uk
Feedback
A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU

A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU

Відкрити в Telegram

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU

Канал A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU (@aahdabofficial) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 32 515 підписників, посідаючи 324 місце в категорії Нерухомість та 1 037 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 32 515 підписників.

За останніми даними від 21 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -120, а за останні 24 години на -2, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 20.81%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 14.33% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 6 767 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 4 660 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 0.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 22 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Нерухомість.

32 515
Підписники
-224 години
+537 днів
-12030 день
Архів дописів
የአዲስ አበባ ምክር ቤት የመሬት እና ግንባታ ጉዳዮች እና የመሰረተ ልማት እና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች በገርጂ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ በሚካሄድበት ሳይት ዛሬ ምልከታ አካሄዱ፡፡ ምልክ
+9
የአዲስ አበባ ምክር ቤት የመሬት እና ግንባታ ጉዳዮች እና የመሰረተ ልማት እና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች በገርጂ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ በሚካሄድበት ሳይት ዛሬ ምልከታ አካሄዱ፡፡ ምልክታው በዋናነት ትኩረት ያደረገው በሳይቱ እየተከናወኑ የሚገኙ ግንባታዎች የደረሱበት ደረጃ እና የመሰረተ ልማት ቅንጅት ስራዎች ግንባታው ከተጠናቀቀ በኋላ ሳይሆን ከጅምር ምን እየተሰራ ነው የሚለውን ለማየት ነው ያሉት የመሬት እና ግንባታ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ዶ/ር አቶሜ አበበ ናቸው፡፡ የመሰረተ ልማት እና የማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ዶ/ር ግዛቸው አይካ በበኩላቸው ቤት በጥራትም በብዛትም እየጨመረ በመሆኑ መንገድ ፤ ውሀ እና ፍሳሽ እንዲሁም መብራት ከቤቶች ጋር በቅንጅት በመስራት ቀድሞ ማለቅ ያለበትን በማጠናቀቅ የህዝቡን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ካስጀመራችው የ100 ሺ ቤት ግንባታዎች መካከል የገርጂ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሳይት እንዱ ነው ያሉት ክብርት ቅድስት ወ/ ጊዮርጊስ የቤቶች ልማት እና አስተደደር ቢሮ ኃላፊ ሲሆኑ መንግስት ከቤት ግንባታ ወደ ቤት አቅርቦት በመሽጋገር አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማጣመር በፍጥነት እና በጥራት 24/ 7 እየሰራቸው የሚገኙ 18 ሳይቶች መኖራቸውንም ገልፀዋል፡፡ አዳዲስ ለተጀመሩ ሳይቶች መሰረተ ልማት አቅርቦት ቅድሚያ የሚሰጠው በመሆኑ የመሰረተ ልማት እቅራቢ ተቌማት በቅንጅት መስራት አለባቸውም ብለዋል፡፡ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aahdab

የመሬት እና ግንባታ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በልደታ ክፍለከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ምልከታ አካሄደ፡፡ የአዱስ አበባ ምክር ቤት የመሬት እና ግንባታ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ በልደታ ክፍለከተማ ቤቶች
+9
የመሬት እና ግንባታ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በልደታ ክፍለከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ምልከታ አካሄደ፡፡ የአዱስ አበባ ምክር ቤት የመሬት እና ግንባታ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ በልደታ ክፍለከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት በመገኘት ምልከታ አካሄዷል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ዶ/ር አቶሜ አበበ ክፍለ ከተማው በርካታ በህገወጥ የተያዙ ቤቶችን በማስለቀቅ እና ለሚመለከታቸው በመስጠት ያከናወነው ተግባር ለሌሎች ክፍለከተሞችም አርአያ የሚሆን ሲሆን ከዚህም ሌላ ጽ/ቤቱ የተሻለ አገልግሎት አሰጣጥም የታየበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ጽ/ቤቱ ጠንካራ እና የተሻሉ አሰራሮችን አጠናክሮ በማስቀጠል ከዚህ በበለጠ አሰራሩን ለማሻሻል መስራት ይጠበቅበታልም ብለዋል፡፡ የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ክብርት ቅድስት ወ/ጊዮርጊስ በበኩላቸው የልደታ ክፍለ ከተማ ቤቶች በቴክኖሎጂ የተሻለ አሰራር መኖሩ ፤ በተለያየ ምክንያት ወደ ሲስተም ያልገቡ ቤቶችን ከስር ከስር እያስገቡ መሆኑ ፤ ውል ያልገቡ ቤቶችን ወደ ውል ስርአት ማስገባታቸው እና በሌሎችም ስራዎች የተሻለ አፈፃፀም ላይ የሚገኝ ነው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aahdab

የመረጠንን ህዝብ የምናመሰግነው በቃላት ብቻ ሳይሆን ችግሩን የሚፈቱ ተጨባጭ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት ነው። በተጣለብን በህዝብ እምነት ዳግም ኢትዮጵያን ለመምራት ተጨማሪ አምስት ዓመት ለፓርቲያችን ብልፅግና በተሰጠበት ማግስት በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት እጅግ የተጎሳቀለውን፥ ለኑሮ ምቹ ያልሆኑ መኖሪያ ቤቶችንና አካባቢውን ወደ ንፁህ ፥ውብ መንደር ለመቀየር ከከንቲባ ፅ/ቤት ጀርባ ላይ “ አራዳ የበጎነት መንደር “ግንባታን ጀምረናል። በክረምት በጐ ፍቃድ 2500 ቤቶችን ለመገንባት ያቀድን ሲሆን ፣ዛሬ ባስጀመርነዉ የአራዳ የበጎነት መንደር ባለ 9 ወለል 8 ህንፃዎች እና ሁለት በላ 4 ወለል የገበያ ማዕከል ያሉት ሲሆን ፥ የተጎሳቆሉ ቤቶችን እና አካባቢውን በመቀየር ለኑሮ ምቹ የሆኑ ፣ ንጽሕናቸውን የጠበቁ የመኖሪያ ቤቶችና አካባቢዎች፣ የጋራ መገልገያዎችን እና አረንጓዴ ሥፍራዎችን እንዲሁም ህፃናት ቦርቀው የሚጫወቱባቸው የስፓርት ሜዳዎች በጥቅሉ ለሰው ልጆች ምቹና ክብር የሚመጥን ዘመናዊ አኗኗርን የሚፈጥር የከተማዋን ውበት የሚቀይር መንደር ነው። በክረምት በጎ ፍቃድ የምንገነባው ቤት ብቻ ሳሆን አካባቢን እናፀዳለን፥ የጐርፍ መከላከያዎች እንገነባለን፣ ምንም ገቢ ለሌላቸው ማዕድ እናጋራለን፥ ደም ልገሳ እናካሄዳለን፥ የጀመርነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ እንተክላለን፣ የማጠናከርያ ትምህርት እንሰጣለን፣ የነፃ ህክምና አገልግሎት ፣ የመንገድ ትራፊክ ማሳለጥ እንዲሁም ከተማችን ውብ ፥ ለኑሮ ምቹ ከተማ የማድረግ ስራችን እጠናክረን እንሰራለን። የምንገነባው መተማመንን፣ ፅናትን፣ አብሮነትን፣ ወንድማማችነትን/ እህትማማችነትን፣ ክብራችንን በጥቅሉ የኢትዮዽያን የብልፅግና መንገድ ነው። የከተማችን ባለሃብቶች የህዝባችን አኗኗር ለመቀየር በምንሰራቸው ልማቶች ሁሉ ስንጠራችሁ ቀና እና ፈጣን ምላሽ ስለምትሰጡን እጅግ አድርገን እያመሰገንን፤ ዛሬም ግንባታውን የጀመርነው የአራዳ የበጎነት መንደር አብራችሁ ለመገንባት ቃል የገባችሁ ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፥ የኢትዮዽያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣በላይነህ ክንዴ ፥ ያደታ ጁነዲን እያንዳንዳቸው አንድ ባለ 9 ወለል ህንፃ የሚገነቡ ሲሆን እንዲሁም ቲኤንቲ ኮንስትራክሽን፣ ግራንድ ሌጋሲ ሃውስ፥ ኢቲ ኦንላይን ኮሌጅ፣ አብይ ማስረሻ፥ ዴማ ሪልስቴት ፥ ቴምር ሪልስቴት፥ ስናፕ ትሬዲንግ፥ ጊፍት ሪልስቴት፥ መሃመድ አድናን ፥ አሚር በድሩ በጋራ ለመገንባት አብራችሁን ስለሆናችሁ በነዋሪዎች እና በራሴ ስም ከልብ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የህዝብ ድምጽ አሸንፏል፤ ኢትዮጵያ በልጆቿ ጸንታለች! መላው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዴሞክራሲን በማፅናታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን! የተከበራችሁ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለፓርቲያችን ብልፅግና የሰጣችሁት ድምፅ የቃል ኪዳናችን ማሰሪያ በማድረግ የጣላችሁብን አደራ በላቀ ስኬት ለመመለስ እንተጋለን። ይህ ምርጫ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት የሀገራችን የዴሞክራሲ ጉዞ ወደ አዲስ ምዕራፍ የተሻገረበት ደማቅ የታሪካችን አካል ሆኖ ተመዝግቧል ። በመዲናችን አዲስ አበባ በተደረገው የከተማ ምክር ቤት ምርጫ፣ ፓርቲያችን ብልፅግና ከጠቅላላው 158 መቀመጫዎች ውስጥ 134፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከ23ቱ የምክር ቤት መቀመጫዎች ውስጥ 20 መቀመጫዎችን በማግኘት የህዝብን ሙሉ አመኔታና አብላጫ ድምፅ በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ከ158 የከተማ ምክርቤት መቀመጫዎች ውስጥ 11 የተፎካካሪ ፓለቲካ ፒርቲዎች 23 መቀመጫዎች ያገኙ ሲሆን የግል ተወዳዳሪ 1 ወንበር ማሸነፍ ችለዋል። አዲስ አበባ ከምትወከልበት ከ23ቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች ውስጥ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች 2 እንዲሁም የግል ተወዳዳሪ 1 ወንበሮችን ማሸነፍ ችለዋል። ይህ እጅግ አስደናቂ ዉጤት እያደገ የመጣዉን የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል እና የህዝብን ፍትሐዊ ዳኝነት ያሳያል። በጥቅሉ ፓርቲያችን በአብላጫ ድምፅ ቢያሸንፍም በዋናነት ያሸነፈዉ መላው የመዲናችን ነዋሪ ፣ ሰላም እንዲሁም ልማት እና እያደገ የመጣዉ የዴሞክራሲ ባህል ነው። የተከበራችሁ መራጮቻችን ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከለሊት እስከ ለ‍ሊት በምርጫ ጣቢያዎች በመሰለፍ ምርጫው ነጻ፣ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ አግባብ እንዲጠናቀቅና ለብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ በመስጠት እምነት ለጣላችሁብን ለቀጣዩ ጉዟችንም የህዝብ አደራን በአግባቡ እንድንወጣ አቅማችን ለሆናችሁ በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን። በቀጣዩ የ5 ዓመቱ ጉዟችን ህዝባችን የሰጠንን ታላቅ አደራ በገባነው ቃል መሠረት ሌት ተቀን በመሥራት፣ የከተማችንን ብሎም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ ተግባራዊ ምላሽ እንሰጣለን። በተለመደው መልኩ ከህዝባችን ጋር በመተባበር በከተማችን የተጀመረውን የለውጥ ጉዞን በማሳለጥ የህዝባችን ኑሮ እና አኗኗር ለመለወጥ ያለንን ቁርጠኝነት ዳግም እናረጋግጣለን! ይህ ድል የብልፅግና ፓርቲ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ድል ነው! ዲሞክራሲን እያፀናን ልዩነቶቻችንን በሰለጠነ መንገድ እያስተናገድን፣ በአንድነትና በፓርቲያችን መሪነት ወደ ላቀ ከፍታ እንጓዛለን። ምርጫውን በማስፈጸም፣ በመታዘብ ፣ ሰላምን በማስጠበቅ ዉጤታማ ስራ የሰራችሁ እንዲሁም የኢትዮጵያን እውነት ለዓለም በማሳየት ረገድ የሀገሪቱን ህግና ስርዓት ተከትላችሁ የዘገባችሁ የሚዲያ ተቋማት ከሁሉ በላይ የሀገራችሁ ዴሞክራሲ አንድ እርምጃ ወደፊት እንዲራመድ የበኩላችሁን የተወጣችሁ በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ! በመጨረሻ በሀገር አቀፍም ሆነ በከተማ ደረጃ የፖለቲካ ልዩነት ወደ ፖሊሲ አማራጭ በማሳደግ በዚህ ምርጫ ላይ ተፎካክራችሁ በህዝብ ይሁንታ ወንበር በማግኘት የአዲስ አበባ ምክርቤት አባል ለመሆን የበቃችሁ የ11 ፖለቲካ ፓርቲዎች ወኪሎችና አንድ የግል ተወዳዳሪ በሰላማዊ መንገድ ህዝባችሁን ለማገልገል ዕድል በማግኘታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን ። ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና በልጽጋ ለዘላለም ትኑር! እንኳን ደስ አላችሁ የብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ 438 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎችን አሸነፈ
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ 438 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎችን አሸነፈ

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያውያን ያደረጉት ስኬታማ ተሳትፎ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ትልቅ እርምጃ ነው - የአፍሪካ ህብረት ኢትዮጵያውያን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያደረጉት ስኬታማ ተሳትፎ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት ታዛቢ ልዑክ እና የህብረቱ የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደህንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት የማሳወቂያ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ ኢትዮጵያውያን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያሳዩት ተሳትፎ ለስኬታማ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ትልቅ እርምጃ መጀመራቸውን በተግባር ያረጋገጠ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያውያን እያደረጉት ላለው ለዚህ ስኬታማ ጉዞ የአፍሪካ ህብረት ትልቅ አድናቆት እንዳለው አረጋግጠዋል። የአፍሪካ ህብረት፣ አባል ሀገራቱ ወደ ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር በሚያደርጉት ጉዞ ፍጹም ገለልተኛ፣ ሚዛናዊ እና ነጻ በሆነ መንገድ የመደገፍ ግዴታ እንዳለው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በቀድሞ የኬንያ ፕሬዚዳንት ዑሁሩ ኬንያታ የሚመራ የህብረቱ የምርጫ ታዛቢ አሰማርቶ እንደነበር አስታውሰዋል። ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማግስትም የአፍሪካ ህብረት ልዑክ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርትን በማስመልከት መግለጫ ማውጣቱን አስረድተዋል። ህብረቱ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር ለነበረው ግንኙነት አድናቆታቸውን ገልጸው፤ በዚህች ታላቅ ሀገር ቀጣይነት ላለው መሻሻልና ለዴሞክራሲ መጎልበት በጋራ ለመሥራት ቃል እንገባለን ብለዋል። አህጉራችን ዴሞክራሲን ከመቀበል ውጪ ሌላ አማራጭ የላትም በማለት፣ ሁሉም የአፍሪካ ሀገራትና ባለድርሻ አካላት ሰላማዊ፣ አካታችና ሙሉ ተሳትፎ የሰፈነበት ዴሞክራሲን ለማስፈን ቁርጠኛ ሆነው እንዲቀጥሉ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያን የሰጡት ድምፅ የህዝብ አደራና የክብር ማህተም ነው-ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያን የሰጡት ድምፅ ከዜጎች የተሰጠ ታላቅ አደ
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያን የሰጡት ድምፅ የህዝብ አደራና የክብር ማህተም ነው-ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያን የሰጡት ድምፅ ከዜጎች የተሰጠ ታላቅ አደራ ብቻ ሳይሆን የህዝብ አገልጋይነት ማረጋገጫ የክብር ማህተም መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ይፋ አድርጓል። በዚህም ቦርዱ እንዳሳወቀው፤ ብልጽግና ፓርቲ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ከተሰጠባቸው እና ውጤታቸው ይፋ ከሆኑ የምርጫ ክልሎች አብላጫ ድምጽ አግኝቷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላት፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ከእያንዳንዱ ህዝብ ድምፅ የተሰጠ ታላቅ አደራ ብቻ ሳይሆን የህዝብ አገልጋይነት ማረጋገጫ የክብር ማህተም ነው ብለዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያን የሰጧቸው ድምጾችም የዕድገትና የብልፅግና ማህተም መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ በድምፁ አመኔታ የሰጣቸው የፖለቲካ ፓርቲዎችና ግለሰቦች ከባዱን ኃላፊነት በጸጋ በመቀበል ለህዝብ የልማት፣ የዕድገትና ብልጽግና ትሩፋት በርትተው እንዲሰሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ የክልል ምክር ቤት ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ አብላጫዉን መቀመጫ አገኘ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ማሳወቂያ መርሐ-ግብር አካሄዷል፡፡ ቦርዱ ግንቦት 2
በአዲስ አበባ ከተማ የክልል ምክር ቤት ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ አብላጫዉን መቀመጫ አገኘ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ማሳወቂያ መርሐ-ግብር አካሄዷል፡፡ ቦርዱ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የምርጫ ክልል በተካሄደዉ የ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ሂደት አብላጫ መቀመጫ ያገኙትን ተወዳዳሪዎች ይፋ አድርጓል፡፡ በአዲስ አበባ በሚገኙ 10 የምርጫ ክልሎች ለክልል ምክር ቤት ከቀረቡ 158 መቀመጫዎች መካከል ብልጽግና ፓርቲ 134 መቀመጫዎችን ሲያገኝ ኢዜማ 8 መቀመጫዎችን ማግኘቱን ቦርዱ ይፋ አድርጓል፡፡ ቦርዱ ይፋ ባደረገዉ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት መሰረት ፡- 👉 የአዲስ አበባ የምርጫ ክልል ብዛት - 10 👉 አጠቃላይ የክልል ምክር ቤቱ መቀመጫ ብዛት - 158 👉 ብልጽግና ፓርቲ - 134 መቀመጫዎች 👉 ኢዜማ ፓርቲ - 8 መቀመጫዎች 👉 አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - 4 መቀመጫዎች 👉 ህዳሴ ፓርቲ - 2 መቀመጫዎች 👉የኦሮሞ ነጻነት ግንባር - 2 መቀመጫዎች 👉 ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት - 2 መቀመጫዎች 👉 ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት - 2 መቀመጫዎች 👉 የወላይታ ህዝቦች የነፃነት ንቅናቄ - 1 መቀመጫ 👉 የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ - 1 መቀመጫ 👉 የወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - 1 መቀመጫ 👉 አቶ ዳንኤል ጌታቸዉ ጋረደዉ የግል ተወዳዳሪ - 1 መቀመጫ ማግኘታቸዉን ቦርዱ ይፋ አድርጓል፡፡ በአዲስ አበባ በተካሄደዉ 7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ 1 ሚሊዮን 957 ሺህ 676 መራጮች ድምጽ ለመስጠት የተመዘገቡ ሲሆን ከነዚህ መካከል 96 መቶ የሚሆኑት መራጮች በየምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምጽ ሰጥተዋል፡፡ AMN

ብልፅግና ፓርቲ በሕዝብ የተሰጠውን አዲስ የዴሞክራሲና ማኀበራዊ ውል መሠረት በማድረግ፣ የሥልጣን ባለቤትነቱ የሕዝብ መሆኑን በተግባር ያረጋግጣል። በቀጣይ ዓመታት መንግሥታችን የሕዝባችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመራቸውን ዘርፈ ብዙ ውጤታማ ሥራዎች አጠናክሮና አስፍቶ የሚሄድ ሲሆን፣ በተለይም የሕዝብ ጥያቄዎች የሆኑና የጋራ ጥረት በሚጠይቁ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ከሕዝባችንና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በሙሉ በመተባበር ምላሽ እንዲያገኙ ርብርብ የምናደርግ ይሆናል። ከዚህ አንፃር ዘላቂ ሰላምና ፀጥታን ለማስፈንና የሕግ የበላይነትን በፅኑ መሠረት ላይ ለመገንባት፣ የኑሮ ውድነትን ለማቃለልና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን በስፋት ለመፍጠርና የዜጎቻችንን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና ሀገራዊ አስተዋጽኦ ለማሳደግ፣ የተጀመረውን የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በሀገር አቀፍ ደረጃ በስፋት በማስፋፋት፣ የቢሮክራሲ ማነቆዎችን በመበጣጠስና የአገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ በማዘመን፣ ሌብነትንና ብልሹ አሠራርን በቆራጥነት ለመከላከልና የተገልጋዩን ሕዝብ እርካታ በከፍተኛ ደረጃ ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት የምንሰራ ይሆናል። በተጨማሪም በመገባደድ ላይ የሚገኘው የሀገራዊ ምክክር ሂደት የታለመለትን ዓላማ እንዲያሳካ በሚገባ በመደገፍ፣ የዴሞክራሲ ተቋማትን ይበልጥ ነፃ፣ ገለልተኛና ጠንካራ እንዲሆኑ በማጠናከር፣ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ብሔራዊ ጥቅማችንን ማዕከል ባደረገ መልኩ በትብብር በመስራት ገንቢ ሃሳቦቻቸውንና አቅማቸውን ለማካተት የጀመርናቸውን ጥረቶች የምናልቅ ይሆናል። በአጠቃላይ ብልፅግና ፓርቲ የገባውን ቃል ሳይሸራረፍ በመተግበር፣ ምርጫ የሥልጣን መቆናጠጫ ሳይሆን ሕዝብን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገያ ታላቅ አደራ መሆኑን በተጨባጭ ያረጋግጣል። ለዚህም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና በተግባር የማረጋገጥ ታሪካዊ ጉዟችንን ከምንጊዜውም በላይ በበለጠ ትጋት፣ አንድነትና ቁርጠኝነት አጠናክረን ለመቀጠል ለተከበረው ሕዝባችን ዳግም ቃላችንን እናድሳለን! ብልፅግና ፓርቲ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት ይፋ መሆንን ምክንያት በማድረግ ከብልፅግና ፓርቲ የቀረበ የምስጋና መልዕክት፤ እጅግ የተከበራችሁ ውድ ኢትዮጵያዊያን፣ የተከበራችሁ የፖለቲካ ማኅበረሰብ አባላትና የምርጫው ባለድርሻ አካላት፤ ዛሬ ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲን በተግባር ያሳዩበት፣ ታሪካቸውን በደማቁ የጻፉበት እና አፍሪካ ስለ ራሷ በራሷ መወሰን እንደምትችል ለአለም ያበሰሩበት ታላቅ ምዕራፍ መመዝገቡ ይፋ ተደርጓል! በታሪካዊው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ሕዝባችን ትናንትን በማከም እና ነገን በፅኑ መሠረት ላይ በመተለም፣ የኢትዮጵያን ከፍታ እውን ለማድረግ ፋና ወጊ ለሆነው ለብልፅግና ፓርቲ ዳግም ታላቅ ኃላፊነትና አደራ ሰጥቷል። ብልፅግና ፓርቲ ይህንን ታላቅ ሕዝባዊ አደራ የተቀበለው በስኬቱ ሳይኩራራ፣ ጉድለቶቹን እያረመ ሕዝብን በቅንነት ለማገልገልና ቃልን በተግባር ለማረጋገጥ ባለው ፅኑ እምነት ነው። ለዚህ ታላቅ ክብር መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሰጠንን የዴሞክራሲ ውል በታላቅ ትሕትና እና በከፍተኛ አክብሮት እንቀበላለን። ይህ የምስጋና መልዕክት እኛን ለመረጡን ዜጎች ብቻ የቀረበ አይደለም፤ ይልቁንም ያሻቸውን አማራጭ በመምረጥ መብታቸውን የተጠቀሙ፣ በካርዳቸው ድምፅ በመንፈግም ቢሆን ሂደቱ ሕጋዊና ሰላማዊ እንዲሆን የበኩላቸውን የተወጡ ዜጎችን ሁሉ ያጠቃልላል። ምክንያቱም የእያንዳንዱ ዜጋ ተሳትፎ የሀገራችን ዴሞክራሲ እውነተኛ አሸናፊ እንዲሆን አድርጓል። በዚህ ምርጫ ሂደት ውስጥ በግልጽ መለየት ያለበት መሠረታዊ እውነት አለ፡- የብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ አግኝቶ መንግሥት የመመሥረት መብት ማግኘቱ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና የማረጋገጥ ራዕይ ሰንቆ ውጤታማ ጉዞ እያደረገ እንዳለ ፓርቲ እንደ ትልቅ እድል የሚወሰድ ሲሆን፤ የምርጫው ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሓዊና ተዓማኒ ሆኖ መጠናቀቅ ግን የውድ ሀገራችን ኢትዮጵያ እና የመላው ሕዝቧ ስትራቴጂያዊ አሸናፊነት ማረጋገጫ ነው! ይህ ምርጫ እንደ ከዚህ ቀደሙ የተለመደ የፖለቲካ ውድድር ወይም ወቅታዊ ኩነት አልነበረም። ይህ ምርጫ የውስጥና የውጭ የሴራ መረቦችን የበጣጠሰ፣ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በተግባር ያደመቀ፣ የዴሞክራሲ ተቋሞቻችንን ብስለት ያጎለበተ ታላቅ የታሪክ እመርታ ነው። ኢትዮጵያ በማንኛውም ውጫዊ ጫና ሳትበገር፣ ሙሉ በሙሉ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ ክንውን ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መሳተፋቸው የሕዝባችንን የፖለቲካ ንቃት የሚያሳይ ሲሆን፣ የሕዝብን ድምፅና ሉዓላዊ ፈቃድ ማክበር የመንግሥትና የማንኛውም የፖለቲካ ተዋናይ ቀዳሚ ተግባር መሆኑ በተግባር ተረጋግጧል። በምርጫው የኢትዮጵያ ጠላቶች ሀገርን ለማወክ የሸረቡት ተንኮልና መፍጨርጨር በሕዝባችን ብስለት ሙሉ በሙሉ እንዲመክን ተደርጓል። የዚህ ታሪካዊ ስኬትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት መረጋገጥ ያለ ባለድርሻ አካላት ተጋድሎ ሊታሰብ አይችልም። በመሆኑም ፓርቲያችን ብልፅግና ለምርጫው ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ የላቀ ምስጋናውንና አክብሮቱን ያቀርባል፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ ሕዝብ የአገር ህልውናንና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በፅኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ያለውን የማይናወጥ ወገንተኝነት በተግባር ባሳየበት በዚህ ታሪካዊ የምርጫ ሂደት፣ በተለይም በምርጫው ዕለት ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ እግር ጥሎት ሳይሆን ራዕይ መርቶት፣ ብርድና ድካምን በሀገራዊ ፍቅር እያሸነፈ፣ እስከ ሚቀጥለው ቀን ሌሊት 10 ሰዓት ድረስ ለሙሉ 24 ሰዓታት ያለመሰልቸት በታላቅ ትዕግሥትና ዲሲፕሊን ተሰልፎ ሕገ-መንግሥታዊ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ታሪካዊ ቁርጠኝነትና የፖለቲካ ብስለት ለፓርቲያችን ብልፅግና ብቻ ሳይሆን ለመላው ታዳጊ ዴሞክራሲዎችና ለአፍሪካ አህጉር አዲስ የተግባር ማስተማሪያና የሉዓላዊነት ተምሳሌት በመሆኑ፣ ለዚህ አስተዋይና ስልጡን ሕዝብ ፓርቲያችን ከፍ ያለ አክብሮቱን፣ ኩራቱንና ጥልቅ የሆነ ሕዝባዊ ምስጋናውን በታላቅ ትሕትና ያቀርባል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ አጠቃላይ የምርጫ ሂደቱን ፍፁም በሆነ ገለልተኝነት፣ በከፍተኛ ሙያዊ ብቃት፣ በትዕግስትና በሕጋዊነት መርህ በመምራት የኢትዮጵያን ተቋማዊ ነጻነት በዓለም ፊት ስላስመሰከረ የላቀ አድናቆትና ምስጋና ይገባዋል። 42 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከ10 ሺህ በላይ ዕጩ ተወዳዳሪዎች በሂደቱ መሳተፋቸው ሕዝባችን አማራጮችን በሰፊው መዝኖ እንዲመርጥ አድርጓል። በመሆኑም ከውጭና ከውስጥ ይነፍስ የነበረውን የሀሰት ወጀብ ተቋቁማችሁ፣ ለሰላማዊ የሃሳብ ውድድር እና ለሕግ የበላይነት ያሳያችሁት ስልጡን ቁርጠኝነት ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ባህል ማበብ ታላቅ መሠረት ጥሏል። እናንተ የሕዝብ ሉዓላዊነት አክባሪዎችና የሀሳብ ፖለቲካ ታጋዮች ናችሁና ትልቅ ክብርና ምስጋና ይገባችኃል። የፌዴራልና የክልል የጸጥታና ደህንነት ተቋማት፣ ሕዝቡ ያለምንም ስጋት በነጻነት ወጥቶ ድምፁን መስጠት እንዲችል ሌት ተቀን በመሥራት፣ መስዋዕትነት በመክፈል እና ሀገርን ከጥፋት ኃይሎች በጽናት በመጠበቅ ታላቅ ኃላፊነት ተወጥተዋል። እናንተ የሀገር ጠበቃ እና የሕዝብ የቁርጥ ቀን ልጆች ናችሁና ትልቅ ክብርና ምስጋና ይገባችኃል። የሚዲያ ተቋማት ሕዝቡ በመብቱ እንዲጠቀም፣ ነፃና ሚዛናዊ የምርጫ ድባብ እንዲፈጠር ከቅድመ ምርጫ እስከ ድህረ ምርጫ ሙያችሁን አክብራችሁና ለሀገራችሁ በፅኑ ታምናችሁ ላበረከታችሁት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ምስጋና ይገባችኋል። የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ በመንቀሳቀስ፣ ለዜጎች ሰፊ የዴሞክራሲና የመራጮች ትምህርት በመስጠት፣ የሕዝባችን የፖለቲካ ንቃት እንዲያድግና መብቱን እንዲረዳ በማድረግ ረገድ የማይተካ ሚና ተጫውታችኋል። በምርጫው ዕለትም በሺዎች የሚቆጠሩ ታዛቢዎችን በየምርጫ ጣቢያው በማሰማራት ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ፣ ሕጋዊና ፍትሐዊ እንዲሆን ሀገር በቀል አቅማችሁንና ተቋማዊ ነጻነታችሁን በተግባር ስላሳያችሁ ታላቅ አክብሮትና ምስጋና ይገባችኋል። የአፍሪካ ህብረት እና ኢጋድ “ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ” የሚለውን ታላቅ መርህ በተግባር በማሳየት፣ አህጉራዊና ቀጠናዊ ተቋማቶቻችን ታሪካዊ ኃላፊነታቸውን በብቃት መወጣት እንደሚችሉ ዳግም አስመስክረዋል። የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የአህጉራችን ኩራትና የተምሳሌትነት ማሳያ መሆኑን በመመስከር፣ የምርጫውን እውነተኛነትና ተዓማኒነት በዓለም መድረክ ከፍ ስላደረጋችሁ፤ ላሳያችሁት ፅኑ ፓን-አፍሪካዊ ወንድማማችነት፣ ቀጠናዊ አጋርነትና ታሪካዊ ቁርጠኝነት ፓርቲያችን ብልፅግና የላቀ ምስጋናውንና አክብሮቱን ያቀርባል። ሌሎች ቀጣናዊ ተቋማትና ወዳጅ ሀገራትም የኢትዮጵያን ተጨባጭ እውነታ በትክክል በመረዳት፣ አጠቃላይ የምርጫውን ሂደት በልዩ ትኩረት ለተከታተላችሁ እና ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁን በመመስከር አዎንታዊና ጠቃሚ ግብረ መልሶችን ለሰጣችሁ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አባላት፣ ቀጣናዊ ተቋማትና ወዳጅ ሀገራት በሙሉ ፓርቲያችን ብልፅግና የላቀ ምስጋናውን ያቀርባል። የእናንተ ሚዛናዊና እውነተኛ ምስክርነት የሀገራችንን ተቋማዊ ተዓማኒነት የሚያጎለብት ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያ ጀመረችውን የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ የሚደግፍ ታሪካዊና ስትራቴጂያዊ አጋርነት ማረጋገጫ በመሆኑ በታላቅ አክብሮት እንቀበለዋለን።

ከተመሠረተ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ፣ መሶብ የኢትዮጵያን የሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት መሠረታዊ በሆነ መንገድ ለውጦታል። ውጤቶቹም በራሳቸው ይናገራሉ። #PMOEthiopia
ከተመሠረተ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ፣ መሶብ የኢትዮጵያን የሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት መሠረታዊ በሆነ መንገድ ለውጦታል። ውጤቶቹም በራሳቸው ይናገራሉ። #PMOEthiopia

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም አረንጓዴ ዐሻራ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር በምስል፡-
+9
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም አረንጓዴ ዐሻራ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር በምስል፡-

አዲስ አበባ በአረንጓዴ ልማት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ በሚያደርጋት መስመር ላይ ናት - አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በአዲስ አበባ የተከናወኑ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ከተማዋ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትን መስመር እንድትይዝ አስችለዋል አሉ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም አረንጓዴ ዐሻራ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ‘‘ተስፋን እንትከል’’ በሚል መሪ ሀሳብ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል፡፡ አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ እንደ ሀገር በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተከናወኑ ሥራዎች ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ለዘላቂ ልማት አይተኬ ሚና እያበረከቱ ነው፡፡ ሀገራዊ ንቅናቄው በተቋም ደረጃ በተቀናጀ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑ ሥራውን ይበልጥ ውጤታማ እንዳደረገው ጠቅሰው፥ በዚህም ዓለም አቀፍ እውቅና መገኘቱን አስታውሰዋል፡፡ በዚሁ የአረንጓዴ ልማትና ውበት ሥራ አማካኝነት አዲስ አበባ በአፍሪካ ደረጃ በምሳሌነት የምትጠቀስ ከተማ እየሆነች መምጣቷን አውስተዋል፡፡ ከተማዋ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ በሚያደርጋት መስመር እየተጓዘች ነው ያሉት አፈ ጉባኤው፥ በተለይም በአረንጓዴ ልማት የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠል በላቀ ትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ ሁሉም ዜጋ የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ በላቀ ተነሳሽነት በመቀላቀል ለሀገር ዘላቂ ልማት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል።

እንኳን ለ2018 ዓ.ም የጋራ አሻራ ማኖር አደረሳችሁ !! ተስፋን እንትከል! በጋራ ሆነን  የአረንጓዴ አሻራን በማኖር ስራችን  ሀገራችን ዘመን የማይሽረው ታሪክ አስቀምጣለች። ባለፉ ሰባት  ዓመታት እንደሀገር በሁሉም ኢትዮጵያዊ ትብብር 48 ቢሊዮን ችግኝ በመትከል ታሪካዊ እና አስደማሚ አሻራ አኑረናል። በከተማችንም ባለፋት ሰባት  ዓመታት 90  ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል የአረንጓዴ ሽፋናችንን እጅግ ዝቅተኛ  ከነበረበት 2 .8 በመቶ  ወደ 24 በመቶ ማድረስ ችለናል። በአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብራችን የተራቆቱ አካባቢዎች አረንጓዴ ለብሰዋል፤ የነጠፉ ወንዞች እና አካባቢዎች ማንሰራራት ችለዋል። አዲስ አበባችንም ንፁህ፣ ውብ፣  ለመኖር ምቹ እና የቱሪስት ማዕከል  መሆን ችላለች። የምንተክለው ተስፋን፣ ልማትን፣ ልምላሜን፣ ጥላን፣ ምግባችንን  ብሎም ብልፅግናን ነው። የምንተክለዉ ለዛሬ ጥቅማችን  ብቻ ሳይሆን ለትውልድ እዳን ሳይሆን  የልምላሜና የብልፅግና ምንዳን ለማውረስ  ነው ። ዛሬ በከተማችን 6 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ ክቡር አቶ አገኘሁ ተሻገር በተገኙበት  በበሻሌ ወንዝ ዳርቻ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂደናል።  ውድ የከተማችን ነዋሪዎች በወንዝ ዳርቻዎች፤ በጤና፣ ትምህርትና  በሃይማኖት ተቋማት፤ በግል ሴክተሮች  እና  በጎዳናዎች ለምግብነት የሚውሉ አትክልት እና ፍራፍሬዎችን፣ የጥላ እና የውበት ዛፎችን በመትከል   ከተማችን ውብ፣ ጽዱ ኢረንጓዴና ለኑሮ ምቹ  ከተማ ለማድረግ  እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ህፃን አዋቂ ሳንል ሁሉም ዜጋ በጋራ በመሆን እንድናሳካው  ጥሪዬን አስተላልፋለሁ። ችግኝ መትከል ብቻ በቂ አይደለም እንክብካቤን  ይፈልጋል ። ስለሆነም የተከልናቸውን ችግኞች መከታተል፤  መንከባከብ ይኖርብናል። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ