ch
Feedback
አርምሞ🧘🏽‍♂

አርምሞ🧘🏽‍♂

前往频道在 Telegram

ጥ ቂ ት ም ና ኔ. .🧘🏽‍♂️

显示更多

📈 Telegram 频道 አርምሞ🧘🏽‍♂ 的分析概览

频道 አርምሞ🧘🏽‍♂ (@armemo_offical) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 11 505 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 7 774,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 901

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 11 505 名订阅者。

根据 26 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 243,过去 24 小时变化为 7,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 15.98%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.42% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 1 838 次浏览,首日通常累积 854 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 24

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ጥ ቂ ት ም ና ኔ. .🧘🏽‍♂️

凭借高频更新(最新数据采集于 27 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

11 505
订阅者
+724 小时
+587
+24330
帖子存档
Ah shit.. here we go again. I don’t even feel like reacting anymore. Some days, you just get tired of everything and put your
Ah shit.. here we go again. I don’t even feel like reacting anymore. Some days, you just get tired of everything and put your phone down. Maybe silence is better than trying to explain yourself!

የኦሾን በእኛ ሀገር የተተረጎመውን ትቼ ብቻ የውጭ መፅሐፍቶችሁን ከ14 በላይ አንብቢያለሁ። ከ20 ያላነሱም ኢንተርቪዎችሁን ደጋግሜ ተመልክቻለሁ። ይህን ስናገር ፉከራ ሳይሆን በ«Addiction» እና «Obsession» መካከል ያለውን ልዩነት ለማሳየት ነው። የኦሾ ንጹህ ወይይት፣ ዲቤት እና ቀጥታ ንግግሩን ማዳመጥ ሱስ ሳይሆን መለከፍ ነበር የሆነብኝ። በተለይ ሲናገር በጣም መረጋጋት ብቻ ሳይሆን በቃላቶችሁ መጨረሻ ላይ የሚጠቀመው «እስስ» የሚለው የድምፅ ቃና አንድን ሰው ሂፕኖታይዝ የማድረግ ኃይል አለው። ኦሾ መፅሐፍ ጽፎ አያውቅም። ነገር ግን በአስርት አመታት ውስጥ ብዙ ኢንተርቪዎች ተደርጓል። ከዛ ኢንተርቪው ተወስዶ ከ700 በላይ መፅሐፍ በስሙ ተጽፏል። አሁን ላይ ግን በእሱ ስም የተጻፈ መፅሐፍም ሆነ ኢንተርቪው ማየት ካቆምኩ ወደሁለት አመት ገደማ ሊሆነኝ ነው። ቢሆንም በኦሾ ስም ከተጻፉት ብሎም እኔ ካነበብኩት የትኛው ህይወህትን ቀይሯል? ወይም አስተሳሰብህን አስፍቶታል? ተብዬ ብጠየቅ «Walking in Zen, Sitting in Zen» ብዬ በመለስኩ ነበር። Walking in Zen, Sitting in Zen 📖 ሞትን የሕይወት ተቃራኒ ጠላት ሳይሆን የሕይወት የመጨረሻ ምልክት ወይም መደምደሚያ አድርጎ ይመለከተዋል። እዚህ ጋር መናገር የምፈለገው መፅሐፉ ሞትን ውደደዱ ወይም ሞትን ፈልጉ አይልም፤ ይልቅስ አንድ ሰው ሕይወትን በሙሉዓት ሲቀበል መሞትን እንደመጨረሻ እንግዳ ሳይሆን እንደ ተፈጥሯዊ እጣ ፈንታ ይቀበለዋል ነው የሚለን። የመፅሐፉ ዋና ማዕከላዊ ትርጉም ሞትን መቀበል ነው። ይህም የሚጀምረው ህይወትን ከመውደድ ነው። ያ ሰው ሞት ሲመጣ እንደ ጠላት አይሸሸውም እንደ እንግዳም አይመለከተውም ብቻ በዝምታ ይቀበለዋል። በነገራችን ላይ ሰዎች ሞትን የሚፈሩት ሕይወታቸውን ስለሚወዱ ሳይሆን ቀናቸውን በቅጡ አጣጥመዋት ስለማይኖሩ ነው። Walking in Zen, Sitting in Zen ውስጥ በአንድ ነገር ብዙ ነገሮችን ተረድቻለሁ። ሞት ከሕይወት የተለየች ጠላት አይደለችም። ለምሳሌ ወደቤት የሚያስገባን አንድ በር ብቻ ነው ያለው በዛ በር መልሰን ስንወጣ ሞት ይሆናል። እዚህ ጋር ነው ልዩነቱ የሚጀምረው። ሰዎች በበሩ በኩል ሲገቡ ያጨበጭባሉ፤ መልሰው በዛ በር ውጡ ሲባሉ ይሸሻሉ። ያ የሆነበት ምክንያት ሞትን ካለማወቅ የሚመጣ እንግዳ ስሜት ስላለብን ነው። ያ እንግዳ የፍርሃት ስሜት ከልጅነታችን ጀምሮ የተማርነው ህይወትን የሚያሳጣ ስህተታችን ነው። ወላጆቻችን ሞትን ይፈራሉ፣ ጎረቤቶቻችንም ይፈሩታል፣ ማኅበረሰቡ በጠቅላላ ይፈራዋል እኛም ፍርሃቱን እንደ ውርስ እንቀበለዋለን። የትም ቦታ ብንሄድ ስለሞት ማውራት የተከለከለ ቃል ሆኖ እናገኘዋለን። ኦሾ ሌሎች እንደሚሉት የህይወት ተቃራኒ ሞት ሳይሆን ወሲብ ነው የሚል አስተሳሰብ አለው። ወሲብ እና ሞት የሕይወት መጀመሪያ እና መጨረሻ ናቸው። ሁለቱም በዝምታቸው ውስጥ ጠፍተዋል ይለናል። በመጨረሻም መፅሐፉ ሊናገር የሚወደው አንድ ነገር ቢኖር፤ ሞትን ማስታወስ ሕይወትን መጥላት አለመሆኑን ነው። በተቃራኒው ሞት እንዳለ ማወቅ የዛሬን ቀናችንን የበለጠ ዋጋ እንዲኖረው ወይም እንድንሰጠው ያደርገናል። ሕይወት መጽሐፍ ከሆነች፣ ሞት የመጨረሻው ገጽ ነው። የመጨረሻው ገጽ ስላለ ብቻ ተበሳጭተን መጽሐፉን አንወረውረውም፤ ይልቅስ እስከምንረዳው ድረስ ገጾችሁን በጥንቃቄ እናነባለን። ያለመጨረሻውም ገፅ መፅሐፉ ትርጉም አልባ አልያም ያልተሟላ ነው የሚሆንብን። ታላቅ ጥበብ ማለት ሞትን ማሸነፍ አይደለም፤ ታላቅ ጥበብ ማለት ሞት እንደሚመጣ እያወቅን ሕይወትን በሙልዓት መኖር መቻል ነው። ምክንያቱም የሕይወት ውበት ለዘላለም መቆየቷ ሳይሆን፤ አንድ ቀን እንደምታልቅ እያወቅን አሁናችንን ማጣጣም ነው። እስቲ ከመፅሐፉ የተመቸኝን አንቀጽ ላጋራችሁና ልሰናበት። «Whenever  death comes he hugs death. he embraces death, he welcomes death, he receives death as a guest. To the man who has not known what life is, death is an enemy; and to the man who knows what life is, death is the ultimate crescendo of life. But everybody is afraid of death; that too is contagious. Your parents are afraid of death, your neighbors are afraid of death. Small children start getting infected by this constant fear all around. Everybody is afraid of death. People don’t even want to talk about death. There have been only two taboos in the world: sex and death. It is very strange why sex and death have been the two taboos not to be talked about, to be avoided. They are deeply connected. Sex represents life because all life arises out of sex, and death represents the end. And both have been taboo don't talk about sex and don’t talk about death!»        Source፦Walking in Zen Sitting in Zen 📖 @Armemo_offical

Walking in zen, Sitting in zen 📚 Recommend ☝🏼
Walking in zen, Sitting in zen
📚 Recommend ☝🏼

ድመት ከሬሳ አጠገብ የማሰር ልማድ አለን፤ እስቲ ለምንድነው የሚታሰሩት ንገሩኝ?። ሪአክት ከዛ ወደኮመንት👇🏼

የአሳማ ስጋ እና የሞተ እንስሳ የማንበላ ነገር ግን እርስ በእርስ የምንበላላ ህዝቦች ነን!።

«አብዛኛውን ጊዜ የሰውን ጭካኔ ለመግለፅ "የዱር እንስሳ" ነው ይባላል፤ ይሁን እንጂ ይህ መገለጫ ለእንስሳት ያልተገባ ስድብ ነው!።» ―ዶስቶይቭስኪ @Armemo_offical
«አብዛኛውን ጊዜ የሰውን ጭካኔ ለመግለፅ "የዱር እንስሳ" ነው ይባላል፤ ይሁን እንጂ ይህ መገለጫ ለእንስሳት ያልተገባ ስድብ ነው!።»                    ―ዶስቶይቭስኪ @Armemo_offical

የቲክቶክ አካውንቴ 👇🏼 https://www.tiktok.com/@imaging_gurus?_r=1&_t=ZS-991JYxk6U9H

ሴት እየመቱ ካሜራ መቅረጽ፣ ሰውን ከነፍሱ እሳት እየከተቱ ካሜራ መቅረጽ፣ ሰውን እየረሸኑ ካሜራ መቅረጽ፣ ሰው እያረዱ ካሜራ መቅረጽ!። እራሴን እያመመኝ ነው በማያቸው ቪድዮዎች!!

በነገራችን ላይ በእንስሳት አለም አንድ ወንድ እንስሳ ሴቷን ከፈለጋት ከሌላኛው ወንድ እንስሳ ጋር መታገል ግዴታው ነው። በሰውም ዘር በጉልበትም ሆነ በገንዘብ ብልጫ ያለው ሴቷን የግሉ ማድረግ ይችላል። እና ምን ማለት የምፈልገው። በሁለቱም አማራጭ ማሸነፍ መቻልህ ጎበዝ ሳይሆን እንስሳ ነው የሚያስብልህ። ለምን መታገል እንዳለበት የማያውቅ ልብስ ሰፊ፤ ለአንድ ቀዳዳዋ ዘጠና ዘጠኝ ቀዳዳዋን ለመድፈን ሲጣጣር እድሜ ያባክናል!። ቫፋንኩሎ 😑

ያኔ ነው «Only the dead have seen the end of war» የምንለው። ይህ በሰሜን አካባቢ የተፈጠረ የጦርነት ትልቁ ምፀቱ ነው። በህይወት ያሉት ሰላምን ይጠብቃሉ፤ የሞቱት ግን ጦርነቱን አያዩትም። በህይወት ያሉት «አንድ ቀን ያበቃል» ብለው ተስፋ ያደርጋሉ፤ ያ ቀን ሲመጣ ግን እነዛ ሰዎች አይኖሩም። ምክንያቱም ሰላም የሚመጣበትን ቀን ሁሉም ሰው ይናፍቃል፤ ያንን ቀን የሚያዩት ግን ሁልጊዜም የሚጠብቁት አይሆኑም። ይኸው ምርጫ ሰጡንና ከራብ ጦርነትን መረጥን፤ ነገር ግን ከሰይፍ ስለት በላቀ የውሃ ጥማት ገደለን!፤ መቀበርያ መሬት እንኳን አልነበረንም። በርግጥ ጦርነት የጀመርነው መሬት ለማግኘት ነበር፤ መጨረሻችን ግን እንኳን ለህይወት ለሚሸተው ሬሳችን እራሱ የሚሆን መሬት ማጣት ሆነ!። ድንበር ለመጠበቅ የተነሱ ሰዎች መጨረሻቸው በሌላ ሀገር መሬት ላይ ተበጣጥሶ መሞት ነው። ባንዲራ እያውለበለበ ክተት የገባው ወጣት በዛው በባንዲራ ተጠቅልሎ ይመለሳል።  ታድያ ይህ ሁሉ ሲያጋጥመን በጦርነት የሚያሸንፈው ማን ነው ብሎ መጠየቅ እንኳን የሚያሳፍር ሆኖ እናገኘዋለን። ምክንያቱም እናት ልጇን ካጣች ወዲያ ሁለቱም ወገኖች ቢያሸንፉ ምን ይጠቅማታል?። አንድ ሕፃን ወላጆችሁን በጦርነት ካጣ ወዲያ የድል ባንዲራ ቢውለበለብ ምን ይፈይድለታል?። አንዲት ሴት በጦርነት ሰበብ ከተደፈረች በኋላ ሰላም ቢመጣ ምን ትጠቀማለች?። ጦርነት በጦርነት አይበርድም። ድልም በመሳርያ አይጸድቅም። ይልቅስ ጦርነቱም ያበቃል መሪዎችም ይጨባበጣሉ። እኚህ ትልቅ እናት የተሰዋው ልጃቸውን ይጠብቃሉ፤ ያቺ ሴትም የምትወደውን ባሏን ትጠብቃለች፤ ህፃን ልጆችም ጀግና አባታቸውን ይጠብቃሉ። አዎ ማን አገር እንደሸጠ ባናውቅም፤ ማን ለአገራችን ዋጋ እንደከፈለ ግን አይጠፋንም። በመጨረሻም ጦርነት ሲያበቃ ሰውነት ይሸነፋል፣ ቤተሰብ ይበተናል። ከጦርነት በኋላ የሚቀረን ብዙ ጊዜ ድል አይደለም፤ ይልቅስ የጸጸት ትዝታ ብቻ ነው። ያም ትዝታ በቤቶች ውስጥ የማይነገር ታሪክ፤ በእናቶች ዓይን ውስጥ የማይደርቅ እንባ፤ በአባቶች ዝምታ ውስጥ የሚኖር ጥያቄ፤ በልጆች ጆሮ ውስጥ የሚያቃጭል የጥይት ድምፅ ሆኖ ይቀራል። «እናቴን ለመጠበቅ የገባውበት ጦርነት በድል ተጠናቀቀ፤ ነገር ግን እናቴ አልነበረችም!»🪦😥 @Armemo_offical

ዛሬ በጣም የመረረኝን ሀሞት ከመዋጥ መትፋት መርጫለሁ። ስለጦርነት፣ ስለህፃናት መደፈር ብሎም የወጣቶች ነፍስ በከንቱ መቀጠፍ እያደር ሲያመኝ ወይ አይገላግለኝ የሆድ ትላትል ሆኖ ነፍሴን አስመረራት!። አንባቢዬ ሆይ ረጅም ጽሁፍ ነው። ከፈለክ አታንብብ!። ነገር ግን እንደአንተ እና እንዳንቺ ያለ ክፉ ሰው በዘመኔም አጋጥሞኝም አያውቅም!። የዘርዓ ያዕቆብ ደቀመዝሙር የሆነው ወልደ ህይወት እንዲህ ይላል፦«ዘመን ማለት እናንተ ናችሁና… ክፉ ዘመን ማለት ክፉ ትውልድ!» እዚህ ጋር ዘመን ማለት የሰዓት መስመር ቲክ ታክ አይደለም። ዘመን በቀን መቁጠሪያ ላይ የሚቀያየር ቁጥር እራሱ አይደለም። ዘመን ማለት የሰው ልብ የተመላለሰበት አቅጣጫ ነው፤ ሕዝብ የተቀበለው እውነት፣ የተረሳ ሕሊና፣ የተለማመደው ግፍ እና በደል፤ ብሎም ዝምታን የመረጠበት ወቅት «የዘመን ገፃችንን» ይሠራሉ። ስለዚህ ክፉ ዘመን ማለት የቀን ክፉ ሳይሆን የሰው ክፉ ነው!። በርግጥ በዘመናችን ክፋትን ማራቅ አንችልም፤ ቢሆንም ክፉ ዘመን ማለት ሰዎች ክፋትን እያዩ መገረማቸውን በቀስታ ሲያጡ፣ የሌላውን ሕመም ከራሳቸው ሕመም ለይተው ሲመለከቱ፣ የሰውን ሕይወት ከፖለቲካዊ ማንነት በታች ሲያስቀምጡ የሚፈጠር አረመኔ ዘመነኛ ሰውነት ነው!። አባት ከትምህርት ቤት የምትመለሰው የሴት ልጁን ድምፅ ቢጠብቅም አይሰማውም። ይልቅ ከቀናት በኋላ ቤቱ በር ላይ ደንኳን ይጣላል፤ ምክንያቱም በሙሉ አይኑ ለማየት የሚሳሳላት ልጁ በአረመኔ ወንዶች ተደፍራና ተገድላ ተገኝታለች። እናትም ሱቅ የተላከው ወንድ ልጇ በድንገት በጥይት ተበሳስቶ ይወድቅባታል። ዛሬ አንድ ወጣት ይሞታል፣ ነገ ሌላኛው ወጣት ይሞታል። ወላጅም የልጁን ነብስ አጥቶ በልጁ የልብስ ጠረን መራር ትዝታውን ይታቀፋል። የሚገርመው እሱ አይደለም። የሚገርመኝ ይሄ ደነዝ ሕዝብ ነው። የመደፈር እና የመገደል ዜና ተሰራጭቶ ስንመለከት እናዝናለን። ቀጥሎ ማዘናችንን በተመለከተ አንድ አሳዛኝ ቪድዮ ወይም ጽሁፍ ፖስት እናደርጋለን። ከዚያ ስልካችንን እንዘጋለን። እዚህ ጋር ግን የሚዘጋው ስልካችን ብቻ አልነበረም፤ የሕሊናችንን መስኮት ጭምር ነው። አሳዛኙ ነገር ሞት ብቻ አይደለም። ሞት እየተደጋገመ ሲመጣ ለሕይወት ያለን ዋጋ ቀስ በቀስ እየረከሰ መምጣቱ ነው። በፊት አንድ ሰው ሲሞት ከተማዋ እንደዛ ትርምስምሷ እንዳልወጣ ዛሬ የአስር ሰዎች ሞት ቁጥር ብቻ ሆኖ መቅረቱ ያማል!። ሕዝብ በተደጋጋሚ ጭቆና ሲያጋጥመው አመጸኛ አይሆንም፤ ይልቅስ ቀስ በቀስ ይደነዝዛል። ሳይኮሎጂ ይህን «desensitization» ይለዋል። በደል ያስደነግጠን የነበረ ነገር ቢሆንም በደሉ እየቆየ ሲመጣ የአስደንጋጭነት ስሜቱ ይደበዝዛል። ከዚያ ግን «normalization of deviance» ይሆናል። ትናንት የማይታሰብ የነበረው ዛሬ የተለመደ እየሆነ ሲመጣ፤ ነገ በተራው አስደንጋጭ የምንለው ወንጀል ለዜና እንኳን ብቁ መሆን ያቅተዋል!። ይህ አስፈሪ የፖለቲካ ሥነልቦና የኒሂሊዝም ነቀርሳም ጭምር ነው። ሥልጣን በቤተ መንግሥት ብቻ አይኖርም፤ በሕዝብ አእምሮ ውስጥም ይገነባል። ሕዝብ ለየትኛውም ግፍ የሚሰጠውን ትርጉም መቀየር የጀመረ ለት ባለሥልጣኑ እንደልቡ እንዲሆን እድል እንሰጠዋለን። ሲጀመርም ፖለቲካን አንድ ሰው ፊት ላይ ብቻ መፈለጋችን ትልቁ ስህተታችን ነው። አንድ መሪን እንደ ሁሉም ነገር ምንጭ እንመለከታለን። ያ ስህተት ነው። የፖለቲካ ሥርዓት ከመሪዎች ብቻ አይገነባም፤ ከሕዝብ ግንኙነት፣ ከፍርሃት፣ ከጥላቻ፣ ከብሔር ማንነት፣ ከዝምታ እና ከሌላው ሕመም ጋር ያለን ግላዊ ስሜትን ይፈትሻል። አንድ ሕዝብ በማንነት ሲተላለቅ፣ በሃሳብ ልዩነት ሲጠላላ፣ የሌላውን ሕመም የእራሳቸው ጉዳይ ብሎ ማለፍ ሲቀናው ግፍ በሀገራችን ትልቅ መሬት ተሰጥቶት መኖር ይጀምራል። ሁሌም እንደሕዝብ ያለብን ችግር አንድ ነው። እሱም የሞተው ከእኛ ወገን ከሆነ እናዝናለን። የሞተው ከሌላ ስፍራ ከሆነ ደግሞ ምክንያት በመፈለግና «ምን አድርጎ?» በማለት አውርተን ማለፋችን ምንያህል moral disengagement እንደተፈጠረብን ያሳያል። ሌላውን ግለሰብ፣ ሌላውን ብሔር እና ሌላውን ሃይማኖተኛ ከሰውነት አርቀን ማሰብ ስንጀምር በእሱ ላይ የሚደርሰውን ማንኛውም ግፍ ላለመቀበል ሕሊናችን ምክንያት መፈለግ ይጀምራል። ሀገሬ የሰውን ሞት ከትንኝ ሞት እኩል አድርሳዋለች። ሰው ከሰውነቱ ይልቅ የብሔር ታፔላ ሲለጠፍበት፤ ሕይወትም ዋጋዋ የፖለቲካ ክርክር ሆኖ ሲቀር፤ ሞት ከመወገዙ አስቀድሞ  «የእኛ» እና «የእነሱ» የሚል ሕሊና ቢስ ፍርደኛ እንሆናለን። ማርያምን የምሬን ነው የኢትዮጲያ ሕዝብ በደልን እየተቃወመ አይደለም፤ ይልቅስ በደልን እንደየክብደቱ እየመዘነው ነው። የሀገሬ ሕመም ይህን ያህል ጥልቅ ነው። አንዱ በደረሰበት በደል አምርሮ ሲያለቅስ ሌላኛው ለምን እንደሚያለቅስ ከመጠየቅ ይልቅ «ኦሮሞ ነው? አማራ ነው?» ብሎ መጠየቅ ለምዶታል። ይሄ ጥያቄ በራሱ የሽንፈታችን ምልክት ነው። ምክንያቱም የሌላው ሞት እኛን ካላሳመመን ጭራቅ መሆን ጀምረናል። እንስሳ እንኳን ከመካከላቸው አንዱን ሲያጡ ያዝናሉ። የሴቶች መደፈር በቃን፣ የወጣቶች ሞት በቃን ከዚህ ሁሉ በላይ ይህ ከንቱ ጦርነት ይበቃናል!። ቋቅ ነው ያለን። በርናንድ ረስል እንዲህ ይላል፦«War does not determine who is right — only who is left.» በአማርኛ ሲመጣ እንዲህ ያለ ነው፦«ጦርነት ማን ትክክል እንደሆነ አይወስንም፤ ማን ይቀራል የሚለውን ብቻ ነው።» ምን መሰላችሁ። ጦርነት እውነተኛ ዳኛ አይደለም። ሚዛን የለውም። ማን ለምን ሰይፍ እንዳነሳ፤ የትኛው ጻድቅ ስለመሆኑ ጉዳዩ አይደለም። ጦርነት ልክ እንደ እሳት ነው። የቤቱ ባለቤት ማን እንደሆነ አይጠይቅም። ስለጸጸት አያውቅም ስለመማጸንም ግድ አይሰጠውም ብቻ የሚያገኘውን በጠቅላላ ያቃጥላል። ታድያ በመጨረሻ ታሪክም ከትክክለኛ ሟቾች በላይ የተረፈውን ሰው ማውሳት ይመርጣል። እንዲህ ያለ ቀመር የጦርነት ድልን በሕይወት ቁጥር ሊለካ የሚችል ከንቱ ኬሚስትሪ ነው፤ ነገር ግን ወንድ ልጇ ወጥቶ የቀረባት ልቧ ስለተሰበረው ያቺ እናት ማንም ጉዳዩ አይደለም። ሄሮተደስ እንዲህ ይላል፦«In peace, sons bury their fathers. In war, fathers bury their sons» በአማርኛ ሳመጣው እንዲህ ያለ ነው፦«በሰላም ልጆች አባቶቻቸውን ይቀብራሉ፤ በጦርነት አባቶች ልጆቻቸውን ይቀብራሉ።» ሰላም ሁሌም የትውልድን ተፈጥሯዊ ሥርዓት ትጠብቃለች። አባት ይኖራል፣ ያረጃል እናም ይሞታል፤ ልጅም አባቱን አልቅሶ ይቀብራል። ጦርነት ግን የዚህን ተፈጥሯዊ ስርዓት ትገለብጣለች። አባት ገና ኖሮ ያልጠገበ ልጁን ይቀብራል፣ እናትም ከልጇ የልጇ የልብስ ጠረን ብቻ ይተርፋታል። ቤቱም በሀዘን ተውጦ የልጁን ድምፅ እየጠበቀ ዝም ይላል። እናም የሰው ልብ ከሚቋቋመው ሀዘን በላይ ሲሸከም ከህይወት ጋር ያለው ውል ያበቃል። የራሱን ልጅ ከቀበረ በኋላ የሌላውን ልጅ ሞት እንደ ቁጥር ማየት ይጀምራል።

#No_More
#No_More

ከዚህ በኋላ በዚህ ልክ ማስተዋቂያ አላበዛም። አንድ ድርጅት ነው። አልሞላ ሲል ተደጋጋሚ የለቀኩት። እኔ ደግሞ የሜምበሩን ሰላም ይበልጥብኛል። እስከዛሬ ከሌሎች የቴሌግራም ቻናሎች ጋር እርስ በእርስ ማስታወቂያ ያልሰራውት ይህን ስብስብ ላለመበትን ነው። እናም ይቅርታ 🙏🏼

#አንቶንዮ ግራሚሽ በመጨረሻ (Hegemony Theory) በማምጣት አጠቃላይ ክርክሩን በትንሹ ይዘጋዋል። በመጀመርያ ግን አንድ ጥያቄ ከግራሚሽ ይነሳል እሱም፦«ሰዎችን ለምን በኃይል ብቻ ማስገደድ ይጠበቅብናል? እነሱ ራሳቸው የሥርዓቱን ሐሳብ እንደ ‘common sense’ እንዲያምኑ ብናደርጋቸውስ?» አንድን ሰው በጠመንጃ ማስገደዳችን የተለመደ የኃይል መንገድ ነው። ነገር ግን በተቃራኒው የምናስገድደው ሰው «እንዲህ ማድረጌ እኮ ኖርማል ተግባር ነው» ብሎ ማመን እንዲጀምር ካደረግን ከዚያ የበለጠ ታላቅ ኃይል እናገኛለን። በፎርሙላም ሲቀመጥ፦Hegemony ≈ Power + Consent + Control of Meaning ይባላል። ለምሳሌ «እውነት ምንድነው?» የሚለውን ማን ነው የሚወስነው?። አንድን ነገር «የተለመደ ነው» ተብሎ የሚታለፈው ከምን አንፃር ነው?። «ትክክለኛው የህይወት አኗኗር እንዲህ ነው» የሚለንስ ማነው?። ይሄን ባጭሩ ስንመልሰው «የማህበረሰብ ኃይል» እንዴት መኖር እና መንቀሳቀስ እንዳለብን ህግ እና ደንብ ያወጣልናል። ነገሩ ከዚህም የበለጠ ጥልቅ ነው። በጣም የተሳካው «ኃይል» ሰዎችን በግድ የሚያስገድድ ብቻ አይደለም፤ ይልቅስ የሥርዓቱን ባህል እንደ ተፈጥሯዊ common sense እንዲቀበሉት ማድረግ መቻልም ጭምር ነው!። ለምሳሌ አንድን ሰው ጠመንጃ ይዘን «እኔን ታዘዘኝ» ብንለው ይህ Power ወይም ኃይል ነው። በቃራኒው ይህን ሰውዬ «ህጋዊ ስልጣን መብታችንን» በመጠቀም ኃይላችንን ብናሳየው ወደ ስልጣን መብት ይቀየራል። ታድያ ይህ የስልጣን መብት እየቆየ ሲመጣ እንደመደበኛ ሥርዓት ብሎም ተፈጥሯዊ የሕይወት መንገድ አድርጎ ማየት ይጀምራል። ያኔ ነው ነገርዬው Social order የሚሆነው። በመጨረሻም ልናገር የምፈልገው። ኃይል መጀመሪያ ላይ ሰውዬውን ሊያስገድደው ይችላል፤ ያ ኃይልም ሲደጋገም ወደህግ ይቀየራል፤ ከዚያ እየቆየ ሲመጣ ልማድ ይሆናል፤ በመጨረሻም ሰውዬው የሚደርስበት የኃይል አካሄድ እንደ እውነት የሚቀበለው አስተሳሰቡ ሆኖ ይቀራል። ያኔ «ኃይል» ከውጭ የምንገደደው ወይም የምናስገድደው ግፊት መሆኑን ትቶ በገዛ አእምሮአችን ውስጥ ህግ ሆኖ መኖር ይጀምራል። አራቱንም አንድ ላይ ካስቀመጥናቸው እንዲህ ያለ ሞዴል መገንባት እንችላለን፦Power = Resources -> Control -> Legitimacy -> Consent -> Normalization። በተርታ ስንመለከተው፦ 1,Marx፦ Resources / Production 2,Weber፦ Authority / Legitimacy 3,Durkheim፦ Norms / Social Order 4,Gramsci፦ Consent / Hegemony ኃይል ከውጭ ሲጫንብን ኃይሉን ከሚጠቀመው ሰውዬ ጋር እንታገላለን። ወደ አእምሮአችን የገባ ግዜ ግን ከገዛ ሃሳባችን ጋር መጣላት እንጀምራለን። በአጭሩ ኃይልን እንደሚፈስ ውሃ አድርገን እናስበው። #ማርክስ፦ውሃውን የያዘው ማን ነው? ብሎ ይጠይቃል። #ዌበር፦ለምን ሕዝቡ ውሃ ስለተሰጠው ብቻ ይቀበላል? ብሎ ይጠይቃል። #ዱርክሄም፦ሁሉም ሰው ውሃ ውሃ መሆኑን እንዴት አውቆ ተማረ? ብሎ ይጠይቃል። #ግራሚሽ ደግሞ እንዲህ ይዘጋዋል፦ሰዎች ውሃን እንደተፈጥሮዋዊ መደበኛ ነገር ተቀብለውታል። ታድያ የመጨረሻው የኃይል ደረጃ የሚባለው ሰውዬውን ማስገደድ መቻል አይደለም፤ ሰውዬው የሚገደድበትን ነገር እንደራሱ ምርጫ እንዲያየው ማድረግ መቻል ነው። ኃይል ከጠመንጃ እስከ አእምሮ የሚያደርስ ጉዞ ነው፤ መጀመሪያ በአንድ ሰው እጅ ውስጥ ይኖራል። ከዚያ ተቋም ሆኖ ይደራጃል፤ ቀጥሎ ሕግ ይሆናል፤ እያለ ልማድ ይሆናል። በመጨረሻም «ግዴታ እንዲህ መሆን አለበት» የሚል የአእምሮ ሃሳብ ባለቤት ያደርገናል። ያኔ ነው ኃይል ከእጅ ወጥቶ ወደ ሰው አእምሮ ቤት በመግባት ብዙ ባርያዎችን የሚያፈራው!። @Armemo_offical

ይሄ ፎቶ ላይ ያለውን «የኃይል ልዩነት» ስመለከት በአጭሩ ላስረዳችሁ መጣሁ። እነዚህ ፎቶው ላይ ያሉት ታላላቅ አሳቢዎች ካርል ማርክስ፣ ማክስ ዌበር፣ ኤምሊ ዱርክሄም እና አንቶኒዮ ግራምሺ ይባላሉ። የእነዚህ ታላላቆች ሃሳብ በደፈናው ብቻ ሳይሆን በፎርሙላ፣ በተጨባጭ ምሳሌያዊ ሜታፎር ካየነው ነገሩ በጣም ጥልቅ ሆኖ እናገኘዋለን። እስቲ አንድ በአንድ እንፈትሻቸዋለን። በመጀመሪያ ግን በPower እና Authority መካከል ያለውን ልዩነት ማስረዳት ይጠበቅብኛል። Power ማለት ሰዎች አንድን ነገር እንዲያደርጉ የማዘዝ አቅም ነው። Authority ደግሞ ያንን Power ወይም ኃይል ስንጠቀም ሰዎች ሕጋዊ እና ትክክለኛ ነው ብለው እንዲቀበሉት የማድረግያ ሲስተም ነው። Power/ኃይል የሚይዘው አካል ግፊት ነው፤ Authority/የስልጣን መብት ደግሞ ሌሎች ያዘዘውን አካል የሚቀበሉበት ምክንያት ነው። ለምሳሌ የአንድ ድርጅት ዘበኛ ጠበንጃውን በመመዘዝ ብቻ ሰዎችን ማስቆም ይችላል። ምክንያቱም «Power» አለው። ፖሊስ ደግሞ በሕግ የተሰጠውን ሥልጣን ተጠቅሞ ሰዎች እንዲታዘዙት ማድረግ ይችላል፤ ይህ ደግሞ Authority ከኃይል በተጠማሪ የስልጣን መብት እንዳለው የሚያሳይ ነው። #የካርል_ማርክስ፦Class Theory/የኢኮኖሚ ኃይል ወይም Marxist Theory of Power ይሰኛል። ማርክስ «social power»ን ከማኀበራዊ ኃይል ጋር አዳቅሎ የሚያነሳበት ዋና ቁልፍ ነገር አለችው። ቲዎሪውም አንድ ጥያቄ ይዛ ትመጣለች፦«የምርት መሣሪያዎችንን ማን ይቆጣጠራል?» (Factory, land, capital, machinery, resources) ወዘተ ናቸው። የኢኮኖሚ ትምህርት ተምሮ የሚያውቅ ሰው ይህቺን ፎርሙላ ያውቃታል፦(Economic Power ≈ Ownership + Control of Resources + Control of Production!) ይባላል። እዚህ ጋር ማርክስ የሚለን ይህን ነው። ኃይል ሁሌም የሚመጣው ሀብት እና ኢኮኖሚን ከመቆጣጠር ነው። የምርት መሣሪያን የሚቆጣጠር ሰው በሌሎች ላይ ተጽዕኖ የማድረግ እድሉ ሰፊ ነው። ለምሳሌ አንድ ሰው ፋብሪካውን አለው እንበል። ከዛ በዛ ፋብሪካ ውስጥ አንድ ሰራተኛ ቀጠረ። ስለዚህ ሁለቱም በሥራ ቦታ እኩል ቢሆኑም በስራክቸራል ፓውር ግን እኩል አይደሉም። ለዛም ነው ማርክስ «ማን ይሠራል?» ብቻ ሳይሆን «ማን በስራው ላይ የመግዛት አቅም አለው?» የሚለውን የሚፈትሸው። ሰው መስራት ከቻለ ኃይል አለው፤ ሌላውን የሚያዝበት አቅም ካለው ኃይልም ስልጣንም አለው። #ማክስ ዌበር ደግሞ የማርክስን ሃሳብ በመቃውም (Power + Authority + Legitimacy) ብሎ ይከፋፍላቸዋል። ይህም ኃይልን ከስልጣን ወደ ሕጋዊነት ወይም ወደ ተቀባይነት መቀየር መቻል የበለጠ አድቫንቴጂንግ ነው እንደማለት ያለህ ነው። ሁሌም Power ወይም ኃይል እንዲህ የሚል ድምፅ አላት፦«የምፈልገውን በጠቅላላ የማድረግ አቅም አለኝ።» Authority/ስልጣን ደግሞ፦«የምንገርህን መቀበል አለብህ ምክንያቱም እኔ እንዲህ ነኝ» ይለናል። እዚህ ጋር ነው legitimacy የሚያስፈልገው። ዌበር በታዋቂው ምደባው ሦስት ዓይነት legitimacy በቲዎሪው ውስጥ አቀምጦ ይገኛል። እነሱም፦ 1,Traditional authority — «ሁሌም እንዲህ ነበር» 2,Charismatic authority — «ይሄ ሰው የሚለየው ነገር አለው» 3,Legal-rational authority — «ሕጉ ወይም ሥርዓቱ እንዲህ ነው የሚለን» የሚል አካሄድ ነው። ፎርሙላውን በምሳሌ ሳስቀምጥላችሁ፦Authority ≈ Power × Legitimacy ይሰኛል። ኃይል አለ ነገር ግን የኃይል ፈቃድ Authority የለም እዚህ ጋር ግጭት መፈጠሩ አይቀሬ ነው። ስለዚህ Power + legitimacy አንድ ላይ ስናጣምር authority ወይም ህጋዊ የፈቃድ መብት ይኖረናል። #ኤምሊ_ዱርክሄም ደግሞ የማርክስ እና የዌበርይ ሃሳብ በማጥላላት (Social Integration Theory) ያስቀምጥልናል። ይሄንምም ሲናገር ኃይል በአንድ ሰው ውስጥ የሚወሰን ግፊት ብቻ አይደለም ይለናል። #ዱርክሄም ደግሞ የሁለቱን ሃሳብ ሙሉ ለሙሉ አይቀበልም። ይልቅስ ኃይልን ከግለሰብ ወደ ወደማህበራዊነት ይወስደዋል። ማህበረሰብ በራሱ ሰዎችን በ(norms, values, customs, institutions) የሚገዛበት ኃይል አለው። ፎርሙላውን በዚህ መልኩ ይቀመጣሌ፦Social Power ≈ Norms + Collective Values + Institutions + Social Pressure. ለምሳሌ ሕግ ስርቆትን ይከለክል። ነገር ግን ሕግ ባይኖርም ማኀበረሰቡ «መስረቅ ነውር ነው ወይም አጢዓት ነው» ብለው ስላስተማሩን ከመስረቅ እንቆጠባለን። እዚህ ጋር የሚሠራው external force ብቻ አይደለም፤ ኃይሉ ወደ conscience ውስጥ የመገንባት ሂደትም ጭምር ነው። ዱርክሄም በአጭሩ የሚለን ኃይል ብቻ በቂ አይደለም። ሰዎች ያንን ኃይል ሕጋዊ እና ተገቢ ነው ብለው መቀበል አለባቸው ያኔ ነው Authority የሚፈጠረው ነው። ማህበረሰቡ ሰዎችን በልማድ፣ በሞራል እና በማህበራዊ ደንብ ይቆጣጠራል። ሁልጊዜ ሰውን በኃይል ማስገደድ አንችልም። ይልቅስ ብልህነት በታከለበት መልኩ «ይሄ ትክክል ነው» ብለው እንዲያስቡ ማድረግ ይበልጥ ሥርዓቱ እንዲቆይ ይረዳዋል ነው። ኃይል ያለው አንድ ሰው የሌላኛውን ሰው በር በግድ ሊያስከፍተው ይችላል፤ የስልጣን ፈቃድ ግን ሰውዬው በራሱ በሩን እንዲከፍት የሚያደርግ የህግ ኃይል ይፈጥርበታል። በጣም ኃይለኛው እስር ቤት ግንብ የሌለው እስር ቤት ነው። ሰውዬው በሩ ክፍት መሆኑን እያወቀ ከዛ ቤት ለመውጣት አንድ እርምጃ እራሱ አይራመድም!።

አትሰልቹ! ✌🏼
አትሰልቹ! ✌🏼

ጥቂት ነው የሚቀረው°° ለ500 ሰው ሰዓቱ እየየረሰ ነው። ስምምነ ትብብረ 😑
ጥቂት ነው የሚቀረው°° ለ500 ሰው ሰዓቱ እየየረሰ ነው። ስምምነ ትብብረ 😑

1ሺህ ሰው አልገባልኝም አዝናለሁ። ቢያንስ 500 ሰው እንግባና ግማሹን ልቀበል።

Red 🛑🥂

አርምሞ🧘🏽‍♂ - Telegram 频道 @armemo_offical 的统计与分析