cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Eshet Pre-Primary,Primary and Middle school

Eshet Pre-Primary,Primary and Middle school 👉 @eshetprime2013 Eshet Library 👉 @eshetprimelibrary

Більше
Рекламні дописи
1 545
Підписники
-524 години
+177 днів
+6630 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Фото недоступнеДивитись в Telegram
ለ2016ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት
Показати все...
👏 2
የ2017 የትምህርት ዘመን የተከለሰ የትምህርት ካላንደር
Показати все...
👍 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
የሚኒስትሪ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡ ➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
Показати все...
👍 2
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅር እና የመተሳሰብ እንዲሆን እንመኛለን።
Показати все...
👍 5
Фото недоступнеДивитись в Telegram
👍 1
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2017 የትምህርት ዘመን የትምህርት ጊዜ ሰሌዳ /የትምህርት ካላንደር/ (ሰኔ 7 /2016 ዓ.ም)  በ2017 የትምህርት ዘመን በከተማ አስተዳደሩ ስር ባሉ የመንግስት፣ የግልና በሌሎች የተያዙ ቅድመ አንደኛ ፣ አንደኛ ፣ መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ወጥነት ያለው የትምህርት አተገባበር በማስፈለጉ የትምህርት የጊዜ ሰሌዳ /የትምህርት ካላንደር/ እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል፡፡ . ከሰኔ 24 እስከ 30/2016 ዓ.ም ድረስ የነባር ተማሪዎች ምዝገባ እና የመጽሐፍት ስርጭት . ነሃሴ 20 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ መምህራን በትምህርት ቤታቸው ተገኝተው ሪፖርት በማድረግ አጠቃላይ የመምህራን ጉባኤ ይደረጋል . ከነሃሴ 21-30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የ7ተኛ እና የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ምዝገባ ይከናወናል:: . ጳጉሜ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን ድረስ አስፈላጊውን መረጃ አሟልተው የሚመጡ አዲስ የተማሪዎች ምዝገባ ይከናወናል . መስከረም 3 ቀን 2017 ዓ.ም  ለተማሪዎች ስለ ት/ቤቱ ህገደንብና ተያያዥ ጉዳይ ላይ ገለጻ ይሰጣል . መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም   መደበኛ ትምህርት ይጀምራል .  መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም ትምህርት በሬዲዮ ስርጭት ይጀምራል .  ህዳር 16-18 ቀን 2017 ዓ.ም አንደኛ ወሰነ ትምህርት አጋማሽ ፈተና ይሰጣል .  ከጥር 7-9 ቀን 2017 ዓ.ም  ለ6ኛ ፣ ለ8ኛ እና ለ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ይሰጣል .  ከጥር 19-23 ቀን 2017 ዓ.ም አንደኛ ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና ይሰጣል .   ከጥር 26-29 ቀን 2017 ዓ.ም መምህራን ፈተና የሚያርሙበት እና ውጤት ማጠናቀሪያ ሳምንት .   ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም መምህራን የተማሪዎችን የፈተና ውጤት የሚያሳውቁበት ይሆና . የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም  የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት ይጀምራል .  ሚያዚያ 6-8 ቀን 2017 ዓ.ም  የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት አጋማሽ ፈተና ይሰጣል .   ግንቦት 19-22 ቀን 2017 ለ6ኛ፣ለ8ኛ እና ለ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ይሰጣል .  ከሰኔ 3-4 ቀን 2017 ዓ.ም  ድረስ የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ይሰጣል .  ከሰኔ 9-11 ቀን 2017 ዓ.ም   ድረስ የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ይሰጣል .   ከሰኔ 16-20 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ  ሁለተኛ  ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና ይሰጣል .  ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ መምህራን የተማሪዎችን የፈተና ውጤት የሚያሳውቁበት ይሆናል .  ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም  የውጤት መግለጫ ካርድ በመስጠት የዓመቱ ትምህርት ይጠናቀቃል ማሳሰቢያ፡- 1.  በ1ኛ ወሰነ ትምህርት 103 የትምህርት ቀናት ሲኖሩ በ2ኛ ወሰነ ትምህርት 101 ቀናት በጠቅላላው በዓመቱ 204 የትምህርት ቀናት አሉ፡፡ 2. ትምህርት ቢሮ የትምህርት ካላንደሩና ካላሻሻለ በስተቀር ማንኛውም ትምህርት ቤት ከካላንደሩ ውጪ የትምህርትን ስራ ማከናወን የተከለከለ ነው፡፡
Показати все...
G6 Exam 2016
Показати все...
Env. Science Exam G6-2015.pdf5.18 KB
👍 2
G 6 Exam 2015
Показати все...
Mathematics Exam G6-2015.pdf3.30 KB
G 6 EXam 2015
Показати все...
English Exam G6-2015.pdf4.12 KB
G6 Exam 2015
Показати все...
Amharic Exam G6-2015.pdf4.69 KB