ ብቻ መጠቀም ⭐️2.የት/ት አይነት መለያ ኮድን ቡክሌት ኮድ በትክክል ማጥቆር ⭐️3.ቡክሌት ኮድን በትክክል ማጥቆር ⭐️4.የመልስ ወረቀት ላይ በአግባቡ ማጥቆር ⭐️5.የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የጥያቄዎቸን ቅደም ተከተል ጠብቆ መስረት ⭐️6.ለአንድ ጥይቄ አንድ መልስ ብቻ ማጥቆር 🌟7.የመልስ ወረቀት ላይ ሌላ ነገር አለመጻፍ ✅8.በፈታኞች የሚሰጠንን መመሪያ ተግባራዊ ማደረግ ⭐️ ለሁሉም ተፈታኞች መልካም ፈተና