A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU
📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU
Канал A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU (@aahdabofficial) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 32 616 підписників, посідаючи 328 місце в категорії Нерухомість та 1 028 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 32 616 підписників.
За останніми даними від 08 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 218, а за останні 24 години на 4, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 24.95%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 15.42% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 8 139 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 5 031 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 0.
📝 Опис та контентна політика
Опис каналу не надано.
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 09 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Нерухомість.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 09 липня | +1 | |||
| 08 липня | +15 | |||
| 07 липня | +4 | |||
| 06 липня | +8 | |||
| 05 липня | 0 | |||
| 04 липня | +1 | |||
| 03 липня | +11 | |||
| 02 липня | +3 | |||
| 01 липня | +7 |
| 2 | Немає тексту... | 2 896 |
| 3 | Немає тексту... | 3 924 |
| 4 | በአከራይ ተከራይ ውል የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም የተከለከለ ነው፡-
✍ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ
መከራየትና ማከራየት፤
✍ በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት የመኖሪያ ቤት
ኪራይ ውል በአዋጁ የተቀመጠው የጊዜ ገደብ
አሳልፎ ማስመዝገብ፤
✍ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ዕድሳት አለማስመዝገብ፤
✍ በአዋጁ ከተፈቀደው አግባብ ውጪ የዋጋ ጭማሪ
ማድረግ፤
✍ አዋጁ ከሚፈቅደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ
ከቤት ማስወጣት፤
✍ በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም
የማስጠንቀቂ ጊዜ ሳይሰጥ ውል ማቋረጥ፤
✍ አዋጁ ላይ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ
ክፍያ እንዲፈጸም ማስገደድ፤
✍ በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ የሆነ የኤሌክትሮኒክስ
መንገድ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ክፍያ አለመፈጸም፤
✍ ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም
ግንባታው ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ መኖሪያ
ቤት ያለአገልግሎት እንዲቀመጥ ማድረግ፤
✍ በአዋጁ ለአከራይ የተሰጠውን ማበረታቻ ያለአግባብ
ለመጠቀም ሀሰተኛ መረጃ ወይም ማስረጃ
ማቅረብ፡፡ | 4 664 |
| 5 | Немає тексту... | 6 265 |
| 6 | Немає тексту... | 6 630 |
| 7 | በአዲስ አበባ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ ጸደቀ ፤ ሕገ-ወጥ «የመንደር እና የአካባቢ ውሎች » በጥብቅ ተከለከሉ፡፡
ከዚህ ቀደም የወጣውን የከተማ ፍትሐዊ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥርና አስተዳደር ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 1320/2016 መነሻ በማድረግ፣ ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% መሆኑን የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል።
ዋጋ ጭማሪውና የውል እደሳቱ መነሻ የሚሆነው ከዚህ ቀደም በነበረው ውል ላይ የተቀመጠው የኪራይ ዋጋ ብቻ መሆኑንም ቢሮው አስታውቋል፡፡
በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል እድሳት ምዝገባ ከዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ መተግበር ጀምሯል።
የተጣሉ ጥብቅ ክልከላዎችና ሕጋዊ እርምጃዎች
አዲሱን የውል እድሳት ምዝገባና የተቀመጠውን የዋጋ ጣሪያ ወደ ጎን በመተው የሚፈጸሙ ማናቸውም ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ላይ ጥብቅ ክልከላ ተጥሏል።
በዚህም መሠረት፡-
በቢሮው ከተመዘገበውና ከሚመዘገበው ውል እንዲሁም ከሚሰጠው አቅጣጫ ውጭ፣ «ልዩ ውል» በሚል የሚፈጸሙ ማናቸውም የመንደር ውሎች፤
ከሕጋዊው አሰራር ውጭ የሚደረጉ የአካባቢ ውሎች፤
በጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) አካባቢ የሚደረጉ ማናቸውም ዓይነት ሕገ-ወጥ ውሎች ሙሉ በሙሉ የተከለከሉ መሆናቸውን ቢሮው አስገንዝቧል።
ማንኛውም አከራይ እና ተከራይ እነዚህን የተከለከሉ ሕገ-ወጥ ውሎች ይዘው ሲገኙ ወይም ከተቀመጠው የ11.5% የዋጋ ጭማሪ ጣሪያ በላይ ፈጽመው ከተገኙ፣ ቢሮው አስፈላጊውን ሕጋዊ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን በይፋ አሳስቧል።
ሀምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aahdab | 6 910 |
| 8 | Немає тексту... | 5 931 |
| 9 | በአዲስ አበባ የ2019 ዓ.ም የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ ተወሰነ ፤ የውል ምዝገባም ከ ዛሬ ሐምሌ 1 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት ታላቅ እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል።
ከዚህ ቀደም በወጣው የቤት ኪራይ ቁጥጥር አዋጅ መሠረት፣ ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው ፍትሐዊ የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መጽደቁን የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል እድሳት ምዝገባ ከዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት በይፋ መተግበር ይጀምራል።
ቢሮው እንዳመለከተው ፣ ይህ የዋጋ ማስተካከያ ውሳኔ በዘፈቀደ የተወሰነ ሳይሆን በከተማዋ ሰፊ ሳይንሳዊ ጥናት ተካሂዶ የነዋሪውን እውነተኛ የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ የተዘጋጀ ነው።
ይህ አሰራር በአንድ በኩል አከራዮች ወቅቱንና የኢኮኖሚ ሁኔታውን ያገናዘበ ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ የሚያረጋግጥ ሲሆን ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ተከራዮች ከገቢያቸው ጋር የተመጣጠነ ኪራይ በመክፈል ከተደጋጋሚ መፈናቀልና ከስነ-ልቦና ስጋት ድነው የተረጋጋ ሕይወት እንዲመሩ ያደርጋል።
ውሳኔው በከተማዋ ያለውን የኑሮ ውድነት ጫና በከፍተኛ ደረጃ በመቀነስ ረገድ የጎላ ማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ እና መልካም አስተዳደር ፋይዳዎች እንዳሉት ቢሮው አረጋግጧል።
የአከራይ-ተከራይ ግንኙነትን በሕግ ማዕቀፍ በመምራት የጋራ ተጠቃሚነትን እናረጋግጣለን!!
ሀምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aahdab | 6 692 |
| 10 | Немає тексту... | 5 653 |
| 11 | የሩሲያ ፌዴሬሽን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር ሰርጌ ላቭሮቭ እና የልዑክ ቡድናቸው ጋር ተወያይተናል።
ማምሻውን በነበረን የጋራ ጊዜ፣ የሁለትዮሽ ግንኙነቶች እና አዳዲስ የትብብር ዕድሎች ዙሪያ የተቃኘ ውይይት አድርገናል።
It was a pleasure to meet with Mr. Sergey Lavrov, Minister of Foreign Affairs of the Russian Federation, and his delegation this evening, during which our discussions focused on bilateral relations and exploring new opportunities for cooperation.
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) | 1 |
| 12 | የሩሲያ ፌዴሬሽን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር ሰርጌ ላቭሮቭ እና የልዑክ ቡድናቸው ጋር ተወያይተናል።
ማምሻውን በነበረን የጋራ ጊዜ፣ የሁለትዮሽ ግንኙነቶች እና አዳዲስ የትብብር ዕድሎች ዙሪያ የተቃኘ ውይይት አድርገናል።
It was a pleasure to meet with Mr. Sergey Lavrov, Minister of Foreign Affairs of the Russian Federation, and his delegation this evening, during which our discussions focused on bilateral relations and exploring new opportunities for cooperation.
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) | 6 097 |
| 13 | የሕ/ተ/ም/ቤት አባላት የ5 ዓመት የአገልግሎት ዘመን ማጠቃለያን በተመለከት የተላለፈ ምስጋና
#የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia | 5 564 |
| 14 | የትግራይን አሁናዊ ሁኔታ በሚመለከት፦
የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በርካታ ጥቅሞችን ያስገኘ ቢሆንም፣ ለምን ተስማማችሁ በሚል ያኮረፉ በርካታ ኃይሎች ተፈጥረዋል። ከሕወሓት ባሻገር፤ በትግራይ ላይ ጥፋት ሊቀጥል ይገባ ነበር ብለው የሚያስቡ አካላት በማኩረፍ ከእኛ የራቁ ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ እርስ በእርስ ለመተባበር የሞከሩበት ሁኔታ አለ።
አሁን ላይ በትግራይ ባሉ ኃይሎች በየቀኑ አዳዲስ ግጭቶችንና ጦርነትን ሊቀሰቅሱ የሚችሉ ትንኮሳዎች እየተፈጸሙ ይገኛሉ። ከሁሉ በላይ የሚያሳዝነውና የከፋው ጉዳይ ግን በአሁኑ ወቅት በርካታ የትግራይ ወጣቶች በጉልበት ታፍሰው በሱዳን እየተካሄደ ላለው ጦርነት እንዲሰለፉ መደረጉ ነው። እነዚህ ወጣቶች በማያውቁትና በማይመለከታቸው ጉዳይ በሱዳን ጦርነት ውስጥ ሕይወታቸውን እያጡ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ችግር ሳይበቃ፣ ጉዳዩ ወደ ሱዳንም ተሻግሯል።
በዚህ ሁሉ ሂደት ውስጥ የትግራይ ሕዝብ የችግሩ ፈጣሪ ሳይሆን፣ የችግሩ ገፈት ቀማሽ ነው። የትግራይን ሕዝብ ይበልጥ የጎዳውና ጉዳቱን ያባባሰው የማይታይ የውስጥ ቁስል መኖሩ ሲሆን እንዲህ ዓይነቱ የውስጥ ቁስል ደግሞ በቀላሉ የማይሽር ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ዛሬ በትግራይ ውስጥ ከሚኖረው ይልቅ በደሴ፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባ እና በአዳማ በሰላም እየኖረና ያለምንም ስጋት ወጥቶ የሚገባው የትግራይ ተወላጅ ቁጥር ይበልጣል።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia | 6 450 |
| 15 | ኢንዱስትሪን በሚመለከት፦
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ ለውጥ እያሳየ ይገኛል። አጠቃላይ የማኑፋክቸሪንግ አቅም ከነበረበት 47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ እንዲል ሰፊ ጥናቶች እና የድጋፍ ስራዎች ተከናውነዋል። ይህ እድገት ከነባሮቹ የኮምቦልቻ፣ የመቐለ እና የሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በተጨማሪ አስር አዳዲስ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመገንባት ከ80 በመቶ በላይ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን መሳብ ተችሏል። በተጨማሪም የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት የመተካት ስትራቴጂ ተግባራዊ ተደርጓል። በዚህም ሲሚንቶ፣ ብረት፣ ብርጭቆ እና ሴራሚክስን የመሳሰሉ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ብቻ ወደ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ መቆጠብ ተችሏል። ዘርፉ እያስመዘገበ ባለው ፈጣን እድገትም በማዕድን ዘርፍ 24 በመቶ፣ በማኑፋክቸሪንግ 20.3 በመቶ እና በኢነርጂ ዘርፍ ደግሞ 23 በመቶ ጭማሪ ታይቷል። ለወደፊቱም ይህን ስኬት ዘላቂ ለማድረግ ትኩረት የተደረገ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ዓመት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ብቻ የ12.7 በመቶ እድገት እና ከኢንዱስትሪ ምርቶች ኤክስፖርት የ1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia | 5 521 |
| 16 | ኤክስፖርትን በሚመለከት
#የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia | 4 653 |
| 17 | ግብርና እና የምግብ ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦
በዘንድሮው የምርት ዘመን 29 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1.3 ቢሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰብ መቻሉ እንዲሁም ዘርፉ የ7.7 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡ፤ የኢትዮጵያ ግብርና እያሳየ ላለው መዋቅራዊ ሽግግር ግልጽ ማሳያ ነው። በሀገር አቀፍ ደረጃ የተተገበረው የ‘ሌማት ትሩፋት’ መርሃ-ግብር አስደናቂ ውጤቶችን ያስመዘገበ ሲሆን፣ በተለይም አቮካዶን ወደ ውጭ በመላክ ከአፍሪካ 2ኛ ደረጃን መያዝ መቻሉ ለሀገሪቱ ተጨማሪ ከፍተኛ ገቢ በማስገኘት አስደናቂ ድል እንዲመዘገብ አስችሏል። ከዚህም በላይ ለረጅም ጊዜ በከባድ ድርቅ ይጎዳ የነበረው የቦረና ቀጣና ዛሬ በሰፊ የስንዴ ልማት ተሸፍኖ ማየት መቻሉ የስትራቴጂያዊ ግብርና ስራችንን ስኬታማነት ያረጋግጣል። ምንም እንኳ የዓለም አቀፍ ጫናዎች ቢበዙም፣ የማዳበሪያ እና የነዳጅ ዋጋ ቢንርም፣ በቁርጠኝነትና በጠንካራ ስራ በምግብ ራሳችንን ለመቻልና በአፍሪካ ላይ የተለጠፈውን የረሃብ ታሪክ ለመቀየር በተግባር እየሰራን እንገኛለን፤ ምክንያቱም ምርጫችን ለምኖ መኖር ሳይሆን ሰርቶ ማደር ነው!
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia | 4 529 |
| 18 | ከ100 በላይ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ ጀምረዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ ከ100 በላይ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች በይፋ ሥራ መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞና የቴክኖሎጂ ሽግግር አስመልክተው በሰጡት ሰፊ ማብራሪያ፣ በሀገራችን ከ5 ሚሊዮን በላይ ወጣቶችን በኮደርስ ሥልጠና ላይ በመመዝገብ በዚህም ትልቅ ስኬት መመዝገቡን ገልጸዋል።
የቴክኖሎጂ ልማቱ በኢኮኖሚውና በማኅበራዊ ዘርፉ ላይ እያመጣ ያለውን ዘርፈ-ብዙ ለውጥ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በአሁኑ ወቅት የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ እያደገ እንደሚገኝና የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ዩኒቨርሲቲ መዋቅርም በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን አስረድተዋል።
አክለውም በተለይም በስታርት አፖች (አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች)፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በገቢ አሰባሰብ እንዲሁም በአጠቃላይ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ላይ ቴክኖሎጂ ከፍተኛና ስትራቴጂካዊ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ በአጽንኦት ገልጸዋል። | 4 923 |
| 19 | የውጭ ጉዳይና ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦
ዓለም ሊካድ በማይችል ሁኔታ ተለዋዋጭ በሆነችበት በዚህ ወቅት፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፣ የውጭ ፖሊሲ እና ሉዓላዊነትን ለማስከበር በስትራቴጂካዊ ራስን መቻል ላይ የተመሠረቱ ሦስት ዋና ዋና መርሆችን እንከተላለን፤ የመጀመሪያው መቋቋም ሲሆን፤ ይህም የውጭ ተጽዕኖዎችን በራስ አቅም ለመቋቋም የሚያስችል ጠንካራ ተቋማዊ አቅምን መገንባት ላይ ያተኩራል። ሁለተኛው መጠቀም ሲሆን፤ ይህም ማንኛውንም የሚያጋጥም ፈተና ወደ ስትራቴጂካዊና መልካም የልማት ዕድል የመቀየር ብቃትን ያካትታል። ሦስተኛው ደግሞ መግራት ሲሆን፤ ይህም ሀገሪቱ የራሷን ብሔራዊ አጀንዳ ቀርጻ ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችን በልበ ሙሉነት እንድትጋፈጥና እንድትመራ ያስችላታል። በእነዚህ ሦስት ምሰሶዎች በመመራት በማንኛውም ብሔራዊ ውሳኔያችን ላይ የትኛውንም የውጭ አካል ጣልቃ ገብነት ፍጹም አንፈቅድም።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia | 4 344 |
| 20 | ሠላምን በሚመለከት
#የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia | 4 308 |
