ru
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Открыть в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Больше
2 936
Подписчики
+1424 часа
+3877 дней
+38530 дней
Архив постов
እኛ በጊዜያዊ የፖለቲካ ማዕበልና በአሉባልታ ነፋስ የምንናጋ ማኅበረሰብ አይደለንም፤ ምክንያቱም ክብራችንና ማንነታችን በፋኖ አጥንትና ደም የተገነባ፣ ስሩ በጥልቅ የታሪክ አፈር ውስጥ የሰመጠ ጽኑ ዓለት ነውና። ​አማራነትን እንደ ጉድለት ወይም እንደ ድክመት ለሚያየው የታሪክ ዕውርነትና የሐሳብ ድህነት ምላሻችን ፋኖ ነው፤ እርሱ የትላንትናው ተጋድሎ፣ የዛሬው ጽናትና የነገው ታላቅነታችን እውነተኛና ሕያው ምስክር ነው! ​"የአማራ ልጅ በማንነቱ አንገቱን እንዲደፋና እንዲሸማቀቅ የሚመኝ ኃይል ካለ፣ ከጀርባው የተሰለፈውን፣ ለክብሩና ለነፃነቱ ነፍሱን አሳልፎ የሰጠውን የፋኖን የጀግንነት ማዕበልና የማይበገሬነት ምንነት ፈጽሞ ያላወቀ ብቻ ነው። #Dave #Amhara

የአርበኛ የረመጡ ደጀን አሸብር ነሐሴ 1/2015 ዓ.ም የማትረሳ ዝክረ ሰማዓታት አማራን አጠፋለሁ ብሎ በቅጀት የተነሳዉ የብልፅግና ሰራዊት ጎንደርን ከተማን በመድፋ በታንክ በዙ23 በሞርተር በድሽቃ በብሬን አገር ሰላም ብሎ በተቀመጠበት ህዝቡ ያላሰበዉ ዶፍ ወረደበት ቅርሶች ተንቀጠቀጡ ቤተክርሲቲያ መስጊዶች ተደበደቡ ህፃናት አዛዉን ተደናገጡ ምኑ ማት መጣ በማለት ተጨነቁ ነበልባሉ ፋኖ አያቶቹ የገነቧት ከተማ የቱሪስ መዳረሻ የሆነችሁ ከተማ እንዲህ በአንድ ፍሽሽት የብልፅግና መንግስት ነኝ በሚል አካል ስትፈርስ ህዝቦቿ ሲጨፈጨፉ ማን ቁሞ ያያል በማለት ጀግና የአማራ ልጅ መሳሪያዉን ወልዉሎ ትጥቁን አንስቶ ለ7 ቀን ከለሊት አንገት ላንገት ተናነቀ አሳሩን አሳየዉ። ጎንደር ከተማን አጠፋለሁ ብሎ የተነሳዉ ቅጀታም በቁርጥ ቀን ልጆቿ ያሰበዉ ያልተሳካለት የገባዉ ሁሉ መቅረት እንጅ መዉጣት ማይታሰብ መሆኑን የተረዱት አብይ አህመድ ጀኔራሎቹ ዕቅዳቸዉ መክሸፉን ሲያስቡ የመጨረሻ አማራጭ የተጠቀሙት በሰሜን በደቡብ በምዕራብ በምስራቅ በ4ቱም አቅጣጫ ያሰቀመጡጥን የትግል አላማ ያልገባዉን የግሪሳ መንጋ ወደ ጎንደር አዘመቱት። ከባሻ ጥጋቡ ጠረፉን የተረከበዉ ረመጡ ደጀን አሸብር ጎንደር ላይ እየተፈፀመ ያለዉን ሲሰማ እንቅልፍ ነሳዉ ወደ ትግል ጓደቹ በመደወል አይዟችሁ እንደርስላችኃለን በማለት የትግል ጓዶችን በማነሳሳት እና በማደራጀት ከሱዳን ጠረፍ በመነሳት ከወንድሞቹ ከሻ/ቃ ሲሳይ አሸብር አርበኛ ሸቴ አሸብር አርበኛ ስጦታዉ መልኬ አርበኛ በለጠ አዱኛ አርበኛ ስማቸዉ የሽነህ አርበኛ ገብሬ አቡሃይ አርበኛ ብርሃኑ ሙላዉ የጠገዴ አርማጭሆ ወጣቶችን በማስተባበር ሳንጃ ላይ በመዝጋት ከአዉደራፊ እና ከሁመራ የሚጓዘዉን የጠላት ሃይል ወደ ጎንደር የሚያደርገዉ ጉዞ ህልም ሆነበት ባለበት መቆም ግድ ሆነ። ረመጡ ደጀን አሸብር በየ አቅጣጫዉ የመጣዉን የአገሪቱ ሰራዊት ነኝ የሚለዉ ሳንጃ ላይ ታጉሯል ወደ ጎንደር ማለፊያ ጠፍቷል የጠገዴ አርማጭሆ ወጣት አይኑን አፍጧል ግንባሩ ተቋጥሯል ፀጉሩ ቁሟል ቦታ ቦታ ይዞ ትዛዝ ይጠባበቃል። አርበኛዉ ረመጡ ደጀን አሸብር ተቆጥቶ ለመከላከያ የሰራዊት አመራሮች ተመለሱ ዳር ድንበሩን ለማን አስረክባችሁት መጣችሁ ማህል አገር ምን አለ በማለት ሲጠይቃቸዉ ጎንደር ለማረጋጋት ነዉ እኛ ከህዝባችን ጎን ነን በማለት ለማታለል ሞከሩ የእናንተ አማራጭ መመለስ ብቻ እንደሆነ እንቅጩን ሲነግሯቸዉ ትዛዝ ነዉ የሚል መልስ ሰጡ እንግዲያዉስ የአርማጭሆን ጥይት ቅመሱት ዉጊያዉ ተጀመረ። አርበኛ ረመጡ ደጀን አሸብር ትዛዝ ከወንድሙ ከየሻ/ቃ ሲሳይ አሸብር ተቀበለ ወጣቱ በየአቅጣጫዉ ጃሌ እያለ እየፎከረ የብልፅግና ሰራዊት ላይ እሳት አነደደበት ጠላት ጎንደርን እያሰበ ሳንጃ ላይ ዶፍ ወረደበት በጣም ብዙ ቁጥር የጠላት ሃይል በአልሞ ተኳሾች እችን አለመን ተሰናበቷት። አርበኛ ረመጡ ደጀን አሸብር ሙሉ ቀን ሲያዋጋ ሲዋጋ ዉሎ በጣም ብዙ ክላሽን ኮፕ ብሬኖች ሲናይፐሮችን ተተኳሽዎች ከጠላት ማርኮ ለትግል ጓደኞቹ ሲያስታጥቅ ዉሏል። አርበኛ ረመጡ ደጀን አሸብር ነሐሴ 1/2015 ዓ.ም ሲዋጋ ሲያዋጋ ዉሎ ከ650 በላይ ጠላትን ደምስሶ ምሸት አካባቢ ከጠላት በተተኮሰች ጥይት የዛሬ 3 ዓመት ለአማራ ህዝብ ነፃነት ሲል የክብር ሰማዓታትነትን ተቀብሏል። በአጠቃላይ ብዙ ጀግኖቻችን አርበኞች ደማቸዉን ያፈሰሱለትን አጥንታቸዉ የከሰከሱለትን ሰማዓታትነትን የተቀበሉበትን ዓላማዉን አሳክተን አደርነት እና አንድነትን እናፀናለን። ክብርና ሞገስ ለሰማዕታት ጀግኖቻችን ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን አርበኛ ባንዴራዉ ግርማይ - ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

ሠበር ሰበር ሠበር የድል ዜና !!! ጀብደኛው ምኒሊክ ዕዝ ወግድ ወረዳ ላይ ድል ተቀናጀ ! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒሊክ ዕዝ 15 ኮር 45ኛ (የመብረቅ) ክፍለ ጦር በዛሬው ዕለት ማለትም በ ዐ1
+4
ሠበር ሰበር ሠበር የድል ዜና !!! ጀብደኛው ምኒሊክ ዕዝ ወግድ ወረዳ ላይ ድል ተቀናጀ ! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒሊክ ዕዝ 15 ኮር 45ኛ (የመብረቅ) ክፍለ ጦር በዛሬው ዕለት ማለትም በ ዐ1 / 12 / 2018 ዓ.ም ራሱን ጥምር ጦር ብሎ በሚጠራው ሠራዊት ከቀኑ 4፡00 ጀምሮ እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ በማድረግ እያሽመደመዱት ይገኛሉ ። ውጊያው እንደቀጠለ ሲሆን በጠላት ላይ ቀላል የማይባል ቁሳዊና ሠብአዊ ጉዳት አድርሰውበታል ። እስካሁን የደረሰን መረጃ እንደሚያመላክተው አብዛሀኛው የተደመሰሰ ሲሆን ቁስለኛውን እያንጠባጠበ በመሼሽ ላይ የሚገኘው ጠላት ገሚሡ ምርኮ በምርኮ ሆኗል ። ውጊያው ሲጠናቀቅ መረጃዉን አጠናቅረን እንመለስበታለን ።

ነሐሴ 1/2018 ዓ/ም ከጎንደር አንድነት ማግስት በሙሉ አቅማችን ለውጊያ ዝግጁ ነን ሲል አርበኛ ወርቁ ዘገየ ተናገረ ። ከአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ  ዕዝ አንድነት ማግስት በሙሉ አቅማችን በአንድነት የብልፅግናን ስርዓት  ለመደምሰስ  እና የአማራ ህዝብን የህልውና ትግል ዳር ለማድረስ  የግዙፉ  ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ አርበኛ ወርቁ ዘገየ ተናግሯል።   ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ሰፊ ቀጠና ይዞ የጎንደርን አንድነት ለማምጣት ከፍተኛ ስራ ከሰሩ ክፍለ ጦሮች መካከል አንዱ ሲሆን የጎንደርን ስምና ክብር  የሚመጥን ፣ትግሉን ከፊት ሁኖ መምራት እንዲችል ከደንቢያ እስከ ወገራ ድረስ ከአመራር እስከ አባል ገብረን የጎንደርን አንድነት እንዲመጣ  አድርገናል ከእንግዲህ በተናጠል ሳይሆን በጋራ ጠላታችንን እናጠፋለን በልዩነት የሚባክን ጊዜ እና የሰው ሀይል የለም ሲል ተናግሯል ። አርበኛ ወርቁ ዘገየ እንደተናገረው በክፍለ ጦራችን ስር  ያሉ  ሁሉም  ብርጌዶች ከአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ለሚሰጡ ወታደራዊ ትዛዞችን እና ግዳጆችን ለመቀበል 24 ሰዓት ዝግጁ ናቸው  ሲል ለመላው የዕዙ አመራርና አባላት መልዕክቱን  አስተላልፏል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን  ! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!

በነፃ ቀጠናዎች የሕዝብ አስተዳደር መዋቅር የመዘርጋት ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል!! ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መንዝና ግሼ አውራጃ የሚንቀሳቀሰው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠራቸው ነፃ ቀጠናዎች የሕዝብ አደረጃጀትና አስተዳደራዊ መዋቅሮችን እያዋቀረ እደሚገኝ ተገለፀ። ዕዙ የማዕከላዊ ኮሚቴውን የመጀመሪያ ጉባዔ ባጠናቀቀ ማግስት ከፍተኛ አመራሮቹን ወደተለያዩ ቀጠናዎች በመመደብ ከህዝቡና ከሰራዊቱ ጋር ሰፊ ጥልቀት ያለው የውይይት መድረክ እያደረገ ይገኛል። በነዚሕ መድረኮች ከህዝቡ የተነሱ ሀሳቦችን በማካተት የትግሉን አላማና ግብ ለማሳካት የሚያስችሉ ውሳኔዎች በጋራ መወሰናቸው ተገለፀ። በመንዝና ግሼ አውራጃ የሚኖረው ህዝብ ለአስተዳደርና ለአገልግሎት አሰጣጥ ይመቻል ያለውን ጊዜያዊ አደረጃጀት በመከተል ቀበሌዎችን በክላስተር እያዋቀረ ሲገኝ በዚህም መሰረት በግሼ ቀጠና የተቆጣጠራቸውን ቀበሌዎች በአራት(4) ክላስተሮች አዋቅሯል፡ ↘ክላስተር አንድ(1) ወዠድ ክላስተር፦ ወዠድ ከተማን፣ አናዝ ቀበሌን እና ስረገደል ቀበሌን ↘ክላስተር ሁለት(2) ግራር አምባ ክላስተር፦ ግራር አምባ ቀበሌ እና ጠበል ጫጩራ ቀበሌ ↘ክላስተር ሦስት(3) አራጣ ክላስተር፦ አራጣና ልጅት ቀበሌ እና አስናፊት ቀበሌ ↘ክላስተር አራት(4) ኮረብቲት ክላስተር፦ ደል ቀበሌ፣ ጎልታ ቀበሌ እና ኮረብቲት ቀበሌዎችን፡ እና ሌሎች የክላስተር አደረጃጀቶችን እያዋቀረ ይገኛል። የአማራ ሕዝብ ለዘመናት የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ በውል በመረዳ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግልን እየታገለ ሦስት አመታትን አስቆጥሯል። ሆኖም እነዚሕን ዓመታት በሕዝቡ ድጋፍና ደጀንነት "የአማራ ፋኖ ሠራዊት" በመገንባት ከግል ታጋይ እሰከ አታጋይ ድርጅት መምስረት የቻለው ሕዝብ ከአመራሮቹና ሠራዊቶቹ ጋር ጥልቅ ውይይት እያደረገ ቀልጣፋ አስተዳደራዊ መዋቅሮችን ለሕዝቡ ማቅረቡን ቀጥሏል። በመንዝ ግሼ አውራጃ የሚንቀሳቀሰው የአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ ዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ብሩኬ ደምሴ ክፍለ ጦር በተመሳሳይ ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ሰፊ የግምገማና የስልጠና መድረክ አድርጎ፡ ከዚሕ በታች በቀረቡት ሀሳቦች ላይ ጥልቅ ውይይት አካሒዷል። ➠ ፖለቲካዊ ግንባታ ▪የድርጅት ተልዕኮ አፈጻጸም ▪የማህበራዊ አኗኗር ደንቦች ▪ቅንጅታዊ አሠራሮች ▪ድርጅታዊ አላማና ግብ እዲሁም አጠባበቅ ➠የሠራዊቱ መብትና ግዴታዎች ▪አካላዊ ብቃት ማሻሻያ ▪አዳዲስ የውጊያ ስልቶች ▪ወታደራዊ ስነ ስርዓቶች ▪ወታደራዊ ስነ ምግባር ▪ወታደራዊ የአወቃቀር ማሻሻያና መሰል አዳዲስ ስልጠናዎች ትምሕርቶች ለሠራዊቱ ተደርጎለታል። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ «ጠላትህንና ራስህን ካወቅክ መቶ ውጊያዎችን አትፈራም» የሚለው መሪ ሀሳብ ጎልቶ የተንጸባረቀ ሲሆን፣ የሸዋ አንድነትና አማራዊ ድርጅት፣ አሁናዊ ሁኔታ፣ የቀበሌዎች የስራ እንቅስቃሴና የክላስተር አደረጃጀቶች እውቅና ላይ ውሳኔ በማሳለፍ መድረኩ ተጠናቋል። ለተዋቀሩት ክላስተሮች የተመደቡት አመራሮችም ህዝቡንና አካባቢያቸውን በቅንነት፣ በታማኝነት፣ በፍትሃዊነትና በጽናት ለማገልገል በህዝቡ ፊት ቃለ መሃላ ፈጽመው ውይይቱ ተጠናቋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ዋግሹም ብርጌድ ባደረገው መብረቃዊ ጥቃት 15 ሚሊሻና 27 ክላሽንኮፍ በመማረክ ታላቅ ጀብዱ ፈፀመ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)  ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር  የ19ኛ ክፍለ ጦር ክንፍ የሆነው ዋግሹም ብርጌድ በዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ዝቋላ ወረዳ ልዩ ስሙ ቀማርያም ከተባለ ቦታ መሽጎ የነበረውን ሚሊሻ ባደረሱበት መብረቃዊ ጥቃት ከፊሉ ሲማረክ ከፊሉ ሙትና ቁስለኛ ሆኗል። ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም ከንጋቱ 12:00 ሰዓት እስከረፋዱ 2:30 ሰዓት  በተደረገው አውደ ውጊያ ጠላት ይዞት የነበረውን ምሽግ ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር 18 የአገዛዙን ሚሊሻ በመደምሰስና 15ቱን በመማረክ ታላቅ ጀብዱ የፈፀሙ ሲሆን በአውደ ውጊያውም 27 ክላሽንኮፍ፣ አንድ አርባ ጎራሽና አንድ ፋል የቡድን መሳሪያ፣ አንድ የብሬን ቧንቧ ተማርኳል ሲል የ303ኛ  አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!     ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!!          ነሀሴ :- 1/ 2018 ዓ/ም

የታሪክ ማዕበል እና የትውልዱ እሳተ-ገሞራ! ​የምስራቅ አፍሪካ ቀንድን ምድር የሚያናውጥ፣ የዘመናት የታሪክ ዝምታን ሰብሮ የታሪክን አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ የሚቀይር ታላቅ የጀግንነት እሳተ-ገሞራ ከደጋው ተራራዎች ስር የፈነዳው! ​ከጎጃም ገደላማ አምባዎች እስከ ወሎ ኩሩ ተራሮች፣ ከሸዋ ሰፊ ሜዳዎች እስከ ጎንደር ታሪካዊ ድንበሮች የተፈጥሮ እንቅፋት፣ የደጋው ቅዝቃዜና የሸለቆው ቁልቁለት አንዳችም ሳይበግረው፣ በክርስቶስ መስቀል አርማ የተሳሰረ አስገራሚ፣ ጥቡቅና የማይበገር የህብረት ጥምረት ተፈጠረ። ይህ ጥምረት ልክ እንደ ንጋት ወፎች ማለዳ የሚዘምሩት ውብና የተናበበ ዜማ፣ በአንድ ልብ፣ በአንድ ዓላማና በአንድ ድምፅ በመላው ምድር አስተጋባ! ​ይህ ታላቅ ጉዞ መጀመሪያ ላይ በእምነት፣ በፅኑ ቁርጠኝነትና በአንድ ነጠላ ግር ክላሽ ብቻ ተጀምሮ፤ ዛሬ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚደነቁት ከፍተኛና ረቂቅ የጦር ጥበቦች ተራ የሚመደብ፣ በጽናትና በዕውቀት ወደ ተገነባ ግዙፍ ሜካናይዝድ አቅም ተሸጋገረ። ይህ የአማራ ልጅ ፋኖ ነው የአማራ ህዝብ ኩራት፣ የምስራቅ አፍሪካ ቀንድ እውነተኛ ነፃ አውጪ! ​ይህ ትውልድ የአባቶቹን አደራና የሀገር ፍቅር በደሙ ውስጥ አዋህዶ የያዘ ህያው ታሪክ ነው። የአሰማነው፣ የበላይ ዘለቀ፣ የዓፄ ሚኒልክ እና የዓፄ ቴዎድሮስን የማይበገር የጀግንነት ወኔ ተጎናጽፎ፣ በታሪክ ገጽ ላይ አዲስ የነፃነት ምዕራፍ እየጻፈ ይገኛል። ​ይህ የኃይልና የወኔ ብቻ ሳይሆን የጥበብና የዕውቀት ታላቅ ስብስብ ነው፤ በበሳል የጦር መኮንኖች፣ በሊቃውንት፣ በህክምና ዶክተሮች እና በልምድ በበሰሉ ጄኔራሎች የሚመራ፣ ሀገርና ወገንን የማዳን ታላቅ ዓላማ ያነገበ ስልጡንና አርቆ አሳቢ ኃይል ነው። የአማራ እናት አምጣ የወለደችው፣ የታሪክን ሚዛን የሚያስተካክለውና የመጭውን ጊዜ ብሩህ ተስፋ የሚያበራው አዲሱ ትውልድ ይህ ነው! #Dave #Amhara

ብልፅግና ያደራጃቸው ዘራፊዎች በቁጥጥር ዋሉ‼️ በደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ በብልፅግና ተደራጅተው የህዝብ መገልገያ ተቋማት ላይ ዘረፋ ሲፈፅሙ የነበሩ ዘራፊዎች እጅ ከፍንጅ ተይዘው ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል። አረመኔው እና አማራ ጠል የሆነው የአብይ አህመድ ስርዓት በደረሰበት ሽንፈት በርካታ የቀበሌ እና የወረዳ ከተሞችን እየለቀቀ በፋኖ ቁጥጥር መግባታቸውን ተከትሎ አገዛዙ በለቀቃቸው እና እንደሚለቃቸው በሚጠራጠራቸው ከተሞች ዘራፊ ቡድኖችን ማደራጀቱ ተረጋገጠ። በደቡብ ወሎ ዞን የደላንታ ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ወገል ጤና ከተማ አገዛዙ ተቋማትን እንድያወድሙ ያደራጃቸው አካላት የህዝብ መገልገያ የሆኑትን ተቋማት እያወደሙ እና ኮምፒውተሮችን እና ሌሎች ቁሳቁሶችን እየዘረፉ ሲያከማቹ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል። አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር ባደረገው ክትትል እና ከህብረተሰቡ በተገኘ ጥቆማ ሀምሌ 30/2018 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ውለዋል። በወንጀለኞቹ ላይተጨማሪ ምርመራ እየተደረገባቸው ሲሆን መጨረሻውን ለህዝባችን የምናሳውቅ ይሆናል። ከዚህም በተጨማሪ አገዛዙ በሰሜን ወሎ ዞን ስር በሚገኙ የወረዳ ከተሞች በርካታ ዘራፊ ቡድኖችን ያሰማራ መሆኑን እየገለፅን ህዝባችን እራሱን አደራጅቶ እራሱን እና የህዝብ መገልገያ ተቋማቶችን በንቃት እንድጠብቅ ስንል እናሳስባለን። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በሰሜን ወሎ ዞን መቀመጫ በሆነችው የወልድያ ከተማ በምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር ስም እያሳበቡ በህዝባችን ላይ በርካታ ዘረፋዎች እየተፈፀሙ ይገኛሉ በመሆኑም በኮራችን ስም እየተጠቀሙ ዘራፋዎችን የሚፈፅሙ አካሎችን ተከታትለን እስከምንይዛቸው ህዝባችን እራሱን ካጭበርባሪዎች እንድጠብቅ ስንል በጥብቅ እናሳስባለን አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒሊልክ ዕዝ 101ኛ ኮር ሚድያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዉን አድርሷል።   መዳረሻውን ድልና ነፃነት ያደረገው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! ©አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ! ነሃሴ 1/2018 ዓ.ም 01/12/2018 ዓ.ም

ጀግናው የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በብልፅግናው አየር ወለድ ሰራዊት ላይ ባካሄደው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ድል መቀዳጀቱን አስታወቀ! ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር፣ እራሱን "101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር" ብሎ በሚጠራው የአገዛዙ ሰራዊት ላይ ትላንት ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ባደረገው የተቀናጀ ወታደራዊ ኦፕሬሽን አኩሪ ድል መጎናፀፉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ። የአገዛዙ ኃይል መነሻውን ከመርሐቤቴ አውራጃ ሬማ ከተማ በማድረግ፣ የህዝብ አለኝታ የሆነውን የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ሰራዊት ለማጥቃት ወደ መጅት እና ቢራባ ቀበሌዎች እንቅስቃሴ አድርጎ ለማጥቃት ቢሞክርም የክፍለ ጦሩ የጦር ጠበብቶች በወታደራዊ ስልት የጠላትን ኃይል ወዳዘጋጁለት የውጊያ ቀጠና በስቦ መምታት ስልት፡ በወታደራዊ የበላይነት የሬማ ዙሪያ አካባቢዎችን በወቅቱ በቁጥጥር ስር በማስገባት ጠላት ወደ ኋላ እንዳይመለስ መንገድ በመዝጋት በተከናወነው በዚህ የተሳካ ኦፕሬሽን፣ የአገዛዙ ኃይል ከፍተኛ ወታደራዊና ቁሳዊ ኪሳራ አስተናግዷል። በዜሮ መስዋዕትነት በተጠናቀቀው በዚህ ልዩ ኦፕሬሽን የተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች፦ ➠ የተደመሰሰ የጠላት ኃይል፡ 09 ➠ የቆሰለ የጠላት ኃይል፡ ከ14 በላይ እንዳቀደው ያልተሳካለት ጠላት ከፋኖ በደረሰበት ሽንፈት የተበሳጨው ወደ መጣበት ሲመለስ እንደለመደው ንፁሀንን የበቀል እርምጃ፡ የብስጭት ማብረጃ እያለ ንፁሀን ወገኖች ከፍተኛ ድብደባ የተፈፀመባቸው ሲሆን የመጅት ቀበሌ የ8 ዓመት ታዳጊ ህፃን ቶፋው ጋሻው የተባለች እንስት በጥይት ተመታ መቁሰሏን የአይን እማኞች ተናግረዋል። ሽንፈቱን የተከናነበው ጠላት የቆሰሉት አባላቱን ለሕክምና በሬማ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና በሬማ ከተማ ጤና ጣቢያ የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና እየተደረገላቸው ሲሆን፣ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው አባላቱን ዛሬ ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም ከንጋቱ 12:30 ላይ ወደ መርሐቤቴ ዓለም ከተማ እናት ሆስፒታል መዛወራቸውን የኮሩ መረጃዎች አረጋግጠዋል። "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

መማረክን ከመሪዎቹ የተማረ ሰራዊት ! እርግጥ በ leadership አስተምህሮት የአንድ መሪ ጥሩ መለኪያዋች ውስጥ ተተኪ መሪ ማውጣት እንደሆነ መፅሐፍት ያስረዳሉ ። ብርሐኑ ጁላም ይሁን በጫ ደበሌ ተተኪ መሪ እያወጡ ይመስላል ። አስተማሪም የሚያስተምረው ተማሪ የተሻለ እንዲሆን ነው ። የብርሐኑ ጁላ ልጆቹም በዚህ እረገድ የተሻለ የመማረክ ሪከርድ እያሳዩ ነው ። ስለዚህ በፋኖ መነፅር እና በወጣንለት ዓላማ አንፃር ብርሐኑ ጁላ ጥሩ መሪ ነው ማለት ይቻላል ¡ እንዴት መከላከያ እንደሆነ ? ማንን እንደሚወጋ ? ምን ዓላማ እንደሚያሳካ ? ማንን ለማስደሰት እንደሚዋጋ ? ተጨባጭ ምክንያት ሳይኖረው ፣ ሳያውቅ እና ሳይረዳ መዳከር ላይ ይገኛል ። የህልውና አደጋ ገጥሞት በአዲሱ አቢዮተኛ ትውልድ ተወክሎ የሚዋደቅን ህዝብ እንዴት ማሸነፍ ይችላል ? መቸም ከባጫ በሶ መበጥበጥና ለጭፈራ ካልሆነ በስተቀር ይሄን ያብራራልናል ብለን አናስብም ታፍሶ የመጣ የአብይ ወንበር ጠባቂ ሀይል ቢማረክ ነገ የጦር አዛዥ የመሆን እድል እንዳለው ብርሐኑ ጁላን ምሳሌ አድርጎ የመጣ ስመ መከላከያ ፋኖ እንደተጠጋው እጅ ይሰጣል እንጅ ለድል የሚያበቃ ስነ-ልቦና ከሲሳይ አጌናም ይሁን ከባጫ ደበሌ መዋስ ስለማይችል ከፋኖ አውደ ውጊያ በኋላ መማረካቻው የተለመደ ሰበር ዜና ከመሆን ውጭ ሌላ አማራጭ የለውም ። ከሁሉም በላይ ግን አስር አለቃ ብርሐኑ ጁላ ከዚህ በፊት በመማረኩ ህይወቱን አትርፎ አሁን የሀገሪቱ ጦር አዛዥ መሆኑን የተረዳ ሰራዊት መሰዋዕት ሁኖ ያውም የአብይን አገዛዝ ለማስቀጠል ይታገላል ማለት "ገሣ ከመብረቅ ይከላከላል" እንደማለት ነው ። ይሄ አቢዮተኛ ትውልድ እንደሚነሳ በመተማመን የክልሉ ርዕሰ መዲና ባህር- ዳር ከተማ ላይ ተኩስ ከፍቶ አቢዮቱን ያስነሳን ምትሐተኛ መሪን ማለትም አርበኛ ዘመነ ካሴን ከፊቱ አድርጎ የወጣ ትውልድ እንዴት የሴት ልጅ ጡት በሚቆርጥ ሞራል የለሽ የካድሬ ዘበኛ ፋኖን ማሸነፍ ይችላል ? እንዴት ግብር እየከፈለ ደሞዝ የሚቆርጥለትን ማህበረሰብ የሚወጋ አመክንዮ የለሽ ሰራዊት በነፃ ለነፃነት የሚዋጋ ሰራዊትን ማሸነፍ ይችላል ? ይሄ ትውልድ እኮ ከአማራነቱ በተጨማሪ በስልጠና ያገኘው ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ የአስተዳደር ብቃት አለው ። ብልፅግና ዛሬ ላይ ወደ ሰሜን ክተት መክት ማርከህ ታጠቅ ብሎ የሚዘምተው ሳይሆን ዛሬ ላይ ለ3 ዓመት ሙሉ የብልፅግናን ክፍለ ጦር ተቋቁሞ እየማረከ ያለ የአማራ ሰራዊት በራሱ ላይ መዝመቱን እረስተውት ነው ? ለማንኛውም ' ውሐ ሲበላ እያሣሣቀ ' የሚለውን አባባል ፋኖ ሲያጠቃ እያስለቀሰ በሚለው አውዳዊ ፍች ቀይራችሁ ተጠቀሙበት ። ከዚህ በፊት በትርፍ ጊዚያችን እየታገልነ ከዚህ ያደረስናችሁ አሁን ላይ በሙሉ ጊዚያችን እየመጣንባችሁ ስለሆነ ቻሉት ። አሁን እኛ ፋኖዎች ብቻችን አይደለንም ከብዙ አጋሮች ጋር ብዙ መሣሪያ ታጥቀን እየመጣን ነው ። ቻሉት ልመርጥላችሁ ነው ያለን ማን ነበር ? ብርሐኑ ጁላ ወይስ ባጫ ደበሌ ? ለማንኛውም ቻሉት እኛም አንመርጥላችሁም ። ሰይፍ ከማንሳቱ በፊት በሰልፍም በደብዳቤም ሲጠይቅ መተዛዘቢያ ከማድረጋችሁ በላይ ልጆቹን ስታስሩ እና ስትገሉበት የነበረው የአማራ ህዝብ ዛሬ ፊት ለፊት ገጥሟችኋል ቻሉት ። ምን ምን እንደሚልም ቅመሱት ። በሁለት ሳምንት እናጠፋዋለን ብላችሁ ሁለት አመት ሞላችሁ ። ሶስት ጥቁር ክላሽ ነው ተሸክመው ሚወዛወዙ ብላችሁ ሹተር በሹተር አደረጋችሁን ። ፅንፈኛ ስትሉን ማርከን በዓለም ፊት ለቀይ መስቀል አስረከብን ከናንተ የተሻልነ ሐላፊነት የሚሰማን ታጋዮች እንደሆነ ዓለም አወቀን ተደመመብን ፋኖ መንግስት መሆን እንደሚችል ትዝብታቸውንም ወሰዱ ። አንድ ሐቅ ግን አለ በቁማችሁ እንደተገተራችሁ የአማራ ህዝብ አንድ የጋራ ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ርዕይ እንዲኖረው የሚያደረገውን ጉዞ አጠናቀን ትመለከቱ ዘንድ ግድ ነው ። ፋኖ የትግሉ የስበት ማዕከል ሁኖ ሌሎቹን ኢትዮጵያዊ ፀረ- ብልፅግና ኃይሎች ከምስራቅ አፍሪካ የትብብር ኃይሎች ጋር አብሮ በመሆን እነ ባጫ በጫት አፋቸው የሚያወሩለትን ቤተ መንግስት ለትክክለኛ አገር ወዳዱ ኃይል ለቀው መፈርጠጣቸው ግድ ነው ። አርበኛ ግሩም ምሳሌ በአፋብን የጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ

የንስር ሻለቃ የትግል ዝግጁነቱን ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ ልዩ የተሀድሶና የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና መድረክ ተካሔደ!!            ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ተወርዋሪው የንስር ሻለቃ፣ ህዝባዊ ትግሉን በተሻለ ስትራቴጂያዊ ዝግጁነትና ወታደራዊ ዲስፕሊን ለማጠናከር ያለመ ልዩ የተሀድሶና የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና ማሳደጊያ መድረክ በታላቅ ድምቀት አካሂደዋል።  በዓላማ ፅናትና በወታደራዊ ስትራቴጂ ዝግጁነት የታነፀው ይህ መድረክ የአማራ ህዝብ እያካሄደ ባለው ፍትሃዊ የህልውና ተጋድሎ ውስጥ የኃይል ሚዛኑን ሙሉ በሙሉ ወደ ድል ለመቀየር ያለሙ ቁልፍ ውሳኔዎች የተበሰሩበት ሆኖ አልፏል።  በመድረኩ ላይ የአፋብን ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ፣ የአፋብን መካናይዝድ ጦር መምሪያ ሃላፊ አርበኛ አብረሃም ኩራባቸውን ጨምሮ የዕዙ ከፍተኛ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች፣ የንስር ሻለቃ መሪዎች እንዲሁም በክብር እንግድነት የተገኙት የአፄ አምደፂዎን ኮር አመራሮች ተሳትፈዋል።           የመድረኩ ዋና ዋና ዓላማዎች ~ የአመራርና የሻለቃውን ወታደራዊ ብቃት ማሳደግ፡ ~የተሀድሶ መድረኩ የወታደራዊ ስልቶች ማሻሻያዎች ~ የግዳጅ አፈፃፀም ግምገማዎችንና የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን በጥልቀት በመገምገም የትግል ዝግጁነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ተማሻገር ~ርዕዮተ-ዓለማዊና ፖለቲካዊ አንድነትን ማጠናከር ~የትግሉን ፖለቲካዊ ግቦች ማስረፅ የሠራዊቱንና የአመራሩን የእርስ በእርስ ውህደትና የዓላማ አንድነት የበለጠ ለማጠናከር  ~የጋራ ትብብርና አድነትን ማጠናከር እንደ ስማቸው ሁሉ በከፍታ ላይ በመብረር የጠላትን እንቅስቃሴ ከሩቅ የሚቃኙትና የመመታት አቅማቸው ከፍተኛ የሆነው የንስር ሻለቃ አባላት በዚህ የፖለቲካና የውጊያ ተሀድሶ ይበልጥ ታድሰውና ተዘጋጅተው ለተጨማሪ ግዳጅ መቅረባቸው ተገልጿል።  ይህ የተሀድሶ መድረክ አመራርና አባላት የህዝባቸውን ነፃነት፣ ክብርና ህልውና ለማረጋገጥ የሚያደርጉትን ተጋድሎ እስከ አሸናፊነት ለመምራት ያላቸውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ሆኗል።  " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ