አርምሞ🧘🏽♂
📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу አርምሞ🧘🏽♂
Канал አርምሞ🧘🏽♂ (@armemo_offical) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 11 658 підписників, посідаючи 7 594 місце в категорії Релігія і духовність та 2 877 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 11 658 підписників.
За останніми даними від 16 вересня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 229, а за останні 24 години на 0, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 16.23%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає N/A% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 1 892 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 0 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 42.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“ጥ ቂ ት ም ና ኔ. .🧘🏽♂️”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 17 вересня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.
በቤኒሻንጉል ጉምዝ ጉባ ወረዳ መከተል ዞን የካቲት 24 በ2014 ዓ.ም ሰውን በእሳት እያቃጠሉ ቪድዮ ቀርጸው የለቀቁ የወታደር ልብስ የለበሱ አካላት ናቸው። EHRC በዜና አርቲክሉ ላይ እንደዘገበው 11 ሲቪሎች በደህንነት ኃይሎች ከተገደሉ በኋላ አስከሬኖቻቸው ተቃጥለዋል፤ ከእነሱ መካከል አንዱ በሕይወት እያለ ታስሮ ወደ እሳት እንደተጣለ የተመረመረው ሪፖርት አረጋጧል። Ethiopia Insight ሆነ የUN ሰነድም የተለያዩ ምንጮችን ጠቅሶ በዚያኑ ቀን ሰዎችሁ ተይዘው ክፉኛ ተደብድበውና ተገድለው እንደተቃጠሉ፤ ከዚያም አንድ ሰው በሕይወት እያለ እንደተቃጠለ ከግፍ ፈጻሚዎችሁ የቪድዮ ቅጂ ማረጋገጥ ተችሏል።
#የ2014ቱ_የታህሳሱ_ጭፍጨፋም ሌላ ትኩሳት ነው። ይሄም እንደሌሎችሁ የቪድዮ ቅጂ ያለው ሲሆን ቦታ ከቪድዮው ጥራት አንፃር በውል ባይታወቅም በድጋሚ በ2015 ዓ.ም መሰል ቪድዮዎች በየቦታው ተሰራጭተው ለመታዘብ ችለናል። ቪድዮው ላይ የወታደራዊ ልብስ የለበሱ ግለሰቦች ከመኪና ላይ ሰዎችን አስወርደው ሲረሽኗቸው ያሳያል። EHRC ቪድዮው ላይ ምርመራ በማድረግ ቢያንስ ወደ 30 የሚጠጉ ሰዎች በጅምላ extrajudicial killing እንደተገደሉ አሳውቋል።
አያችሁ ይህ ሁሉ ጭፍጨፋ ያስተናገዱት ወታደሮች እርስ በእርሳቸው ተዋግተው ሳይሆን ምንም የማያውቁ ንጹሃን ተጠርተው ነው። በእኛ ሀገር ጦርነት ተዋጊውን ሲገድል እንብዛም አይታይም። ይልቅስ በብዙ ግጭቶች ውስጥ የሚገደሉት ሰዎች በግጭቱ ውስጥ ምንም ድርሻ የሌላቸው ሲቪሊያንስ ናቸው። ምክንያቱም ጦርነቱ ከግለሰቦች ጋር የሚፈጠር ግጭት ሳይሆን ቡድኖችን ግምት ውስጥ የሚያስገባ አካሄድ ነው። አንድ ሰው በተወለደበት ቦታ፣ በቋንቋው፣ በብሔሩ ወይም በማንነቱ ብቻ «የጠላት አካል» ተደርጎ ይወሰዳል።
በነገራችን ላይ ይህን ሁሉ በቀላሉ የጦርነት አሰቃቂነት አልለውም፤ የሰዎች መመናመን ብቻም አይባልም፣ ይልቅስ ይህ የሰውነት ትርጉም መጥፋትም ጭምር ነው። እኔ በበኩል እንዲህ ዓይነት ፎቶዎች፣ ዜና እና ቪድዮዎችን ማየት አቁሚያለሁ። እንደዚህ ዓይነት የግፍ ፎቶ ሲለጠፍ አዕምሮዬ ላይ ቀጥታ የሚመጣው፦«የሳምንት አጀንዳ» የሚለው ምፀት ነው!።
አንድ ማኅበረሰብ እንዲህ አይነት በደሎችን ማየት ሲያበዛ ግፍ በሰው ዓይን ውስጥ ከአሰቃቂነቱ ወደ ተለመደ ነገር መለወጥ ይጀምራል። የአንድ ሀገር ትልቁ አደጋ ሰዎች መሞታቸው ብቻ አይደለም፤ ሰዎች ሌሎች ሰዎች ሲሞቱ ምንም ሳይሰማቸው መቅረቱ ነው። ያኔ ጦርነት ከመሬት ግጭት ወጥቶ ወደ ሰው ነፍስ ይገባል!። የሰዎችም ሞት የቁጥር እና የቃላት ማዳመቂያ የሳምንት አጀንዳ ሆኖ ይቀራል!። ከዚህ ሁሉ ውጥንቅጥ በኋላ ሀገራችን ሰላም ትሆናለች ብሎ እንደሚያስብ አማኝ ጥሬ የለም!። ከዚህ በኋላ ከዚህም የበሳ እንጂ የሚበርድ እሳት የለም!። አዲስ አበቤም በቅርቡ ጠብቂ የደም ምድር..!
@Armemo_officalይህ የፖለቲካ ሳይኮሎጂ ሰውን «ወንጀለኛ» ወይም «ክፉ» ብሎ መጥራት በእሱ ላይ የሚደርስበት ግፍ እንደመደበኛ ወይም እንደምክኒያታዊነት እንዲቀበሉት የማድረጊያ ሲስተም ነው። «ሁለት ፋኖዎች ዛሬ ገድለናል፣ አራት ጁንታዎች ተረሽነዋል፣ አንድ ክፈለ ጦር ሸኔ ደምስሰናል!» የሚለው የስም ታፔላ የሟችሁን ሞት ዋጋ የሚያሳንስ Dehumanization ነው። ሌላውን ሰው እንደ ሙሉ ሰው ማየት ሲቀር ሞታቸው «እነሱ» የሚል የቁጥር ስያሜ ተሰጥቶት ዋጋ ያለው ክብር ህይወትን የማሳነስ እስራቴጂ ነው። በጁንታው እና በፋኖ ከለላ ስማቸው፣ ቤተሰባቸው፣ ሕልማቸው፣ ፍርሃታቸው እና ሕይወታቸው በሌላ ሰው ዓይን ይረክሳል። ያኔ ነው ሰውን መግደል እንደነፍስ ማጥፋት ከማሰብ ይልቅ ጠላትን ማስወገድ መስሎ እንዲሰማን የሚያደርገን።
ቅርብ ግዜ የተከሰተው ፋኖ ናችሁ በሚል የተረሸኑትና አስከሬናቸውም እንዳይነሳ ለቀናት የተከለከለው ተመስገን ጌታቸው፣ ይታገሱ አሰግደው፣ ግዛው ግርማዬ እንደምሳሌ ማየት በቂ ነው። እንዲህ አይነቱን የፖለቲካ ስልት ማወቅ ከፈለጋችሁ «Social Identity» ቲዎሪን ሰርች አድርጋችሁ ማንበብ ትችላላችሁ። የሰው ልጅ ማንነት «እኛ» እና «እነሱ» በሚል ጎራ ሲከፈል የሌላው ቡድን ሕይወት ከእኛ ሕይወት ያነሰ ዋጋ ያለው እንደሆነ የሚያስብ አደገኛ የሞራል ልዩነት በማኀበረሰቡ ዘንድ ሊፈጠር ይችላል።
ይህ Collective Punishment አንድ ሰው ወይም አንድ ቡድን በፈጸመው ነገር ተነሳስተው ከግጭቱ ጋር በቀጥታ ያልተያያዙ ሰዎችን የመቅጣት ሰይጣናዊ አካሄድ ነው። እንዲህ አይነቱ ግፍ በጦርነት ውስጥ ከሚከሰቱት እጅግ አደገኛ የጭፍጨፋ መዋቅሮች አንደኛው ነው። ቢሆንም ግን ቪድዮ መቅረጹ ደግሞ ሌላ የአረመኔነት ደረጃ ነው። ይሄም ከላይ እንደጠቀስኩት «Spectacle of Violence» ወይም «የግፍ ትዕይንት» ይባላል። ግፍ ከተፈጸመ በኋላ ማስረጃ ለመያዝ ብቻ ሳይሆን ለማስፈራራት፣ ለማዋረድ፣ ለማሳየት እና «እኛ እንዲህ ማድረግ እንችላለን» የሚል የኃይል መልዕክት ለማስተላለፍ በሞተ ሬሳ ላይ ቪድዮ እንደመስራት ያለ ሌላ የፖለቲካ መልዕክት ጭምር ነው። ሰዎችን መግደል የተለመደ ግፍ ቢሆንም የሞቱትን አስከሬን ለሌሎች ለማስፈራራት ማሳየት ግን ግፉን ወደ terroristic communication ይቀይረዋል። በቪድዮው ላይም ለማስተላለፍ የሚፈልጉት፦«እኛን ብትቃወሙ ይህ ይደርስባችኋል» የሚል መልዕክት ነው።
በተደጋጋሚ በሶሻል ሚዲያ ላይ እንዲህ ዓይነት መሰል ቪድዮዎች ሲሰራጩ የሰው ልጅ ነፍስ እንዲረክስ ምክንያት ሆኖታል። መጀመሪያ ሊገደል የታሰበውን ሰው ከሰውነቱ ማስወጣት፤ ቀጥሎ ደግሞ ስሙን «ሸኔ እና ፋኖ» በሚል መለያ መተካት፤ ከዚያ «ጠላታችን» ነው ማለት፤ በመጨረሻም ሰለባ የሆነውን ሰውዬ እንደተራ ነፍስ በማየት መግደል። ታድያ ማኀበረሰቡ ሌላውን ሰው እንደ ሰው ማየት በሚያቆምበት ቅጽበት ግፍን የሚቃወምበት የሞራል ግድግዳው ይፈርሳል። ከዚያ በኋላ ግን ገጀራው ሳይሆን ሀሳብ ነው መሳርያ የሚሆነው። ጥይቱ ብቻ አይገድልም፤ የተዛባው ማንነት ጭምር ነው ገዳይ የሚሆነው። እሳቱ ሰውዬውን ብቻ አያቃጥለውም፤ ይልቅስ የሰውን ሕይወት ዋጋ የሚያሳንሰው ርዕዮተ ዓለም ጭምር ነው አብሮ የሚቃጠለው። እነዚህ ከስር ያስቀምጥኳቸው በሀገራችን ኢትዮጵያ የተከሰቱ የቪድዎ እና የፎቶ ማስረጃ ያላቸው ጭፍጨፋዎች ናቸው። ያልተዘገቡት ደግሞ ከዚህ የበለጡ እንደሆነ ልቦናችን ያውቀዋል።
#ማይካድራ በ2013 ዓ.ም ጥቅምት 30 በማይካድራ ምዕራብ ትግራይ የተፈጸመው መቼም ከልባችን የማይወጣ ክስተት ሆኖ ነው ያለፈው። በትግራይ ጦርነት መጀመሪያ ወራት አካባቢ ከተፈጸሙ እጅግ አስከፊ ጭፍጨፋዎች አንዱ ነው ሊባልም ይችላል። በዛ ወቅት የተፈጠረውን ክስተት «Amnesty International» በድህረ ገፁ የፎቶ እና የቪድዮ ማስረጃ አስቀምጦለታል። በቪድዮ እና በፎቶ ባስቀመጠው ዜና ላይም በውድቅት ሌሊት ብዙ ሰዎች በቢላዋ፣ በገጀራ እና በሌሎች ስለታም መሣሪያዎች እንደተገደሉ ዘግቧል። ከዚህ ሌላም ሰፊ ምርመራም በማካሄድ በማይካድራ የአማራ ሲቪሎች በገጀራ፣ በመጥረቢያና በሌሎች ባህላዊ መሣሪያዎች መገደላቸውን ዝርዝር መረጃ አውጥተዋል። (source፦Amnesty International UK
Human Rights Watch እና Amnesty)
#ማህበረ_ደጎ በ2013 በጥር እና በታኅሣሥ ወራቶች በትግራይ አካባቢ የተከሰተ ሌላኛው አሳዛኝ ክስተት ነው። ማስረጃውም Bellingcat ከBBC Africa Eye እና Newsy ጋር ተጣምሮ በመስራት አምስት ቪድዮዎችን በgeolocation አውጥቷል። ቪድዮዎቹም ወታደራዊ ልብስ የለበሱ ሰዎች ሲቪሎችን እየገደሉ የሚያሳይ ሲሆን፤ ክስተቱም በ2013 ጥርና ታህሣሥ ወር ላይ በማህበረ ደጎ አካባቢ መከሰቱን ምርመራው አረጋግጧል።
#አክሱም ላይ በተመሳሳይ አመት ከህዳር 19 እስከ 20 ባሉት ወቅቶች የኤርትራ ወታደሮች ምንም ያልታጠቁ ሲቪሎችን በጎዳናዎች ላይ እና በቤት ለቤት ፍተሻ በማካሄድ እንደጉድ የትግራይ ንጽሃንን እየጨፈጨፉ እንደነበር Amnesty International ዘግቧል።ዛሬ በዚህ ጉዳይ የመጨረሻ ፖለቲካል አርቲክሌ ነው። ስለዚህ እስከመጨረሻው በማንበብ እንሰነባበት። መጻፉ ላይ ልምድ ቢኖረኝም መረጃ ለማሰባሰብና የመረጃውን ተአማኒነት ለማረጋገጥ ግን ብዙ ሰዓት ፈጅቶብኛል። ስለዚህ ላይክ በማድረግ ጀምሩ።
በሀገራችን ኢትዮጲያ ጦርነት የተለመደ አሳዛኝ ክስተት ነው። በተለይ ከደርግ እስከ ኢሕአዴግ ብዙ የእርስ በእርስ ጦርነቶችን አስተናግደናል። ነገር ግን ከ2010 በኋላ የመጣው የሽግግር መንግስት ተከትሎ ታይቶ የማይታወቅ የሰብዓዊነት ጭካኔ በሀገራችን ኢትዮጲያ ተፈጽሟል። ይህ የጭካኔ አካሄድ የተለመደ ነገር ቢሆን ፖለቲካዊ ሰብዓዊነትን በመንፈግ ጥቃትን ወደ ትዕይንት በመቀየር ፎቶ እና ቪድዮ ሰርተው የሚለቁ አውሬዎች መብዛታቸው ያስደነግጣል።
እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከ2020 እስካለንበት 2026 ድረስ ግፍን መስማት የተለመደ ነገር ሆኗል። ከዛ በላይ ግን ግፍን ወደ ቪድዮ ቀይሮ በሶሻል ሚዲያ ፖስት የሚያደርጉ ሰዎች መብዛታቸው ብቻ ሳይሆን ያንን ቪድዮ እና ፎቶ ደጋግሜ ማየቴ የአዕምሮ ቀውስ ውስጥ አስገብቶኝ ነበር። እንዲህ አይነት የጭካኔ ትዕይንት በሱዳን እና መሰል ጎረቤት ሀገሮች ላይ የሚፈጸም በፖለቲካ አጠራሩም «Political Dehumanization and the Spectacle of Violence» ይባላል።
በሀገራችን ኢትዮጲያ ሰዎችን በገጀራ እያረዱ ቪድዮ የሚቀርጹ፣ ሰዎችን እየረሸኑ የሚቀርጹ፣ ሰውን ከእነህይወቱ በእሳት እያቃጠሉ ቪድዮ የሚቀርጹ ነብሰ በላ ሰዎች ማየት የተለመደ ከሆነ ሰነባብቷል። ክስተቱም «የአንድ ሳምንት አጀንዳ» ነው። ቢሆንም ይህንን ጭካኔ ብሎ ብቻ መግለጽ በቂ አይሆንም። ይልቅስ በፖለቲካል ሳይኮሎጂ ከሚጠቀሱ ጽንሰ-ሐሳቦች መካከል Moral Disengagement ጭምር ነው።በርግጥ አንዳንድ ወንዶች ፌሚኒዝምን የሚደግፉት ሴትን እንደነፃ ሰብዓዊ ፍጡር ስለሚመለከቷት ነው፤ ሌሎች በተቃራኒው ፌሚኒዝምን የራሳቸውን ማህበራዊ ምስል ለመገንባት ይጠቀሙበታል። የመጀመሪያው ሰውዬ ለአንድ መርህ የቆመ ነው፤ ሁለተኛው ሰው ግን በመርሁ በኩል ራሱን የሚሸጥ asshole ነው። አንደኛው «ይህ ትክክል ስለሆነ እደግፈዋለሁ» ይላል፤ ሌላውኛው በተቃራኒው «ይህን ብናገር እኮ እኔን እንደ ጥሩ፣ እንደ ዘመናዊ እና ሴቶችን የሚያከብር ወንድ እንድታይ ያደርገኛል» ብሎ የሚያስብ ዘገምት ነው። ልዩነታቸው በቃላቱ ላይ ሳይሆን በዓላማቸው ላይ ነው።
ይህን አካሄድ በሳይኮሎጂው «validation seeking እና impression management» ይባላል። ሰውየው በውስጡ የሚሰማው የራስ ዋጋ በቂ እንዳልሆነ ስለሚሰማው ከሌሎች አድናቆት ለመሰብሰብ ይጋጋጣል። በዚህ ምክንያት «Nice guy» ወይም ጥሩ ሰው መሆን ለእሱ ከውስጡ የሚጣ ሳይሆን እንደ social currency ከውጭ የሚቀበለው ማንነት አድርጎ ይወስደዋል። ለዛም ነው ሴቶችን ሲያወድስ እና ስለእኩልነት ሲያወራ ስንመለከተው ሞራሊዝምን አክብሮ ሳይሆን፤ ያን ስነምግባር ሲፈጽም በሌሎች ዓይን የሚሰጠውን ዋጋ ቀመር ውስጥ የሚያስገባ እንጭጭ መሆኑን የምነግራችሁ!።
እንዲህ አይነቶችሁ ወንዶች ሃላል ሴቶችን ከሚተቹት በላይ ጨለምተኛ አስተሳሰብ የታቀፉ instrumentalization ባለቤት ወይም ባልቴት ናቸው። instrumentalization ማለት ዋጋን እንደ መጨረሻ ግብ ከመከተል ይልቅ ሌላ ነገር ለማግኘት በእሱ መጠቀሚያ የሚደርጉ እንቁሊጥያሞች ስብስብ ነው። እንዲህ አይነት ወንዶች ሴቷን የእራሷ መብት ያላት ሰው ሳይሆን የራሳቸው self-image የምታረጋግጥ መስታወት ነው የሚያደርጓት።
ብዙ ግዜ እሰማቸዋለሁ። በአፋቸው «ሴቶች ነፃ መሆን አለባቸው» ይላሉ፤ ነገር ግን በውስጣቸው የሚፈልጉት የሆነች ሻፉ ያሉባት ሴት እነሱን እንደምርጥ ወንድ ተመልክታ እንድትመርጣቸው ነው። የሚገርመው ደግሞ እንዲህ አይነት ወንድ ሴቷ ከእሱ በላይ ነፃ መሆኗን ሲመለከት የሌለ የበታችነት ስሜት ነው የሚሰማው። እኩልነት ብሎም የሚያወራለት አይዶሎጂ የሴቷን ነፃነት በማሰብ ሳይሆን የራሱን ምስል ለማረጋገጥ የሄደው እርቀት ነው። ይህ covert contract የሚባል የስነልቦና ሆነ የስነ መታወክም ምልክት ነው!። እንዲህ አይነቱን ወንድ አዕምሮውን በቪድ በርግደን ብናየው እንዲህ የሚል ድምፅ አለው፦«እኔ ላንቺ ጥሩ እሆናለሁ፤ አንቺም በምላሹ እምስሽን ትሰጪኛለሽ።» የሚል ድብቅ አላማ ያነገተ ላም አለኝ በሰማኝ ጡታ ግን ደርቋል 😂 ነገር ግን ስማኝ ወዳጄ ፍቅር ለሞራላዊ ባህሪ የሚከፈል ደመወዝ አይሆንም፤ ሌላ ሰውን ማክበርም የሌላውን ሰው ፍቅር ለመግዛት የሚሰጥ ተመን አይደለም።
ስለዚህ ምክሬን ስማ። ይህ Nice guy ለመሆን የምትጋጋጠው ነገር ውጤቱ ደም በደም ሆኖ መቅረት ብቻ ነው። በመጨረሻም የሌለ ወይም የትዬለሌ ስትጎዳ ውስጥ የሚቀረው ጥያቄ ይህ ብቻ ነው፦«እኔ ይሄ ሁሉ ነገር አድርጌላት እሷን ግን ግድ አልሰጣትም!»።
እዚህ ጋር ነው የተደበቀው ጥላህ አፈትልኮ የሚወጣው። አንተ ያደረገከው መልካምነት በእውነት ከልብ የመጣ ቢሆን ኖሮ ከእሷ ምላሽ አለማግኘት የሞራሉን ዋጋ ባላሳነሰው ነበር። ነገር ግን ምላሽ አለማግኘትህ ቁጣ ከፈጠረብህ፤ ያ መልካምነት ከአላምህ ይልቅ ኢንቨስትመንት ነው። ወዳጄ ይህ moral grandstanding ጭምር ነው። ሰው ሞራላዊ አቋሙን ለአላማው ትግል ከማዋል ይልቅ ራሱን እንደ ሞራላዊ ሰው ለማሳየት ሲጠቀምበት የሚፈጠር ሰልፊሽነት!።
ሁሌ ቢሆን እንዲህ አይነት ወንድ ስለ ሴቶች መብት ይሰብካል፣ ስለ toxic masculinity ይተቻል፣ ስለ patriarchy ይናገራል፣ የናዋል ኢል ሳዳዊ እና የሲሞን ዴ ቤውቬር አባባሎችን በቃሉ ይሸመድዳል። እንዲህ ማድረጉ እኮ ችግር የለውም። ነገር ግን የሚናገረው ዕውን ስለሚያምንበት ነው? ወይስ ሰዎች እንደዛ አድርገው እንዲያስቡት ስፈለገ ነው?። በርግጥ ይህ ውስጣዊ ግጭት የሚፈጥር የተሳሳተ አካሄድ ነው። አንድ ሰው ራሱን እንደ ጥሩ ሰው ለማየት ሲፈልግ እና ያ ጥሩ ሰው መሆኑን ግን ማረጋገጥ የሚፈልገው ከውጭ ሰው ሲሆን የሚፈጠር cognitive dissonance ግጭት ነው።
ከዚህ ግጭት በኋላ አዕምሮ እውነቱን ከመቀበል ይልቅ ለራሱ የሚያጽናና ታሪክ ይፈጥራል። እነዚህ የውሸት ትርክቶች ደግሞ ወደለየት አጥፊ የሚቀይሩ አስፈሪ አስተሳሰቦች ናቸው። «ጥሩ ወንድ ነህ» መባሉትን ከውጭ ማግኘት ስለቸገረው በውስጡ self-deception ለእራሱ መልሶ መናገር ይጀምራል። በስራው ውጤት ሌሎች ሰዎችን ከማሳመን ይልቅ እራስን ማታለል ቀላሉ መንገድ ነው የሚባለው ከዚህ አንፃር ነው። ቢሆንም አንዳንዴ ሰውየው ራሱን እየጠቀመ መሆኑን እንኳ ሳያውቅ ሞራሊቲን ለራሱ ጥቅም ሊያውል የሚችልበት አድቫንቴጅም አለ። ሴቶችን እየተከላከለ መስሎት ሊሆን ይችላል፤ በእውነቱ ግን የሚፈልገውን በውስጡ የሚጮኸው ድምፅ «ጥሩ ወንድ ነህ» ወደሚል ንግግር የመቀየር ፍላጎት ነው።
በመጨረሻም የሞራሊቲ እውነተኛ ፈተና በሰዎች ፊት የሚረጋገጥ ማስረጃ ሳይሆን፤ ማንም ሳያየን የምናደርገው የውስጥ ድምፅ ነው። ማንም ባያመሰግንህ አቋምህን ትጠብቃለ፤ ማንም ባይወድህም መንገድህን በፀጥታ ትከተላለህ። ያኔ ነው ዋጋ ያለው ሰው ወይም ዋጋ ያለው ወንድ የምትሆነው!። ነገር ግን ሞራሊዝምን የምትከተለው በሌሎች ዘንድ ሽልማት ለማግኘት ከሆነ ይህ ሞራሊቲ ስትራቴጂ ብቻ ሳይሆን ደናቁርትነት ጭምር ነው። ይህ ኢድየትነት ነው፣ ይህ ቫፊንኩሎ መሆን ነው ይህ ቢችአስ መሆንንም ያካትታል!።
እኔም ለዛ ሽልጥልጥ ወንድ ጥያቄ ብቻ ነበር ያቀረብኩለት፦አንተ በእውነት ለሴቶች እኩልነት ለመቆም አስበ ነው ወይስ እኩልነትን በመጠቀም ከሴቶች ፑሲ ለማግኘት የሄድከው እርቀት ነው?። ምክንያቱም አንድ ሰው ሴቷን ነፃ እንድትሆን እየሰበከ በውስጡ ግን እሷ እሱን እንድትመርጥ የሚጠብቅ ከሆነ፤ ይህ እኩልነት ሳይሆን የሴት ገላ ጥምዓት ነው!።
ጀለስ እንደዛ ወንድ ሲያበሻቅጥ የፌሚኒዝምን አይዶሎጂ እየደገፈ አለመሆኑ ገብቶኛል፤ ይልቅስ ዕድል እንዲሰጠው እየጠበቀ ነበር። እደሉም በአፉ፦«እኔ ከሴቶች ጎን ነኝ» ይላል፤ በውስጥ ደግሞ «እቺን ልጅ መቼ ይሆን የምተኛት?» የሚል ኤስቱፒዶ ቶንቶ ወይም የወንድ ደናቁርት መገለጫ ነው!።
@Armemo_officalትናንት አንድ ሽልጥልጥ ወንድ አጋጥሞኝ አንጀቴ ተቃጥሎ ነበር የዋልኩት። ወንድ እንደወንድነቱ እንጂ በሴቶች ለመወደድ የማይሆን ሴታሴት ባህሪ ሲያሳይ ዓሳ እንደሚያድን የጫካ ሰው በጦር ውጋው ውጋው የሚል ስሜት ነው የሚፈጥርብኝ። ልጁ ወጣት ነገር ነው። ችግሩ እሱ አይደለም። ችግሩ ሴቶችን አለቅጥ ማወደስና ወንዶችን ማጥላላት የሚወድ ቫፋንኩሎ ነገር መሆኑ ነው!። በዛ ላይ ፌሚኒዝምንን እንደሃይማኖት የሚሰብክ ቆለጥ አይን ጭምርም ነው። እኔም የዋዛ አይደለውም አንገት እስከመታነቅ የሚያደርስ ሎጃካሊ ስድብ ሰድቤው ልብስ ተያያዝን። በርግጥ አያገባኝም ነበር። ነገር ግን ሴቶች እንዲስቁለት በእኔ ላይ ሙድ ለመያዝ ሲሞክር መጀመርያ ሙዝ በመያዝ ጠግቦ ማደር እንዳለበት አስረግጬ ነገርኩት።
በነገራችን ላይ እንዲህ አይነት ወንዶች «Morality as a Mask, Equality as a Strategy» የሚል ስያሜ የሚሰጣቸው ወንድም ሴትም ያልሆኑ አዲስ ፍጡሮች ናቸው። Morality as a Mask, Equality as a Strategy ማለት ሞራልን እንደ ጭንብል፣ እኩልነት እንደ ስትራቴጂ የሚጠቀሙ የሰው ዓይነቶች ናቸው። በነገራችን ላይ እዚህ ጋር ፌሚኒዝምን የሚደግፍ ሰው ለመውቀስ አስቤ አይደለም። እኩልነትን መደገፍ በራሱ ችግር አይደለም፤ ችግሩ የሚጀምረው አንድ ሰው እኩልነትን እንደ እኩልነት ማሰብ ሲያቆምና እንደ መሳሪያ መጠቀም ሲጀምር ነው። ያኔ ነው ሞራል ወይም ስነምግባር ከውስጣዊ መርህ ወደ ውጫዊ ፍላጎት የሚቀየረው። እኩልነትም ከፍትህ ጥያቄ ወደ ግል ጥቅማጥቅ ይለወጣል።የኦሾን በእኛ ሀገር የተተረጎመውን ትቼ ብቻ የውጭ መፅሐፍቶችሁን ከ14 በላይ አንብቢያለሁ። ከ20 ያላነሱም ኢንተርቪዎችሁን ደጋግሜ ተመልክቻለሁ። ይህን ስናገር ፉከራ ሳይሆን በ«Addiction» እና «Obsession» መካከል ያለውን ልዩነት ለማሳየት ነው። የኦሾ ንጹህ ወይይት፣ ዲቤት እና ቀጥታ ንግግሩን ማዳመጥ ሱስ ሳይሆን መለከፍ ነበር የሆነብኝ። በተለይ ሲናገር በጣም መረጋጋት ብቻ ሳይሆን በቃላቶችሁ መጨረሻ ላይ የሚጠቀመው «እስስ» የሚለው የድምፅ ቃና አንድን ሰው ሂፕኖታይዝ የማድረግ ኃይል አለው። ኦሾ መፅሐፍ ጽፎ አያውቅም። ነገር ግን በአስርት አመታት ውስጥ ብዙ ኢንተርቪዎች ተደርጓል። ከዛ ኢንተርቪው ተወስዶ ከ700 በላይ መፅሐፍ በስሙ ተጽፏል። አሁን ላይ ግን በእሱ ስም የተጻፈ መፅሐፍም ሆነ ኢንተርቪው ማየት ካቆምኩ ወደሁለት አመት ገደማ ሊሆነኝ ነው። ቢሆንም በኦሾ ስም ከተጻፉት ብሎም እኔ ካነበብኩት የትኛው ህይወህትን ቀይሯል? ወይም አስተሳሰብህን አስፍቶታል? ተብዬ ብጠየቅ «Walking in Zen, Sitting in Zen» ብዬ በመለስኩ ነበር።
Walking in Zen, Sitting in Zen 📖 ሞትን የሕይወት ተቃራኒ ጠላት ሳይሆን የሕይወት የመጨረሻ ምልክት ወይም መደምደሚያ አድርጎ ይመለከተዋል። እዚህ ጋር መናገር የምፈለገው መፅሐፉ ሞትን ውደደዱ ወይም ሞትን ፈልጉ አይልም፤ ይልቅስ አንድ ሰው ሕይወትን በሙሉዓት ሲቀበል መሞትን እንደመጨረሻ እንግዳ ሳይሆን እንደ ተፈጥሯዊ እጣ ፈንታ ይቀበለዋል ነው የሚለን።
የመፅሐፉ ዋና ማዕከላዊ ትርጉም ሞትን መቀበል ነው። ይህም የሚጀምረው ህይወትን ከመውደድ ነው። ያ ሰው ሞት ሲመጣ እንደ ጠላት አይሸሸውም እንደ እንግዳም አይመለከተውም ብቻ በዝምታ ይቀበለዋል። በነገራችን ላይ ሰዎች ሞትን የሚፈሩት ሕይወታቸውን ስለሚወዱ ሳይሆን ቀናቸውን በቅጡ አጣጥመዋት ስለማይኖሩ ነው።
Walking in Zen, Sitting in Zen ውስጥ በአንድ ነገር ብዙ ነገሮችን ተረድቻለሁ። ሞት ከሕይወት የተለየች ጠላት አይደለችም። ለምሳሌ ወደቤት የሚያስገባን አንድ በር ብቻ ነው ያለው በዛ በር መልሰን ስንወጣ ሞት ይሆናል። እዚህ ጋር ነው ልዩነቱ የሚጀምረው። ሰዎች በበሩ በኩል ሲገቡ ያጨበጭባሉ፤ መልሰው በዛ በር ውጡ ሲባሉ ይሸሻሉ። ያ የሆነበት ምክንያት ሞትን ካለማወቅ የሚመጣ እንግዳ ስሜት ስላለብን ነው።
ያ እንግዳ የፍርሃት ስሜት ከልጅነታችን ጀምሮ የተማርነው ህይወትን የሚያሳጣ ስህተታችን ነው። ወላጆቻችን ሞትን ይፈራሉ፣ ጎረቤቶቻችንም ይፈሩታል፣ ማኅበረሰቡ በጠቅላላ ይፈራዋል እኛም ፍርሃቱን እንደ ውርስ እንቀበለዋለን። የትም ቦታ ብንሄድ ስለሞት ማውራት የተከለከለ ቃል ሆኖ እናገኘዋለን።
ኦሾ ሌሎች እንደሚሉት የህይወት ተቃራኒ ሞት ሳይሆን ወሲብ ነው የሚል አስተሳሰብ አለው። ወሲብ እና ሞት የሕይወት መጀመሪያ እና መጨረሻ ናቸው። ሁለቱም በዝምታቸው ውስጥ ጠፍተዋል ይለናል።
በመጨረሻም መፅሐፉ ሊናገር የሚወደው አንድ ነገር ቢኖር፤ ሞትን ማስታወስ ሕይወትን መጥላት አለመሆኑን ነው። በተቃራኒው ሞት እንዳለ ማወቅ የዛሬን ቀናችንን የበለጠ ዋጋ እንዲኖረው ወይም እንድንሰጠው ያደርገናል። ሕይወት መጽሐፍ ከሆነች፣ ሞት የመጨረሻው ገጽ ነው። የመጨረሻው ገጽ ስላለ ብቻ ተበሳጭተን መጽሐፉን አንወረውረውም፤ ይልቅስ እስከምንረዳው ድረስ ገጾችሁን በጥንቃቄ እናነባለን። ያለመጨረሻውም ገፅ መፅሐፉ ትርጉም አልባ አልያም ያልተሟላ ነው የሚሆንብን።
ታላቅ ጥበብ ማለት ሞትን ማሸነፍ አይደለም፤ ታላቅ ጥበብ ማለት ሞት እንደሚመጣ እያወቅን ሕይወትን በሙልዓት መኖር መቻል ነው። ምክንያቱም የሕይወት ውበት ለዘላለም መቆየቷ ሳይሆን፤ አንድ ቀን እንደምታልቅ እያወቅን አሁናችንን ማጣጣም ነው። እስቲ ከመፅሐፉ የተመቸኝን አንቀጽ ላጋራችሁና ልሰናበት።
«Whenever death comes he hugs death. he embraces death, he welcomes death, he receives death as a guest. To the man who has not known what life is, death is an enemy; and to the man who knows what life is, death is the ultimate crescendo of life.
But everybody is afraid of death; that too is contagious. Your parents are afraid of death, your neighbors are afraid of death. Small children start getting infected by this constant fear all around. Everybody is afraid of death. People don’t even want to talk about death.
There have been only two taboos in the world: sex and death. It is very strange why sex and death have been the two taboos not to be talked about, to be avoided. They are deeply connected. Sex represents life because all life arises out of sex, and death represents the end. And both have been taboo don't talk about sex and don’t talk about death!»
Source፦Walking in Zen Sitting in Zen 📖
@Armemo_offical«አብዛኛውን ጊዜ የሰውን ጭካኔ ለመግለፅ "የዱር እንስሳ" ነው ይባላል፤ ይሁን እንጂ ይህ መገለጫ ለእንስሳት ያልተገባ ስድብ ነው!።»
―ዶስቶይቭስኪ
@Armemo_officalሴት እየመቱ ካሜራ መቅረጽ፣ ሰውን ከነፍሱ እሳት እየከተቱ ካሜራ መቅረጽ፣ ሰውን እየረሸኑ ካሜራ መቅረጽ፣ ሰው እያረዱ ካሜራ መቅረጽ!። እራሴን እያመመኝ ነው በማያቸው ቪድዮዎች!!