የኔ ዜማ የአድማጮች የሙዚቃ ምርጫ
前往频道在 Telegram
- በፌስቡክ👇 https://www.facebook.com/100022318509408/posts/1859085851512014/?app=fbl https://www.facebook.com/share/1AMgudXhJr/ - በቴሌግራም ገፅ👇 https://t.me/biggrs - ቲክቶክ ገፅ 👇 tiktok.com/@temesgen_ukare - በዩትዮብ ተከታተሉን👇 https://youtube.com/@temuyehag
显示更多276
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
-230 天
帖子存档
"የውስጤን ማንነት እኔን ይጠይቃል
ሁሌ መልስ ወደ አለው ወጥቶ ይፈልጋል"…
ድምፃዊት ሄቨንሊ ትባላለች ለሙዚቃው ኢንደስትሪ አዲስ ድምፃዊ ናት ከባባድ ሐሳቦችን ይዛ የመጀመርያ ነጠላ ሙዚቃ "ለምን?" የተሰኘው ለራሷ የዩትዮ ገፅ አድርሳለች፡፡
ዓለምን በተረዳችሁ ልክ በልጅነት አይምሮ ገልፃለች፡፡ ብዙ ገርመውን የማያበቁ ሐሳቦች በአዲሱ ትውልድ ውስጥ ይፀባረቃሉ ፣ የውስጥን ለመግለፅ በተመቻቸው የማህበራዊ ገፅ ላይ ራሳቸውን ያሳያሉ ይፈትሻሉ፡፡ ኤደንም እንዲያ ናት፡፡
በአራዳ ኤፍኤም 95.1 ላይ እንዳ ሆኖ ብዙ ተጨዋውተናል፡፡ በቅርብ ቀን ይጠብቁ፡፡
https://youtu.be/W-_0ckQZq_s?si=IhlACbGMrUbxj05O ለምን የተሰኘው ሙዚቃ አዳምጡት
ተመስገን ኡካሬ
(ብልዝ እና አህመድ ተሾመ ልካቸው ይሄ ነው)
አይበለው -ና
አሁንማ ሎሌሽ በዝቶ
ያሳለፍነው ያ ሁሉ ቀርቶ
ከፋኝ ሳይዘንብ ሰው ደመነና
መተያየቱ በሩቅ ሆነና
የልብ እንባ ልቤ ቢያነባም
በሳቅሽ ቤት ሀዘን አይገባም
ግጥም፡ወንደሰን ይሁብ
ዜማ፡አህመድ ተሾመ ዲንቢ
ቅንብር፡ታምሩ አማረ
መነሻ ሁሳብ፡ቴዎድሮስ ፀጋዬ
አንድ ሀሳቦች ፈቅለውን እንዲህ ያስነቡናል🥹
Repost from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1
+1
ድምጻዊ ልጅ ሚካኤልና ድምጻዊት ቬሮኒካ አዳነ ለዘንድሮው አፍሪማ ሽልማት ታጩ
ሐምሌ 8፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የአፍሪካ ሚውዚክ ሜጋዚን አዋርድ ወይንም አፍሪማ ለሁለት ዓመታት ከተቋረጠ በኋላ ዘንድሮ እንደገና እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡
ይህ ውድድር በ34 ዘርፎች የሚከናወን ሲሆን እጩዎቹ በዛሬ እለት ይፋ ተደርገዋል፡፡
በዚህ መሰረት የዓመቱ የምስራቅ አፍሪካ ምርጥ ወንድ አርቲስት በሚለው ዘርፍ ልጅ ሚካኤል በእጩነት የቀረበ ሲሆን ምርጥ የዓመቱ የምስራቅ አፍሪካ ሴት አርቲስት በሚለው ዘርፍ ደግሞ ቬሮኒካ አዳነ በእጩነት እንደ ተካተተች ተገልጿል፡፡
የ2026 አፍሪማ አሸናፊዎች ይፋ የሚሆኑት የፊታችን መስከረም 12 ቀን 2026 በአሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ከተማ በሚከናወን ፕሮግራም ይሆናል፡፡
መራጮች ለተወዳዳሪዎቹ ከዛሬ ጀምሮ አፍሪማ ድረ ገፅ ላይ መምረጥ ይቻላሉ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በአፍሪካ ህብረት ድጋፍ የሚከናወነው ሌላኛው አፍሪማ የተሰኘው ሽልማት እንደሚኖር ተጠቁሟል፡፡
ተመስገን ኡካሬ
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
Repost from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1
ድምፃዊ አህመድ ተሾመ አዲስ አልበም ሊለቅ ነው
ሐምሌ 7፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) ድምፃዊ፣ የዜማ ደራሲና ሙዚቃ አቀናባሪ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ሶስተኛ የሙዚቃ አልበም ሐምሌ 10 ቀን እንደ ሚያለቀቅ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
የድምጻዊ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ሦስተኛ አልበም ‘ጊዜ አይሄድም’ 13 የሙዚቃ ስብስቦችን የያዘው ሲሆን፥ ድምፃዊው ከ13 ዓመታት በኋላ ከአድማጮች ጋር የሚገናኝበት ሥራው ነው።
ግጥምና ዜማ አሰናጅነት ናትናኤል ግርማቸው፣ ምልዕቲ ኪሮስ፣ ከድር አሊ፣ አቡዲ፣ ወንድወሰን ይሁብ የተሳተፉ ሲሆን፥ በሙዚቃ ቅንብር ሚካኤል ኃይሉ፣ ታምሩ አማረ እና ፋኑ ጊዳቦ እና ሌሎችም ተሳትፈውበታል።
አልበሙ ስለ ሀገር ስለ ፍቅር ፍልስፍናዊ ጉዞ ያሉ ሁለት ተቃራኒ ሐሳቦችን በአንድ ላይ የያዘ ሲሆን፥ በሙዚቃ ቅንብሩ አዳዲስ ጣዕም ያላቸው ሥራዎች ተካተውበታል ተብሏል።
ድምጻዊ አህመድ ተሾመ ከዚህ ደቀም ‘እዮሪካ’ እና ‘ኦሜርታ’ የተሰኙ አልበሞቹን ከዓመታት በፊት ለአድማጮች ማድረሱ ይታወሳል።
ድምፃዊው ከራሱ ሥራዎች በተጨማሪ ለፀሐዬ ዮሐንስ፣ ማዲንጎ አፈወርቅ፣ አሊ ቢራ፣ ሀይማኖት ግርማ፣ ሀመልማል አባተ፣ ታረቀኝ ሙሉ፣ ዘቢባ ግርማና ሌሎች በርካታ አንጋፋና ወጣት አርቲስቶች የዜማ ሥራዎችን በመሥራት የሙዚቃ ዓለም ውስጥ የራሱን የጎላ አሻራ አስቀምጧል።
ተመስገን ኡካሬ
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
ይህንን የድምፃዊት አስቴር አወቀ "ገላገላ" አልበም የምን አትተቸውም ብላቹ ጠይቃችሁኛል፡፡ በብዙ ሚዛን መመዘን አለብን… ጅምሬው የሚጀምረው የሙዚቃ አልበም ማስተዳደር ላይ ነው ያን አጥንታችሁት ይሁን?ሊደቱስ በምን ደረጃ እያደገ መጣ? የትውልድ ጉራ ልየታ የቱ ጋር ነው?
በቅርቡ ጠብቁ ጠንከር ያለ ትችት እና ሚዛናዊ የአልበም መልክ
Repost from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1
የኔዜማ የአድማጮች የሙዚቃ ምርጫ ዘውትር እሁድ ከ 3:00-5:00 በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 ይደመጣል፡፡
ለዛሬ የመረጥናቸው ሙዚቃዎች
-ድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ (ቻልኩት)
-ድምፃዊ ታምራት ደስታ(ሰው መክሮሽ)
-ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋ(እሱ ያለ ቀን)
-ድምፃዊት ኤደን አሸሹም(ፈራ ተባ)
ከተለያዩ ቦታ አድማጮች እየተሳተፋችሁ ለወዳጅ፣ለዘመድ፣ ለፍቅር አጋርዎ በቀጥታ መስመር እየገባችሁ መጋበዝ ትችላላችሁ፡፡
☎️ስልኮቻችን 011 5 58 54 31 ወይም 011 5 58 54 32 ይደውሉ፡፡
አዘጋጅ እና አቅራቢ፡-ተመስገን ኡካሬ
"ክረምቱን በናዝሬት በአዳማ ከተማ
ምሽት ለእግር ጉዞ የምትወጣው ቀድማ
በፍቅረኞች መንገድ ነበር የማገኛት
ያኔ ለህረፍት በክረምቱ
ነው ብዬ ዘግይታ ስንቱን ቀን ጠበኳት ብረዱኝ ችዬ በምሽቱ"…
በልጅነታችን በአፍላ አይምሮ "ዲንቢ ለዲንቢን" በክረምቱ ስንጫወት ጨዋታው ያሰባስበናል በዝናብ በካፍያው እየተመታን ሳንጠለል ከጓደኞቻችን ጋር ሆነን የማይረሳ ትዝታን ዘርተናል፡፡
ዛሬ አሰብ አረግንና ልጅነታችንን እና አህመድ ተሾመ (ዲንቢ)ን ፍለጋ ተጠያቂ ናዝሬት ብለህን በፍቅር ጣታችንን ስንጠቁም እሱም በሶስተኛ አልበሙ ተከሰተ
እውነትም "ጊዜ አይሄድም" ሲል መጥቷል፡፡ የጉብዝናን ጥንካሬ የካበ የዙ ጊዜ ቆይታውን ለበጎ መሆኑን የነገረን ነው፡፡ ዲንቢዬ ልፍትህን አውቀዋለው እንኳን ለዚህ በቃህ በርካታ ባለሞያተኞች እንደ ተሳተፉ አውቃለው ሀምሌ 10 ከዝናብ ካፍያ ሳንጠለል ወደ ልጅነታችን ተጎዘን አልበምህን ለማዳመጥ ተዘጋጅተናል፡፡
"ክረምቱን በናዝሬት በአዳማ ከተማ
ምሽት ለእግር ጉዞ የምትወጣው ቀድማ
ምነው ዘንድሮ ላይ ለዓይኔ ተከለለች
ተጠያቂ ናዝሬት ያቺ ልጅ የታለች"❤️
መልካም እድል ዲንቢዬ ጓደኛዬ ከተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ
Repost from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1
የቅዳሜን በአራዳ እንግዳ
ድምፃዊት ብስራት ተክሉ(ዶናት) "ዓሀዱ" የተሰኘ የመጀመሪያ የሙዚቃ አልበም ለአድማጮች አድርሳለች።
በርካታ ጉዳዮችን በተመለከተ ከጣቢያችን ጋር ቆይታ አድርጋለች ቅዳሜን በአራዳ የመዝናኛ ፕሮግራም ክፍል አንድ በዛሬው እለት ከስድስት እስከ ስምንት ሠአት በሚተላለፈው ፕሮግራም ጠብቁን፡፡
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
ይድረስ ለድምፃዊት ቤቴልሄም ሸረፈዲን
(ከተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ)
ለጋ በሆነ ዕድሜ ውስጥ በድምፃዊቷ ልክ የተሰፋ፣ በብዙ መልክ የተዋደና ዕድሜን ያማከለ፣ በመቀጠልም የአስተሳሰብ በደራሽነት ማረፊያውን አግኝቶ የተሰራ የሙዚቃ አልበም ነው፡፡ የሁለት ሰዎች ጥበብ ቅርሳቸውን ማስቀመጥ፤ አንዱ በግጥም እና በዜማ ሸብ አድርጎ ሲይዘው፣ ይህንን ሥራ በቅንብር መደገፍ የዚህ አልበም አንዱ ትልቅ ጥንካሬ ነው፡፡
የአሁኑ ትውልድ ፈጣን ነው፤ አዲስ እና ያልበረዱ ሐሳቦችን ማድረስ ይሻል፤ ከዘመኑ ጋር ፈጥኖ መገኘትን ይመርጣል፡፡
ዘመኑ መሸሽን ሳይሆን መጋፈጥን ይወዳል፤ ለወጣት ጆሮ ተስማሚውን የሙዚቃ ጣዕም ለማሰማት ሌት ከቀን ይደክማል፡፡ "ደስተኛ" የተሰኘውን አልበም የሰሩ ሰዎች በትክክልም እንዲያ ናቸው፡፡
*Identity of Betelhem Sherefedin (የቤቴልሔም ማንነት)ከዚህ በፊት ከምትሰራቸው የሙዚቃ ሥራዎቿ ተለይቶ ለመውጣት እና አዲስ ቀለም ለመፍጠር የአራት ዓመት ድካም መሆኑን ያስታውቃል፡፡ በተለያዩ የሙዚቃ ቅርጾች (ዘውጎች) ውስጥ ራስን ሆኖ ማዜም ከብዙኃኑ ለጥቂቶች ብቻ የሚሰጥ ጸጋ ነው፡፡ በእለቱ የሚሰራውና ያልቆመው የጉሮሮ ሥልጠና፣ በአዲስ ማንነት ለመገለጥ የለፋችበት መሆኑን ያሳያል፡፡ ለዚህም ማረጋገጫ "አካልዬ" እና "ልቤ" የሚሉትን ሙዚቃዎች ማየት በቂ ነው፡፡
*Idea / Target (የሐሳብ ዓላማ)በሕይወት ጉዞዎቿ ሁሉ የሚመላለሱ የሕይወት ገጽታዎች አሉ፤ ከራሷ የሕይወት መስመር በተጨማሪም በእሷ ዕድሜ ያሉ ወጣቶች የሚያጋጥሟቸውን የሕይወት ውጣ ውረዶች የተረከ ሥራ ነው ማለት እንችላለን፡፡ በይበልጥ ወደ ኋላ አልተጓዘም፤ የፊትንም አብዝቶ አልተነበየም፤ መሃል ላይ ባለው የአሁን ሰዓት ላይ በራሷ ዓለም ላይ ሌላ ዓለም ፈጥራለች። "ቻው" እና "ና ጌታዬ" የሚሉትን ሙዚቃዎች ማዳመጥ ያሻል፤ እነዚህ ሥራዎች በቅርበት የድምፃዊቷን እሳቤ በአጠረችው የዕድሜ ክልል ውስጥ እንድንረዳት ያስችሉናል፡፡
* Arrangement Concept (የቅንብር መልክ)የአንድ አልበም ትልቁ ቅርስ የተለያዩ የሙዚቃ ቅንብሮችን ሰርቶ ማቅረብ ነው፤ ልክ እንደ ቡፌ አይን አዋጅ አድርጎ መሥራት ያስፈልጋል፤ ምክንያቱም የተለያየ ምርጫ ያለው ሰው ስለሚያዳምጠው የወደደውን ይመርጣል፡፡ ይህ አልበም የተለያየ መልክ አለው፤ ድምፃዊቷን ባልለመድናት "ዣንራ" ወይም "የሙዚቃ ዘውግ" አይተናታል፡፡ ብሉዝ፣ ሬጌ፣ ፈንክ የሙዚቃ ስልቶችን መመልከት ለዳኝነት ወይም ሐሳብ ለመስጠት ያመቻል፤ በእነዚህም ስኬታማ ነበሩ ማለት ይቻላል፡፡
*Nati and Tameru's Hard Work (የናትኤል ግርማቸው እና የታምሩ አማረ ጠንካራ ሥራ)በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ ለአንድ ድምፃዊ ሁለት ሰዎች በጋራ ፕሮዲውስ ማድረጋቸው (ማዘጋጀታቸው) ያልተለመደ ነው፡፡ አንዱ በግጥም እና በዜማ አብስሎ መቅረጽ፣ ሌላው በስቱዲዮ ቆይታ ውስጥ የቅንብር ፍሰቱን ከተሰሩት ግጥሞች እና ዜማዎች ጋር ማስተሳሰር አንዱ ዓላማ ነበር፡፡ ደግሞም በትክክል አስበውበት እንደሰሩት ያስታውቃል፤ በተጨማሪም ነፍስ ያለው ነገር ለመሥራት አብሮ መሆን እንደሚያስፈልግ የታምሩ እና የናቲ "እጅና ጓንት" መሆን ቤቴልሔምን በሚገባ ሰርቷታል ማለት ይቻላል፡፡
*Voice of This Generation (የትውልድ ድምፅ)በብዙ መልኩ የትውልድ ድምፅ ይኮናል፤ ስሜቶቻችን ከዘመኑ ጋር እንዲዋሃዱ ማጥናት እና ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ የዚህ ዘመን ወኪል ሆኖ ማዜም ለትውልዱ ያላትን ከፍተኛ የማወቅ ጥግ ለመመልከት የሄደችበትን ርቀት ያሳያል፡፡ በፍቅር ለደከመው ብርታት ስትሰጥ "ና ጌታዬ" እያለች ትጣራለች፤ ለልብ ዕረፍት እንዲሰጠንና ከዚያም በዓለም ወዳጅ እንዳንጠፋ ለመናገር "ተገኘ" ስትል ትገልጻለች፡፡ ከዘፈኖቹ መካከል የወደድኳቸውን ላንሳላችሁ፡፡
*አካልዬ (ብሉዝ)፦ በናፍቆት እና በተስፋ መካከል የሚዋልል ፍቅር ያጠነከረው፣ በፍቅር ታላቅነት ለተገነባው ልብ እና ቤት፣ በተጨማሪም ደብዝዞ ያልጠፋ ማንነትን ተሸክማ ትማጸናለች፡፡ በአዲስ ማንነት ለመላበስ ፈውስን የምትሻ የምስኪን ሴት ገጸ-ባህሪን የተሸከመ ሥራ ነው፡፡
"ከእጄም ባላዞራት፣ እንደ ሸክላ ሰሪ ውብ ገላ አይደለች ወይ ዓለም ተሰባሪ እንደ ፀሐይ እንደ ፀሐይ ልብን የሚያሞቀው መድኃኒት አይደል ወይ ተስፋ ለጨነቀው"
ግጥም፡ ናትናኤል ግርማቸው | ዜማ፡ ምህረትአብ ደስታ | ቅንብር፡ ታምሩ አማረ (ቶሚ)
*ልቤ (ፈንክ)፦ ቀጠሮ የሚያስቀር ፍቅር… ይህ ሙዚቃ የቤቴልሔም ሸረፈዲንን የሙዚቃ ቅርጽ የተፈታተናት ነው ማለት ይቻላል፡፡ በአፍላ ፍቅር ውስጥ ባሉ ሰዎች ዘንድ የሚሰማ ዓይነት ስሜት ነው፡፡ በፍቅር ውስጥ ፈራ ተባ ያለ ስሜት፣ ጥሎ ለመሄድ አስቸጋሪ ሆኖ ልቧን ሰርቆ ለሄደ ሰው በአደባባይ እሱን ለማግኘት ማስነገርና በፍለጋ ውስጥ የሚዳክር ሕይወትን ያሳየችንበት ነው፡፡
"በመነን ጌጥ ጠልፈው፣ እንደ ሰሩት ሸማ አየሁት አካሌን ከገላህ ሲስማማ ይዞ አለቅም አለኝ እጅ አንገትህን ዞሮ እቅፍቅፍ አድርጌህ ቢቀርስ ቀጠሮ"
ግጥም እና ዜማ፡ ናትናኤል ግርማቸው | ቅንብር፡ ታምሩ አማረ (ቶሚ)
* ሸልመኝ (ችክችካ)፦ የአብሮነት ምኞት… የሚያዋድድ ንጹሕ ልብን መስጠትና መሸለም… ሞቅ ያለ ነገር ግን የራሱ ፍጥነት ካለው የሙዚቃ ቅንብር ጋር አስተሳስሮ ማዜም በራሱ ትልቅ ብልሃት ነው፤ ይህንንም ቤቲ አሳክታዋለች፡፡ በአብሮነት ውስጥ ፍቅር ይወለዳል፤ በግፊያ ውስጥም ብልሃትን ያሸልማል፡፡
"አንተዬ በመውደድ ላይ መውደድ በፍቅር ላይ ፍቅር እኔ አለሁኝ ይቅር ሆድዬ ለዚህ ለዚህማ፣ ለሐሳብ ጭንቀቱማ ይቅር አንዘልቅማ"
ግጥም፡ ናትናኤል ግርማቸው | ዜማ፡ ምህረትአብ ደስታ | ቅንብር፡ ታምሩ አማረ (ቶሚ)
"ባለቤቴ"፣ "አይታለፍም"፣ "እንዴት" የመሳሰሉ የሙዚቃ ስራዎች በዚሁ "ደስተኛ" አልበም ውስጥ ተካተዋል፡፡ ታምሩ አማረ (ቶሚ)፣ ናትናኤል ግርማቸው፣ ምህረትአብ ደስታ እንዲሁም ሌሎቻችሁም በዚህ አልበም ላይ ለተሳተፋችሁ ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳችሁ። ይድረስ ለድምፃዊት ቤቴልሄም ሸረፈዲን ከተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ፡፡
ድምፃዊት ራሄል ዮሐንስ ስትታወስ
"አዝማሪ ይሏታል ራሄል ሆዴነህ
አዝማሪ ይሏታል ጭንቄ ራሄልን
ልጆች ለማሳደግ ያረገችውን..."
ድምፃዊት ራሄል ዮሐንስ ሚያዚያ 27 ቀን 1939 ዓ.ም አዲስ አበባ ካዛንቺስ ግቢ ገብርኤል አካባቢ ተወለደች።
ለቤተሰቧ የበኩር ልጅ የነበረችው ራሄል፣ "ሃና ሃና" እያለ መላው ሀገሪቱን ካወዛወዘው ታናሽ ወንድሟ ድምፃዊ ሰይፉ ዮሐንስ ጋር በቄስ ትምህርት ቤት ፊደልን ቆጥረው አድገዋል።
በአስፋው ወሰን ትምህርት ቤት የአንደኛ ደረጃ ትምህርቷን የተከታተለችው ራሄል በልጅነቷ የበረራ አስተናጋጅ የመሆን ህልም ቢኖራትም፥ ዕጣ ፈንታዋ ሌላ ቦታ ወስዷት በታዋቂው ራስ ሆቴል የመስተንግዶ ስራን ጀመረች።
ቀጥላም በጊዮን ሆቴል ለሁለት ዓመታት የወይን መስተንግዶ ተምራ በዲፕሎማ ተመርቃ ከጥቂት "የወይን ስፔሻሊስቶች" አንዷ ሆነች።
ጉዞዋ ከመቀጠር ወደ መቅጠር፣ ከሰራተኝነት ወደ ጀነራል ማናጀርነት ከፍ ያለ ነበር፤ ሂልተን፣ ሸበሌ፣ ራስ ሆቴል፣ ጊዮን... አልፎ ተርፎም በአርጀንቲናና ታንዛኒያ ኤምባሲዎች ጭምር ሰርታለች።
ተጨማሪ ለማንበብ https://web.facebook.com/share/p/1BbzfTFTPn/
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
Repost from Arada FM 95.1 Digital-አራዳ ኤፍኤም ዲጂታል
ቅዳሜን በአራዳ እንግዳ
የድምፃዊ ነብዩ ኤልያስ (ነባ) የመጀመሪያ ያለው አልበም "እንደ ልጅነቴ" የተሰኘውን አድርሶናል፡፡
በአልበሙ ዙሪያ እና የኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንዱስትሪው በተረዳው ልክ አቅጣጫውን ጠቁሞናል፡፡
ይህን መሰናዶ በቅዳሜ በአራዳ እንግዳ ከስድስት እስከ ስምንት ሠአት በሚተላለፈው ፕሮግራም ላይ ይጠብቁን፡፡
Repost from Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1
ድምፃዊት ዶናት ተክሉ
ተመስገን ኡካሬ
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
ሰው እንዴት ሙዚቃውን እየሰማ ያለቅሳል፡፡🥹
(ቻው)የሚለው ሙዚቃ ስሙት ገፀ በሀሪውን ዳብሱት "እተጎዳህ ቻው ማለት ይከብዳል"🥹ምን ብታጠፋ ነው የሰውን ስሜት በሙዚቃ ይገለጣል🥹
"ያጓጓኝ ፍቅራችን አየሁኝ ሲያከትም
የሳሱለት ነገር ለካ አይበረክትም
ዛሬም ለበደልህ ላረከኝ ጣልጣል
ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል" ይላል🥹
ግጥም፡ናትናኤል ግርማቸው ዜማ፡ምህረት አብ ደስታ ቅንብር፡ ታምሩአማረ (ቶሚ) ሌላ ምን ልበል አመሰግናለው ወዳጆቼ
"ወጣት የነብር ጣት" ይለዋል ይሄ ነው፡፡
ጆሮዋችሁን ለማከም ይህ አልበም ቀርቦላችኃል፡፡
በቅርቡ ሙሉ ትንታኔ አቀርባለው ግን ታምሩ አማረ፣ ናትኤል ግርማቸው፣ ምረት አብ ደስታ እና ሌሎቻችሁን ልጆችን እንዴት መቅረፅ እንዳለባችሁ ታውቃላችሁ፡፡
መልካም እድል ቤቲሻ❤️
ይድረስ ለድምፃዊት ዶናት ተክሉ ከተመስገን ኡካሬ (የሐጌ ልጅ)
ይህንን አልበም ለመስማት ረጅም ጊዜ የጠበቅኩት ሲሆን፣ እንድጠብቅ ካደረጉኝ ምክንያቶች ቀዳሚው ከታላቁ የሙዚቃ ሰው ኤልያስ መልካ ጀምሮ እስከ ያምሉ ሞላ ድረስ ስራዎቹ እንዴት ተጠናቀቁ? የሚለው ጥያቄ ነበር። ከEP ከፍ ያለ፣ ከሙሉ አልበም ደግሞ ዝቅ ያለ ቅርፅ ያላቸው እነዚህ የሙዚቃ ስራዎች በውስጣቸው ትልቅ የጥበብ ስንቅ የያዙ ናቸው። በታላቁ ኤልያስ መልካ እጅ የተጀመረውንና በያምሉ የተጠናቀቀውን ይህንን አልበም ምን ጠግኖት ለዛሬ አበቃው? የኤልያስ የሙዚቃ ስራዎች የእድገት ደረጃዎች ቆይታ በኃላ "ዓሀዱ አልበም" ተብሎ ተለወጠ ወይስ በፊት ተሰርቶ እንደ ወይን እየጣፈጠ ቆይቶ ዛሬን ጠብቆ ወጣ? የግጥምና የዜማውን ውህድ ግብ በጥልቀት ለመረዳት አልበሙን በጥንቃቄ፣ በሚዛናዊነትና በሰላ ጆሮ ማዳመጥ የግድ ይላል።
አልበሙ ከአቀናባሪ ያምሉ ሞላ እጅ እንዲያይወጣ ለመቆጣጠር የተደረገው ጥረት፣ የሙዚቃ መንፈሱንና እስካሁን የመጣበትን የሙዚቃ ጉልበት በሚገባ ያሳየበት ነው። በእርግጠኝነት 15% የነበረውን የሙዚቃ ትርፍ ወደ 85% ለማድረስ ሌት ተቀን እንደተደከመበት ያስታውቃል። ይህ ጥረት ምን ያህል ተሳካ? ለሚለው መልስ የተረዳሁትን ነጥቦች በሚከተለው መልኩ አጠቃልላቸዋለሁ፦
አልበም ቁጥጥርና የሙዚቃ አረዳድ (Album Control & Music Understanding) በስቱዲዮ ቆይታ ውስጥ ብዙ ነገሮችን ሚዛናዊ ለማድረግ ትልቅ ልፋት ተደርጓል። የሌላን ሰው የጥበብ መስመር ተረድቶ ለማስቀጠል በራሱ መደጋገም የሚፈልግ ከባድ ስራ ነው። የአልበሙን ቅርፅ ጠብቆ ለማስኬድ በአቀናባሪ ኤልያስ እና በያምሉ ሞላ መካከል ባለው ሂደት ላይ ያምሉ በተወሰነ መልኩ "ነፃነት የተነፈገ" ይመስላል። የአንዱ የሙዚቃ ስራ ወደ ሌላኛው ሲያልፍ ልዩነቶች ቢኖሩም፣ የድምፅ ከለሩ በግልፅ ይታወቃል። በአጠቃላይ ይህ አልበም ያምሉ ነፃነቱን ያገኘበትም የተጨነቀበትም ስራ ሆኖ አልፏል።
የሐሳብ ጥንካሬ በግጥምና ዜማ ቅለት (Soft Lyrics & Melody, Hard Concept) የአልበሙ አንዱ ጠንካራና ልዩ መገለጫ፣ ለአድማጭ ሊተላለፍ የተፈለገው መልዕክት በቀላሉ እንዲደርስና እርስ በርስ የመታረሚያ ትስስር እንዲፈጥር ተደርጎ ግጥሞቹ ቀለል ተደርገው መሰራታቸው ነው። ይህንን በአልበሙ ውስጥ በግልፅ እንድንረዳው አድርጎናል። የብሌን ዮሴፍ የሙዚቃ ጥሞና የታከለበት መሆኑ እንዲሁም ድምፃዊቷ ለኤልያስ ያላትን አክብሮትና ፍቅር ከአድናቆት ባለፈ በግጥም ማስመስከሯ ለአልበሙ ሌላ ትልቅ ጉልበትና ስኬት ሆኖታል።
ኃላፊነት መወጣት (Responsibility) ይህ ረጅም ጊዜ የወሰደውን አልበም ዳር ለማድረስ የተኬደበት ርቀት ትልቅ መመዘኛ ነው። በሌላ በኩል በስምንቱ የሙዚቃ ስራዎች ውስጥ የአልበሙን ጥፍጥና በሚገባ ለማሳየት ተሞክሯል። ስራዎቹ ደርሰው ዝም የሚባሉ ሳይሆኑ፣ ደርሰው በልብ የሚሰሙ ሆነዋል።
ማህበረሰብን ያማከለ ጥናታዊ አልበም (Social Experimental Research Album) ይህንን ያልኩበት ምክንያት እያንዳንዱ የአልበሙ ክር ከእኛ ልብ ጋር በቀረበ መልኩ በመሰራቱና በተራማጅ አስተሳሰብ፣ በፍቅር፣ በይቅርታ እንዲሁም በተስፋ ውስጥ የራሱን እውነታ ስለገለጸ ነው። ከነዚህም ውስጥ የወደድኳቸውን ለመጥቀስ ያህል፦
ይቅርታ (ሬጌ):- ይህንን ሙዚቃ ለመረዳት ከራሳችን ሐሳብና ልቦና ጋር ማስተሳሰር ይኖርብናል። ይቅርታ የሁሉም የበላይ ነው። በሱ ሕግ ስትመራ ጥፋትህ ይቀንሳል፤ ነፃነትን ተላብሰን እንድንጓዝም ይረዳናል። ተደብቀህ ሰውን የምትሰድብ ከሆነ ለይቅርታ ተዘጋጅ፤ በሌለበት ሰው ማማት ለሰላምታ እራሱ በር ይዘጋል። "ተደብቀህ ስትሰድብ ለይቅርታ ተዘጋጅ" የሚለው የዘፈኑ ዋና ነጥብ ነው።
"አሞኝተህ ሳትል ይቅርታ
አታስበው የለም ሰላምታ
ማሩኝ ሳይል ላይሞት ያጠፋ
የለም እድል የፍቅር ተስፍ"
ግጥም እና ዜማ ኤልያስ መልካ ቅንብር፡ያምሉ ሞላ እና ኤልያል መልካ
አቅፎ አድራሽ (ችክችካ):- ይህ ሙዚቃ የኤልያስን የግጥም ጅማሮ መሰረት አድርጎ በሙዚቃ ባለሙያዋ ብሌን ዮሴፍ የተጠናቀቀ ነው። የኤልያስ መረዳት ሁሌም ይገርማል፤ ነገን እያየ ግን እያስጠነቀቀና እያስተማረ ይነግረናል። በዚህ ዓለም አዲስ ነገር እንደሌለ በማመን ወደ እምነታችን እንድንጓዝ፣ እዚህ የምንሰራው ደግ ስራ እላይም የእኛ መሆኑንና ምርጫችንም በእጃችን እንዳለ ይጠቁማል። ኤልያስ ማረፊያውን ስላደላደለ ቀድሞ የነበረውንና የቀረውን ሕይወት ተናግሯል። ኤልያስ ያለበት ሁኔታ በዶናት በኩል የተገለጸልን ያህል ይሰማኛል።
"አቅፎ አድራሽ ያፋጥነኝ እንጂ
እጄን ይዞ ወዳልኩት ደጂ
----------
በል በል ተነሳ በል ልቤ ፍጠን እግሬ
እዚህም ሐገር እዚያም ሀገሬ
ግጥም እና ዜማ፡ ብሌን ዮሴፍ እና ኤልያስ መልካ ቅንብር፡ኤልያስ መልካ እና ያምሉ ሞላ
ቆም ያዝ (ፎክ እና ሞገር ሙዚቃ በጉራጌ ቶን):- በዚህ ሙዚቃ ላይ ያምሉ ሞላ ሙሉ በሙሉ የነፃነቱን ጥግ የተጠቀመበት ይመስላል። ቀደም ሲል በቸሊና፣ በቤቲ ጂ፣ በሚኪ ሐሴትና በደሳለኝ አበጀ የሙዚቃ ስራዎች ውስጥ በታየው የጉራጊኛ ቅኝት ቅርፅ ውስጥ፣ ዶናት ተክሉ በራሷ መንገድ እንድትራመድ ያምሉ ትልቅ እድል ከፍቶላታል። የዋሽንትና የማሲንቆ አገባቡ፣ የመግቢያና የመውጫ ስልቱ አዲስ ጣዕም ያለው ነው። አድናቆት የተሞላበትና ቀልባችን ሳይበታተን ደስታዋን እንድንጋራ የሚጋብዝ ድንቅ ስራ ነው
''ልብህን መልሰው ቀልብህን በል ያዘው
ለመጣ ለሄደው እየወዘወዘው
የረጋ ልብህን አተረማመሰው"
ግጥም እና ዜማ፡ዶናት ተክሉ ቅንብር፡ያምሉ ሞላ
ከነዚህ በተጨማሪ "ይቅርብኝ"፣ "ለኔ ማ"፣ "የልብ ዋጋ" እና "በቃ" የተሰኙ ሌሎች ድንቅ ስራዎች የተካተቱበት ሲሆን፣ አልበሙን ሙሉ በሙሉ በሽር ጉድ ኢንተርቴመንት (Shur good Entertainment) የዩቲዩብ ቻናል ማግኘት ይቻላል። በዚህ አልበም ላይ ኤልያስ መልካ፣ ብሌን ዮሴፍ፣ ያምሉ ሞላ፣ ዘሩባቤል ሞላ፣ አዲስ አለማየሁ (ሀዲንቆ) እና ሌሎችም የተሳተፋችሁ የጥበብ ባለሙያዎች በሙሉ ስራችሁ ስላማረ እናመሰግናለን። ይድረስ ለ ለዶናት ተክሉ ከ ተመስገን ኡካሬ
ኤልያስ መልካ ዛሬም አልደበዘዝክም😭😭😔
ዶናት ተክሉ አዲስ አልበም ሰጥታናለች ኤልያስ አለ
"ሲታደል የልብ ዋጋ
አያረጅ ሰርክ አይደክምም ለካ"
ይታደስ ይብስ ለካ
ወይ ፍቅር እያደር ሲነጋ"
============
አድምጬው አብሬው አውርቼው ነግሬው
ይጥመኛል ወሬው
አልበም፡ዓሀዱ
ድምፃዊት፡ ዶናት ተክሉ ወይም ብስራት ተክሉ
ግጥም እና ዜማ፡ ኤልያስ መልካ
ቅንብር፡ኤልያስ መልካ እና ያምሉ ሞላ
ኤላ ለዛ በዘላለማዊ መውደድ ያለሽ
ሽር ጉድ ኢንተርቴመንት ለቋል ገብታችሁ ስሙ
