የኔ ዜማ የአድማጮች የሙዚቃ ምርጫ
Відкрити в Telegram
- በፌስቡክ👇 https://www.facebook.com/100022318509408/posts/1859085851512014/?app=fbl https://www.facebook.com/share/1AMgudXhJr/ - በቴሌግራም ገፅ👇 https://t.me/biggrs - ቲክቶክ ገፅ 👇 tiktok.com/@temesgen_ukare - በዩትዮብ ተከታተሉን👇 https://youtube.com/@temuyehag
Показати більше275
Підписники
-224 години
-37 днів
+430 день
Архів дописів
ሰው እንዴት ሙዚቃውን እየሰማ ያለቅሳል፡፡🥹
(ቻው)የሚለው ሙዚቃ ስሙት ገፀ በሀሪውን ዳብሱት "እተጎዳህ ቻው ማለት ይከብዳል"🥹ምን ብታጠፋ ነው የሰውን ስሜት በሙዚቃ ይገለጣል🥹
"ያጓጓኝ ፍቅራችን አየሁኝ ሲያከትም
የሳሱለት ነገር ለካ አይበረክትም
ዛሬም ለበደልህ ላረከኝ ጣልጣል
ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል" ይላል🥹
ግጥም፡ናትናኤል ግርማቸው ዜማ፡ምህረት አብ ደስታ ቅንብር፡ ታምሩአማረ (ቶሚ) ሌላ ምን ልበል አመሰግናለው ወዳጆቼ
"ወጣት የነብር ጣት" ይለዋል ይሄ ነው፡፡
ጆሮዋችሁን ለማከም ይህ አልበም ቀርቦላችኃል፡፡
በቅርቡ ሙሉ ትንታኔ አቀርባለው ግን ታምሩ አማረ፣ ናትኤል ግርማቸው፣ ምረት አብ ደስታ እና ሌሎቻችሁን ልጆችን እንዴት መቅረፅ እንዳለባችሁ ታውቃላችሁ፡፡
መልካም እድል ቤቲሻ❤️
ይድረስ ለድምፃዊት ዶናት ተክሉ ከተመስገን ኡካሬ (የሐጌ ልጅ)
ይህንን አልበም ለመስማት ረጅም ጊዜ የጠበቅኩት ሲሆን፣ እንድጠብቅ ካደረጉኝ ምክንያቶች ቀዳሚው ከታላቁ የሙዚቃ ሰው ኤልያስ መልካ ጀምሮ እስከ ያምሉ ሞላ ድረስ ስራዎቹ እንዴት ተጠናቀቁ? የሚለው ጥያቄ ነበር። ከEP ከፍ ያለ፣ ከሙሉ አልበም ደግሞ ዝቅ ያለ ቅርፅ ያላቸው እነዚህ የሙዚቃ ስራዎች በውስጣቸው ትልቅ የጥበብ ስንቅ የያዙ ናቸው። በታላቁ ኤልያስ መልካ እጅ የተጀመረውንና በያምሉ የተጠናቀቀውን ይህንን አልበም ምን ጠግኖት ለዛሬ አበቃው? የኤልያስ የሙዚቃ ስራዎች የእድገት ደረጃዎች ቆይታ በኃላ "ዓሀዱ አልበም" ተብሎ ተለወጠ ወይስ በፊት ተሰርቶ እንደ ወይን እየጣፈጠ ቆይቶ ዛሬን ጠብቆ ወጣ? የግጥምና የዜማውን ውህድ ግብ በጥልቀት ለመረዳት አልበሙን በጥንቃቄ፣ በሚዛናዊነትና በሰላ ጆሮ ማዳመጥ የግድ ይላል።
አልበሙ ከአቀናባሪ ያምሉ ሞላ እጅ እንዲያይወጣ ለመቆጣጠር የተደረገው ጥረት፣ የሙዚቃ መንፈሱንና እስካሁን የመጣበትን የሙዚቃ ጉልበት በሚገባ ያሳየበት ነው። በእርግጠኝነት 15% የነበረውን የሙዚቃ ትርፍ ወደ 85% ለማድረስ ሌት ተቀን እንደተደከመበት ያስታውቃል። ይህ ጥረት ምን ያህል ተሳካ? ለሚለው መልስ የተረዳሁትን ነጥቦች በሚከተለው መልኩ አጠቃልላቸዋለሁ፦
አልበም ቁጥጥርና የሙዚቃ አረዳድ (Album Control & Music Understanding) በስቱዲዮ ቆይታ ውስጥ ብዙ ነገሮችን ሚዛናዊ ለማድረግ ትልቅ ልፋት ተደርጓል። የሌላን ሰው የጥበብ መስመር ተረድቶ ለማስቀጠል በራሱ መደጋገም የሚፈልግ ከባድ ስራ ነው። የአልበሙን ቅርፅ ጠብቆ ለማስኬድ በአቀናባሪ ኤልያስ እና በያምሉ ሞላ መካከል ባለው ሂደት ላይ ያምሉ በተወሰነ መልኩ "ነፃነት የተነፈገ" ይመስላል። የአንዱ የሙዚቃ ስራ ወደ ሌላኛው ሲያልፍ ልዩነቶች ቢኖሩም፣ የድምፅ ከለሩ በግልፅ ይታወቃል። በአጠቃላይ ይህ አልበም ያምሉ ነፃነቱን ያገኘበትም የተጨነቀበትም ስራ ሆኖ አልፏል።
የሐሳብ ጥንካሬ በግጥምና ዜማ ቅለት (Soft Lyrics & Melody, Hard Concept) የአልበሙ አንዱ ጠንካራና ልዩ መገለጫ፣ ለአድማጭ ሊተላለፍ የተፈለገው መልዕክት በቀላሉ እንዲደርስና እርስ በርስ የመታረሚያ ትስስር እንዲፈጥር ተደርጎ ግጥሞቹ ቀለል ተደርገው መሰራታቸው ነው። ይህንን በአልበሙ ውስጥ በግልፅ እንድንረዳው አድርጎናል። የብሌን ዮሴፍ የሙዚቃ ጥሞና የታከለበት መሆኑ እንዲሁም ድምፃዊቷ ለኤልያስ ያላትን አክብሮትና ፍቅር ከአድናቆት ባለፈ በግጥም ማስመስከሯ ለአልበሙ ሌላ ትልቅ ጉልበትና ስኬት ሆኖታል።
ኃላፊነት መወጣት (Responsibility) ይህ ረጅም ጊዜ የወሰደውን አልበም ዳር ለማድረስ የተኬደበት ርቀት ትልቅ መመዘኛ ነው። በሌላ በኩል በስምንቱ የሙዚቃ ስራዎች ውስጥ የአልበሙን ጥፍጥና በሚገባ ለማሳየት ተሞክሯል። ስራዎቹ ደርሰው ዝም የሚባሉ ሳይሆኑ፣ ደርሰው በልብ የሚሰሙ ሆነዋል።
ማህበረሰብን ያማከለ ጥናታዊ አልበም (Social Experimental Research Album) ይህንን ያልኩበት ምክንያት እያንዳንዱ የአልበሙ ክር ከእኛ ልብ ጋር በቀረበ መልኩ በመሰራቱና በተራማጅ አስተሳሰብ፣ በፍቅር፣ በይቅርታ እንዲሁም በተስፋ ውስጥ የራሱን እውነታ ስለገለጸ ነው። ከነዚህም ውስጥ የወደድኳቸውን ለመጥቀስ ያህል፦
ይቅርታ (ሬጌ):- ይህንን ሙዚቃ ለመረዳት ከራሳችን ሐሳብና ልቦና ጋር ማስተሳሰር ይኖርብናል። ይቅርታ የሁሉም የበላይ ነው። በሱ ሕግ ስትመራ ጥፋትህ ይቀንሳል፤ ነፃነትን ተላብሰን እንድንጓዝም ይረዳናል። ተደብቀህ ሰውን የምትሰድብ ከሆነ ለይቅርታ ተዘጋጅ፤ በሌለበት ሰው ማማት ለሰላምታ እራሱ በር ይዘጋል። "ተደብቀህ ስትሰድብ ለይቅርታ ተዘጋጅ" የሚለው የዘፈኑ ዋና ነጥብ ነው።
"አሞኝተህ ሳትል ይቅርታ
አታስበው የለም ሰላምታ
ማሩኝ ሳይል ላይሞት ያጠፋ
የለም እድል የፍቅር ተስፍ"
ግጥም እና ዜማ ኤልያስ መልካ ቅንብር፡ያምሉ ሞላ እና ኤልያል መልካ
አቅፎ አድራሽ (ችክችካ):- ይህ ሙዚቃ የኤልያስን የግጥም ጅማሮ መሰረት አድርጎ በሙዚቃ ባለሙያዋ ብሌን ዮሴፍ የተጠናቀቀ ነው። የኤልያስ መረዳት ሁሌም ይገርማል፤ ነገን እያየ ግን እያስጠነቀቀና እያስተማረ ይነግረናል። በዚህ ዓለም አዲስ ነገር እንደሌለ በማመን ወደ እምነታችን እንድንጓዝ፣ እዚህ የምንሰራው ደግ ስራ እላይም የእኛ መሆኑንና ምርጫችንም በእጃችን እንዳለ ይጠቁማል። ኤልያስ ማረፊያውን ስላደላደለ ቀድሞ የነበረውንና የቀረውን ሕይወት ተናግሯል። ኤልያስ ያለበት ሁኔታ በዶናት በኩል የተገለጸልን ያህል ይሰማኛል።
"አቅፎ አድራሽ ያፋጥነኝ እንጂ
እጄን ይዞ ወዳልኩት ደጂ
----------
በል በል ተነሳ በል ልቤ ፍጠን እግሬ
እዚህም ሐገር እዚያም ሀገሬ
ግጥም እና ዜማ፡ ብሌን ዮሴፍ እና ኤልያስ መልካ ቅንብር፡ኤልያስ መልካ እና ያምሉ ሞላ
ቆም ያዝ (ፎክ እና ሞገር ሙዚቃ በጉራጌ ቶን):- በዚህ ሙዚቃ ላይ ያምሉ ሞላ ሙሉ በሙሉ የነፃነቱን ጥግ የተጠቀመበት ይመስላል። ቀደም ሲል በቸሊና፣ በቤቲ ጂ፣ በሚኪ ሐሴትና በደሳለኝ አበጀ የሙዚቃ ስራዎች ውስጥ በታየው የጉራጊኛ ቅኝት ቅርፅ ውስጥ፣ ዶናት ተክሉ በራሷ መንገድ እንድትራመድ ያምሉ ትልቅ እድል ከፍቶላታል። የዋሽንትና የማሲንቆ አገባቡ፣ የመግቢያና የመውጫ ስልቱ አዲስ ጣዕም ያለው ነው። አድናቆት የተሞላበትና ቀልባችን ሳይበታተን ደስታዋን እንድንጋራ የሚጋብዝ ድንቅ ስራ ነው
''ልብህን መልሰው ቀልብህን በል ያዘው
ለመጣ ለሄደው እየወዘወዘው
የረጋ ልብህን አተረማመሰው"
ግጥም እና ዜማ፡ዶናት ተክሉ ቅንብር፡ያምሉ ሞላ
ከነዚህ በተጨማሪ "ይቅርብኝ"፣ "ለኔ ማ"፣ "የልብ ዋጋ" እና "በቃ" የተሰኙ ሌሎች ድንቅ ስራዎች የተካተቱበት ሲሆን፣ አልበሙን ሙሉ በሙሉ በሽር ጉድ ኢንተርቴመንት (Shur good Entertainment) የዩቲዩብ ቻናል ማግኘት ይቻላል። በዚህ አልበም ላይ ኤልያስ መልካ፣ ብሌን ዮሴፍ፣ ያምሉ ሞላ፣ ዘሩባቤል ሞላ፣ አዲስ አለማየሁ (ሀዲንቆ) እና ሌሎችም የተሳተፋችሁ የጥበብ ባለሙያዎች በሙሉ ስራችሁ ስላማረ እናመሰግናለን። ይድረስ ለ ለዶናት ተክሉ ከ ተመስገን ኡካሬ
ኤልያስ መልካ ዛሬም አልደበዘዝክም😭😭😔
ዶናት ተክሉ አዲስ አልበም ሰጥታናለች ኤልያስ አለ
"ሲታደል የልብ ዋጋ
አያረጅ ሰርክ አይደክምም ለካ"
ይታደስ ይብስ ለካ
ወይ ፍቅር እያደር ሲነጋ"
============
አድምጬው አብሬው አውርቼው ነግሬው
ይጥመኛል ወሬው
አልበም፡ዓሀዱ
ድምፃዊት፡ ዶናት ተክሉ ወይም ብስራት ተክሉ
ግጥም እና ዜማ፡ ኤልያስ መልካ
ቅንብር፡ኤልያስ መልካ እና ያምሉ ሞላ
ኤላ ለዛ በዘላለማዊ መውደድ ያለሽ
ሽር ጉድ ኢንተርቴመንት ለቋል ገብታችሁ ስሙ
ይድረስ ለቀነኒሳ በቀለ
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ይንን ምስል በራሱ የማዕበራዊ ገፅ ላይ ያጋራው ነው፡፡
"በል አንሳን ፎቶ ለብሰን ባንዲራ
ብለህ ፃፍበት ታሩክ ተሰራ"
እኔ ዛሬ ስለ ቀኒሳ ትንሽ ልበል ሐገር የምትኮራበት የምን ጊዜም እንቁ አትሌት ነው፡፡ ሩጫው በጊዜ ላዩ ተመልካች ና አድማጭ እንዴት ልብ ሰቅሎ ልብ አርሶ የሚጨርስ ሯጭ መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡
ዛሬ ቪድዮቹን ወደ ኃላ እያየዋቸው ከ ዘመን ጋር እያቀራረብኩት ስደነቅ እና እኔም በኩራት የምናገረው ታሪክ አለኝ ብዬ እንባዬ እያገዘኝ በደስታ በትውስታዬ ጋር አነባው፡፡
የጥበብ ባለቤት ቴዎድሮስ ካሳሁን ብዕሩን አንስቶ በስሜት እና በሰከነ የጥበብን ማዕበል በማናወጥ ከ ።የሙዚቃ ቀማሪ ዳዊት ጥላሁን ጋር በመሆን በ24 ሰዓት ውስጥ የወለዱት ሙዚቃ ነው ብዙ ይናገራል፡፡👇
"እዩት ንጉሱን ግርማ ሞገሱን
ዘውድ ሸለመው ሰጠው ለአዲሱ
ይቺ ባንዲራ ናት እድለኛ
ዛሬ የሚኮራት ቀነኒ ኬኛ"
መልካም ልደት
(ቀነኒሳ በቀለ) ከተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ
ከፍታ የጋዜጠኝነት ሥልጠና ምዝገባ ከሰኔ 2 ጀምሮ መጀመሩን አስታውቋል።
ይህ የሥልጠና ፕሮግራም የጋዜጠኝነት ምንነት፣ ዜና፣ የቢዝነስ ዘገባ፣ ቃለ መጠይቅ፣ የጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባርና የብዙኃን መገናኛ ሕጎች፣ የማስታወቂያ ሥራ፣ የምርመራ ጋዜጠኝነት፣ ሚዲያ ሳይኮሎጂ፣ የሬዲዮና ቴሌቪዥን ፕሮግራሞች አዘገጃጀት እንዲሁም ዲጂታል ጆርናሊዝምን ያካተቱ ዋና ዋና ይዘቶች ያሉት ሲሆን፣ ምዝገባውና ሥልጠናው የሚከናወነው «ሃያ ሁለት» በተባለው ቦታ እንደ ሆነ አሳውቀዋል፡፡
የምዝገባ ሰዓቱ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ በሥራ ሰዓት ሲሆን፣ የሥልጠናው ፕሮግራም ደግሞ ቅዳሜ ከሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን (ረፋድ) እንዲሆን ተመቻችቷል፤ ፍላጎት ያላቸው አካላትም በስልክ ቁጥሮች 0974641213፣ 0960056369 ወይም 0965194242 ደውለው መመዝገብና መረጃ ማግኘት እንደሚችሉ አሳውቀዋል ተብሏል፡፡
ይምጡ ከሕልምዎ ይወዳጁ
ከፍታ 'ለልብዎ መሻት!"
ከፍታ የጋዜጠኝነት ሥልጠና ምዝገባ ከሰኔ 2 ጀምሮ መጀመሩን አስታውቋል።
ይህ የሥልጠና ፕሮግራም የጋዜጠኝነት ምንነት፣ ዜና፣ የቢዝነስ ዘገባ፣ ቃለ መጠይቅ፣ የጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባርና የብዙኃን መገናኛ ሕጎች፣ የማስታወቂያ ሥራ፣ የምርመራ ጋዜጠኝነት፣ ሚዲያ ሳይኮሎጂ፣ የሬዲዮና ቴሌቪዥን ፕሮግራሞች አዘገጃጀት እንዲሁም ዲጂታል ጆርናሊዝምን ያካተቱ ዋና ዋና ይዘቶች ያሉት ሲሆን፣ ምዝገባውና ሥልጠናው የሚከናወነው «ሃያ ሁለት» በተባለው ቦታ እንደ ሆነ አሳውቀዋል፡፡
የምዝገባ ሰዓቱ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ በሥራ ሰዓት ሲሆን፣ የሥልጠናው ፕሮግራም ደግሞ ቅዳሜ ከሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን (ረፋድ) እንዲሆን ተመቻችቷል፤ ፍላጎት ያላቸው አካላትም በስልክ ቁጥሮች 0974641213፣ 0960056369 ወይም 0965194242 ደውለው መመዝገብና መረጃ ማግኘት እንደሚችሉ አሳውቀዋል ተብሏል፡፡
ይምጡ ከህልሞ ጋር ይወዳጁ
የጋዜጠኝነት ሥልጠና ምዝገባ ከሰኔ 2 ጀምሮ መጀመሩን አስታውቋል።
ይህ የሥልጠና ፕሮግራም የጋዜጠኝነት ምንነት፣ ዜና፣ የቢዝነስ ዘገባ፣ ቃለ መጠይቅ፣ የጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባርና የብዙኃን መገናኛ ሕጎች፣ የማስታወቂያ ሥራ፣ የምርመራ ጋዜጠኝነት፣ ሚዲያ ሳይኮሎጂ፣ የሬዲዮና ቴሌቪዥን ፕሮግራሞች አዘገጃጀት እንዲሁም ዲጂታል ጆርናሊዝምን ያካተቱ ዋና ዋና ይዘቶች ያሉት ሲሆን፣ ምዝገባውና ሥልጠናው የሚከናወነው «ሃያ ሁለት» በተባለው ቦታ እንደ ሆነ አሳውቀዋል፡፡
የምዝገባ ሰዓቱ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ በሥራ ሰዓት ሲሆን፣ የሥልጠናው ፕሮግራም ደግሞ ቅዳሜ ከሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን (ረፋድ) እንዲሆን ተመቻችቷል፤ ፍላጎት ያላቸው አካላትም በስልክ ቁጥሮች 0974641213፣ 0960056369 ወይም 0965194242 ደውለው መመዝገብና መረጃ ማግኘት እንደሚችሉ አሳውቀዋል ተብሏል፡፡
ይምጡ ከህልሞ ጋር ይወዳጁ
ጊዜ አይሄድም
በቅርብ ቀን እኔም ጓጉቻለው የማን ይሁን አልበም ወይስ ነጠላ ዜማ?
እኔ ወድጄው ከ እናተ እኩል በድጋሚ ናፈኩት
ይጠብቁ
ዲኑዬ መልካም ልደት ይሁንልሽ
ከድምፃዊት ዲና አንተነህ ጋር ዋጋዬ የተሰኘ አዲስ አልበም ለማውጣት አዲስ አበባ መጥታ ነበር፡፡ በጥቂት ሰዓት ውስጥ ከሰዎች ጋር ያላት ተግባቦት ይገርማል፡፡ ገና ስተዋወቃት ፈግታዋን ሁሉ ለመተዋወቅ ይጋብዛል፡፡ ዲኑ ሁሌም እንደ ሳቀች ነው፡፡
ተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ
Repost from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1
አርቲስት ሰላማዊት ደስታ ስትታወሰ
ተመስገን ኡካሬ
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
ግጥም እና ዜማ፡ ነባ
ቅንብር፡ዮሲያስ አድማሱ
ስልት፡ሶፋቲ ሮክ (ቀለል ያለ ሮክ)
አልበም፡እንደ ልጅነቴ
"የምወድሽዋ ዘውድ የንግስና
ይብቃሽ እሺ በይ ነይ የበዛ ስቃዬ"
- እዮሲያስን ተቀበሉት አዲስ አቀናባሪ ነው❤️
ይድረስ ለድምፃዊ ነባ (እንደ ልጅነቴ)
(ከተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ)
ፀጥ ብለው (ያለ ትልቅ ማስታወቂያ) የሚለቀቁ አልበሞች ሲጣፍጡ፤ የግዝፈታቸውን ልክ እንድንለካና "ይሄስ እንዴት ተሰራ?" ብለን በረቅቅ መንገድ እንድንመረምርና እንድንጠይቅ ያስችሉናል።
ሰሞኑን ይህንን "ልጅነቴ" የተሰኘውን አልበም ደጋግሜ ስሰማው ነበር። የወደድኳቸውን ነጥቦች ከማንሳቴ በፊት አንድ ነገር ልበል፤ የተረጋጋ መንፈስ ይዛችሁ የምትመርጡበትን ዕድል የሚሰጥ፣ የሙዚቃን እውነተኛ መንገድ እንድትፈትሹ የሚጋብዝ እና ጆሮዋችሁን የምታሰለጥኑበት አልበም ቢኖር በዚህ አይነት መንገድ የተሰራው ነው።
ድምፃዊ ነባ የመጀመርያ አልበሙን ለሕዝብ ሲያደርስ መጠነኛ መተዋወቅ የተደረገለት እንጂ የጎላ የሚዲያ ጋጋታ እንዳልነበረበት ያስታውቃል። በዚህም ምክንያት፣ በአሁኑ ሰዓት የሰሚው ጆሮ የሰለጠነ በመሆኑ፣ መርጦና አድምጦ እንዲቀበለው ዕድልና አማራጭ የሰጠበት ይመስለኛል። በ16 የሙዚቃ ስራዎች (ክሮች) ውስጥ የተካተቱት የተለያዩ ዘውጎችና የሙዚቃ እሳቤዎች አድማሳችንን እንድናሰፋ ያደርጋሉ። እንዲሁም ድምፃዊው ነባ የሌሎች ድምፃውያንን ስራዎች ሲጫወት የኖረበትን የሙዚቃ ጉዞ፣ አሁን ወደ ራሱ ማንነት እንዴት እንዳመጣው በግልፅ እንድናይ ያደርገናል። ከእነዚህም ውስጥ የወደድኳቸውን ነጥቦች ልጠቁማችሁ…
* Non-Dependent on the Arrangement (በቅንብር ላይ ያልተደገፈ ሙዚቃ)፦ አንዳንድ ሙዚቃዎችን ስትሰሙ፣ ለድምፃዊውና ለቅንብሩ መመጣጠን እንዳለ ሆኖ፣ የሥራውን ትልቅነት (ግዝፈት) በደንብ የምናየው በድምፃዊው የድምፅ ብቃት ደረጃ ነው። ይህ ደግሞ የራሱን መተማመንና የብቃት ልክ ለመመዘን ያስችላል። ከመግቢያው እስከ መውጫው ያለው የሙዚቃ መሣሪያዎች አጫዋወት ከተወሰኑ የፈጠራ ስራዎች ውጪ፣ የድምፃዊው የድምፅ ጉልበትና ምጥንነት በጉልህ ጎልቶ የታየበት ነው፡፡
* Emotional Music (ስሜት የሚኮረኩር ሙዚቃ)፦ ሁሉም ሙዚቃዎች እውነታን ያዘሉ እስኪመስሉን ድረስ በተመስጦ እንድንሰማቸው ያደርጉናል። ቀድሞ ልባችንን አግኝተው ከሐሳባችን ጋር እንድንጓዝ ይጋብዛሉ። ከአጀማመሩ እስከ ማጠቃለያው የአንድን ሰው ሐሳብ በበጎ መንገድ መማረክ (መስረቅ) ትልቅ መታደል ነው፤ የዚህ አልበም አንዱ ጥንካሬ ይህንን መንገድ የተከተለ መሆኑ ነው።
* Acoustic and Reggae (አኮስቲክ እና ሬጌ)፦ ሁለቱም በሙዚቃ ዘውግነታቸው ከፍ ያሉና የራሳቸውን ጉልበታማ ስሜት የሚፈልጉ ናቸው። ድምፃዊው ድምፁን ያሟሸው በእነዚህ የሙዚቃ ቴክኒኮች እንደሆነ የሚጠቁሙ ድንቅ የድምፅ አጠቃቀሞች አሉት። የመጣበትን የሙዚቃ መንገድ በአልበም ደረጃ ማሳየት ደግሞ "ራስን ሆኖ እንደ መቅረብ" ይቆጠራል። በራስ ዓለም ውስጥ መሆንና መኖር፣ የራስ የምንለውን አድናቂና ደጋፊ እንድናፈራ ያደርጋል፤ ይህ አልበም ያንን ታስቦ የተሰራ ይመስለኛል።
* Creative Lyrics and Content (የግጥምና የይዘት ፈጠራ)፦ የአንድ አልበም ዋነኛ ቁመና የፈጠራ ጥበቡና ግጥሙ ተሰባስበው ገና ያልተወለዱ (አዳዲስ) ሐሳቦችን ማሻገርና ልዩ ችሎታን መፍጠር መቻላቸው ላይ ነው። ይህንን ድምፃዊው በሚገባ አሳክቶታል ማለት ይቻላል። "አዋቂ" እና "የምወድሽዋ" የተሰኙትን ሙዚቃዎች በማዳመጥ ብቻ ለዚህ ምክንያቶቼ ግልፅ ይሆኑላችኋል።
* Sound Flavor (የድምፅ ጣዕምና ቀለም)፦ በድምፃዊ ነባ ላይ የሚገርማችሁ ነገር፣ በብዙ ሰዎች ላይ የማይታየውንና እሱ ላይ በጉልህ ያስተዋልኩትን "ስሞኪ" (Smoky) ወይም "ሸካራ" ብለን የምንጠራውን አይነት የድምፅ ከለር መያዙ ነው። ገና ሙዚቃው ሲጀምር ድምፁ የማን እንደሆነ ወዲያውኑ ሰሚው እንዲለየው የሚያደርግ መለያና መታወቂያው የሆነ ድምፀት አለው። ከእነዚህም ውስጥ ይበልጥ የወደድኳቸውን ሙዚቃዎች ልጠቁማችሁ፦
አወይ ሰውነቴ (ሬጌ)፦ እያንዳንዱ ሰው በዚህች ምድር ሲፈጠር ችግሩንም ሆነ ድሎቱን እንዲያይ በነፃነትና በንፅህና ይፈጠራል። ጊዜውን ሲጨርስ ደግሞ በነፃ የተረከበውን ሰውነት፣ የመጣበትን ዘላለማዊ ዳኝነት ጠብቆ በንፅህና ይጓዛል። ሙዚቃው ያንን ጠቁሞ ማሰሪያውና መፍትሄው ፍቅር መሆኑን ያሳየናል።
"ሳሰላስል በቀን በቀን አንዱን ይዞ ሌላውን ስመዘን አወይ ሰውነቴ አወይ ሰውነቴ እኔነቴ..." (ግጥምና ዜማ፦ ነባ | ቅንብር፦ ሚኪያስ ሞገስ)ኑሪ በፈገግታ (አኩስቲክ)፦ ሙሉ በሙሉ በዚህ ቅርፅ የተሰራው ይህ ሙዚቃ ፍቅር ነፃነትን እንደሚሻ ያሳያል። ድንበር ጥሶ የልባችንን መሻት በምኞት ይገልፃል። ላብ የሚያጠምቀውን ሰውነት ማዘለል ሳይሆን የልባችንን ሐሴት ማፍካት ነው። ሙዚቃውም ያንን ይጠቁማል፤ ልክ ሲጀምር ዜማው ከፍካት ነው የሚነሳው።
"አለኝ ሌላ ፀሎት አለኝ ሌላ ጥድፊያ ባላይ የሷን ብሶት፣ ባላይ የሷን ኩርፊያ ኑሪ በፈገግታ ሁልጊዜ ደስታ..." (ግጥምና ዜማ፦ ነባ | ቅንብር፦ ዮሲሳ አድማሱ እና ነባ)ቀሪዎቹን "ዋጋዬ"፣ "መውጫ"፣ "ትንሽረጋ"፣ "ኳስ ሜዳ" የመሳሰሉትን ድንቅ ስራዎች እንድታዳምጡ እጋብዛችኋለሁ። በሚኪያስ ሞገስ፣ ዮሲሳ አድማሱ፣ አቤነዘር መሳይና በመሳሰሉት የሙዚቃ ባለሙያዎች በአልበሙ ላይ ተሳትፈዋል። ሁላችሁንም እናመሰግናለን! ይድረስ ለድምፃዊ ነባከተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ
Repost from Arada FM 95.1 Digital-አራዳ ኤፍኤም ዲጂታል
አንጋፋው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
ግንቦት 24፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በኢትዮጵያ የጥበብ ዘርፍ በተለይም በውዝዋዜ፣ በኬሮግራፈርና በትወና ዘርፎች ላይ ደማቅ አሻራውን ያሳረፈው አንጋፋውና ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ሁለገቡ ጥበበኛ ባደረበት ህመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ60 ዓመቱ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ነው ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው።
ለበርካታ ዓመታት በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ እንዲሁም በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት በውዝዋዜ አሰልጣኝነትና ኬሮግራፈርነት ያገለገለው ይህ ሁለ ገብ አርቲስት፥ ባህላዊ ውዝዋዜዎችን በማጥናትና በማበልጸግ የኪነጥበብ ሙያ አሁን ለደረሰበት ከፍታ ትልቅ አስተዋጽዖ ያበረከተ የሀገር ባለውለታ ነበር።
የአስከሬን ሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሐ ግብሩ የኪነጥበብ አጋሮቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ነገ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ይካሄዳል።
ተጨማሪ ለማንበብ https://web.facebook.com/share/p/1HVUp5sERp/
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
Repost from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1
የኔዜማ የአድማጮች የሙዚቃ ምርጫ ዘወትር እሁድ ከ 3:00-5:00 በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 ይደመጣል፡፡
ለዛሬ የመረጥነው ሙዚቃዎች…
-ጥላሁን ገሰሰ (ኢትዮጲያ)
-ተዓምር ግዛው (ምነዋ)
- ፀጋዬ እሸቱ(አንቺ ቅናተኛ)
-ሕብስት ጥሩነህ(ተጣልተናል ወይ?)
የዛሬ የመረጥናቸው ሙዚቃዎች ላይ ከተለያዩ ቦታ አድማጮች እየተሳተፋችሁ
ለወዳጅ ፣ ለዘመድ ፣ ለፍቅር አጋሮ በቀጥታ መስመር እየገባችሁ መጋበዝ ትችላላችሁ፡፡ ስልኮቻችን 011 5 58 54 31 ወይም 011 5 58 54 32 ይደውሉ፡፡
አዘጋጅ እና አቅራቢ፡-ተመስገን ኡካሬ
Repost from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1
'አቧራው ጨሰ' አዲስ የኮሜዲ ቴአትር በዓለም ሲኒማ ይታያል
ግንቦት 20፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በሀገራችን የኪነ-ጥበብ መድረክ ልብ አንጠልጣይና የሳቅ ማዕበል የተሞላበት የተባለለት አዲስ የኮሜዲ ቴአትር ለዕይታ ዘወትር አርብ በዓለም ሲኒማ ለዕይታ ይበቃል።
'አቧራው ጨሰ' የተሰኘው ይህ አዲስ ቴአትር በሱራፌል ብስራት የተደረሰ ሲሆን፣ በጎበዙ የመድረክ አዘጋጅ አቤል ሰለሞን አማካኝነት ለታዳሚ በሚመጥን መልኩ ተሰናድቷል።
ቅድስት ገብረ ስላሴ፣ ቃልኪዳን ታምሩ፣ ሱራፌል ብስራት እና አቤል (የወይንዋ ልጅ) በጋራ በመሆን ልዩ የትወና ብቃታቸውን ያሳዩበታል።
ሳምንቱን በሳቅና በፈገግታ ለመታደም ለሚሹ የጥበብ አፍቃሪያን ሁሉ የቀረበው ይህ ድንቅ ቴአትር፣ ዘወትር አርብ አመሻሽ 12፡00 ሠአት ጀምሮ በዓለም ሲኒማ ለታዳሚዎች ይቀርባል።
ተመስገን ኡካሬ
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
+3
🔥 WINNER FASHION 🔥
ኦርጂናል ጫማዎችን በቅናሽ ዋጋ
Call : 0923047173/ 0913194910
Inbox : @DAMFIS
https://t.me/winnerfashion
https://t.me/winnerfashion
https://t.me/winnerfashion
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
