Leaguesport
Відкрити в Telegram
ሊግ ስፖርት በየሳምንቱ ቅዳሜ እምትወጣ የስፖርት ጋዜጣ ናት https://www.leaguesport.net
Показати більше2 405
Підписники
-124 години
-97 днів
-5130 день
Архів дописів
2 405
ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ማጣርያ ላይ ተሳታፊ የሆነው ኢትዮጵያ ከ20 ዓመት ብሔራዊ ቡድን 40 ተጫዋቾችን በመጥራት ባካሄደው ናሽናል ካምፒንግ ለቅድመ ዝግጅቱ ብቁ የሆኑ ተጫዋቾችን በመለየት የጊዜያዊ ስብስቡን ቁጥር ወደ 25 ቀንሷል።
ቡድናችን የሴካፋ ቅድመ ዝግጅቱን ቅዳሜ የሚጀምር ይሆናል።
2 405
ከ23 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ድልድል ይፋ ሲሆን ኢትዮጵያ በመጀመርያው ዙር ከዩጋንዳ ጋር ተደልድላለች። ጨዋታዎቹ ከመስከረም 10-26 ሲደረጉ ወደ ተከታዩ ዙር የሚያልፈው ሀገር በሁለተኛው ዙር ሞሮኮን የሚገጥም ይሆናል።
2 405
ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ማጣርያ ላይ ተሳታፊ የሆነው ኢትዮጵያ ከ20 ዓመት ብሔራዊ ቡድን ለሚያደርገው ቅድመ ዝግጅት ናሽናል ካምፒንግ የተጠሩ 40 ተጫዋቾች ዝርዝር
ጥሪ የተደረገላችሁ ተጫዋቾች ረቡዕ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ/ም በኢትዮያ ስፖርት አካዳሚ ሜዳ እንድትገኙ ጥሪ ቀርቧል።
2 405
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የምድብ 10 የመጀመርያ ጨዋታ ሱዳንን የሚገጥምበት ቀን እና ቦታ ታውቋል።
የሱዳን እግር ኳስ ማኅበር የሜዳውን ጨዋታ ለማድረግ የደቡብ ሱዳኑ ጁባ ናሽናል ስታዲየምን መምረጡን አሳውቋል። በዚህም መሠረት ጨዋታው ዓርብ መስከረም 15 ቀን 2019 ዓ/ም ምሽት 1:00 ላይ ይካሄዳል።
2 405
+3
በካፍ የሴቶች ቻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ማጣርያ ተሳታፊ የሆነው የ2018 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ አሸናፊው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የጁቡቲው ኡጄኮን 11-0 በማሸነፍ ውድድሩን በድል ጀምሯል።
ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እሙሽ ዳንኤል (5)፣ ረድዔት አስረሳኸኝ (2)፣ ሊድያ ኢያሱ (2)፣ እፀገነት ግርማ እና ታሪኳ ዴቢሶ ጎሎቹን ማስቆጠር ችለዋል።
2 405
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የምርጫ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ለፌዴሬሽኑ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት በላከው ደብዳቤ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም ለሚደረገው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንታዊ እና በፕሬዝዳንቱ አቅራቢነት የሚመረጡ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ከነተጠባባቂያቸው በፌዴሬሽኑ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት እስከ ነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት እንዲልኩ ማሳወቁ ይታወሳል፡፡
ኮሚቴው ነሐሴ 5 ፣ ነሐሴ 11 እንዲሁም ነሐሴ 13 ባደረጋቸው ስብሰባዎች የቀረቡ እጩዎችን ሰነድ የምርመራ እና የማጣራት ተግባር አከናውኗል፡፡ በዚህም መሠረት ለዕጩ ፕሬዝዳንታዊ ተወዳዳሪነት የቀረቡት ብቸኛ ተወዳዳሪ አቶ ኢሳያስ ጅራ ቦሾ መሆናቸውን አሳውቋል።
2 405
የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ የ2019 የውድድር ዘመን ጥቅምት 28/2019 የሚጀመር ሲሆን የተጫዋቾች የዝውውር እና ምዝገባ ጊዜ ከነሐሴ 14/2018 - ጥቅምት 4/2019 ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
2 405
የኢትዮጵያ ሊግ አንድ የ2019 የውድድር ዘመን ጥቅምት 28/2019 የሚጀምር ሲሆን የተጫዋቾች የዝውውር እና ምዝገባ ጊዜ ጊዜ ከነሐሴ 25/2018 - ጥቅምት 16/2019 ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
2 405
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ2019 የውድድር ዓመት ጥቅምት 21/2019 የሚጀመር ሲሆን የተጫዋቾች ዝውውር እና ምዝገባ ጊዜ ከነሐሴ 18/2018 እስከ ጥቅምት 8/2019 ክፍት ሆኖ ይቆያል።
2 405
+9
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የሜዳ ላይ ልምምዱን በዛሬው ዕለት ሽሮ ሜዳ አካባቢ በሚገኘው ጨፌ ሜዳ ላይ ረፋድ 3:00 እና ከቀኑ 10:00 ላይ አከናውኗል።
2 405
ካፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የሜዳው ጨዋታውን በባህር ዳር ስታዲየም እንዲያከናውን ጊዜያዊ ፈቃድ መሰጠቱ ይታወሳል።
በዚህም መሰረት በ2027 የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ 10 ሁለተኛ የምድብ ጨዋታውን ከሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ጋር በባህር ዳር ስታዲየም ማክሰኞ መስከረም 19/2019 ከቀኑ 10፡00 ላይ የሚያከናውን ይሆናል።
