ru
Feedback
A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU

A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU

Канал A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU (@aahdabofficial) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 32 656 подписчиков, занимая 324 место в категории Недвижимость и 1 030 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 32 656 подписчиков.

Согласно последним данным от 12 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 201, а за последние 24 часа — -14, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.36%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 14.71% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 8 279 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 4 802 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 0.

📝 Описание и контентная политика

Описание канала не предоставлено.

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 13 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Недвижимость.

32 656
Подписчики
-1424 часа
+377 дней
+20130 день
Архив постов
‎"የቤኒን ፕሬዝዳንት ክቡር ሮሙዋልድ ዋዳግኒን ተቀብዬ በወል ጉዳዮች ዙሪያ መክረናል። ‎ ‎የሁለትዮሽ ግንኙነታችን መጠናከር እና በጋራ ጥቅሞች ላይ የላቀ ትብብር ለማድረግ በሚያስችሉ እድሎች ዙሪያ
+2
‎"የቤኒን ፕሬዝዳንት ክቡር ሮሙዋልድ ዋዳግኒን ተቀብዬ በወል ጉዳዮች ዙሪያ መክረናል። ‎ ‎የሁለትዮሽ ግንኙነታችን መጠናከር እና በጋራ ጥቅሞች ላይ የላቀ ትብብር ለማድረግ በሚያስችሉ እድሎች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል። ለጥልቅ አጋርነት እና ለዘላቂ ወዳጅነት ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት ይበልጥ እንደምናሳድግ ጽኑ ፍላጎት አለን። " ‎ ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ‎

"ምከር ቤቱ ለህዝብ ተጠቃሚነት፣ ለዲሞክራሲያዊ ስርዓትና ለሃገር ግንባታ ወሳኝ መሆኑን በ 5 ዓመታት ቆይታ በተጨባጭ ማረጋገጥ ችሏል፡፡" ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከንቲባዋ ይህን ያሉት በም/ቤቱ 2ኛ ቀን ጉባዔ የቀረበዉን የም/ቤቱን የ 5 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት መነሻ በማድረግ ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነዉ፡፡ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ባለፉት 5 ዓመታት የህዝብን አደራ እና ኃላፊነት በተገቢዉ ሲወጣ መቆየቱን የጠቀሱት ከንቲባ አዳነችአቤቤ  የምክር ቤቱ ግምገማዎች እና የግምገማ ዉጤቶች ለከተማ አስተዳደሩ ግብዓት በመሆን ታላላቅ ስኬቶች በከተማዋ እንዲመዘገቡ የላቀ አስተዋፅኦ እንደነበረዉ ገልፀዋል፡፡ አያይዘዉም ከማከል እስከ ታችኛዉ መዋቅር ድረስ በአካል በመገኘት ፤ጠንካራ ክትትል እና ቁጥጥር በማድረግ  የአመራሩ እና የተቋማት አፈፃፀም ዉጤታማ እንዲሆን አስችሏል ብለዋል ፡፡ የምዘና ዉጤቶቻችን የእዉቅና ስርዓቶችም አንዱ የምክር ቤቱ የስራ ዉጤት ማሳያዎች ናቸዉ ሲሉ አክለዉ ገልፀዋል፡፡ በኦዲት ግንቶች ላይ ማስተካከያ እንዲደረግ ከማድረግ ባሻገር የአሰራር ተጋላጭነትን ለማስቀረት እንዲሁም ተጠቂነትን እንዲሰፍን ለማድረግ የተመራበት አግባብ ጠንካራ እንደነበረና ይህም የበለጠ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም የህዝብ ልሳን በመሆን ህዝቡ ለሚያነሳቸዉ ጥያቆዎች ትኩረት በመስጥት በአፈፃፀማቸዉ ዙሪያ ጭምር ትክክለኛ መረጃ ተደራሽ እንዲሆን የሚዲያ አካላት የበኩላቸዉን ሚ,ና እንዲወጡ ም/ቤቱ ያደረገዉ ጥረት የላቀ ነዉም ብለዋል፡፡ በሌላ በኩልም ምከር ቤቱ ለህዝብ ተጠቃሚነት፤ለዲሞክራሲያዊ ስርዓትና ለሃገር ግንባታ ወሳኝ መሆኑን በ 5 ዓመታት ቆይታ በተጨባጭ ማረጋገጥ በመቻሉ ለቀጣይ በበለጠ ማጠናከር ይገባልም ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ከቋሚ  ኮሚቴዉ ባለፈ እስከ ባለሙያዉ ድረስ በእዉቀት የታገዘ ጠንካራ የክትትል እና የቁጥጥር ስርዓት በመዘርጋት ሳይንሳዊ ትንታኔዎችን በተጨባጭ በመተግበር ለሁለተናዊ ለዉጥ በቅንጅት ተግቶ መስራትም አንዱ የትኩረት አቅጣጫ መሆን እንዳለበት ከንቲባ አዳነች በምላሻቸዉ ገልፀዉ ልባዊና የላቀ ምስጋናቸዉን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡

ማንኛውም የመኖሪያ ቤት አከራይና ተከራይ በውል እድሳት ወቅት ማሟላት ያለባቸው👇 👉 ቀደም ሲል የነበራቸውን የውል ስምምነት ሰነድ ፤ 👉 ኪራይ ሲከፋሉበት የነበረው የኤሌክትሮኒክስ የክፋያ ሠነድ
ማንኛውም የመኖሪያ ቤት አከራይና ተከራይ በውል እድሳት ወቅት ማሟላት ያለባቸው👇 👉 ቀደም ሲል የነበራቸውን የውል ስምምነት ሰነድ ፤ 👉 ኪራይ ሲከፋሉበት የነበረው የኤሌክትሮኒክስ የክፋያ ሠነድ ፤ 👉 የአከራይ እና የተከራይ የዲጂታል መታወቂያ የነዋሪነት መታወቂያ ፣ የመስሪያ ቤት መታወቂያ ፣ መንጃ ፍቃድ ፣ ፓስፖርት ፣ የጠበቃ ፍቃድ ፣ የሰራተኞች ጡረታ መታወቂያ ፣ የዩኒቨርሲቲ ወይም ኮሌጅ ተማሪ የሙያ ስራ ፍቃድ ኦርጅናል ኮፒ ፤ 👉 የመኖሪያ ቤት ውሉን የሚያድሰው በወኪል ከሆነ ህጋዊ ውክልና ፤ ኦርጅናል እና ኮፒ ይዘው መገኘት አለባቸው በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aahdab

የከተማችን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን ውሎ በማካሄድ ላይ እንገኛለን ። በዛሬ ማለዳው ክፍለ ጊዜ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5 ዓመት የህግ ማውጣት ሚና፣
+9
የከተማችን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን ውሎ በማካሄድ ላይ እንገኛለን ። በዛሬ ማለዳው ክፍለ ጊዜ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5 ዓመት የህግ ማውጣት ሚና፣ የህዝብ ውክልና አፈፃፀም፣ የአስፈፃሚ አካላት ክትትልና ቁጥጥር አፈጻጸም ሪፖርትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተወያይተን አፅድቀናል። በአሁኑ ሰአት የከተማችን ዋና ኦዲተር 107 የከተማዋ ተቋማት ላይ ያዘጋጀው ሪፓርት እየቀረበ ነው ። ውድ የከተማችን ነዋሪዎች ሁሉም አጀንዳዎች በአዲስ ሚድያ ኔትዎርክ ስርጭት እየተላለፈ ስለሆነ መከታተል ትችላላችሁ ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ያቀረቧቸው 12ቱ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች:: 1. የኢኮኖሚ መረጋጋት እና የኑሮ ውድነትን ማቃለል፡- የከተማዋ ነዋሪ ቀዳሚ ጥያቄ የሆነውን የኑሮ ውድነት መቋቋም ዋነኛ የትኩረት ሥራ ይሆናል። 2. የሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የሚመጡ ዕድሎችን በመጠቀም በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሥራ አጥነት ምጣኔን መቀነስ። 3. የመሠረተ-ልማት አስተዳደር፡- ባለፉት ዓመታት የተገነቡ ግዙፍ መሠረተ-ልማቶችን እና የኮሪደር ልማቶችን መጠበቅና አገልግሎታቸውን በዘላቂነት ማስቀጠል። 4. የሀብት አያያዝና ጥገና ፡- አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ከመጀመር ጎን ለጎን የተገነቡ መንገዶችን፣ መናፈሻዎችንና መብራቶችን በጥራት የመያዝና የመጠገን ባህል ላይ በጀት መመደብ። 5. የከተማ ውበትና ፅዳት፡- የተገነቡ የኮሪደር መስመሮች በፅዳትና በአረንጓዴነት እንዲቀጥሉ ከህብረተሰቡና ከግሉ ዘርፍ ጋር የተቀናጀ አሰራር መዘርጋት። 6. ትራንስፖርት እና የትራፊክ ፍሰት፡- ከከተማዋ ፈጣን እድገት ጋር አብሮ የሚሄድ ቀልጣፋ የሕዝብ ትራንስፖርት አቅርቦትና አስተዳደር ሥርዓትን ማጠናከር። 7. መልካም አስተዳደርና ዲጂታላይዜሽን፡- ብልሹ አሰራርን ለመቀነስ በ"አዲስ መሶብ" 50 በመቶ የደረሰውን አገልግሎት ወደ 100 በመቶ በማሳደግ አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ማዘመን። 8. የማህበራዊ ልማት ማጠናከር፡- የተማሪዎች ምገባና አልባሳት አቅርቦትን ማስቀጠል፤ እንዲሁም አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የጤና ባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ። 9. የገቢ አሰባሰብና ፋይናንስ ዲሲፕሊን፡- ለዘላቂ ልማት የሚውሉ ገቢዎችን በአግባቡ መሰብሰብ፣ የታክስ መሠረቱን ማስፋት እና ቁጠባን ማረጋገጥ። 10. ሰላምና ጸጥታን ማረጋገጥ፡- የማኅበረሰብ አቀፍ የጸጥታ አደረጃጀቶችን በማጠናከር ወንጀልን መቀነስ፣ እንዲሁም ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራና ግንባታን በመከላከል የሕግ የበላይነትን ማስፈን። 11. የቤት ልማት ፕሮግራሞች፡- የነዋሪውን የቤት ጥያቄ ለመመለስ በመንግስት፣ በግል ዘርፍና በሕብረት ሥራ ማኅበራት የቤት ልማትን በስፋት ማከናወን። 12. የውሃ እና የመንገድ ፕሮጀክቶች፡- የተጀመሩ ሜጋ የውሃ አቅርቦት ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ፣ እንዲሁም የመንገድ መሰረተ ልማትን በማስፋፋት ኔትወርኩን ማጠናከር። በአጠቃላይ አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ስሟና ግብሯ የተናበበ ስማርት ከተማ ለማድረግ የጀመርነው ልማት በጥራት፣ በስፋትና በፍጥነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል።

በ2018 በጀት ዓመት 350 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ችለናል። የገቢ መሰረትን በማስፋትና የሚሰበሰብ ገቢ ፍትሀዊነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲሰበሰብ በማድረግ በሰፊው በመሰራቱ የ2ዐ18 ገቢ አሰባሰብ
+4
በ2018 በጀት ዓመት 350 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ችለናል። የገቢ መሰረትን በማስፋትና የሚሰበሰብ ገቢ ፍትሀዊነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲሰበሰብ በማድረግ በሰፊው በመሰራቱ የ2ዐ18 ገቢ አሰባሰብ ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንፃር በ 116.3 ቢሊዮን ብር ወይም 50 % እድገት አሳይቷል። ግብር ከፋዮቻችንን ከልብ እናመሰግናለን!! ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ባስመዘገበቻቸዉ ስኬቶች በዓለም አቀፍ መድረክ እዉቅና ካገኘችባቸዉ ዋና ዋና ዎቹ፤- መዲናችን አዲስ አበባ በሁለንተናዊ መልካም ገጽታ በዓለም መድረክ ላይ በግልጽ ያሳዩ የቱሪዝም እና የኢ
+8
አዲስ አበባ ባስመዘገበቻቸዉ ስኬቶች በዓለም አቀፍ መድረክ እዉቅና ካገኘችባቸዉ ዋና ዋና ዎቹ፤- መዲናችን አዲስ አበባ በሁለንተናዊ መልካም ገጽታ በዓለም መድረክ ላይ በግልጽ ያሳዩ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ እድገት ታላላቅ ስኬቶችን አስመዝግባለች ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ፡፡ ከንቲባዋ አክለዉም በሪዮደጀነሪዮ የተቀበለችው የምገባ ኘሮግራም ሽልማት፤በደቡብ ኮሪያ የተበረከተውና ለከተማዋ አመራር እውቅና የሰጠው የሴኡል ስማርት ከተማ ሽልማት (2024) እንዲሁም ለቆሻሻ አወጋገድ ስርዓት መሻሻል በቦነሳረስ የተሰጠው እውቅና “ የC40 ከተሞች የብሉምበርግ ሽልማት ተጠቃሾች ናቸዉ ብለዋል፡፡ አያይዘዉም በናይሮቢ ኬንያ በተካሄደው የአፍሪካ ስማርት ከተሞች ኢንቬስትመንት ሰሚት የተሰጠው የአፍሪካ ምርጥ ስማርት ከተማ ሽልማት (2024) ሲሆን በመንገድ ደህንነትና ፍጥነት ማስተዳደር ላይ ባስመዘገበችው ውጤት በአለም አቀፍ የከተሞች የዘርፉ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ጭምር መሆኗን ተናግረዋል፡፡ በመጨሻም ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በተያያዘ አዲስ አበባ የብሉምበርግ ፊላንትሮፒስ የከተሞች ጥምረት አባል ለመሆን ችላለች ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለምክር ቤት አባላት ባቀረቡት ሪፖረት ገልፀዋል፡፡

የመኖሪያ ቤት አቅርቦትና አስተዳደር በተመለከተ፡- የነዋሪውን የቤት ጥያቄ ለመመለስ ባለፉት አምስት ዓመታት 496,971 ቤቶች ተገንብተዋል። ከእነዚህም ውስጥ 26,563 የመንግስት ቤቶች ለልማት ተነ
+8
የመኖሪያ ቤት አቅርቦትና አስተዳደር በተመለከተ፡- የነዋሪውን የቤት ጥያቄ ለመመለስ ባለፉት አምስት ዓመታት 496,971 ቤቶች ተገንብተዋል። ከእነዚህም ውስጥ 26,563 የመንግስት ቤቶች ለልማት ተነሺዎች፣ እንዲሁም ከ98 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በእጣ ተላልፈዋል። በአሁኑ ወቅትም በተለያዩ አማራጮች የ179,516 ቤቶች ግንባታ በመፋጠን ላይ ነው። በፋይናንስ አስተዳደር በኩል፤ ለረጅም ዓመታት የነበረ 62 ቢሊዮን ብር የጋራ መኖሪያ ቤት የባንክ ዕዳ የተከፈለ ሲሆን፣ በዘንድሮው በጀት ዓመትም 3.18 ቢሊዮን ብር የቦንድ ዕዳ ተመልሷል። በቤት አስተዳደር ዘርፍ ደግሞ የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባና ቁጥጥር የመጀመሪያ ምዕራፍ እየተጠናቀቀ የኪራይ ዋጋ ተመን ተወስኗል። በዚህም ከ500 ሺህ በላይ የነባር ውል እድሳትና አዳዲስ ምዝገባ ለማድረግ ዝግጅት ተጠናቋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ባህላዊ፣ ኪነ ጥበባዊ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሮአዊ ሀብቶችን መጠበቅና ማሳደግ በሚመለከት ብሔራዊ አንድነትና የጋራ ትርክት ከመገንባት፣የሀገርን መልካም ገጽታ ለመገንባት፣ የሕዝቦችን አንድነት፣ አብሮነትና
+9
ባህላዊ፣ ኪነ ጥበባዊ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሮአዊ ሀብቶችን መጠበቅና ማሳደግ በሚመለከት ብሔራዊ አንድነትና የጋራ ትርክት ከመገንባት፣የሀገርን መልካም ገጽታ ለመገንባት፣ የሕዝቦችን አንድነት፣ አብሮነትና ወንድማማችነት የሚያጠናክሩ በርካታ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል። የባህልና እሴቶች ጥበቃ ስራ ጋር ተያይዞ ፡ ባህላዊ እሴቶችንና አገር በቀል ዕውቀቶችን ለማሳደግ፣ እንዲሁም ጎጂ ልማዶችንና መጤ ባህሎችን ለመከላከል 6 የቶክሾው ውይይቶችና በርካታ የስልጠና ስርፀቶች ተካሂደዋል። የጀግኖች መታሰቢያ ስራችን በተመለከተ፡ በሀገርና በትውልድ ግንባታ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የኪነጥበብ ሰዎችና የሀገር ኩራት ለሆኑ አትሌቶች የክብር ሐውልት ቆሟል። የኪነጥበብ መሠረተ ልማት፡ ቲያትርና ሲኒማን ለማሳደግ ዘመናዊ መሣሪያዎች የተሟሉላቸው እጅግ ዘመናዊ ኮምፕሌክሶች ተገንብተዋል። ጥበብን ለሕዝብ ከማቅረብ አኳያ፡ ኪነጥበብ ወደ ሕዝብ ይበልጥ እንዲጠጋ ለማድረግ በርካታ አንፊ ቲያትሮችና የሕዝብ ፕላዛዎች በሰፊው ተገንብተው ለአገልግሎት በቅተዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የኑሮ ውድነትን ከማቃለል አንፃር የኅብረተሰቡን የኑሮ ጫና ለማቃለልና የምርት አቅርቦትን ለማሳደግ 259 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ተስፋፍተዋል። በተጨማሪም በ15.9 ቢሊዮን ብር ወጪ መጋዘኖችን፣ የጅ
+9
የኑሮ ውድነትን ከማቃለል አንፃር የኅብረተሰቡን የኑሮ ጫና ለማቃለልና የምርት አቅርቦትን ለማሳደግ 259 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ተስፋፍተዋል። በተጨማሪም በ15.9 ቢሊዮን ብር ወጪ መጋዘኖችን፣ የጅምላና የችርቻሮ ሱቆችን ያካተቱ 7 ዘመናዊ የግብርና ምርቶች መሸጫ ማዕከላት በከተማዋ መግቢያዎች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል። ቢሮክራሲን በመቀነስም ከ270 ሺህ በላይ አዳዲስ ነጋዴዎች ወደ ንግድ ሥርዓቱ እንዲቀላቀሉ ተደርጓል። በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ጫና ለማቃለል ለትራንስፖርት፣ ለጤና መድህን፣ ለተማሪዎች ምገባና ለዳቦ ምርት 18.2 ቢሊዮን ብር የመንግስት ድጎማ ተደርጓል። በተጨማሪም ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ መነሻ ካፒታል ያለው የንግድ ኮርፖሬሽን ሲቋቋም፤ መሠረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች በተለይም ስኳር እና የምግብ ዘይት በፍትሃዊነት እንዲሰራጩ ተከናውኗል። አቅርቦትን ለማጠናከርም ለ11 ዩኒየኖች የ825 ሚሊዮን ብር የተዘዋዋሪ ብድር ፈንድ ተሰጥቷል። ህጋዊነትን ለማረጋገጥ በተደረገ ቁጥጥር ህገ-ወጥ በነበሩ 24,568 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ሲወሰድ፣ 20,617ቱ ወደ ህጋዊነት ተመልሰዋል። በሌላ በኩል አዲስ አበባን አምራች ለማድረግ በተሰራው የከተማ ግብርና እና የሌማት ትሩፋት ስራ 1.2 ሚሊዮን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ሆነዋል። እንዲሁም ከይዞታቸው ለተፈናቀሉ አርሶ አደሮች 19,507 የይዞታ ማረጋገጫ ካርታዎች በመስጠትና ወደ ኢንቨስትመንት እንዲገቡ በማድረግ ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥ ተከናውኗል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አረንጓዴ አሻራ በተመለከተ:- በአረንጓዴ አሻራ የልማት ስራ፣ ቀደም ሲል 2.8 በመቶ ብቻ የነበረውን የከተማዋን የአረንጓዴ ሽፋን ባለፉት አምስት ዓመታት ወደ 24 በመቶ ማሳደግ ተችሏል። ከተማዋን ው
+9
አረንጓዴ አሻራ በተመለከተ:- በአረንጓዴ አሻራ የልማት ስራ፣ ቀደም ሲል 2.8 በመቶ ብቻ የነበረውን የከተማዋን የአረንጓዴ ሽፋን ባለፉት አምስት ዓመታት ወደ 24 በመቶ ማሳደግ ተችሏል። ከተማዋን ውብና ማራኪ ለማድረግ 7 ሺህ ሄክታር መሬት ለአረንጓዴ ልማት የዋለ ሲሆን፤ የችግኝ ተከላና እንክብካቤ ስራዎችም በስፋት ተከናውነዋል። በተጨማሪም እነዚህን አረንጓዴ ስፍራዎች ከህገ-ወጥ ወረራ ለመጠበቅ ለ266 ቦታዎች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተዘጋጅቶላቸዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ከጤና አገልግሎት በተመለከተ:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ዓመታት ከተማዋን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ በሰራው ስራ፤ የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ከእጥፍ በላይ በማደ
+9
ከጤና አገልግሎት በተመለከተ:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ዓመታት ከተማዋን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ በሰራው ስራ፤ የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ከእጥፍ በላይ በማደጉ የእናቶችና የጨቅላ ህፃናት ሞት ምጣኔን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ መቻሉን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሪፖርታቸው ገልጸዋል። በመሰረተ ልማት ረገድ፤ አዳዲስ እና ግዙፍ ሆስፒታሎች (እንደ አበበች ጎበና፣ ላፍቶ፣ ኮልፌ እና ገላን) እንዲሁም 9 አዳዲስ ጤና ጣቢያዎች ተገንብተዋል። የሆስፒታል አልጋዎች አቅም ከ1,384 ወደ 4,195 ያደገ ሲሆን (ይህም ባለፉት 100 ዓመታት ከተመዘገበው በእጥፍ ይበልጣል)፣ የአምቡላንስ ቁጥርም ወደ 109 ከፍ ብሏል። ሆስፒታሎቹም በዘመናዊ መሣሪያዎች ማለትም በMRI እና ሲቲ ስካን ተደራጅተዋል። በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን 2.7 ሚሊዮን ነዋሪዎች የታቀፉ ሲሆን፤ ከተማ አስተዳደሩ በየዓመቱ ከ1.3 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ ያደርጋል። የወረቀት አልባ የጤና መረጃ ስርዓትም (EMR) በ68 ተቋማት ተተግብሯል። በተጨማሪም ለማህበራዊ ፍትህ ሲባል ለ200 ታካሚዎች በዓመት 100 ሚሊዮን ብር በመመደብ ነፃ የኩላሊት እጥበት አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል። በሌላ በኩል የህዝብን ጤና ለመጠበቅ በተደረገ ጥብቅ ቁጥጥር፤ 193 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው 350 ሺህ ኪሎ ግራም የምግብ ምርቶች፣ 42 ሺህ ሊትር መጠጦች፣ እና 21 ሺህ ኪሎ ግራም ጊዜ ያለፈባቸው መድሃኒቶች እንዲወገዱ መደረጉን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል።

ፅዳት በተመለከተ በደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ከ5 ሚሊዮን ቶን በላይ ቆሻሻ ተሰብስቧል። የቆሻሻ አያያዝን ከመጣል ባለፈ ወደ 484 ሺህ ቶን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል፣ ኮምፖስት በማምረት እና ከ910 ሺ
+7
ፅዳት በተመለከተ በደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ከ5 ሚሊዮን ቶን በላይ ቆሻሻ ተሰብስቧል። የቆሻሻ አያያዝን ከመጣል ባለፈ ወደ 484 ሺህ ቶን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል፣ ኮምፖስት በማምረት እና ከ910 ሺህ ቶን በላይ ለኃይል ማመንጫ በማቅረብ ቆሻሻን ወደ ሀብትነት መቀየር ተችሏል። በዚህም አዲስ አበባ ከአፍሪካ 10 ፅዱ ከተሞች አንዷ በመሆን ዓለም አቀፍ እውቅናን አግኝታለች። ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የተቋም ግንባታ እና አገልግሎት አሰጣጥ በተመለከተ የከተማ አስተዳደሩ የተቋማት አገልግሎት እንዲዘምን በሰጠው ልዩ ትኩረት መሰረት ዋና መስሪያ ቤትን ጨምሮ 11 አዲስ "መሶብ" የአንድ ማዕከል ዲጂታል
+9
የተቋም ግንባታ እና አገልግሎት አሰጣጥ በተመለከተ የከተማ አስተዳደሩ የተቋማት አገልግሎት እንዲዘምን በሰጠው ልዩ ትኩረት መሰረት ዋና መስሪያ ቤትን ጨምሮ 11 አዲስ "መሶብ" የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ተከፍተዉ ወደ ስራ በመግባታቸዉ 150 የሚሆኑ አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል እየተሰጡ ይገኛሉ፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን ከ8 ተቋማት የተለዩ 41 የሚደርሱ አገልግሎቶች በከተማው ውስጥ ህዝብ በሚበዛባቸው አደባባዮች በመገኝት ተንቀሳቃሽ የአዲስ መሶብ አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን በአዲስ መሶብ ማዕከላት እስካሁን 262,784 በላይ ለሚሆኑ ተገልጋዮች አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ በእነዚህ ማእከላት የተገለገሉ የተገልጋዮች እርካታ በአማካይ 99 በመቶ ደርሷል። ወደ ማእከሉ ያልገቡ 45 አገልግሎቶች ዲጂታላይዝ በማድረግ አገልግሎት እየሰጡ በመሆኑ አጠቃላይ በዲጂታል የሚሰጡ አገልግሎቶችን ወደ 392 ማሳደግ ተችሏል፡፡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ተቋም ግንባታ በተመለከተ:- አዳዲስ ሪፎርሞችና አሰራሮች፡- በየተቋሙ የተጀመሩ አዳዲስ የሪፎርም ስራዎችን በመተግበር "በወርቃማዋ ሰኞ" አመራርና ሰራተኛው ስለተልዕኮው የሚወያዩበት፣ በረቡዕ እና አር
+3
ተቋም ግንባታ በተመለከተ:- አዳዲስ ሪፎርሞችና አሰራሮች፡- በየተቋሙ የተጀመሩ አዳዲስ የሪፎርም ስራዎችን በመተግበር "በወርቃማዋ ሰኞ" አመራርና ሰራተኛው ስለተልዕኮው የሚወያዩበት፣ በረቡዕ እና አርብ ደግሞ አመራሩ ተገልጋዮችን በአካል የሚያስተናግድበት አሰራር ሰፍኗል። በዚህም 87 በመቶ ተገልጋዮች በአግባቡ አገልግሎት ማግኘት ችለዋል። ከዚህም በተጨማሪ የተገልጋዮች መማክርት ጉባኤን በማቋቋም ተሳትፎን የሚያሳድግና ሌብነትን የሚቀንስ ሥርዓት ተዘርግቷል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ

7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በተመልከተ:- 7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ የዲሞክራሲና የፖለቲካ ባህል መሻሻል የታየበት እና በርካታ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በምክር ቤት ወንበር የገኙበት ይህም ህዝባችንን በትብብር ለማገልገ
+4
7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በተመልከተ:- 7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ የዲሞክራሲና የፖለቲካ ባህል መሻሻል የታየበት እና በርካታ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በምክር ቤት ወንበር የገኙበት ይህም ህዝባችንን በትብብር ለማገልገልና የጋራ ሀገራችንን ለመገንባት ወደ አዲስ ምዕራፍ የተሻገርንበት ከለዉጡ ማግስት ጀምሮ የተጎናፀፍነዉ የዚህ ትዉልድና ዘመን ድምር ዉጤታችን ነዉ፡፡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ከአፍሪካ አስር ፅዱ ከተሞች አንዷ ሆናለች!! የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2018 ዓ.ም ሪፖርት እና የ2019 ዋና ዋና አቅጣጫዎችን ለከተማው ምክር ቤት እያቀረቡ ይገኛሉ
+7
አዲስ አበባ ከአፍሪካ አስር ፅዱ ከተሞች አንዷ ሆናለች!! የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2018 ዓ.ም ሪፖርት እና የ2019 ዋና ዋና አቅጣጫዎችን ለከተማው ምክር ቤት እያቀረቡ ይገኛሉ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ እያቀረቡ ባለው ሪፖርት፤ ባለፉት አምስት ዓመታት ከተማዋን የሰላምና የልማት ማዕከል ለማድረግ ስር ነቀል ለውጦች መደረጋቸውንና እንደ አድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ የወል ትርክት መሰረቶች መገንባታቸውን ገልፀዋል። የከተማዋ ጎስቋላነት ከ74% ወደ 30% መቀነሱን፣ የ2.8% አረንጓዴ ሽፋን ወደ 24% ማደጉን እና መዲናዋ ከአፍሪካ አስር ፅዱ ከተሞች አንዷ መሆኗን ገልጸዋል። የጎዳናዎች መስፋትና መብራት የአዲስ አበባን የኮንፈረንስና ዲፕሎማሲ ማዕከልነት ይበልጥ እንዳጎላው አብራርተዋል። በማህበራዊ ፍትህ፤ የተማሪዎች ምገባ፣ የቤት ግንባታ፣ የሥራ ዕድል ፈጠራና የኑሮ ውድነትን የማቃለል ሥራዎች በስፋት መከናወናቸውን አንስተዋል። መዲናዋ በራስ ገቢ ከ60 ሺህ በላይ ፕሮጀክቶችን እንዳጠናቀቀችም ገልጸዋል። በተጨማሪም ብክነትንና ሌብነትን በማስቀረት ለዘላቂ ልማት የሚመደበውን የበጀት መጠን ከ47% ወደ 71% ማሳደግ መቻሉ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጡን ከንቲባዋ ለምክር ቤቱ እያቀረቡ ባለው ሪፖርት አብራርተዋል፡፡