cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ኖህቶኤል ከመጻሕፍት ገፅ📚

ይህ የኖህቶኤል ሀሳቦች የሚንፀባረቁበት ቻናል ነው። የምትስማሙባቸውን ለወዳጆ ሼር ያድርጉላቸው።🙏 @Noahtoael በማንበብ ብቁ እና ጤናማ እውቀት ያላቸውን ትውልድ እናፍራ! በዚህም ቻናል.! ፦አጫጭር አዝናኝ እና አስተማሪ ታሪኮች ፦ተከታታይ ታሪኮች ፦ትረካዎች ፦ግጥም እና ስነፅሁፎች .......ያገኛሉ!

Більше
Ефіопія6 351Амхарська4 700Книги8 099
Рекламні дописи
2 512
Підписники
+224 години
-57 днів
-2030 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

✅Bestselling
Показати все...
My Life in Shambles_ A Novel - Halle, Karina.pdf1.26 MB
Фото недоступнеДивитись в Telegram
📖My Life in Shambles: A Standalone Romance by Karina Halle ✅Bestselling
Показати все...
1
-- አብረን ዝም እንበል --- ከሰው መንጋ እንገንጠል ለአንድ አፍታ እንኳ እንገለል በእፎይታ ጥላ እንጠለል ዝም ብለን አብረን ዝም እንበል ምነው አዋሽ ማዶ ቆቃ የሸለቆ ግርጌ ሸሽተን የቆቃን ሰቆቃ ሰምተን ሲቃውን ሲሰብቀው አይተን ሰቀቀኑን ተወያይተን የምሽት ጀንበር ቢውጠን ውሃ አንደ ዱታ ሲተምም በድን ሸለቆ ሲናገር ሰማያዊ ፈረስ ተጭኖ ከአጥናፍ አጥናፍ ሲንደረደር ሲያስጉተመትም ሲያስገመግም በአይነ ህሊና ለመመስከር ሳንጨነቅ ሳንገደብ ለማንም ምንም ሳናዋይ ሳንናገር ሳንጋገር ካይንሽ ከልብሽ ከልቤ አዋሽ ማዶ አብረን እንብራር አዋሽ ማዶ አብረን እንውረድ አጉል ነው ብለን ሳንፈርድ ድንቅም ነው ሳንል ሳንወድ ዝም ብለን አብረን ብንወርድ ከሰው መንጋ ተለይተን ከጠረኑ ተነጥለን ከጉምጉምታው ተገንጥለን ከኳኳታው ብንከለል ከላንቃው ከድምፁ ሸሽተን በእፎይታ ጥላ እንጠለል በቆይታ በፀጥታ ዝም ብለን አብረን ዝም እንበል መቼም አይሆንም ካልሽ ቅሪ ግድ የለም አትገደሪ ልቦናሽ በመተረልሽ ባሳደረብሽ እደሪ ተስፋ መቀነን ነው መቼም የሰው ልብ አይችለው የለም ብቻ ዳግመኛ ሞት ሳንሞት አዲስ ቀን ሳይጨልምብን ድፍን ደመና ሳይቋጥር ክረምት ውጅት ሳይወርድብን ኮከባችንን ሳንጠራ ሳንቆጥርባት ሳትቆጥርብን ሞራችንን ሳናስነብብ ሳናሳያት ሳታይብን ጨረቃን መስክሪ ሳንል ሳናውቅባት ሳታውቅብን አዋሽ ማዶ ቆቃ በረን እባክሽ ጀንበር ትጥለቅብን ውሃ እንደ ዱታ ሲተምም በድን ሸለቆ ሲናገር በሰማይ ፈረስ ተጭኖ ከአጥናፍ አጥናፍ ሲንደረደር ሲያስጉተመትም ሲያስገመግም በአይነ ህሊና ለመመስከር ሳንጨነቅ ሳንገደብ ለማንም ምንም ሳናዋይ ሳንናገር ሳንጋገር ካይንሽ ከልብሽ ከልቤ አዋሽ ማዶ አብረን እንብረር ከሰው ኳኳታ እንነጠል ላንድ አፍታ እንኳ እንገለል በእፎይታ ጥላ እንጠለል ዝም ብለን አብረን ዝም እንበል ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን @Noahtoaels_idea
Показати все...
👍 1
Repost from Bemnet Library
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ትግረኛ አትችልም "አባቴ ይሙት !>> አለችኝ እየሳቀች። እውይ ጥርሶቿ ታይተው አይጠገቡም። የውበት አምላክ በጥንቃቄ የደረደራቸው የቀይ ባህር ዕንቁዎች ይመስላሉ። << ይህ ጉሮሮ የሚፍቅ ቋንቋ ! መጓጉጥ ነው። አልኳት << እንጥላችሁ ስላልተቆረጠ ይሆናል >> << እሰኪ መቶ በይ >> << ሞቶ >> << እስኪ አንተ በይ >> << አንቴ >> << አንቺም አማርኛ አትችይም አባቴ ይሙት >> አልኳትና መጠጧን ላመጣላት ሄድኩ። መጠጧን አመጣሁላትና << ሕራይ ትግርኛ ክትምህርኒ እሺ >> ሺ እምበአር ? ጸጋዬ ኃይለማርያም እባላለሁ >> አልኳትና መጠጧን ቀምሼ ሰጠኋት። እውነትም ጥሩ መጠጥ ነው። << በቲቪ አውቅሀለሁ አንተም አማርኛ ታስተምረኛለህ >> አለች ፡ ጠጉሯን እየነሰነሰች ፈገግታዋ ይናፍቃል። << ማን ብዬ ልጥራሽ ሰሜናዊት ጽብቖቲ ?>> ብዬ ስሟን ጠየኳት ሳቀችና << ፊያሜታ ጊላይ እባላለሁ >> ብላ ስሟን ነገረቺኝ። ስሟ ደንቆኝ ቅንድቤን ከፍና ዝቅ ሳደርግ አይታኝ "ምነው አለች። << እንግዳ ስም ነው ....>> << የጣሊያን ስም ነው ....>> << ምን ማለት ነው ? >> << ትንሽ ነባልባል ....>> << እውነት አንቺን ከሩቅ መሸሽ ይሻላል >> አልኳት " << ለምን አለችኝ >> << ስምን መላክ ያወጣዋል ይባላል። እንደ ስምሽ ከሆንሽ አደገኛ ነው። በትንሽ ነበልባል ተቃጥሎ ማለቅ ደግ አይደለም። እንደ ስምሽ እንዳልሆንሽ ተስፋ አደርጋለሁ አልኳት። << ነኝ አባቴ ይሙት >> አለች ስቃ። << እንዴት ? >> << በሕፃንነቴ እሳት ነበርኩ። እያቀስኩ ፣ እቃ እየሰበርኩ ፣ ከቤት እየጠፋሁ እናትና አባቴን ሳስቸግራቸው ነበር። ብቻዬን ደግሞ መተኛት አልወድም ነበር። ብቻዬን ካስተኙኝ ሌቱን በሙሉ ሳለቅስ አድራለሁ። ከእነሱም ጋር ተኝቼ እነሱ ሲጫወቱ የሰማሁ እንደሆነ አለቅሳለሁ። ለዚህ ሳይሆን አይቀርም ፊያሜታ የሚል ስም ያወጡልኝ >> በማለት አስረዳችኝ። << አሁንስ ? ብዬ ጠየኳት >> << አአሁንም ነባልባል ነኝ። ለምወደው ግን አይደለሁም። ለምወደው ሰው ማርና ወተት ነኝ። ስኳር ነኝ። << እና የምትወጂው ምን አይነት ሰው ይሆን >> << እንደ ድንጋይ የጠጠረ ፣ እንደ ብረት የጋለ ፣ እንደ ስኳር የጣፈጠ ወንድ >> ብላ እንደገና ሳቀች። << እውነት ? >> << ቀልዴን ነው። ምስጢሬን አሁን አልነግርህም .... >> << ምናለበት ? >> << ምስጢር ነው >> አለች። << እሺ ራሴ አንድ ቀን እደርስበት ይሆናል። ግን ስምሽን ብትውጪው ጥሩ ነበር .... >> << ለምን ? >> << የባዕድ ስም ነው። የአሥመራ መንገዶች ፣ ሱቆች ፣ ቡና ቤቶች ፣ ሆቴሎችና ሬስቶራንቶች ፋብሪካዎች ሳይቀሩ በባዕዳን ስም ነው የሚጠሩት። የጣሊያን ቅሪት ያው የባዕድ አስተሳሰብና አመለካከት ማስከተሉ አይቀርም። በዚህ ክፍለ ሀገር ከፍተኛ የባህል አብዬት ማካሄድ ያስፈልጋል ፣ በእውነት አይመስልሽም አልኳት። << ፊያሜታ ካስጠላህ ፋና በለኝ >> ብላ ዝም አለች። ደራሲ ፦ በዓሉ ግርማ ርዕሰ ፦ ኦሮማይ
Показати все...
3👍 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
አንዳንድ ቀን ገና ከእንቅልፍ ስተነሳ ትከሻህ ቅልል ይልሃል። ተንደርድረህ ሻወር ትገባለህ በስልክህ የሮፍናንን ዘፈን ከፍተህ እርቃንህን ሆነ እየዘፈንክህ ትወናወናለህ ። ባዘቦት ልብስህ ገድግደህ የዘነጥክ ይመስልሃል ። የጠዎቷ ፀሃይ ደስስ ትልሃለች። ጎረቤትህን እትዬ ጌጤ... ጋሽ ይልማ እንዴት ኖት ብለህ ድምፅህን አጮኸህ ሰላም ትላቸዋለህ ። የምታቃቸውን ሰዎች ድምቅ ያለ ሰላምታ እየገጨህ ትሄዳለህ ። እጮኛህ በፍቅረኛዋ ከተበደለችው ጓደኛዋ አንፃር አይታህ አንተ የኔ ቅዱስ አፈቅርሃለሁ ትልሃለች። እኔ ራሴ አፈቅርሻለሁ እስትንፋሴ ትላታለህ። መንገድ ላይ ያገኘከው ወዳጅህን አስጨንቀህ እንደው ስሞት ብለህ ወስደህ ጋብዘኸው ተጨዋውታቹ ቢል ስትል ተከፍሏል ትባላለህ። እንደው ምን ይሻለኛል ማን አለ እንደ እኔ እድለኛ የሚል ዘፈን ማውጣት ያምርሃል። የሞከርከው ስራ ተሳክቷል ለበለጠ መረጃ ቢሮ ና ትባላለህ። ቱግ ያለብህን ገለሰብ ዛሬ ደብሮት ነው የሚሆነው ብለህ ትረዳዋለህ። መንገድ ላይ አንድ ብር ስጠኝ የሚልህን ሰዎዬ ለምን አንድብር ብቻ ትጠይቃለህ ብለህ አስር ብር ትሰጠዋለህ ። ። ጤንነትህ ካንተ ጋ እንዳለ ይታወቅሃል ፤ በዙሪያህ ያሉ ፀዴ ፀዴ አብረውህ የሚሰሩ ፤ ወዳጆችህ፤ የሰፈር ሰዎች እንደሚወዱህ ይሰማሃል። እውነት ዛሬ ህይወት ደስ ትላለች። እወድሻለሁ ህይወት 😍❤
Показати все...
🥰 4👍 1
ምን አስባለው መሰላችሁ አንድንዴ ስኬት ሁሉ ደስተኛ አያረግም!! ህልምም በስኬት አይገባደድም! በሰዎች የተሻለ እና ምርጥ የሚባለው ቦታ ስኬት አይደለም!!
Показати все...
5
ላንቺና ለመንግስት የተፃፈ ደብዳቤ አንቺ እንዴት ነሽ ውዴ እኔ አለሁ አብጄ ሆዴን ውሸት ነፍቶት ከኩንታል ከብጄ፣ ወድጄ አይደለም ሰካራም የሆንኩት ለነፃነት ስል ነው መጠጥ የጀመርኩት። ምክንያቱም መንግስት አስሮ አያውቅም የሚጠጣን በአካል መሬት አይጠይቅም፣ ቀድሞንስ ሰካራም መች ቤት ሰርቶ ያውቃል። እንዲያው እንበልና ቢሰራም በላቡ ቢሰራም በእጁ መቼ ችሎ ይገባል ይወድቃል ከደጁ። እናልሽ ፍቅርዬ. . ጠዋት እነሳና መስኮቴን ከፍቼ ወደ ውጭ ወጣለው ባትሪዬን አብርቼ። አብጄ እንዳይመስልሽ እንዲህ የምሆነው መንግስትን ሰድቤ እብድ ለመባል ነው። ደግሞስ. . . ከጠላና ከጠጅ ሌላ እንደው ምን ይላል የህዝብ እንባ ጠጥቶ ከመስከር ይሻላል። እናልሽ ወዳጄ እኔ ያንቺን ደብዳቤ ፅፌ እስክጨርስ ስንት ርቆ ሔደ ዳግም ላይመለስ ስንቱ ቤቱን አጣ ስንቱ ፈረሰበት ስንቱ መንግድ አጣ ስንቱ ራቀበት ስንቱ ጥርሱን አጣ ስንቱ ደሞ አይኑን ስንቱ እጁን አጣ ስንቱ ደሞ ራሱን ይሔ ሁሉ ሲሆን እንዴትስ አልጠጣ እንዴትስ አልሰክር ሰው ህይወቱን ሲያጣ ለማይነጋ ጀምበር። ተራራ ነው ብለን የገፋነው ሁሉ አልተናደም ፍቅሬ ሲመሽ ጨለማ ነው ሲነጋም ጨለማ ካልነጋልን ዛሬ። እናልሽ ወዳጄ የላኪ ስም ብዬ ከደብዳቤው አናት እኔ ስም አልፃፍኩኝ ምናልባት አንብበው ከርቸሌ እንዳይከቱኝ። 😂😂😂😂 እንግዳወርቅ ከሰኔ ወር ትዝታዎች @semetnbegtm @semetnbegtm @semetnbegtm
Показати все...
👍 2 2
ምርጥ ታሪክ ፅፌ አቀረብኩላችሁ!! አንድ ኩራተኛ የሆነ ሰው ጥሩ ልብስ ለብሶ በኩራት ታጅቦ እራሱን እየቆለለ፤ በአንድ ገበያ ይዘዋወር ነበር። ታድያ ፈሳሽ ጁስ የምትሸጥ ሴትዬ በአጠገቡ ስታልፍ ይመለከታል። ጠራትና "ምንድነው የምትሸጭው አላት?" እሷም: "ፈሳሽ ጁስ ነው ጌታዬ" አለችው እሱም፡ አሳይኝ በእንስራ የያዘችውን ፈሳሽ ከጀርባዋ ላይ ለማውረድ ስትሞክር ድንገት የሰውየው ልብስ ላይ ይህ ፈሳሽ ይደፋበታል። ሰውየው ከባድን ቁጣ ተቆጣ። እንዲህም አላት "የዚህን ልብስ ዋጋ እስከምትከፍይኝ ከዚህ ቦታ የትም አልሄድም" ሲል ዛተ። ሴትየዋም እያለሳለሰች ትለማመጠው ጀመር። "እባክህ ተወኝ ጌታዬ ምክንያቱም እኔ ምስኪን ነኝ" አለችው። ሰውየውም " እስክትከፍይኝ የትም አልሄድም" አላት። እሷም ዋጋውን "ስንት ነው?" ስትል ጠየቀችው። እሱም "1000ብር" ሲል መለሰላት። እሷም... "እኔ እኮ ደሃ ሴት ነኝ ከየት አመጣለሁ" አለችው። እሱም.. "ምን አገባኝ" በማለት ፍፁም ጭካኔውን አበረታባት። እያስፈራራትና እየዛጠባት ሳለ፤ አንድ ወጣት በመንገድ ሲያልፍ ይመለከትና "ምን ሆነሽ ነው?" ሲል ጠየቃት። እሷም የተከሰተውን በደንብ አስረዳችው። ወጣቱም እንዲህ አለ... "ብሩን እኔ ሰጥሃለው" ብሎ አንድ ሺህ ብር በማውጣት ለሰውየው ከፈለው። ኩራተኛው ሰውየም ብሩን ቆጥሮ ተረክቦ ሊጓዝ ሲል፤ ወጣቱ ልጅ... "ተረጋጋ እንጂ ወደየት ነው!?" አለው። ሰውየውም.. "ምን ፈለግክ!?" አለው። ወጣቱም... "የልብስህን ዋጋ ወስደሃል አይደል!!" አለው። ሰውየውም.. "በሚገባ እንጂ!!" አለ። ወጣቱም... "ታድያ ልብሱ የታለ?" ሲል ጠየቀው። ሰውየም "ለምን!?" አለው። ወጣቱም... "የልብስህን ዋጋ ሰጥተንሃል፤ ስለዚህ ልብሱን ስጠን አለው። ሰውዬውም.. "ራቁቴን ልሄድ ነው!?" አለው። ወጣቱም... "አይመለከትኝም! ምን አገባኝ!!" አለው። ሰውዬውም.. "ልብሱን ካልሰጠውህስ?" ሲለው ወጣቱ.. "ገንዘብ ትከፍለናለህ አለው" ሰውዬውም "አንድ ሺ ብሩን ነው አለ?" ወጣቱም... "አይይ አይደለም። እኛ የምንልህን ነው" ሲል መለሰለት። ኩራተኛውም ሰው እንዲህ አለ... "እንዴ የከፈልከኝ እኮ አንድ ሺ ነው" ወጣቱም.. "ስለከፈልኩት አያገባኝም አለው" ሰውዬውም... "ስንት ነው ምትፈልገው?" አለው። ወጣቱም... "ሁለት ሺህ ብር" አለው። ሰውዬውም... "ይህ ብዙ ነው!!" ሲል ተናገረ። ወጣቱም... "እንግዲህ ልብሱን ስጠና!!" አለው። ሰውዬውም... "ልታዋርደኝ ፈልገህ ነው ራቁቴን" አለው። ወጣቱም.... "ሴትየዋን ልታዋርድ እንደፈለግከው አዎ!!" አለው። ሰውየውም .. "ይህ በደል ነው!!" አለ። ወጣቱም.... "እንዴ አሁን ስለ በደል ታወራለህ!! ድንቅ ነህ" አለው። ሰውየውም በማፈር የተባለውን ብር ለወጣቱ ከፈለው። ወጣቱም ይህ ሁለት ሺህ ብር ለምስኪኗ ሴት ስጦታ መሆኑን አውጆ በደስታ ሸኛት። @Noahtoaels_idea ክርክሮችን ለመፍታት #ጥበብ ሁነኛ መፍትሄ ናት!! ህይወትም ኩራትና እኔ የበላይ ነኝ የምንልባት የፋከራ መድረክ አይደለችም።
Показати все...
10👍 1
Показати все...
ረጋ ስትል ታስተውላለህ! ስትፈጥን በቶሎ ካሰብከው ትደርሳለህ! ሁለቱም ትክክል ናቸው ግን ትክክል የማይሆኑበት ሰአት ይኖራል... እያሰባችሁ አንብላሉት እኔ ይህን ተረድቻለው @Noahtoaels_idea
Показати все...
👍 6
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.