uk
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Відкрити в Telegram

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Assaye Derbie

Канал Assaye Derbie (@asayede) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 345 підписників, посідаючи 2 649 місце в категорії Блоги та 2 354 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 345 підписників.

За останніми даними від 24 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -112, а за останні 24 години на -7, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 39.43%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 12.21% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 656 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 752 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 33.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 25 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Блоги.

14 345
Підписники
-724 години
-387 днів
-11230 день
Архів дописів
አባ ሳሙዔል እስር ቤት ውስጥ እርሱ የተኛበትን ፍራሽ ተረክቤ ከአንድ ነባር እስረኛ አንደበት፣ ስንታየሁ በተለያዩ እስር ቤቶች በጽናት እና በአይበገሬነት ያሳለፋቸውን እጅግ አሳዛኝ ግፎች ስሰማ በመከ
አባ ሳሙዔል እስር ቤት ውስጥ እርሱ የተኛበትን ፍራሽ ተረክቤ ከአንድ ነባር እስረኛ አንደበት፣ ስንታየሁ በተለያዩ እስር ቤቶች በጽናት እና በአይበገሬነት ያሳለፋቸውን እጅግ አሳዛኝ ግፎች ስሰማ በመከራ ብዛት ተሸንፎ ትግሉን እንዳያቆም ሰግቼ ነበር። እርሱ ግን የእስክንድርን ጽናት እና እውነት የወረሰ ብርቱ ሰው በመሆኑ "ስንታየሁ" እንደተባለው ስንትና ስንት ግፍ ሲያስተናግድ ከርሞም ከወትሮ አቋሙ ዝንፍ ማለት አልቻለም።

ለአማራ ብልጽግና ከፍተኛ አመራሮች ባሕር ዳር ▬▬▬▬ ጉዳዩ፦ ቲተር እና ብዕር እንዲታስረክቡ ስለማሳሰብ ባለንበት ወቅት ላይ "የጸረ ሙሥና ብሔራዊ ኮሚቴ" መቋቋሙ ሙሥናን እና ሙሠኞችን ከማክሰም ባለፈ ከበላይ አካል የሚላክን የትኛውንም አይነት ትዕዛዝ ለመፈረም እና ለመፈጸም የተዘጋጁ ድንጉጥ አመራሮች በመፍጠር ረገድ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም በሙሥና ከነቀዘው ድርጅት ውስጥ "አሳሪ" እና "ታሳሪ" ተብሎ የተደለደለው አመራር በግልጽ እስኪታወቅ ድረስ በፌደራልም ሆነ በክልል ደረጃ የተሾማችሁ የአማራ ብልጽግና ከፍተኛ አመራሮች ከአበል እና ከሰማንያ ውል ውጭ ባሉ ሰነዶች ላይ የመፈረም ሥልጣናችሁ መታገዱን አሳውቃለሁ።😆 ግልባጭ ▬▬▬ ➔ለአፍሪካ ሕብረት ➔ለፌ.መንግሥት እና ለህውሓት

በወልቃይት ጉዳይ መሬት ላይ መሠራት ያለበት ሁሉ ተጠናቅቋል! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ለእራሱ ጥያቄ መልስ ለመስጠት እንቅፋት የሚሆንበት ምድራዊ ሕግ አለመኖሩን በሚገልጽ መልኩ ትናንት መሀል አገር ላይ
በወልቃይት ጉዳይ መሬት ላይ መሠራት ያለበት ሁሉ ተጠናቅቋል! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ለእራሱ ጥያቄ መልስ ለመስጠት እንቅፋት የሚሆንበት ምድራዊ ሕግ አለመኖሩን በሚገልጽ መልኩ ትናንት መሀል አገር ላይ ሕዝብን ሳያሳትፍ፣ ፍላጎታቸውን እና ቋንቋቸውን ከግምት ውስጥ ሳያስገባ.... የድንበር ማካለል ሥራ ተፈጻሚ አድርጎ ያደረ አካል፤ ከሕዝብ የመጣን እንዲሁም በብዙ መስዋዕትነት የተገኘን የማንነትና የድንበር ጥያቄ ላለመመለስ "አማርኛህ ጥርት ያለ አይደለም፤ መሬት ላይ መሥራት ያለብህንም አልሠራኽም" እያለ ሲያሾፍብህ "አልሰማኽም" ማለት እንጂ "መሬት ላይ መሥራት ያለብንን እንሥራ" እያሉ ማለቅለቅ ልክ አይደለም። ምክንያቱም... ያለ ሕዝብ ፍላጎት በኃይል የተወሰደ ማንነት በሕዝብ ደምና አጥንት በኃይል የተመለሰ እለት የምድሩ ሥራ ተጠናቅቆ ፋይሉ ወደ መድረክና ወደ ቢሮ ተሸኝቷል። እናም መድረክ ላይ ያጋጠመኽን ችግር ማለፍ ሲሳንህ "ምድር ላይ መሥራት ያለብንን እንስራ" እያልክ አትንደፋደፍ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ወልቃይት ምድር የረጨው ምራቅ ታብሶ እንዲሁም ወደ ባንኩ ተመልሶ ብር እንዲቆጠርበት ተደርጓል። ወልቃይት ሆይ የጨበጠሽ እጄ የለቀቀሽ እንደሆን የሰለተ ይሁን ብለናል!!
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ወልቃይት ምድር የረጨው ምራቅ ታብሶ እንዲሁም ወደ ባንኩ ተመልሶ ብር እንዲቆጠርበት ተደርጓል። ወልቃይት ሆይ የጨበጠሽ እጄ የለቀቀሽ እንደሆን የሰለተ ይሁን ብለናል!!

ወልቃይትን ከጎንደር እና ከአማራ አብራክ ሲነጥሉ የታዩት ጠቅላይ ሚኒስትር "ኦነግ ሸኔ በሸዋ እና በወለጋ ተቧድኖ ኦሮሚያን እያፈረሰብኝ ነው" የሚል ቁጭታቸውን አቅርበዋል። 😆
ወልቃይትን ከጎንደር እና ከአማራ አብራክ ሲነጥሉ የታዩት ጠቅላይ ሚኒስትር "ኦነግ ሸኔ በሸዋ እና በወለጋ ተቧድኖ ኦሮሚያን እያፈረሰብኝ ነው" የሚል ቁጭታቸውን አቅርበዋል። 😆

እንኳን ለቤትህ አበቃህ ወንድማለም‼️ ለጋዜጠኝነት እና ለእውነት ያንተን ያህል ዋጋ የከፈለ ማን ይሆን?
እንኳን ለቤትህ አበቃህ ወንድማለም‼️ ለጋዜጠኝነት እና ለእውነት ያንተን ያህል ዋጋ የከፈለ ማን ይሆን?

በብልጽግና እና በህውሓት መሀከል የተካሄደው ስምምነት ጦርነትን የሚያስቀር ሳይሆን ጦር ሜዳ እና ጥምር ጦር የሚያስቀይር ከንቱ ቁማር መሆኑን ለመረዳት የለገሰ ቱሉን እና የኢታማዦሩን ዛቻ ማስተዋል በ
በብልጽግና እና በህውሓት መሀከል የተካሄደው ስምምነት ጦርነትን የሚያስቀር ሳይሆን ጦር ሜዳ እና ጥምር ጦር የሚያስቀይር ከንቱ ቁማር መሆኑን ለመረዳት የለገሰ ቱሉን እና የኢታማዦሩን ዛቻ ማስተዋል በቂ ነው።

ልክ እንደ ወልቃይት ጠ/ሰ/ሁ ዞን ሁሉ በአማራ ክልል የሚገኙ ሁሉም ዞኖች "ንግድ ባንክ በኢዜአ በኩል አማራ ላይ ያዝረበረበው ምራቅ በአፋጣኝ ታብሶ ብር እንዲቆጠርበት መጠየቅ ብሎም ማስጠንቀቅ ይገባቸዋል።

ሼህ ሑሴን ጅብሪል አልሞቱም 😂

ከናይሮቢው ሰነድ ጋር አብሮ የተለቀቀው የሄዊ መግለጫ ዋነኛ ዓላማው ብልጽግና ኬንያ የፈረመውን ሸፍጥ ማድበስበስ ነው። የእኛዎቹ ደላላዎችም የኬንያውን አጀንዳ በመቀሌው ለመጥለፍ እየተንደፋደፉ ነው።
ከናይሮቢው ሰነድ ጋር አብሮ የተለቀቀው የሄዊ መግለጫ ዋነኛ ዓላማው ብልጽግና ኬንያ የፈረመውን ሸፍጥ ማድበስበስ ነው። የእኛዎቹ ደላላዎችም የኬንያውን አጀንዳ በመቀሌው ለመጥለፍ እየተንደፋደፉ ነው።

የሰሜኑ ጦርነት የፈጠረለትን መልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ ሸገርን ቀረጣጥፎ የበላው አካል በወልቃይትና ራያ ላይ መቆመር ካሰኘው፣ የአራት ኪሎ ወንበር ቀርቶ ኢትዮጵያ የምትባል አገር መቀጠሏ ያጠራጥራል። ስ
የሰሜኑ ጦርነት የፈጠረለትን መልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ ሸገርን ቀረጣጥፎ የበላው አካል በወልቃይትና ራያ ላይ መቆመር ካሰኘው፣ የአራት ኪሎ ወንበር ቀርቶ ኢትዮጵያ የምትባል አገር መቀጠሏ ያጠራጥራል። ስለዚህ ብልጽግና ሆይ ከጦርነት ወደ ጦርነት ባታሸጋግረን ጥሩ ነው!

ከአገር ውጭ መደራደርን ለእነ ጄኔራል ታደሰ ወረደ የፈቀደው አካል፣ ከአገር ውጭ መታከምን ለጄኔራል ተፈራ የከለከለው "በሕልውና ዘመቻው ወቅት ሄዊ ላይ ጉዳት አድርስኻል" የሚል ክስ ሊመሠርትበት ፈል
ከአገር ውጭ መደራደርን ለእነ ጄኔራል ታደሰ ወረደ የፈቀደው አካል፣ ከአገር ውጭ መታከምን ለጄኔራል ተፈራ የከለከለው "በሕልውና ዘመቻው ወቅት ሄዊ ላይ ጉዳት አድርስኻል" የሚል ክስ ሊመሠርትበት ፈልጎ ይሆን?😆

የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወንድም ጎበዜ ሲሳይ በመቶ ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ ወስኗል። እንኳን ለቤትህ አበቃህ ወንድማለም‼️
የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወንድም ጎበዜ ሲሳይ በመቶ ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ ወስኗል። እንኳን ለቤትህ አበቃህ ወንድማለም‼️

አገራዊውን ጦርነት እንደ ክልል ተሸክሞ "ዝመት ፥ አንክት" ሲል የከረመ ድርጅት፣ ዋነኛ ተደራዳሪ መሆን ሲገባው እራሱን ከድርድር ውጭ አድርጎ የስንዴ ማሳ ሲጎበኝ አስበኸዋል? አቅመ-ቢስ ድርጅት‼️
አገራዊውን ጦርነት እንደ ክልል ተሸክሞ "ዝመት ፥ አንክት" ሲል የከረመ ድርጅት፣ ዋነኛ ተደራዳሪ መሆን ሲገባው እራሱን ከድርድር ውጭ አድርጎ የስንዴ ማሳ ሲጎበኝ አስበኸዋል? አቅመ-ቢስ ድርጅት‼️

ጌታቸው ረዳን ስካይ ላይት ሆቴል እያቀማጠሉ ጎበዜን እና ተመስገንን እስር ቤት ማሰቃየት ተገቢ አይደለም። መከላከያ ውስጥ ያለ አሠራርን መተቸት መከላከያን ከመውጋት በላይ የሚያስጠይቅ ወንጀል አይደለ
ጌታቸው ረዳን ስካይ ላይት ሆቴል እያቀማጠሉ ጎበዜን እና ተመስገንን እስር ቤት ማሰቃየት ተገቢ አይደለም። መከላከያ ውስጥ ያለ አሠራርን መተቸት መከላከያን ከመውጋት በላይ የሚያስጠይቅ ወንጀል አይደለም።

አቦይ ስብሐትን የፈታው ኃይል ታዲዮስ ታንቱን መልቀቅ ሲከብደው፣ ከጻድቃን ጋር የተደራደረው አካል ከዘመነ ካሴ ጋር መነጋገር ሲሳነው ማየት በእጅጉ ያስገርማል። #ሰለባዎቻችሁን ፍቷቸው‼️
አቦይ ስብሐትን የፈታው ኃይል ታዲዮስ ታንቱን መልቀቅ ሲከብደው፣ ከጻድቃን ጋር የተደራደረው አካል ከዘመነ ካሴ ጋር መነጋገር ሲሳነው ማየት በእጅጉ ያስገርማል። #ሰለባዎቻችሁን ፍቷቸው‼️

ጌታቸው ረዳ "ከባዱ ነገር ስምምነቱን መፈረሙ ሳይሆን የተስማሙትን መፈጸሙ ስለሆነ መንግሥት የአንዳንድ ውጫዊና ውስጣዊ ሃይሎችን ጫና ተቋቁሙ በቁርጠኝነትና በፍጥነት ስምምነቱን ተፈጻሚ ማድረግ ይኖርበታል" ብሏል። እናስ... ጌቾ የአፈጻጸሙ ጉዳይ ያሳሰበው ትጥቅ የማስፈታቱና ጊዜያዊ አስተዳደር የመመስረቱ ሒደቱ በጎረቤት ኃይሎች ተጽዕኖ እንዳይጓተትበት ሰግቶ ነው?😆 ቹቹ አለባቸውና ጌታቸው ሽፈራሁ መልስ ይኖራችሁ ይሆን?

"ሕዝባችን ጦርነት ሰልችቶታል" በማለቱ የተነሳ በእነ ናትናኤል መኮነንና ሙክታሮቢች ትዕዛዝ ወደ እስር ቤት የተወረወረ ወንድማችንን ፍቱት።
"ሕዝባችን ጦርነት ሰልችቶታል" በማለቱ የተነሳ በእነ ናትናኤል መኮነንና ሙክታሮቢች ትዕዛዝ ወደ እስር ቤት የተወረወረ ወንድማችንን ፍቱት።