Our Side of the Story
Відкрити в Telegram
"To those who hurt and hunger” Since Oct 14, 2019 Here to help @DebbieTesfaye
Показати більше1 683
Підписники
-124 години
+167 днів
+330 день
Архів дописів
ሚስ አለምፂ፣ ኤደን፣ ኤልሳ…ጎብጬም የምረሳቸው አይመስለኝም። They were the most kind, soft and friendly of all our teachers.
ሚስ አለምፂ is popular in every generation of mount olive students. በክፉ የሚያስታውሳት ካለ እኔ እቀጣለሁ።
ጎበዝ ፀሀፊ እንደሆንኩ ከ twitter እና instagram በፊት እሷ ናት የነገረችኝ።
Now after all those years, እኔም Miss እየተባልኩ (even though I don’t teach lol), i always remind myself that this place is not just a school for these kids, it’s where they learn how to be humans, to love and receive love, how to find solace in their friends and teachers when things are rough at home, i have so little influence in their lives but i try to be intentional.
“Miss they don’t want to be my friend, i try so hard to make them forgive me but they keep saying go back to your school” he’s only eight, but he has already mastered people pleasing so he can be accepted and loved. ባልወልዳቸውም፣ ብውጣቸው ደስ ይለኛል ልማኦ።
it keeps getting worse አልል ነገር ያሳዝኑኛል።
with the same heartbreak i cried about when i was eight to my favourite teachers, i now am the responsible adult for giving the antidote for the heartbreak of these kids.
ah time.
whatever led me to this job and place, every experience i had as a child ተመልሶ መጥቶ ሳባብላቸው ሳስቃቸው…when their perspective shifts right before my eyes and they get their little spark back, i know and believe that all is well.
this moment right here just like my childhood and now memories, is a pavement that someday i’ll be grateful for.
ወይ ጉድ እና ተመስገን ነው ብቻ :).
ትላንት a ride chauffeur, who I was very nice to, made me cry so bad, gave me a full on body tremor. I don’t know how to react when someone is verbally violent, ግራ ይገቡኛል በጣም። like do you hear how ugly you sound? self concept’አችሁ አይበላሽባችሁም?
He deliberately missed two routes and I only asked which way he was planning to go both times. I don’t think he’s used to being questioned, ደበረው፣ የምሩን።
ተመናጨረ፣
“ቀድመሽ መናገር ነበር”
“ግልፅ እኮ ነው የምታውቀው ሰለመሰለኝ ነው ይቅርታ”
ደረስን፣ እንደምንም
“ወደ ቀኝ እሺ” እኔ
ፀጥ፣ ገልመጥ…እሱ
“ወደ ቀኝ እእ”
“ሰማሁሽ እኮ እናቱ”
ለምንም ነገር ሁልጊዜ መልስ እፈልጋለሁ፣ ሰው ዝምብሎ ሊቆጣኝ፣ ክፉ ሊሆንብኝ የሚችል አይመስለኝም፣ የሆነ ነገር ማጥፋቴ የግድ ነው…ቀድሜ I can’t see the fault in people, i’m always the issue. ድሮ ነው ግን ይሄ፣ ልጅ እያለሁ። apparently not አልኩ ትላንት።
“እየተቆጣኸኝ ነው ታዉቆሀል?”
“ኧ?? እየተቆጣኸኝ? ስቆጣ አታቂኝማ”
Adult Debbie left the car, I don’t remember when, and my inner child took over. ሳሳዝን እጥፍ ነገር አልኩ፣ እምባዬ መጣ፣ ትልቅ ሰው መሆኔን ረስቼው፣ ሲሰድበኝ ዝም አልኩት፣ ችግር የለውም debs you can defend yourself now ማለት ጠፋብኝ፣ my hands started shaking I couldn’t hand him the money right
“አፍጥኚው አፍጥኚው”
“እሺ ይቅርታ” ብዬ ወረድኩ።
it was that Tuesday night in 5th grade all over again, ያ ሰኞ 4 ሰአት in 9th grade where i said the same “እሺ ይቅርታ” without knowing where my fault was, all the years of apologising for existing.
ትዝ ሲለኝ ልሰራ ነው አመጣጤ፣ ሳግ እንዳነቀኝ መታጠቢያ ቤት ገብቼ የጋለ ፊቴን አብርጄ፣ የልጅ ልቤን አባብዬ፣ በሗላ journal ትደረጊያለሽ አንቺ trigger ብዬ ወደ ስራዬ።
In so many ways ለ ትንሿ Debbie ደርሼላታለሁ፣ ድብድቡ ላይ እና standing up for her ላይ ትንሽ ይቀረኝ መሆኑ ነው።
baby steps፣ በደንብ የቻልኩበት አፍንጫችሁን የምላችሁ🤭
Repost from History
Sir David Attenborough (b. 1926, turns 100 today) in the 1950s. He joined the BBC in the 1950s as a trainee, going on to present Zoo Quest as his first major nature documentary.
Repost from The Conscientious Observer
Official Blender3D video for Dead Internet Society featuring Mussie Gebreselassie.
On this piece, I cover the constant state of invisibility within the writer's realm over a concept video done by the ever so talented and brilliant Moss.
The link to the full video:
https://youtu.be/fwcm4SCy1Oo
Repost from Brown Empire
Pretty hurts
ብድግ ብዬ እንደነገሩ አስይዤው የምሄደው ፀጉር፣ ቆንጆ የምለው ፊት እስኪመጣልኝ መዘጋጀት ባይኖርብኝ፣ መጥቶልኝም እስካምነው ድረስ መስታወት ፊት ባልሻጥ፣ ስንት እድሜ አተርፍ ነበር?
ከተማ መወለድ ለብዙ ነገር ትርፋማ ቢያደርግም፣ ለመልክ ግን ገበያ ነው። ምን አይነ ግቡ ብንሆን የሚያወዳድሩብን በጣም የምታምር ደግሞ ሌላ አለች፣ እንደሷ ማማር ትችያለሽ የሚል ገንዘብ የሚያስበዘብዝ ማስታወቂያ በየስክሮሉ አለ።
ቆንጆ መባል ጎበዝ ከመባል እስኪበልጥብን፣ ሳናምር መውጣት ጠልተን መገኘት ከአለብን ቦታዎች እስክንቀር? ገና እግራችን ሲያደከድክ፣ ከወፌ ቆመች ቀጥሎ ስለመልካችን አስተያየት አልሰማንም ወይ? “አፍንጫዋ ነው እንጂ፣ ጆሮዋ ባይተልቅ፣ ፀጉሯስ ሶስት ፍሬ ናት፣ ሴት ስትቀላ ነው እንጂ፣ ተረከዟ ምን ያክላል?” እየተባልን ቅንጥ ቅንጣችንን ተብለን እሳት እንደነካው ላስቲክ ያልተሰበሰብን አምስት እንሞላለን ወይ?
አሁን ላይ “ግን እኮ ቆንጆ ነሽ ለምን እንዲህ ይሰማሻል?” የሚልን አስተያየት ለመስማት ጆሯችን እንደሚያመነታ፣ አይናችን መስታወት ላይ ያለ ምስላችንን ለማመን እድሜውን ደርድሮ በቦውሊንግ ኳስ እንደረመረመ ያለሀፍረት እንዴት ማስረዳት እንችላለን?
ብንቆምም፣ ከገላችን ልክ አልቆም እያለ እንደ ሰፊ ውስጥ ልብስ ውልቅ ውልቅ የሚል ቅስም እንዳለን እንዴት ማውራት እንችላለን?
“ልጅን ሲወዱ...” ብሎ የተረተ ሀገር መች ከነ ወደደን? ፍቅራቸው በአፍንጫችን ቅናት እና ማጎንበስ አልተወሰነም? ሀሳባችንን ለመሸጥ ስንዝር የማይሞላ ወገብ እንደማይጠበቅብን ሁሉ፣ እድሜያችን 14 ሳይሆን ውሀ ቻፒስቲክ የልጅ ከንፈራችን ላይ ስናፈስ “እሱን ትተሽ ትምህርትሽ ላይ አታተኩሪም?” ተብለናል። በተንኳሽ አለም ተተንኳሽ ይጠነቀቃል:)
እኔን ትተህ ትምህርቴ ደጃፍ ላይ ተኮልኩለው የልጅነት ባቴን ከልጅነት ባቷ የሚያወዳድሩንን ጎረምሶች፣ ለገና ማርያምን ለመሆን ቅላት እንደሚያሰፈልግ የምታምነዋን አስተማሪ ተዪ፣ ተው አትልልኝም? አትሉልንም?
እድሜ ዘመን የሚከተል ድምፅ እንደምትሰጡን አታውቁም? የውስጥ ድምፃችን የትንኮሳ ቃል እና አሽሙር መሆኑ አያሳዝናችሁም? ስራችሁ ፍሬ አፍርቶ በሌላችሁበትም ለስላሳ ድምፃችንን አሸንፎ የሚወጣው ሸካራ ድምፃችሁ ነው።
የፀጉራችን ቴክስቸር ስንት ሚዶ በድዱ እንዳላስቀረ፤ በለስላሳ ሉጫ ፀጉር የሚሰራው ማስታወቂያ እኛን እንዳላየ አልፎን በየቲቪው የሰራጫል። በጥቁር ሀገር ቅላት ይሰበካል፣ ልጅ ያወጣው ፓውች ሁለት ሳምንት ከተቀመጠ የአእምሮ ጤናን የሚያናጋ አስተያየት በየመታጠፊያው እንደመንገድ አበባ ይቀጠፋል፣ በፀጉራችን መሆን ነውር እስኪመስል ድረስ የቀጠልን ለት በተውሶ ውበት በተለየ እንደነቃለን።
መጀመሪያ ኢንሴኪዩሪቲው ይሸጣል፣ ያን ኢንሴኪዩሪቲ ተጫርተን ቦዲ ዲስሞርፊያ እንገዛለን፣ ከዛ ጊዜያዊ መፍትሄ በተጋነነ ዋጋ ይከተላል፣ ያቺንም እንደያቅማችን እንቃረጣለን። መፍትሄው አልዘልቅ ሲል ማየት ከምንፈራው መልክ፣ ባዶ ኪስ እና ድባቴ ጋ እንቀራለን።
“በሰያፍ በኩል ስታይ ምን እመስል ይሆን?” ብላ በሶስት መስታወት ያንን አንግል ለማየት ያልሞከረች እንስት ለትምህርት እና ለሌላ የህይወት ቁምነገር በቂ የአእምሮ ቦታዋን ያልሰዋች እና መሽቶ በነጋ ቁጥር ለሚፈለፈሉ አሸን ኢንሴኪዩሪቲዎች ያልተሸነፈች ሴት ለኔ ጠንካራዋ እሷ ነች።
አብዛኞቻችን ግን ለሲስተሙ እና ለማህበረሰቡ አይን ተሸንፈንለታል። ካፒታሊዝም የቀናው በሴቶች ራስ አለመተማመን ላይ ነው። ገበያውም የጦፈው በሚቀጠለው ፀጉር፣ ጥፍር፣ ሽፋሽፍት፣ የተለያዩ ውበት መጠበቂያ(ማፅናኚያ) ሸቀጦች ነው።
ለሀበሻ ማስቀየም እንደንቀት ነው፣ how dare you look like this? Whats with the ድንች አፍንጫ?
“ኧረ በመቤቴ ማሰብ ይሻላል?” ብንልም
“ዱላ በማይመልሰዉ ነገር አንስማም” የሚለው ብዙ ነው። ደግሞ እኮ nose job, boob job, face lifting, tummy tuck? ካልን ኪሳችንም እንደማህበረሰቡ መሳለቁ አይቀሬ ነው። ይሄ ሁሉ ተደማምሮ ጢባጢቤዉን የሚጫወተው በራስ መተማመናችን ላይ ነው።
ገና በልጅነታችን በራስ ያለመተማመን ከጉድሞርኒንግ ሻይ ጋር ነው የሚሸጥልን። "መሆን አለመሆን" የሚለው ጥያቄ የሚጀምረው እዛላይ ፒግቴል ያሲያዘችውን ቆንጆ ትንሽ ልጅ ስናይ ነው። እናማ የውበት ኢንደስትሪው በለጋ እድሜያችን ለበረዶ ባስቀመጥነው ሳንቲም ነው ፐርም(የፀጉር ማለስለሻ) የሚያስገዛን።
ቀጭን ሆኖ መታየት፣ ሸንቃጣ መሆንን ያላለመች ሴት፣ በሆርሞን፣ በስራ፣ በኑሮ ምክንያት አልመች ብሏት ከገዛ ሰውነቷ ተኮራርፋ የምትኖረዋም፣ በተገኘው ለማስተካከልም ከጂም ጀምሮ የተለያዩ የሚጠጡ፣ የሚዋጡ ነገሮችንም ያልሞከረች ሴት ቤት ይቁጠራት። ብጉር፣ ማዲያት፣ ዲስከለሬሽን የመሳሰሉትን ለማጥፋት አለ በተባለው ፕሮዳክት ገንዘቧን ያልከሰከሰች ሴት መኖሯም አጠራጣሪ ነው።
ስንት ብራ የልጅነት ቀናችን፣ ሮጦ መስሪያ ወጣትነታችን በነዚህ መነጫንጮች ያላግባብ አልፈዋል፣ ፊታችን ላይ ሀፍረት ተሸክመን ኖረናል። አንገታችን በውድድር ብዛት አጎንብሷል።
አንዳንዶቻችን ድርድር ያላለ ወጣ ገባ ጥርሳችንን ጮክ ብለን “ሲያምር” ለማለት 34 አመት ፈጅቶብናል።
Ain't got no doctor or pill that can take the pain away
The pain's inside and nobody frees you from your body
It's the soul, it's my soul that needs surgery
(It's my soul that needs surgery)
Plastic smiles and denial can only take you so far
Then you break when the fake façade leaves you in the dark
You're left with shattered mirrors and the shards of a beautiful past
It took me years of wandering through oceans of friendships and connections to realise that my belief in me being unlovable came from the exposure to people who were not kind, people who projected so much of their insecurities and anger towards me and not because I was cursed.
Learning to accept that I’m lovable, people enjoy my company and look forward to our conversations has been the most bittersweet experience I’ve had. I had to unlearn the pattern of always looking for that hint of disgust, jealousy and competitiveness in the eyes of people.
I’m grateful to have learned that there are days where I have been the problem but that’s not always the case. For I write this from a place of knowing whatever unkindness, negativity and spite thrown at me has nothing to do with who I am as a human being. And I will not make the mistake of believing it determines how I speak and think about myself again. This statement stays even if you someday find yourself to be the problem too.
no answers from me today, just questions for you to ponder on until we meet this Sunday @thesocialaddis to rant about our concepts of love.
📍 Social Addis
🗓 February 15th
⏰ 6PM (12LT)
🎟 400 ETB
🔗 Link in bio.
Just sat in the living room with my mom and listened to old albums like we used to do when I was younger, I’m beefing with time now. I’ll write about it tomorrow.
ሳራ (we were neighbours) had this ቴፕ መሳይ phone, and every time I had no school መዝሙር ክፈቺ እያልኩ እጨቀጭቃት ነበር። Sara, who introduced me to the beauty of Afaan Oromo songs. We were around the same age, she was a little older but if you stared a little bit longer you could see the lines of aging without her will drawn on her face. ልቧ እስኪጠፋ ነበር መዝሙሮቹን የምትዘምራቸው፣ እያለቀሰች ምናምን። እኔ መዝሙሮቹ ስለሚያምሩኝ ነበር ክፈቺ የምላት፣ the raw emotions I can hear in their voices and the melodies magical ስለነበሩ። She barely understood Amharic and I with no knowledge of her language. ረጅም ሰዓት አብረን እንድንቀመጥ የሚያደርጉን መዝሙሮቹ ብቻ ነበሩ። Every time I come across an Afaan Oromo song, she’s all I can remember. ዛሬም ቋንቋው ሳይገባኝ፣ just the beauty making me float እሰማለሁ።
Repost from አማዶን
እንዲሁ
ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ
አድሮ ቃሪያ ፥ ታጥቦ ጭቃ
ዝማሬና እንጉርጉሮ
ጠዋት ተስፋ ፥ ማታ ሲቃ
ፀደይና ምድረ በዳ
ሰላምና አምባ ጓሮ
አይሰለችም አይሰለችም
ትርጉም የለሽ ፥ ቆንጆ ኑሮ።
01|07|17
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
