ch
Feedback
Gurage Zone Government Communication Affairs

Gurage Zone Government Communication Affairs

前往频道在 Telegram

Gurage Zone Government Communication Affairs

显示更多
1 557
订阅者
无数据24 小时
无数据7
-1030
帖子存档
በዞኑ ማህበረሰቡ ባለሀብቱና አጋሮችን በማሳተፍ እየተሰሩ ያሉ የትምህርት ልማት ስራዎች ሌሎችም በአርዓያነት ሊወስዱት የሚገባ መሆኑ ተገለፀ። ነሐሴ 23/2018(ወልቂጤ)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በጉራጌ ዞን በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ37 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የታተሙ መጽሀፍትን ለወረዳዎች አስረክበዋል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት አዲሱ የትምህርት እና ስልጠና ፖሊሲ እና ስርዓተ ትምህርት ከተሻሻለ ወዲህ የአዳዲስ መጽሀፍት ህትመት እየተካሄደ ነው ብለዋል። በሁለተኛ ደረጃ ባሉት ትምህርት ቤቶች ትምህርት ማኒስቴር ከቅድመ አንደኛ እስከ 8ኛ ክፍል መጽሀፍት የማቅረብ ኃላፊነት የክልሎች ድርሻ ስለመሆኑም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል። የመጽሀፍት አቅርቦት ከፍተኛ ሀብት ይጠይቃል ያሉት አቶ አንተነህ በክልሉ መንግስት አቅም ብቻ መሸፈን ስለማይቻል በሁሉም አካባቢዎች ህብረተሰቡን በማሳተፍ እየተሰራ ነው ብለዋል። አርሶ አደሩን፣የንግዱን ማህበረሰብ፣ዲያስፖራውን፣ ክልሉ እና ከክልሉ ውጪ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ መጽሀፍት የማሟላት ስራ ተግባራዊ መደረጉን ጠቅሰዋል። በክልሉ በመካከለኛ ደረጃ 1ለ5 የመጽሀፍት ጥምርታ ማዳረስ ተችሏል ያሉት አቶ አንተነህ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል ደግሞ 1ለ3 መድረሱን አብራርተዋል። በክልሉ 1መጽሀፍ ለአንድ ተማሪ ንቅናቄ በጉራጌ ዞን ከ227 ሺ በላይ መጽሀፍት የማሰራጨት ስራ ተግባራዊ መደረጉን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል። በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት ከአጋር አካላት ከ 2 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ መጽሀፍት ጥራቱን የጠበቀ የመጽሀፍት ህትመት ማሰራጨት መቻሉን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። የመማር ማስተማሩን ስራ ስኬታማ ለማድረግ የክልሉ መንግስት ለመጽሀፍት ህትመት ከፍተኛ ሀብት መድቦ እየተሰራ ስለመሆኑም ጠቁመዋል። የመንግስትን፣የህዝብን ብሎም የአጋር አካላትን አቅም በመጠቀም የመጽሀፍት ተደራሽነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን አቶ አንተነህ አስረድተዋል። በዘርፉ እየተደረገ ያለው ጥረት የትምህርትን ጥራት እና የተማሪዎችን ውጤት በማሻሻል ረገድ ጉልህ አበርክቶ እንዳለውም ጠቅሰዋል። በክልሉ በ2019 የትምህርት ዘመን አንድ መጽሀፍ ለአንድ ተማሪ ኢንሼቲቭ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የተናገሩት አቶ አንተነህ ለዚህም መላው ህዝብ የጀመረውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። በፕሮግራሙ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ ጨምሮ የክልል የዞን የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች ተሳትፈዋል።

በእውቀትና በስነምግባር የታንጸ ተወዳዳሪ ትውልድ ለማፍራት ዘመኑን የሚዋጅና የሚመጥን ትምህርት ቤት መገንባት ፋይዳው ከፍተኛ ነው:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) ነሐሴ 23/2018(ወልቂጤ)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን የጉንችሬ ብራይት ቅድመ 1ኛ እና 1ኛ ደረጃ ት/ቤት በዛሬው እለት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት ጥራት ያለው ትምህርት ተደራሽ በማድረግ ብቁ፣ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ እንዲፈጠር በልዩ ትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል። ትምህርት ቤቱ ተገንብቶ ለውጤት እንዲበቃ ላደረጉ ለሚስተር ሮቤርቶ ቤተሰቦች እና ካንትሪ ዳይሬክተር ሆነው እየሰሩ ላሉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። የትኛውም ፕሮጀክት የሚነሳው ከሀሳብ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ሀሳብን ወደ ተግባር በመተርጎም ፕሮጀክቱን እውን ላደረጉ ሁሉ ርዕሰ መስተዳድሩ በራሳቸው እና በክልሉ መንግስት ስም ምስጋና አቅርበዋል። በኢትዮጵያ የልማት ስራ ተጀመረ እንጂ አዳጊ የሆነውን የህዝብ ፍላጎትን በማሟላት ረገድ ቀሪ ስራ ይኖራል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በቀጥተኛ የልማት ስራ መሳተፍ ከጀመረች ጥቂት ዓመታት መቆጠራቸውን ጠቅሰዋል። የአካባቢው ተወላጆች ተባብረን የልጆቻችንን የወደፊት ብሩህ ተስፋ ማለምለም ይገባል ብለዋል። የዚህ ዘመን ትውልድ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳዳሪ መሆንን ይሻል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ለዚህም ዘመኑን የሚመጥን እና የሚዋጅ ስራ ይጠይቃል ብለዋል። ትምህርት አለምን የሚለውጥ መሳሪያ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ህጻናት ተገቢውን እንክብካቤ አግኝተው ማደግ እንዲችሉ በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል። ተያይዘን ኢትዮጵያን እና ክልላችንን እንገነባለን ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የኢትዮጵያን ትንሳኤ እውን እናደርጋለን ሲሉም ጠቅሰዋል። ከትምህርት ቤት ግንባታ ባለፈ በጤናውም ዘርፍ የህዝብ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል እርስቱ ይርዳው በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት መጀመሪያ መዋዕለ እጻናት መገንባት ታሳቢ ያደረገ እንደነበር የተናገሩት መንግስት የህዝቡን የመሰረተ ልማት ፍላጎት ለማሟላት በልዩ ትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑም ምክትል ኮሚሽነር ጀነራሉ አመላክተዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች በተለይም ወጣቶች የህጻናት ትምህርት ቤት እንዲገነባላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ በልበ ቀናነት በመቀበል ወደ ተግባር በመገባቱ ለውጤት በቅቷል ብለዋል። በከተማው ቅድመ 1ኛ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት በዛሬው እለት ለምረቃ ማብቃት መቻሉን ጠቅሰዋል። ትምህርት ቤቱ አሁን ለደረሰበት ደረጃ እንዲበቃ ዲዛይን ከመንደፍ ጀምሮ የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ የቼንትሮ ኢትዮጵያ መስራች እና ፕሬዝዳንት ለነበሩት ሮቤርቶ ራባቴኒ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራሉ ምስጋና አቅርበዋል። ዛሬ እኒህ ልበ ቀና አባት በህይወት ባይኖሩም ህያው ስራቸው በትውልዱ ዘንድ ሲታወስ እንደሚኖርም ጠቁመዋል። ከነባር ይዞታቸው ተነስተው ለትምህርት ቤት ግንባታ እንዲሆን ትብብራቸውን ለገለጹ ነዋሪዎች እና ለወንድም ተስፋዬ ይገዙ ምስጋና አቅርበዋል። የመደመር መንግስት ለህብረተሰቡ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን እያበረከተ ይገኛል ያሉት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራሉ ዛሬ የትምህርት እና የጤና ፕሮጀክቶችን አስመረቅን እንጂ ከዚህ በላቀ ደረጃ በሁሉም አካባቢዎች የልማት ስራዎችን ተደራሽ እየተደረገ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። በከተማም ሆነ በገጠር አካባቢዎች የህብረተሰቡን ህይወት ለማሻሻል የጋራ ትብብር እና ጥረት ይጠይቃል ሲሉም ኮሚሽነር ጀነራሉ ጥሪ አቅርበዋል። የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው ትምህርት የሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ ሁሉም በዘርፉ ኢንቨስት ሊያደርግ ይገባል ብለዋል። በዞኑ የትምህርት ጥራትና የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻል የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አቶ ላጫ ጋሩማ ገለጻ የዞኑ መንግስት በዘርፉ ውጤት ለማስመዝገብ ለቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በከተማው የተገነባው ቅድመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዞኑ ግንባር ቀደምና አርአያነት ያለው መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህ ደረጃውን የጠበቀው ትምህርት ቤት በእውቀት የበለጸገ ተወዳዳሪ ትውልድ በማፍራት ረገድ ፋይዳው ከፍተኛ ነው ያሉት። የኢፌዲሪ መስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ እና የትምህርት ቤቱ ግንባታ አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ ይገዙ እንደገለጹት በአካባቢና በሰፈር ሳንታጠር መስራት ከቻልን የህዝባችንን ህይወት መለወጥ ቀላል ነው ብለዋል። በእርሳቸው አስተባባሪነት በተለያዩ አካባቢዎች 30 ትምህርት ቤቶችን ማስገንባት ችለናል ያሉት አቶ ተስፋዬ በትምህርት ዘርፍ የሚደረገው ኢንቬስትመንት ድንበር የለውም ብሲሉም ጠቁመዋል። የጉንችሬ ከተማ ከንቲባ አቶ አብድልቋድር ሂጅራ የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻል የትምህርት ተቋማት ደረጃቸው ማሻሻል ወሳኝ ነው ብለዋል። በቀጣይም በዘርፉ የተጀመረውን የትምህርት ጥራትና የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻል የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ ይኖርበታል ብለዋል። የቼንትሮ አዩቲ ፔርሌ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ፖውላ አሪቼ እንዳሉት ትምህርት የህጻናትን የወደፊት ህይወት የሚለውጥ መሳሪያ ነው ብለዋል። በዞኑ የተገነባው ትምህርት ቤት ሀገር የሚለውጡ ዜጎች የሚፈጠሩበት ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። ትምህርት ቤቱ ቀጣይነት እንዲኖረው መሰረተ ልማቱን መጠበቅና መንከባከብ ተገቢ ስለመሆኑም አመላክተዋል።

ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ አስተዳደር በ74 ሚሊዮን ብር በመንግስትና በአጋር ድርጅት ትብብር የተገነባው የጉንችሬ ብራይት ቅድመ መደበኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መርቀው ከፈቱ። ነሀሴ 23/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ ተገኝተው የጉንችሬ ብራይት ቅድመ መደበኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መርቀው ከፍተዋል። በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል እርስቱ ይርዳው ሀሳብ አመንጪነት የቼንትሮ ለኢትዮጵያ አጋር ድርጅት ትምህርት ቤቱን ገንብቶ ለምረቃ በቅቷል። በ74 ሚሊዮን ብር ወጪ በመንግስትና በአጋር ድርጅት የተገነባው ትምህርት ቤቱ 24 የመማሪያና 4 የአስተዳደር ክፍሎች እንዲሁም 2 ደረጃቸውን የጠበቁ መጸዳጃ ቤቶች ያካተተ መሆኑን ተገልጿል። ይህ ቅድመ መደበኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በከተማው መገንባቱ ህጻናት በአቅራቢያቸው ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል። በዞኑ የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥና የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻል ቅድመ መደበኛና ቅድመ አንደኛ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተጠቁሟል። ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ጨምሮ የመንግስት የስራ ኃላፊዎቹ በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ የአረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል። በምረቃ መርሃ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር አቶ እርስቱ ይርዳው፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ናስር ሀሰን፣ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሸው ጣሰው በጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የጉንችሬ ጤና ጣቢያ መርቀው ከፈቱ። ነሀሴ 23/2018(ወልቂጤ) ጤና ጣቢያው ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በመንግስት፣ በህብረተሰብና በአጋር ድርጅት ትብብር መገንባቱንም ተጠቁሟል። ይህ ጤና ጣቢያ በከተማው መገንባቱ የሆስፒታሉ የስራ ጫና ከመቀነስ ባለፈ የዞኑ የጤና ሽፋን ከፋ በማድረግ ረገድ ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑን ተገልጿል። ከዚህም ባለፈ የእናቶችና ህጻናት ሞት በመቀነስ ህብረተሰቡ በአቅራቢያቸው ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል። በምረቃ መርሃ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር አቶ እርስቱ ይርዳው፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ናስር ሀሰን፣ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የግብቻነ ኢትዮጵያ ክልል ቡር ኣተድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በጉራጌ ዞን ጉንችርየ ቤሮ ተ40 ሚሊዮን በᎈር ቀርሺ ያረሰዊ ኣፉያ ቤት መነቆም ከፈቶም። ናሴ 23/2018(ወርቕጤ) በጉራጌ ዞን ጉንችርየ ቤሮ ተ40 ሚሊዮን በᎈር ቀርሺ በመንግስት፣ በሐልቅም በአጉዣ ድርጅት ያረሰዊ ኣፉያ ቤት የግብቻነ ኢትዮጵያ ክልል ቡር ኣራባር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው፣ የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ይትኸተሮ ኮሚሽነር ኣበቃጥ እርስቱ ይርዳው፣ የክልልዌ ይትኸተሮ ኣራባሪም ትምርት ቢሮ ዳነ፣ የጉራጌ ዞን ቡር ኣራባሪ ኣበቃጥ ላጫ ጋሩማ፣ የክልል፣ዞን፣ ወረዳም የከተማ ንቅ ንቅ የሜና ዳነ ባነዎᎄ ወመንቅ ቈነሺም። ተዝ የበደረ ሐልቅዌ ይትረጠብወ ጤና ጣቢያ በቁርቤ ባምበሮተታ ንቅ ጅጓረ ይሰራወ የረፐረሐማ ኦጂም። አሗ ዝሕ ጤና ጣቢያዌ በቾቺጋ ጨረተነ አገክሮት ባዎት የሐልቅዌ አፉያ ይትቅዬ ንቅ ደረግ ይሸክት ቧሪም። ሑዌት ኣርዋ ኣዶት ቲትኽታተረማ፣ ቲተርፈማም በተነፈማ ኣንቐም ይትረጠበማᎌዬ ያጘጝርቃር ወሕረታ ኦጂም። ተዝም በፎር ኣፉያ ጣቢያዌ በቤሮዌ ያነ ያተነ ደረጃ ሆስፒታል ንዥነር ያትቓንር ቲሐር የዞንዌ ያፉያ ሽፋን ያትረቅቃር ወሕረታ ኦጂም። አኪምቤትዌ ያረሰዊ ተ40 ሚሊዮን በፎር ቀርሺ ያጨᎌ ቲሐር መንግስት፣ ሐልቅም የአጉዣ ድርጅት ያመነበዊ ድጋፍ ንቅ ኣሐዳ ያቴብ ቃሩ።

የጉራጌ ዞን ምክር ቤት አባላት የመንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ያዘጋጀውን የፎቶ ኤግዚብሽን ጎበኙ። ነሀሴ 22/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ ) የጉራጌ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ ዓመት 31ኛ መደበኛ ጉባኤ ተሳታፊ የምክር ቤት አባላቶች የጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ያዘጋጀውን የአዳራሽ ፎቶ ግራፍ ኤግዚብሽን ጉብኝት አደረጉ። የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕዩ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማና የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ ሪቫን በመቁረጥ አስጀምረውታል። የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ የፎቶ ኤግዚቢሽኑ በተመለከቱበት ወቅት እንዳሉት ሚዲያ ለሰላም ፣ለልማት ፣ለአብሮነት፣የጋራ ገዢ ትርክት ለመገንባት ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። በዞኑም በኢኮኖሚያዊ ፣በማህበራዊና በፖለቲካዊ ዘርፎች እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ለህዝብ በማድረስና ህዝቡም በልማት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን የኮሚኒኬሽን ዘርፉ ከፍተኛ ሚና ነበረው ብለዋል። ለአብነትም በግብርና ፣በማህበረሰቡ ባህልና ታሪክ፣በቋንቋ በአጠቃላይ በሁሉም ዘርፎች የዞኑ ጸጋዎች የበለጠ ጎልተው እንዲወጡ እድል ፈጥሯል ነው ያሉት አቶ ላጫ። የጉራጌ ማህበረሰብ በመላዉ አለምና የሀገሪቱ ክፍሎች ተዛዙሮ የሚሰራ እንደመሆኑ መጠን በዞኑ እየተከናወኑ ያሉ ሁነቶች መረጃ እንዲያገኝም አስችሏል። መረጃዎችን በተለይ በህትመት፣ በኤሌክትሮኒክስና በማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲዳረሱ መደረጉ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው አመታዊ የፎቶ ኤግዚቢሽን መዘጋጀቱ ማህበረሰቡ በአመቱ በዞኑ የተሰሩ ስራዎች በጥቅሉ በአንድ ቦታ ሆነው እንዲመለከቱ የሚያደርግ መሆኑን ጠቁመዋል። በመምሪያው የተጀመሩ ስራዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። አቶ ላጫ አክለውም በቀጣይ የዘመናት የማህበረሰቡ ጥያቄ የነበረው የጉራጌ የማህበረሰብ የቴሌቬዥን ጣቢያ በቅርቡ ስራ እንዲጀምር በልዩ ትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የፎቶ አውደ ርዕይ ዝግጅት ጉብኝት ካደሩጉ የምክር ቤት አባል መካከል አቶ ፍቃደ ቢረዳና አቶ ምራ መሀመድድ እንዳሉት የፎቶ አውድ ርዕዩ በወረቀትና በሪፖርት ከሚቀርበው በላይ በተጨባጭ ህዝቡ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በቀላሉ የሚያይበት እንደሆነ ጠቅሰዋል። በዞኑ በሁሉም ዘርፎች በርካታ የሚታዩ የሚጨበጡና የሚዳሰሱ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ በቂ ማሳያና ማስረጃም ጭምር እንደሆነም ተናግረዋል። በጉብኝቱ አንዳንድ ተረስተው የነበሩ እንደ ነቕ ያሉ ባህሎቻችን ባለፉት አራትና አምስት አመታት ትውልዱ እንዲያውቃቸው በደንብ እየተሰራበት ይገኛልም ብለዋል። በፎቶ አውደ ርዕዩ የቀረቡ ሁነቶች በዶክመንቴሽን ሰብሰብ አድርጎ እንዲታዩ ማድረግ ማህበረሰቡ ጥሩ ትምህርት እንዲቀስምና አዲሱ ትውልድ ትልቅ ልምድ የሚወስድበት እንደሆነም አብራርተዋል። የገጠር ኮሪደር ወይም ጀፎረ ለሀገራችን ትልቅ ቅርስ መሆኑም አመላክተው ይህ እሴት ትላንት የነበሩ አባቶቻችን ምንም ሳይማሩ የቀየሱት የምህንድስና ጥበብ እንደሆነና ከትውልድ ትውልድ እየተሸጋገረ የመጣ ትልቅ ሀብታችን ነው ብለዋል። አውደ ርዕዩ የቀደሙ ታሪካዊና ባህላዊ እሴቶችን ለአዲሱ ትውልድ ለማስተላለፍ ትልቅ ትምህርት ሰጪ ነው ብለዋል ሲል የዘገበው የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ነው።

የጉራጌ ዞን የሐልቅ ወባጀ ቤት የ4ተነ ወረር 13ተነ ዘበር 31ተነ የርወሰዊ ዮባጀ ቤት ድሙድ በወርቕጤ ከተማ ኣትባዶት ቈነሺም። ‎ ‎ናሴ 21/2018 ዘበር (ወርቕጤየ) በግብቻነ ኢትዮጵያ ክልል የጉራጌ ዞን የሐልቅ ወባጀ ቤት 4ተነ ወረር 13ተነ ዘበር የ31ተነ ወባጀ በወርቕጤ ከተማ ዋትባዳ ቀነሰም። ቦባጀዌ የ4ተነ ወረር 13ተነ ዘበር 11ነ ድርሑት ወባጀ ጉባኤ ቃለ ጉባኤም፣ የ2018 ዘበር ኣትያኖት ሜና፣ ሪፖርት፣ የ2019 ዘበር ኣትያኖት ሜና፣ ያታት የሜና ዳነ ሹመት፣ የ2019 ዘበር በጀት ተቐነዎም ያጸድቒሐማ በረከውዮ ወሬ ሗሪም። ቦባጀዌ የጉራጌ ዞን ቡር አራባሪ አበቃጥ ላጫ ጋሩማ፣ የዞንዌ ወባጀ ቤት ቡር አፈጉባኤ አበቃጥ ሐይሩ መሓመድ፣የዞንዌ ፍትድ ቤት ቡር አተድር አበቃጥ ሙዘኪር አወል፣የዞንዌ ዝፓና ፓርቲ ጥፈት ሸመነ አራባሪ አበቃጥ ናስር ሀሰን እንጎድ የክልልም የዞንዌ የሐልቅ ወባጀ ቤት አባል ተረከዎም።

የዞኑ የልማት ጸጋዎችና እሴቶች አጉልቶ ለማውጣት የኮሚኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፉ በሰው ሀይል፣ በቁሳቁስና በበጀት መደገፍ ይገባል፦አቶ አበራ ወንድሙ ነሀሴ 20/2018(ወልቂጤ) መምሪያው የ2018 የስራ አፈጻጸም እና የ2019 እቅድ ላይ ያተኮር የውይይትና የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል። የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ ሚዲያ በዞኑ እየተሰሩ ባሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ ህዝብና መንግስትን የሚያገናኝ ድልድይ መሆኑን ገልጸዋል። የዞኑ የልማት ጸጋዎችና እሴቶች አጉልቶ ለማውጣት የኮሚኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፉ በሰው ሀይል፣ በቁሳቁስና በበጀት መደገፍ ይገባል፦አቶ አበራ ወንድሙ ‎ በዞኑ ጀፎረን ጨምሮ በርካታ ያልታዩና ያልተጎበኙ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፀጋዎች መኖራቸውን ጠቁመው እነዚህ ሃብቶችን በማልማት በሃገር ደረጃ እንዲታወቁ በባለቤትነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን በዚህ ወቅት እንዳሉት ለተቋሙ የአመለካከት ለውጥ በማድረግ በሰው ሀይል፣ በቁሳቁስና በበጀት መደገፍ ይገባል። የሚሰሩ የሚዲያ ስራዎች በጥራት በፍጥነትና በተደራሽነት በመስራት የዞኑ ማህበረሰብ የሚመጥን የሚዲያ ስራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። አቶ ሸምሱ አክለውም የጉራጊኛ ቋንቋ ለማሳደግ ሚዲያ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዷል ያሉ ሲሆን ዘገባዎችን በጉራጊኛ መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። የሚዲያ ስራዎችን በገጽ ለገጽ፣በኤሌክትሮኒክስ ፣በህትመትና በማህበራዊ ሚዲያዎች ፕላትፎርሞች በመስፋት በመስራት የዞኑ ጸጋ፣እሴትችና ልማቶች ለአለም ማስተዋወቅ እንደሚገባ አስታውቀዋል። ለኮሚኒኬሽንና ሚዲያ ስራዎች ውጤታማነት ከሚመለከታቸው ተቋሟትና ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንዲሰራ የተናግረዋል። በቀጣይ በጀት አመትም የጉራጌ የማህበረሰብ ቴሌቪዥን ስራ ለማስጀመር የዞኑ መንግስት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን አቶ ሸምሱ አመላክተዋል። የዞኑ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሃዲሞ ሃሰን በኮሙኒኬሽን ዘርፉ የሚከናወኑ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን በመግለጽ በቀጣይም ማህበረሰቡን የሚመጥኑና ትውልድ ተሻጋሪ ተግባራትን መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው መምሪያው መረጃን ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገው ጥረት አበረታች መሆኑን ገልጸው በቀጣይም ለስራ ማነቆ የሆኑ የግብዓትና የባለሙያ ውስንነቶችን በመቅረፍ በጥራት ላይ የተመሰረተ መረጃ ለህዝብ ማድረስ እንደሚገባ አሳስበዋል። የተለያዩ የሚዲያ አድማሶች በማስፋትና በማሰራጨት በበዞኑ በሚዲያ የበለጸገ ማህበረሰብ መፍጠር ይገባል ብለው ለዚህ ደግሞ አመራሩና ባለሙያዎች ስራቸው የበለጠ ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት። በ2018 የተገኙ ጠንካራ ውጤቶች በማስቀጠልና ክፍተቶች በማስተካከል በ2019 የተሻለ ስራ ለመስራት አቅደው እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በመጨረሻም መምሪያው ከሁሉም መዋቅሮች የ2019 እቅድ ላይ የግብ ስምምነት በማድረግ በ2018 የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ መዋቅሮች እና ተቋማት እውቅናና ሽልማት አበርክቶላቸዋል። በዚህም እኖር እና ምሁር አክሊል ወረዳዎች 1ኛ፣ቸሀ ወረዳ ደግሞ 2ኛ ሲወጡ በከተሞች ወልቂጤ ከተማ 1ኛ በመሆን እውቅናና ሽልማት አግኝተዋል።