es
Feedback
አርምሞ🧘🏽‍♂

አርምሞ🧘🏽‍♂

Ir al canal en Telegram

ጥ ቂ ት ም ና ኔ. .🧘🏽‍♂️

Mostrar mĂĄs

📈 Análisis del canal de Telegram አርምሞ🧘🏽‍♂

El canal አርምሞ🧘🏽‍♂ (@armemo_offical) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 11 314 suscriptores, ocupando la posición 8 096 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 943 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 11 314 suscriptores.

SegĂşn los Ăşltimos datos del 30 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los Ăşltimos 30 dĂ­as la variaciĂłn de miembros fue de 66, y en las Ăşltimas 24 horas de -10, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificaciĂłn: No verificado
  • Tasa de interacciĂłn (ER): El promedio de interacciĂłn de la audiencia es 27.89%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 8.10% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicaciĂłn recibe en promedio 3 156 visualizaciones. En el primer dĂ­a suele acumular 916 visualizaciones.
  • Reacciones e interacciĂłn: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicaciĂłn es 44.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ጥ ቂ ት ም ና ኔ. .🧘🏽‍♂️”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (Ăşltimos datos recibidos el 01 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analĂ­tica demuestra que la audiencia interactĂşa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categorĂ­a ReligiĂłn y espiritualidad.

11 314
Suscriptores
-1024 horas
-337 dĂ­as
+6630 dĂ­as
Archivo de publicaciones
አሁን ከለሊቱ 6 ሰዓት ነው። ጭር ብሏል ከውሻ ጩኸት በቀር ምንም በአካባቢው የሚሰማ ድምፅ የለም። ይህን ቅጽበት ለማጣጣም ማጨስ ፈለግኩ። ታድያ ኪሴን ስፈትሸው በሲጃራ ፓኬት ውስጥ አንድ የመጨረሻ ትንባሆ ቀርሃለች። ታድያ ከዛ ሁሉ የሲጃራ ዱላዎች አንዲት ሲጃራ ብቻ መቅረቷን አስመልክቶ የሆነ ነገር ተማርኩ። እቺ በእጄ ላይ የቀረችው የመጨረሻ ሲጃራ በጣዕሟ ከሌሎች በተለየ መልኩ የምትጣፍጥ አይደለችም፤ በቅርጽም ብዛትም ልዩ አይደለችም፤ በኒኮቲን ራሽዮ እና በሳንባዬ ውስጥ በምታስቀረው ጭስም አትለይም። ሆኖም ግን ከሌሎች የትንባሆ ዱላዎች ፈጽሞ የተለየ የሚያደርጋት የራሷ ድባብ አላት። አንድ ሰው ፓኬቱ በሲጃራ ዱላዎች ጥቅጥቅ ብሎ ሲሞላ ያለአሳብ እየመዘዘ ያጨሳል። ምክንያቱም የሚያሰጋው ነገር የለም የጀመረው ሲያልቅ ሌላኛውን መዝዞ ያጨሳል። ቢሆንም ግን የሲጃራ ፓኬቱ ውስጥ ያሉት ትንባሆዎች ተመናምኖ አንድ ብቻ ሲቀረው ሁሉም ነገር ይቀየራል። በድንገት ስለቀጣዩ ማሰብ ይጀምራል። እሱን ተከትሎ የሚመጣውን ባዶነት ልብ ይላል፤ የፓኬቱን ባዶ ስፍራ በሲፊው እያስተዋለ ይመጣል። ለዛም ነው አንዳንዴ አላዋቂነትን በእራስ ላይ መፍጠር ለመኖር ተመራጩ ድንዛዜ የሚሆነው። ይህን የማጣት ስሜት ወደ ጎን ታደርጋለህ፤ አንድ የቀረችውን የመጨረሻዋን ሲጃራ ከሌሎች አጭሰ ካለፍካቸው ሲጃራዎች በላቀ መልኩ እስከመጨረሻው ታጣጥማታለህ። በዚች አንዲት ቀሪ ሲጃራ ብዙ ነገሮችን እንማራለን። አብዛኛው ግዜ የሰው ልጆች ነገሮችን ማጣት አያስፈራቸውም። ይልቅስ የሚያስፈራቸው ያ ነገር ቀስ በቀስ ቁጥሩ እየቀነሰ መምጣቱን ማስተዋል ሲጀምሩ ነው። ለዛም ነው ሳምንቱን ሙሉ በስራ ከደክመን በኋላ የምናገኛት የመጨረሻዋ የእረፍት ቀን ከሌሎቹ ቀናት የተለየች የምትሆንብን፤ የምንወደው የልቦለድ መፅሐፍ የመጨረሻዋን ገፅ ማንበብ የሚያስደስተን ብሎም ከምንወደው ሰው ጋር ከለመለያየታችን በፊት የቀረችው የመጨረሻዋ ደቂቃ ከሌሎች የተለየች የምትሆንብም በዚህ ምክንያት ነው። ዋጋ ያላቸው ነገሮች የሚመጡት ከነገሩ ምንነት ወይም ብዛት አይደለም፤ ይልቅስ ያ ነገር ተመናምኖ ልናጣው ጥቂት ሰከንዶች ሲቀረን ነው። ለዛም ነው በሃያዎቹ እድሜ ውስጥ የሚገኝ አንድ ወጣት የህይወትን ዋጋ በቅጡ የማይረዳው። ምክንያቱም ፓኬቱ አሁንም ድረስ ሙሉ እንደሆነ ይሰማዋል። ዓመታቶች ብዙ ናቸው፣ እድሎቹ ብዙ ናቸው፣ ጓደኞች ብዙ ናቸው። ከዚያ ግን በድንገት ጊዜ ይሄዳል ህይወትም የፓኬቷን ባዶነት ማሳየት ትጀምራለች። የሁላችንም ችግር በመጨረሻዋ የሲጃራ ዱላ ላይ አልተቀመጠም፤ ይልቅስ ድሮ በነበረን የፓኬት ሙሉነት ውስጥ አሁን ያለን ባዶነት መንጸባረቅ ሲጀምር ነው። @Armemo_offical

ባን ተደርገሃል ብሎ ቆይቶ እየመለሰው ነው ቻናሉን 😥 @Imagination_officially

Mensaje de voz01:15

ፎሎ አድርጉ ከዚህ በኋላ ወደፊት ነው። 150 Follower ነው ያለኝ። እስቲ ዛሬ 500 እንግባ። ይህ መቼስ አያቅተንም። ቀጣይ ፍልስፍና፣ ህልምን በተመለከተ ሂፕኖሲስ እና አስትራል ፕሮጀክሽን ብሎ
ፎሎ አድርጉ ከዚህ በኋላ ወደፊት ነው። 150 Follower ነው ያለኝ። እስቲ ዛሬ 500 እንግባ። ይህ መቼስ አያቅተንም። ቀጣይ ፍልስፍና፣ ህልምን በተመለከተ ሂፕኖሲስ እና አስትራል ፕሮጀክሽን ብሎም በጂኦፖለቲክስ ጠብቁኝ እከሰታለሁ። ዛሬ እስቲ 500 Follower አታሳፍሩኝ👇🏼 https://www.tiktok.com/@imaging_gurus?_r=1&_t=ZS-97cIU9iDrtg

Repost🎯 አታሳድዳት.. ልዩ አይደለችም.. በዚህ አለም ላይ 4,915,868,736 ሴቶች አሉ። ቁጥሩን ችላ እንዳልከው ሁሉ እሷንም ችላ በላት 🤗
Repost🎯 አታሳድዳት.. ልዩ አይደለችም.. በዚህ አለም ላይ 4,915,868,736 ሴቶች አሉ። ቁጥሩን ችላ እንዳልከው ሁሉ እሷንም ችላ በላት 🤗

የስ መብራት መጣ የስ 🤗

ይህን ክረምት የማመልጥበት ሁለት አማራጭ አለኝ። አንደኛው ትኩስ ቡና ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ መፅሐፍ ነው። ዛሬም ከትኩስ ቡና ጋር Thus spoke Zarathustraን እየገረብኩ ነው። በነገራችን ላይ በዚህ መጽሐፍ መለከፍ የራስን ሃይማኖት የመመስረት የመጀመርያው እርምጃ ነው። ለክርስትና ክርስቶስን፣ ለእስልምና ነብዩ መሐመድን፣ ለሳይንስ ኒኮላ ቴስላን፣ ለሂሳብ ደግሞ ፓይታጎረስን እንደሰጠው ያህል ለፍልስፍና የተሰጠው ደግሞ ዛራቱስትራ ነው። ዛራቱስትራ philosophical prophet ነው። የመልካምነት እና የክፋት ፈጣሪም አድርገው የሚወስዱትም አልታጡም። ይህ ፐርሺያዊ በዚህ ምድር አልነበረም ብሎ መካድ አይቻልም። ምክንያቱም ከፐርሺያ በዘለለ በአለም ደረጃ ተጽህኖ ፈጥሮ ያለፈ አሳቢ ነው። በእንግሊዝኛ፣ ዕብራይስጥ እና አረብ መሰል ቋንቋዎች ላይ ስሙ በደማቅ ተጽፏል። እሱ ፍልስፍናን አልፈጠረም ነገር ግን ለአመታት የተከተልነውን ፍልስፍና የሚሰብር እሳቤን ለአለም አምጥቷል። አብዛኛው ቃሎችሁ የስብከት ለዛ አላቸው። ምስባኩም ናዝራዊ ለመሆን የቃጣው ፐርሺያዊ ነው። የኒቼ Anti Christ ሌላኛው ክርስቶስን እንዲፈጥር የተመቻቸ ነው። ይህም Thus spoke Zarathustraን እንዲፈጥር ምክንያት ሆኖታል። ጥንት የሚታወቀው ዛራቱስትራ ህግጋቶችን የፈጠረ ሲሆን፤ የኒቼ ዛራቱስትራ ግን ህጎችን የማይቀበል ነው። ከ1883 እስከ 1885 አካባቢ የተጻፈው ህግየለሹ ወይም የእራሱን ህግ ፈጣሪው Thus spoke Zarathustra በ1986 Beyond Good and Evil የሚለውን መፅሐፍ እንዲጽፍ ምክንያት ሆኖታል። ዛራቱስትራን ለመቀበል አስቀድመን Beyond Good and Evilን ማንበብ አለብን። ዛራቱስትራ የተናገረውን ሃሳብ እንደወረደ የተቀበለው ማንነት inner chaos ይከሰትበታል። ስለዚህ በBeyond Good and Evil መፅሐፉ መጀመርያ መታሸት ይሻል። Philosophical prophet ወይም የፍልስፍናው ነብይ የሚባለው ዛራቱስትራ በመፅሐፉ ውስጥ እንዲህ የምትል አባባል አለችው፦«Nothing gives you strength like realizing that you have nothing left to lose, and that the world you were afraid of betraying is, by its very nature, a world that has already betrayed youÂť ይህ አባባል በተራሮች መካከል ብቻውን የቆየው ዛራቱስትራ aphorism ነው። ሰው እንዳይከሰትብኝ ብሎ በጣም የሚፈራው ነገር ቀድሞውንም የተከሰተ እውነት ነው። ከሌላው የሚጠብቀው ታማኝነት በራሱ ውስጥ ተሰብሯል። ዓለም ባመናት ልክ ለመታመን አልተዘጋጀችም። ስለዚህም ነው ሰው ከሚያጣው ብዙ ነገሮች በላይ የሚያገኘው አንድ ነገር ሙሉ ትርጉም የሚሰጠው። ይህም አንድ ነገር ፍርሃት የለሽነት ነው። ሰዎች በህይወታቸው ፍርሃት ከሌለ ይፈራሉ። ያለሱ መኖርን ግራ ይገባቸዋል። ነገር ግን እውነቱ ያ አይደለም። ፍርሃት ስለጠፋ ሞራል አይሞትም፤ ይልቅስ የበለጠ ይታደሳል። ከዛ በኋላ ነው ትክክለኛው ኃይል የሚጀምረው። በመፍረስ ሳይሆን መልሶ መፍጠር ውስጥ ይወለዳል። አብዛኛው ሰዎች ጥንካሬ ብለው የሚያስቡት ነገር  ከውጭ የሚመጣ ኃይል አይደለም። ይልቅስ ጥንካሬ የሚመጣው ፍርሃትን በማወቅና በመናቅ፣ ችላ ብሎ በመልቀቅ ውስጥ ነው። ሰው ምንም የሚያጣው ነገር እንደሌለው ሲሰማው፤ ምንም ነገር ለማድረግ ዝግጁ ይሆናል። ምክንያቱም በፍርሃት ታስሮ ምንም ካለማድረግ፤ ከፍርሃት ጋር አብሮ ምንም ማድረግ ይሻላል። ያኔ ታድያ ቀስ በቀስ ሕይወቱ ላይ የነበረው ጫና ይላቀቀዋል። ለፍርሃት የነበረው ቦታ ይቀንሳል። ውሳኔ የማድረግ ነፃነቱ ይጨምራል። ነገር ግን ይህ ለውጥ አንድ ሌላ እውነት ያስገነዝበናል፤ ሰው ብዙ ጊዜ የሚያመነው እና የሚጠብቃት ያቺ ዓለም ሁልጊዜ እንዳሰባት ሆና አትገኝም። የተስፋ እና የመተማመን ስርዓቶች ሲበጠሱ ሳይወድ በግዱ ወደ እውነታው ይመለሳል፤ ዓለም ፍጹም ታማኝ ወይም ፍጹም ጠላት አይደለችም፤ ነገር ግን የራሷ ተፈጥሮ ያላት ድብቅ የማትተነበይ ስርዓት ነች። በዚህ አመለካከት ውስጥ ጸንተን ስንቆይ የሚፈጠረው ለውጥ አንድ ነው፤ ሰው «ከመጠበቅ» ወደ «መቀበል» ይሸጋገራል። ከፍርሃት ቅጽር ወጥቶ በጥንካሬው ይበረታል!። ዓለም እንደምናስባት ከባድ አይደለችም፤ ይልቅስ የእኛ ትከሻ ይሄን ገፈት ለመሸከም ዝግጁ አይደለም!። «ታካች ሰው አደንን ምንም አያድንም፤ ለሰው የከበረ ሃብቱ ትጋቱ ነው..Âť ÂŤNothing gives you strength like realizing that you have nothing left to lose, and that the world you were afraid of betraying is, by its very nature, a world that has already betrayed youÂť «የምታጣው ነገር እንደሌለህ የማወቅን ያህል ጥንካሬ የሚሰጥህ ምንም ነገር የለም። እንዲሁም  በፍርሃት እንዳትከዳት የጣርክላት ዓለም ቀድሞውን በተፈጥሮዋ ከሃዲ መሆኗን ስትረዳ።» @Armemo_offical

You spent 10 seconds reading my post. Maybe you smiled. Maybe you agreed. Then you left without React. Humanity is fascinating. አንዳንድ ሰዎች ተራራ ይወጣሉ፣ አንዳንዶች ደግሞ ውቅያኖስ ያቋርጣሉ እናንተ ግን ሰክንድ የማትፈጅ የሪአክት በተን ለመጫን እራሱ ከብዷችኋል። Reactions cost nothing. No money. No time. Not even a second. Yet they can say everything. ምክንያቱም ያልተገለጸ አድናቆት ምናልባት እንዳልነበረ ይቆጠራል። Sometimes the smallest gesture speaks the loudest ወዳጆቼ ✌🏼

ከህይወት እንግዳ ድሎች መካከል አንድ ሰው አላርሙ ከመጮኹ ጥቂት ደቂቃዎች በፊት አስቀድሞ መንቃቱ ነው። በጨለማ ውስጥ አይናችንን እንገልጣለን። ሰአቱን ስናየው 11:56 ይላል። ማታ አላርሙን ከጠዋቱ 12:00 ላይ ነበር የሞላነው፤ ልንነሳ አራት ደቂቃ ብቻ ነው የሚቀረን። እኛ ግን ነቅተናል። ምክንያቱም አራት ደቂቃ በሰዓት ውስጥ ምንም ዋጋ የለውም ብለን እናምናለን። ሆኖም ግን በድንገት የመከዳት ስሜት ይሰማናል። የሆነ ሰው ዋጋ ያለው ነገራችንን ሰርቆናል። ታድያ መልሶ እንቅልፍ እንዲወስደን ዓይናችንን ለመጨፈን ብንሞክር፣ ያለመታከት በግራና ቀኝ ጎናችን ብንገላበጥ፣ አልነጋም ግዜው ገና ነው ብለን ለእራሳችን ብነግረውም ውሸት ነው ለሊቱ አብቅቷል። የፈለገ ተመልሰን ለመተኛት ብንሞክርም አንችልም ምክንያቱም ከአላርሙ ጩኸት በፊት በውስጣችን አንድ የተራበ ማንነት ነቅቶ እያንኳኳ ነው። ልጅ እያለን እንቅልፍ ወዲያው ነበር የሚወሰደን። ማታ በቂ እንቅልፍ ስለምንተኛ ማንም ሳይቀሰቅሰን በጠዋት ቀድመን የመንቃት ልምድ ነበረን። የቀን ውሎን የምንፈራበት ምንም ምክንያት አልነበረንም። ማታም ለመተኛት አንቸገርም ነበር። አንድ ሰው በሃያዎችሁ እድሜ ላይ ሲገባ አይኑን ሳይገልጥ ማለዳው ይጀምራል። የሚጠብቀው ቀጠሮዎች አሉ፣ የሚከፍለው እዳ አለበት፣ የሚደውልለት ደንበኛ፣ ያልተመለሱ ቴክስቶች እና የተራበ ቤተሰብ ይጠብቀዋል። ስለወደፊት ህይወቱ በፍርሃት የታጠረ ግለሰብ ወይም ደግሞ ግዜ ከሚገባው በላይ ፈጥኖ እያለቀ እንደሆነ ይሰማዋል። á‹¨áˆšá‹ŤáˆľáŒˆáˆ­áˆ˜á‹ ግን ከዓመታት በኋላ አላርም የሚባለው የቁስ ዕቃ የገዛ ስርዓትን ለመጠበቅ የተዘጋጀ ፎርማሊቲ ሳይሆን የባርነት ጩኸት እንደሆነ እንረዳለን። ለመጥፎ ልማዶቻችን መቆጣጠርያ ይሆን ዘንድ ጠረጴዛ ላይ የተቀመጠ የመቀጣጫ በትር ሆኖ ይቀራል። ቢሆንም ግን አላርሙ አይደለም የሚያነቃን፤ ይልቅስ ከእንቅልፍ የሚቀሰቅሰን ስሜት የሚመጣው ከውስጣችን ባለው የፍርሃት ማንነት ነው። ይህ መንቃት በጭንቀት፣ በኃላፊነት፣ በጊዜ እና ሙሉ በሙሉ እፎይ ብሎ ካላረፈ የአእምሮ ክፍል የሚከሰት ቀንበር ነው። ሰው ተኝቶ እራሱ ያ የአዕምሮ ክፍል ትልቅ ቤት እንደሚጠብቅ ዘበኛ ለሊቱን ቆሞ ያድራል። እና ያ የአዕምሮ ክፍል የምንነቃበት ሰዓት ሲቃረብ የሞላነውን አላርም የማያምነው ይመስል አስቀድሞ ይቀሰቅሰናል። ለዛም ነው እነዚህ 4 ደቂቃዎች የሚረብሹን። ምክንያቱም መቀበል የማንፈልገውን እውነት ያሳዩናል። ሰውነታችን መተኛት ያለበትን ያህል ሰዓት ተኝቷል። ነገር ግን እኛ አልነቃንም። ቢሆንም ይሄን ስሜታችንን አያከብርልንም ምክንያቱም በሕይወታችን ውስጥ መቅረፍ ያለብን አንድ ሺህ አንድ ችግሮች አሉብን። ህፃን ልጅ አዲስ ቀን ለመኖር ይነቃል፤ ሽማግሌዎች ደግሞ የቀራቸውን ቀን ለመጨረስ ይነቃሉ። ወጣት ግን ቀኑን ለመስራት መንቃት አለበት!። እና በመጨረሻም የምላችሁ አንድ ነገር ቢኖር። አላርሙ ከመጮኹ በፊት አስቀድመን የምንነቃት ያቺ አጭር ቅጽበት የረጅም ግዜ ትልቅ ትምህርት ታስተምረናለች። የሚቀሰቅሰን የሞላነው አላርም አይደለም፤ አላርም ማቴሪያሊስቲክ ሜታፎር ብቻ ነው። እኛን የሚቀሰቅሰን የገዛ ህይወታችን ናት፤ ቀን በቀን፣ ወራቶችን ሳያቋርጥ ጠዋት ጠዋት ለዓመታት ያለ ርኅራኄ የአዕምሮ ደጃፋችንን ይቆረቁራል!። ተነስ/ተነሺ ነግቷል..°°                       @Armemo_offical

እዕቴ ከሁለት ሳምንት በፊት የሆነ ቡቲክ ከፍታ ነበር። እና እዛ ቡቲክ ውስጥ የሆነ የድግምት ወረቀት ተቀብሮ አገኘው። የድግምት ስራዎችን አውቃለሁ ግዕዝ ማንበብ በከፊል ብችልም የዛን ያህል ግን ኤክስፐርት አይደለውም። ከዛ ሆዬ ኪሴ ላይ ይዤ ወደቤት። ታድማ ማታ እንዴት ልተኛ። ሰባቴ ነው የነቃውት ቅዠት እያሰቃየኝ። አንዴ ጫጫታ፣ አንዴ ውሻ መጥቶ ጆሮዬን ይልሰኛል፣ ፊቴን የሚውጠኝ የሆነ መምጠጫ ነገርም ያለ ይመስለኛል። የምር ጸለይኩ። ሰላም እለኪ ደገምኩ። ልተኛ ነው ታድያ ከረባበተኝ። የድግምቱን ፎቶውን ከስር ኮመንት ላይ ልኬላችኋለው። እኔ እንደሚመስለኝ ይህን ድግምት የሚጠቀመው ሰው የሚያስቸግሩት አጋንት እንዳሉና እነሱንም አጋንቶች ለራሱ ጥቅም እንዲገዙለት፣ እንዲታዘዙት የአየር መነፋስታንን እየጠራ ነው።

ብዙ ግዜ እንዲህ እናደርጋለን። ወደ ፍሪጅ እንሄድና በሩን ከፍተን ውስጡን እንመለከታለን፤ ምንም የለውም ስለዚህ መልሰን እንዘጋዋለን። ከአሥር ደቂቃ በኋላ ያንኑ ተመሳሳይ ትዕይንት እንደገና እንደጋግማለን። ከውጭ ሆኖ ሲታይ ይህ ነገር ትንሽ አስቂኝና ከንቱ ነገር ይመስላል። ምክንያቱም ፍሪጁን ከመክፈታችን በፊት ውስጡ ምን እንዳለ አስቀድመን እናውቃለን። እኛ በሌለንበት ማንም መጥቶ ጣፋጭ ምግብ፣ ውድ መጠጥ፣ ወይም ለመኖር መመገብ ያለብንን መደርደሪያው ላይ አያስቀምጡልንም። ቢሆንም ተመልሰን ያንኑ አንድዓይነት ተግባር እንደጋግማለን። ለምን ግን?። ምክንያቱም ሁልጊዜ ፍሪጁን በከፈትን ቁጥር አዲስ ምግብ እየፈለግን አይደለም። ከዛ በተለየ ስሙን በስትክክል እራሱ የማናውቀውን አዲስ ነገር እየፈለግን ነው። ካለፉት ደቂቃዎች የተለየች አንዲት ደቂቃን ፍለጋ፣ ትንሽ የአዲስነት ስሜት፣ የቀኑን ድብርት የሚሰብር አንዲት የተለየች ነገር፤ አልያም ከተቀመጥንበት እንድንነሳ የሚያደርገን ተራ ምክንያትን ፍለጋም ይሆናል። ብዙሃን ሰዎች ፍሪጃቸውን የሚከፍቱት በርሃብ ስሜት ሳይሆን በድብርት ውስጥ ሆነው ነው። ድብርት ማለት ሰው ከራሱ ጋር ረጅም ጊዜ መቆየት እንደማይችል የሚያሳይ እንግዳ ስሜት ነው። በድሮ ግዜ ድብርት የሕይወት ተፈጥሯዊ ክፍል ነበር። ሰዎች ከሐሳባቸው ጋር ብቻ ያወሩ ነበር፣ ይራመዱ ነበር፣ ያሰላስሉ ነበር፣ ወይም ዝም ብለው ተቀምጠው ባዶ ወደሆነ ስፍራ ለረጅም ሰዓታት ያፈጡ ነበር። ዛሬ ላይ ግን ድብርት ሲሰማን ወዲያውኑ መጥፋት ያለበት ጠላት አድርገነዋል። ስልክ ቴሌቪዥን ሙዚቃ ጌሞች እነዚህም ከሌሉን ፍሪጅ እየከፈትንና እየዘጋን በመብራቱ ከመጫወት ወደኋላ አንልም። ምንም ቢሆን ምን ጭር ያለችውን ያቺን ባዶና አጭር ቅጽበት ከመጋፈጥ ይህን አማራጭ አድርገነዋል። ስለዚህ ይህ የስነልቦና ማረፊያችን ይሆን ዘንድ ፍሪጅ ከቤት ዕቃዎች በላይ ትርጉም ሰጥቶናል። የፍሪጁ በር አዲስ ነገር ያመጣልን ይመስል ለመቶ አንደኛ ግዜ እንከፍተዋለን፤ ነገር ግን የምናገኘው ከዚህ በፊት ያስቀመጥነውን ነገር ብቻ ነው። እዚህ ጋር ነው እርብሽ የሚያደርግ ሃሳብ የሚከሰትብን። ሕይወት ልክ እንደ ፍሪጅ ነች።       ወደተመሳሳይ ሰዎች እንመለሳለን           ወደተመሳሳይ ልማዶች             ወደእነዚያ ቦታዎች            ወደ ትናንት ሐሳቦች። ከዚያ ግን ውጤቱ ለምን አልተቀየረም? ለምን አዲስ ነገር አልመጣም ብለን እንጠይቃለን። ለመለወጥ የሚሆን የተለየ ተግባር ሳንፈጽም ሕይወታችን እንዲቀየር ግን እንፈልጋለን። አንድ ዓይነት መፅሐፍ እያነበብን አዲስ ሐሳብ እንዲፈጠር እንፈልጋለን። ተመሳሳይ ባህሪ እያንጸባረቅን የተለየ ግንኙነት እንመኛለን። ትናንት ያለፍናቸውን ቀናቶች ደግመን ለመቶኛ ጊዜ እየኖርነው አዲስ ስሜት እንዲመጣ እንጠብቃለን። ታድያ ምንም የሚቀየር ነገር የለም። ስለዚህ በኮሪደር ልማት ጉርጓድ የሰራውን መንገድ አሳበን እናማርራለን። አሁንም አንሰለችም ፍሪጁን አሥር ጊዜ እየከፈትን እንመለከተዋለን። ቢሆንም ያው ነው፤ በውስጡ አዲስ ነገር የለም። እንቆጣለን፣ እናጉረመርማለን። ሞደርን ቲንከር ለዚህ የሚሆን አንድ አማራጭ ብቻ ነው የሚያስቀምጥልን። እሱም ባዶነትን ከውጭ በመጣ አዲስ ፍጆታ ይሞላ የሚል የቅዠት ዲስኩር ነው። ከደበራችሁ አዲስ ነገር ግዙ፣ ሀዘን ከተሰማችሁ መጠጥ ጠጡ፣ ከጨነቃችሁ ዩቲዩብ ወይም ቲክቶክ ክፍታችሁ ቀልድ ተመልከቱ፤ ብቸኝነት ከተሰማችሁ የማነቃቂያ ንግግሮች ያሉበት ሌላ ቪዲዮ ክፈቱ። ቢሆንም ግን እነዚህ ከላይ መፍትሔ ተብለው የተቀመጡት በጠቅላላ ፍሪጅን እንደ መክፈት ያለ ተመሳሳይ ተግባሮች ናቸው። ለአጭር ጊዜ የሚሆን ጥቂት ስሜት ይሰጡናል፤ እውነተኛ ለውጥ ግን አያመጡልንም። ከትንሽ ደቂቃዎች በኋላ ያኛው ተመሳሳይ ስሜት ተመልሶ ይመጣብናል። ስለዚህም ነው ይህን የምላችሁ፦የዘመናዊው ሰው ችግር የመዝናኛ እጥረት አይደለም፤ በተቃራኒው የመዝናኛ መንገዶች እንደአሸን ስለበዙ ችግር ሆኖበታል። በተለይ በዚህ ግዜ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ይሄን ያህል የመዝናኛ  አማራጮች በዝተው አያውቁም። ሆኖም የዛሬ ሰዎች ከድሮ ሰዎች በላቀ ባዶነትታቸውን ሲያማርሩ በተደጋጋሚ ይሰማል። ነገር ግን ይህ ባዶነት የሚባለው የድብርት ስሜት የሚፈጠረው በእንቅስቃሴ እጥረት አይደለም፤ ይልቅስ ትርጉም በማጣት ውስጥ ይከሰታል። ትርጉም በፍሪጅ መደርደሪያ ላይ ተንጠልጥሎ አናገኘውም፤ በስልኮቻችን ውስጥ  በተቀመጡ የቪድዮ ክምር ውስጥ የለም፤ በጊዜያዊ ዋጋም አይገዛም። ከዚያ በላቀ የጠለቀ ነው። ራስን ከመሸሽ ይልቅ ራስን መጋፈጥን የሚጠይቅ ጽናትን ይመስላል። በመጨረሻም ይህ ለማለት እወዳለሁ፤ በሚቀጥለው ጊዜ ያለግልጽ ምክንያት ፍሪጁ ፊትለፊት ቆማችሁ ከተገኛችሁ አንድ ቀላል ጥያቄ ብቻ እራሳችሁን ጠይቁ፦           «እውነት እርቦኝ ነው?Âť «ወይስ ለረጅም ጊዜ ዝም ለማሰኘት የሞከርኩት ሌላ ነገር በሕይወቴ ውስጥ አለ?Âť @Armemo_offical

ፍሪጁን ለምን ከፈታችሁት?
ፍሪጁን ለምን ከፈታችሁት?

ኸረ ፎሎ አድርጉ በዚህ @imaging_gurus ወይም በዚህ 👇🏼 https://vt.tiktok.com/ZSQELcwSs/
ኸረ ፎሎ አድርጉ በዚህ @imaging_gurus ወይም በዚህ 👇🏼 https://vt.tiktok.com/ZSQELcwSs/

There are ideas that deny God, and there are ideas that deny meaning. Heresy begins where the second survives the first: not by arguing that God does not exist, but by insisting that even if He does, existence itself remains without purpose. These poems emerge from that philosophical abyss—not as a rejection of divinity, but as a rebellion against the belief that divine presence is sufficient to redeem human suffering. They speak in the language of faith while standing at the edge of despair, where God is neither denied nor embraced, only questioned°°       #ምንፍቅና_1 ..ሙታናም በድኔን ደጁን አሳልፌ ክርስቶስን ለመንኩ ጸጸቴን ታቅፌ እሱም.. በእርሱ ፈንታ መስቀሉን አቆመው  áŠ¨áˆľá‰ƒá‹Ź ይልቅ ስጋዬን ሰቀለው !           #ምንፍቅና_2 የእግዜር መልዕክተኛ.. መንፈስ ቅዱስ ባርኮ ለአህዛብ እየሰጠ የእኔ ተራ ሲደርስ ሀሳቡን ለወጠ፤   የከፈኔን ጋቢ ሆም ብሎ እየቋጨ በስመ አብ ተማጽህኖ ማርያም ብቅል ፈጨ!፤ የእግዜር መልዕክተኛ ለእኔ አልደረሰም    ከፈሰሰው ዘሬ መሬት አላረሰም፤ ይልቅስ ደረቀ ፥ ወጣት ደንግባቴ ተቀበረ ህልሜ ፥ ልክ እንደ እትብቴ፤ አሁንማ መሽቷል ፥ ፀዐይ ሌት አይነጋ እርጥብ ዝናብ ስመኝ ፥ የከሰዓት በጋ   በለሴ ደረቀች ፥ ከደሜም ሳልረጋ   መንፈሴን አወከው ፥ የረከሰ ስጋ!፤ የእግዜር መልዕክተኛ .. እኔን አይፈልግም ፥ ነፍሴን ነው የሚሻ    ሰውነቴ እርኩስ ፥ እዳሪ ቆሻሻ!፤ ወደሲዖል ወርዶ ፥ እስከ'ሚያስረክበኝ ሞቴን ይደግሳል ፥ መኖር እየራበኝ!!። @Imagination_officially      

Repost from N/a
ÂŤYou are not your job. You're not how much money you have in the bankÂť «አንተ ስራህን አይደለህም። በባንክ ሂሳብህ ውስጥ ያለው ገንዘብም አንተን አይደለም።» ከላይ ያለው አባባል Fight club በተባለው ፊልም ውስጥ ታይለር የተጠቀማት መሳጭ ንግግር ነች። Fight clubን ሁለቴ በስነስርዓት አይቼዋለሁ። በፊልሙ ውስጥ ታይለር የተባለው ገፀባህርይ ውስብስብ የሆነውን የሰው ልጅ የአዕምሮ ክፍል ምን እንደሚመስል በግላጭ መልኩ ያሳየናል። በተለይም የጁንግ ÂŤShadow selfÂť በቂ ምሳሌ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ታይለር አመፅን፣ ብጥብጥን ብሎም ከማህበረሰብ ውስንነት ነፃ መውጣትን የሚገልጽ ገፀባህርይ ነው። ፊልሙ በአዕምሮ ሰንሰለት የታጠሩ ማህበራዊ ስርዓቶችን ካለመቀበል አኳያ Capitalist culture የሆነውን የቁስ እቃ ባርነት ይተቻል። በዚህ መልኩ የሚመጡ የውሸት ደስታዎች በጠቅላላ አይቀበልም። ዋና ገፀባህሪ ቁሳዊ አለምን ለማግኘት መባዘኑ እውነተኛ ማንነቱን እንዳያገኝ ገደብ ከመሆን በቀር ትርፉ ትርፍ አንጀት ሆኖበት በቅዠት ሲሳቃይ እንመለከታለን። ታይለር በስጋ የተገለጠ ሰው ሳይሆን የዋናው ገፀባህርይ ÂŤShadow selfÂť የጨለማው ጎን ጥላ ነው። አመጹ የተጨቆነ ምኞቱን ቁጣውም ከንቱ የሆነ ሕይወቱን ይወክላል። ይህም የተደበቀ የስሜት ባህሪው ወደስርዓት አልበኝነት የገፋው የተበላሸ ባህሪው ውጤት ነው። ከዋናው ገፀባህሪይ ይልቅ በዋናው ገፀባህሪ ውስጥ የተጸነሰው ታይለር ተፅእኖ ፈጣሪ ከመሆን አልፎ ብዙ ሰዎችን ወደ ሀሳቡ በመሳብ እንደ ÂŤFight ClubÂť አይነት የለሊት ግጥሚያዎችን በይፋ መስርቷል። በርግጥ ወጥ ስብዕናው ከስነልቦና አንጻር ብንፈትሽ የተከፋፈለ ማንነት ÂŤDissociative identity disorderÂť ነው። ዋናው ገፀባህርይ በአዕምሮ የተፈጠውን «ታይለር» የተባለ Multiple personality አያውቀውም። ከዚህ የምንረዳው አእምሮ እርዳታ የለሽ፣ ጭንቀት ወይም የብቸኝነት ስሜትን ሲያስተናግድ የውሸት እውነታን በመፍጠር ውስጥ ሌላ ማንነት እንደሚወለድ ነው። በመጨረሻም ታይለር የተባለው shadow self በቅጡ የተረዳው ፊልም ተመልካች ስለራስ፣ ስለነፃነት እና ስለህይወት ትርጉም ፍልስፍናዊ እና ስነልቦናዊ ጥያቄዎችን እንዲጋፈጡ የሚያስገድድ ገፀባህሪ ነው። የሙሉ ፊልሙን መርሐግብር በጥልቀት ለተረዳው ታይለር ታላላቅ ከምንላቸው ውስብስብ ሲኒማቲክ ገፀባህሪያት ተርታ የሚሰለፍ ሌላኛው ሰው ሆኖ እናገኘዋለን።               @Mid_Cinema

Repost from N/a
Fight Club 📽️
Fight Club 📽️

ዛሬ በኮነሬል፣ በጀነራል ተከብቤ ምሳ እየበላው ነው። የምሬን ነው እንዴት እንደሚያሳቅቅ። ወላህ ማታ ኪሴ ውስጥ የራሳውት ሮች ጭምር ነው ትዝ ያለኝ። አባቴ የስራህን ይስጥህ። ወለድከኝ እንጂ አልገዛኸኝም እኮ 😥