Gurage Zone Government Communication Affairs
Відкрити в Telegram
1 566
Підписники
-124 години
-17 днів
-930 день
Архів дописів
በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ለተጎዱ ወገኖች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የምንሰራው ስራ አጠናክራረን እናስቀጥላለን፦ዶ/ር ዳንኤል አንጪሶ
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ማህበር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ2018 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸምና የ2019 እቅድ ባለድርሻ አካላቶች በተገኙበት በወልቂጤ ከተማ ገምግሟል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ማህበር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር ዳንኤል አንጪሶ እንዳሉት የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በዋናነት ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል የአደጋ ምላሽ ፣የአደጋ ዝግጁነት ፣ የውሃና የጤና ስራዎች ፣የአባላት ቁጥር ማሳደግ፣ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራ እንዲሁም የሰብአዊ የኮሚኒኬሽን ስራዎችና በሌሎችም ተግባራት ላይ አጽኖት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ከዘር ፣ከሀይማኖት ፣ ከቋንቋ ከብሔርና ከተለያዩ ነገሮች ነጻ በመሆን ሰው ሰው በመሆኑ ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ነው ብለዋል።
ማህበሩ በበጀት አመቱ በርካታ ማህበረሰቡን የሚጠቅሙ ስራዎች ማከናወኑም አመላክተው በክልሉ በሁሉም ቅርንጫፎች የሚገኙ 11 አምቡላንሶች 24 ሰአት አገልግሎት እየሰጡ እንደሆነም አመላክተው ።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአባላቱ ላይ የተመሰረተ እንደሆነ ያመላከቱት ዶክተር ዳንኤል በጎ ፍቃደኞች በአደጋ ጊዜ ፣በስፖርት ሜዳና በተለያዩ አካባቢዎች ላይ የሚሰጡት ነጻ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የሚሰጡም እንደሆነ ተናግረዋል።
ትምህርት ቤቶች ላይ ያሉ የቀይ መስቀል አገልግሎት ክበቦች ተሳትፎ ምን እንደሚመስል በመድረኩም በስፋት የገመገሙ እንደሆነ ያመላከቱት ዶክተሩ በቀጣይ ጉድለቶቻቸውን በማረም እንዲጠናከሩ ይደረጋል ብለዋል።
ህብረተሰቡን ለማገልገል የተቋቋሙ ፋርማሲዎች ማጤመና ሌሎች አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ እየተሰራ ሲሆን የመድሐኒት አቅርቦት ችግር ፣የዋጋ ፣የጥራትና የገበያ ችግሮች ላይ በመገምገም በጥራትና በዋጋ ከሌሎች መድሐኒት ቤቶች የተሻለ መድሐኒት ቤት መሆኑንም ገምግመናል ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀይመስቀል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መለሰ ዘውገ እንዳሉት የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ከ90 አመት በላይ በሀገሪቱ በሚደርሱ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ሲከሰቱ የመንግስት አጋዥ በመሆንና ፈጥኖ በመድረስ ፣በማገዝና መልሶ በማቋቋም ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ያለ ማህበር ነው።
ማህበሩ ባለፈው በጀት አመት በሀላባ ፣በስልጢ፣ በጉራጌ፣ በከንባታና በሀድያ ዞኖች በመሬት መንሸራተት፣በቤት ቃጠሎና በተለያዩ ግጭቶች የተጎዱ የህብረተሰብ አካላት በቅርብ በመድረስ ምግብ ነክና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ድጋፍ በማድረግ የመንግስትን ክፍተት የመሸፈን ስራ መስራቱም አመላክተዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፕሮግራም ዘርፍ ሀላፊ አቶ ዘውዱ ገረመው እንዳሉት በመድረኩ በ2018 በጀት አመት የተከናወኑ ተግባራት በጥንካራ የተለዩትን በማስቀጠልና በጉለት የለያቸውን በ2019 በጀት አመት በማረም የተሻለ ስራ እንደሚሰራም አብራርተዋል።
የጉራጌ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፕሮግራም ዘርፍና የቅርንጫፉ ተወካይ አቶ ሻሚል የሲሩ እንዳሉት በዞኑ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች በሚደርሱበት ወቅት ፈጥኖ በመድረስ የሰው ልጆች ህይወት የማዳን ስራ ይሰራል።
በዞኑ ባለፈው በጀት አመት የማህበረሰቡ የሳር ቤት ቃጠሎ አደጋ ላይ ማህበሩ በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ግጭት የተፈጠረባቸው አካባቢዎች በመገኘት የአደጋ ምላሽ ስራ መስራታቸውም አስታውሰዋል።
በዞኑ በሚገኙ የአምቡላንስ አገልግሎት የሚሰጡ ሶስት እስቴሽኖች መኖራቸውም አመላክተው አምቡላንሶች የተለያዩ አደጋዎች በሚደርሱበት ወቅት ፈጥነው በመድረስ ድጋፍ የመስጠት ስራ ይሰራል ያሉት አቶ ሻሚል በተያዘውም በጀት አመት ስራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።
#ወሔም_ሳረናሑም
#እንኳን_ደስ_አላችሁ_እንኳን_ደስ አለን!!
🏆 የጉራጌ ዞን ዝፓና ፓርቲ ጥፈት ቤት በክልልዌ ያ1ነ ደረጃ አሸናፊ በሕሮተተሰ ተሸለመም።
ኣምሬ 21/2018 ዘበር (ወቕጤ)
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት "ሁሉ አቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በሆሳዕና ከተማ ባካሄደው የ2018 ዓ.ም የፓርቲ ስራዎች ማጠቃለያ መድረክ የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት በክልሉ ካሉ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በላቀ አፈፃፀሙ የ1ኛ ደረጃ እውቅናና የሞተር ሽልማት ተበርክቶለታል።
ይህ አበረታች ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በዞኑ አመራር፣ በፓርቲው አባላትና በሰፊው የጉራጌ ህዝብ የተቀናጀ ጥረት፣ ጠንካራ ህዝባዊ አደረጃጀትና የጋራ ስራ ውጤት በመሆኑ ነው።
ፅህፈት ቤቱ ላስመዘገበው ውጤት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ ምስጋናውን እያቀረበ፤ በቀጣይም የፓርቲውን እሳቤዎች በመተግበር፣ የህዝባችንን የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በላቀ ደረጃ ለመመለስ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጧል።
ለተመዘገበው ታላቅ ውጤት በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን!
"ሁሉ አቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ!
በጎነት በብዙ ሀብትና ገንዘብ የሚወሰን ሳይሆን ከትልቅ ልብ፣ አዕምሮና ሀሳብ የሚመነጭ በመሆኑ ተግባሩ ሁሉም አጠናክሮ ሊያስቀጥለው እንደሚገባ ተገለጸ።
ሀምሌ 21/2018(ወልቂጤ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽንና የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ተቋማት በጋራ በመሆን በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ መሀልአምባ ከተማ በ2018 በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የመከላከያ ሰራዊት ተመላሽ አባል ወታደር አህመኑር ጀማል የቤት ግንባታ አስጀምረዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን እሼቱ እንዳሉት በጎነት በብዙ ሀብትና ገንዘብ የሚወሰን ሳይሆን ከትልቅ ልብ፣ አዕምሮና ሀሳብ የሚመነጭ ነው።
ይህ ተግባር የብልጽግና ፓርቲ እሳቤ የሆነውን የሰው ተኮር ፕሮግራም የምናረጋግጥበት ከመሆኑም ባሻገር የመረዳዳትና የማህበራዊ እሴታችን እንዲጎለብት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም ተናግረዋል።
እንደ አቶ ዘሪሁን ገለጻ የወታደሩ የቤት ግንባታ ከማስጀመር ጎን ለጎን በመሀል አምባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ የአረንጋዴ አሻራቸውንም ማኖራቸውን ጠቅሰው ይህም ዘላቂ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑንም አስረድተዋል።
በጎነት የአንድ ወቅት ተግባር ብቻ ሳይሆን ሁሌም አንዳችን ለአንዳችን በመደጋገፍ የኢትዮጵያን የመረዳዳት እሴት የምናሳድግበት ተግባር በመሆኑ ሁሉም ተግባሩ ማስቀጠል እንዳለበትም ገልጸዋል።
የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰላሙ አማዶ በበኩላቸው በ2018 የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ በሚል መሪ ሀሳን እንደ ሀገር ብሎም በክልሉ በርካታ ስራዎች እየተሰራ ነው።
በጎነት ከቅንና ከመልካም ልቦና ይመነጫል ያሉት አቶ ሰላሙ ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ያለው በመሆኑ በዘርፉ በትኩረት እየተሰራበት ነው ብለዋል።
በጎነት ላይ ተቀባዩ ብቻ ሳይሆን ሰጪው ጭምር የሚደሰትበት የህሊና ተግባር መሆኑን አንስተው፣ ይህ ተግባር አንድነት፣ ፍቅርና መተባበርን በማጠናከር ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን አስረድተዋል።
በዛሬው እለት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ መሀል አምባ ከተማ ያስጀመሩት ከመከላከያ ሰራዊት ተመላሽ አባል ቤት የክልሉ መንግስት በዞኑ በተለያዩ ከተሞች በክልል ተቋማት በክረምት በጎ ፈቃድ ከሚገነባቸው ቤቶች አካል መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህ ተግባር የሀገር ዋጋ የከፈለው ወታደር አህመኑር ጀማል ማገዝ ሌሎች የሱን ፈለግ ተከትለው ለሀገር የሚቆሙ ዜጎች በማበረታታት ረገድ ፋይዳው የላቀ ነው መሆኑን ተናግረዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን በወረዳው በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በርካታ ስራዎች እየተሰራ ነው ብለዋል።
በዛሬው እለት የክልሉ ተቋማት በወረዳው መሀል አምባ ከተማ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ተመላሽ ሰራዊት ወታደር አህመድኑር ጀማል የቤት ግንባታ በማስጀመራቸው ምስጋና አቅርበዋል።
በወረዳው መሀል አምባ ከተማ 01 ቀበሌ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት በክብር የተሰናበቱ ወታደር አህመኑር ጀማል እንዳሉት ከዚህ ቀደም በውትድርና ሀገራቸውን በታማኝነት ሲያገለግሉ እንደነበር ጠቅሰው፣ በዚያን ወቅት በደረሰባቸው አደጋ ጉዳት እንደደረሰባቸው አንስተዋል።
በዚህም ከባድ ችግር ላይ እንደነበሩ አንስተው በዛሬው እለት የክልሉ ተቋማት ከችግራቸው ለማላቀቅ የቤት ግንባታ በማስጀመራቸው መደሰታቸውን ጠቁመው መሰል ተግባራት በቀጣይም ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ገልጸዋል።
በ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ጠቅላላ ተማሪዎች ውስጥ 81.1 በመቶ የሚሆኑት የማለፊያ ነጥብ አስመዝግበዋል- አቶ አቶ አንተነህ ፈቃዱ
ሀምሌ 21/2018(ወልቂጤ)፣ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ በተሰጠው የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ጠቅላላ ተማሪዎች ውስጥ 81.1 በመቶ የሚሆኑት 50 እና ከ50 በላይ ለአካል ጉዳተኞች 45 እና ከ45 በላይ አማካይ የማለፊያ ነጥብ አስመዝግበው ወደ 7ኛ ክፍል ማለፋቸውን አቶ አንተነህ ፈቃዱ አስታውቀዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት ዘንድሮ በክልሉ ፈተናውን ከወሰዱ 88,927 ጠቅላላ ተማሪዎች ውስጥ 72,160 ወይም 81.15 በመቶ የሚሆኑት ማለፍ ችለዋል።
ይህ ውጤት ከ2017 የትምህርት ዘመን ፈተና ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ እድገት ማሳየቱን ጠቁመው የአምናው ተመሳሳይ ወቅት ያለፉ ተማሪዎች መጠን 75 በመቶ ነበር ብለዋል።
በትምህርት ቤት ደረጃም ካስፈተኑ 1839 ትምህርት ቤቶች ውስጥ 582 (31.1 በመቶ) የሚሆኑት ሙሉ በሙሉ ያሳለፉ ሲሆን ምንም ያላሳለፉ ደግሞ 10 ትምህርታቸውን ቤቶች ናቸው። ባለፈው አመት ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች 424 እንደነበር አስታውሰዋል ። ውጤቱ በትምህርቱ ዘርፍ መሰረታዊ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያመላክታል ሲሉ አቶ አንተነህ ገልጸዋል ።
በዘንድሮው ክልል አቀፍ ፈተና የመንግስት ትምህርት ቤቶች ከጠቅላላ ተማሪዎቻቸው ውስጥ 79.8 በመቶ የሚሆኑትን፣ የግል ትምህርት ቤቶች ደግሞ 93.5 በመቶ የማሳለፍ ምጣኔ ማስመዝገብ ችለዋል ።
ለለውጡ መገኘት የትምህርት ቤት ሪፎርም ትግባራ፣ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል፣ የማጠናከሪያ ትምህርት ፣የትምህርት ግብኣት አቅርቦት፣የመማር ማስተማር ተግባር ላይ እየታየ ያለው ውጤታማነት ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል ።
ከትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ጋር ተያይዞ የህዝቡ ተሳትፎና የወላጆች ሚናም ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመው በቀጣዩ አመት እነዚህን ውጤታማ ተግባራት ይበልጥ አጠናክሮ በመቀጠልና ክፍተቶችን በማረም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ከወዲሁ የተሟላ ዝግጅት እንደሚደረግም አቶ አንተነህ አስታውቀዋል ።
የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽንና የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ተቋማት በጋራ በመሆን በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ መሀል አምባ ከተማ በ2018 በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአንድ የመከላከያ ሰራዊት ተመላሽ አባል ቤት ግንባታ አስጀመሩ።
ሀምሌ 21/2018(ወልቂጤ)
የክልሉ ተቋማት በጋራ በመሆን በወረዳው መሀል አምባ ከተማ በ2018 በክረምት በጎ ፈቃድ የወታደር አህመኑር ጀማል የቤት ግንባታ አስጀምረዋል።
የክልሉ መንግስት በዞኑ በተለያዩ የወረዳና ከተማ አስተዳደሮች የክረምት በጎ ፍቃድ ተግባራት አጠናክሮ መቀጠሉን ተመላክቷል።
ለሀገር ህይወታቸውና አካላቸውን የሚሰጡ የመከላከያ አባላት የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ሀገርን የማላቅና ለተጎጂዎችም እውቅናም የመስጠት ጉዳይ ነው።
ከቤት ግንባታ ጎን ለጎን በመሀል አምባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ የአረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
በፕሮግራሙም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰላሙ አማዶ፣ የክልሉ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቱ፣ የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙራድ ረሻድ፣ የጉራጌ ዞን የከተማና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትብለጥ እስጢፋኖስ፣ የዞኑ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የስራ ኃላፊዎችና ሌሎችም ተገኝተዋል።
የግብቻነ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት አትራኸቦት ቤሮ ቡር ዳነ አበቀጣ ዘሪሁን እሸቱም የሳይንስ ኢንፎርሜሽንም ቴክኖሎጂ ቤሮ ቡር ዳነ አበቃጥ ሰላሙ አማዶ የሑዌት ሁም አስራ ስሙት ዘበር የዘር በነ የወሄነት ሜና በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የወታደር ቤት በቶቶት ኣትቀነሶም።
ኣምሬ 21/2018 (ወርቕጤ)
በግብቻነ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ያትዋነዮ ቡችር ቡችር የክልል ቢሮ በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ መሀልአምባ ከተማ የ2018 ዘበር የዘር በነ የወሄነት ሜና የዜጋ ቤት ዋርሽ ቀነሶም
የዘር በነ የወሄነት ሜና የጉርማሳ ቤት አርሶት፣ ኣፈር ቶቶትም ገግ ተገግ ይትራከውቦ ወሔ ሴራው።
የዘር በነ የወሄነት ሜና የመንግስትም የፓርቲ አሚሸ ይተዎቦዬ ያጘኽር ቧሪም።
በዘድረ ዘበር በክልልዌ ጉራጌ ዞን ያትዋነዮ ቡችር ቡችር ቢሮ በዞንዌ በቡችር ቡችር ወረዳም ከተማ የጉርማሳ ቤት ታርሰዎት በፎር እንጎድ ሜና ይቾቺሐማ ኢዶም።
በዘር በነ ወሔነት ቢቆርሽቦ ፕሮግራም የግብቻነ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት አትራኸቦት ቤሮ ቡር ዳነ አበቀጣ ዘሪሁን እሸቱም የሳይንስ ኢንፎርሜሽንም ቴክኖሎጂ ቤሮ ቡር ዳነ አበቃጥ ሰላሙ አማዶ፣ የጉራጌ ዞን የወረዳም የሜነ አራባሪ እንጎድ ባዘራ ተረከዎም።
