uz
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Kanalga Telegram’da o‘tish

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Ko'proq ko'rsatish
2 941
Obunachilar
+224 soatlar
+3727 kun
+36730 kun
Postlar arxiv
ዋግሹም ብርጌድ ባደረገው መብረቃዊ ጥቃት 15 ሚሊሻና 27 ክላሽንኮፍ በመማረክ ታላቅ ጀብዱ ፈፀመ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)  ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር  የ19ኛ ክፍለ ጦር ክንፍ የሆነው ዋግሹም ብርጌድ በዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ዝቋላ ወረዳ ልዩ ስሙ ቀማርያም ከተባለ ቦታ መሽጎ የነበረውን ሚሊሻ ባደረሱበት መብረቃዊ ጥቃት ከፊሉ ሲማረክ ከፊሉ ሙትና ቁስለኛ ሆኗል። ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም ከንጋቱ 12:00 ሰዓት እስከረፋዱ 2:30 ሰዓት  በተደረገው አውደ ውጊያ ጠላት ይዞት የነበረውን ምሽግ ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር 18 የአገዛዙን ሚሊሻ በመደምሰስና 15ቱን በመማረክ ታላቅ ጀብዱ የፈፀሙ ሲሆን በአውደ ውጊያውም 27 ክላሽንኮፍ፣ አንድ አርባ ጎራሽና አንድ ፋል የቡድን መሳሪያ፣ አንድ የብሬን ቧንቧ ተማርኳል ሲል የ303ኛ  አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!     ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!!          ነሀሴ :- 1/ 2018 ዓ/ም

የታሪክ ማዕበል እና የትውልዱ እሳተ-ገሞራ! ​የምስራቅ አፍሪካ ቀንድን ምድር የሚያናውጥ፣ የዘመናት የታሪክ ዝምታን ሰብሮ የታሪክን አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ የሚቀይር ታላቅ የጀግንነት እሳተ-ገሞራ ከደጋው ተራራዎች ስር የፈነዳው! ​ከጎጃም ገደላማ አምባዎች እስከ ወሎ ኩሩ ተራሮች፣ ከሸዋ ሰፊ ሜዳዎች እስከ ጎንደር ታሪካዊ ድንበሮች የተፈጥሮ እንቅፋት፣ የደጋው ቅዝቃዜና የሸለቆው ቁልቁለት አንዳችም ሳይበግረው፣ በክርስቶስ መስቀል አርማ የተሳሰረ አስገራሚ፣ ጥቡቅና የማይበገር የህብረት ጥምረት ተፈጠረ። ይህ ጥምረት ልክ እንደ ንጋት ወፎች ማለዳ የሚዘምሩት ውብና የተናበበ ዜማ፣ በአንድ ልብ፣ በአንድ ዓላማና በአንድ ድምፅ በመላው ምድር አስተጋባ! ​ይህ ታላቅ ጉዞ መጀመሪያ ላይ በእምነት፣ በፅኑ ቁርጠኝነትና በአንድ ነጠላ ግር ክላሽ ብቻ ተጀምሮ፤ ዛሬ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚደነቁት ከፍተኛና ረቂቅ የጦር ጥበቦች ተራ የሚመደብ፣ በጽናትና በዕውቀት ወደ ተገነባ ግዙፍ ሜካናይዝድ አቅም ተሸጋገረ። ይህ የአማራ ልጅ ፋኖ ነው የአማራ ህዝብ ኩራት፣ የምስራቅ አፍሪካ ቀንድ እውነተኛ ነፃ አውጪ! ​ይህ ትውልድ የአባቶቹን አደራና የሀገር ፍቅር በደሙ ውስጥ አዋህዶ የያዘ ህያው ታሪክ ነው። የአሰማነው፣ የበላይ ዘለቀ፣ የዓፄ ሚኒልክ እና የዓፄ ቴዎድሮስን የማይበገር የጀግንነት ወኔ ተጎናጽፎ፣ በታሪክ ገጽ ላይ አዲስ የነፃነት ምዕራፍ እየጻፈ ይገኛል። ​ይህ የኃይልና የወኔ ብቻ ሳይሆን የጥበብና የዕውቀት ታላቅ ስብስብ ነው፤ በበሳል የጦር መኮንኖች፣ በሊቃውንት፣ በህክምና ዶክተሮች እና በልምድ በበሰሉ ጄኔራሎች የሚመራ፣ ሀገርና ወገንን የማዳን ታላቅ ዓላማ ያነገበ ስልጡንና አርቆ አሳቢ ኃይል ነው። የአማራ እናት አምጣ የወለደችው፣ የታሪክን ሚዛን የሚያስተካክለውና የመጭውን ጊዜ ብሩህ ተስፋ የሚያበራው አዲሱ ትውልድ ይህ ነው! #Dave #Amhara

ብልፅግና ያደራጃቸው ዘራፊዎች በቁጥጥር ዋሉ‼️ በደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ በብልፅግና ተደራጅተው የህዝብ መገልገያ ተቋማት ላይ ዘረፋ ሲፈፅሙ የነበሩ ዘራፊዎች እጅ ከፍንጅ ተይዘው ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል። አረመኔው እና አማራ ጠል የሆነው የአብይ አህመድ ስርዓት በደረሰበት ሽንፈት በርካታ የቀበሌ እና የወረዳ ከተሞችን እየለቀቀ በፋኖ ቁጥጥር መግባታቸውን ተከትሎ አገዛዙ በለቀቃቸው እና እንደሚለቃቸው በሚጠራጠራቸው ከተሞች ዘራፊ ቡድኖችን ማደራጀቱ ተረጋገጠ። በደቡብ ወሎ ዞን የደላንታ ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ወገል ጤና ከተማ አገዛዙ ተቋማትን እንድያወድሙ ያደራጃቸው አካላት የህዝብ መገልገያ የሆኑትን ተቋማት እያወደሙ እና ኮምፒውተሮችን እና ሌሎች ቁሳቁሶችን እየዘረፉ ሲያከማቹ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል። አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር ባደረገው ክትትል እና ከህብረተሰቡ በተገኘ ጥቆማ ሀምሌ 30/2018 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ውለዋል። በወንጀለኞቹ ላይተጨማሪ ምርመራ እየተደረገባቸው ሲሆን መጨረሻውን ለህዝባችን የምናሳውቅ ይሆናል። ከዚህም በተጨማሪ አገዛዙ በሰሜን ወሎ ዞን ስር በሚገኙ የወረዳ ከተሞች በርካታ ዘራፊ ቡድኖችን ያሰማራ መሆኑን እየገለፅን ህዝባችን እራሱን አደራጅቶ እራሱን እና የህዝብ መገልገያ ተቋማቶችን በንቃት እንድጠብቅ ስንል እናሳስባለን። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በሰሜን ወሎ ዞን መቀመጫ በሆነችው የወልድያ ከተማ በምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር ስም እያሳበቡ በህዝባችን ላይ በርካታ ዘረፋዎች እየተፈፀሙ ይገኛሉ በመሆኑም በኮራችን ስም እየተጠቀሙ ዘራፋዎችን የሚፈፅሙ አካሎችን ተከታትለን እስከምንይዛቸው ህዝባችን እራሱን ካጭበርባሪዎች እንድጠብቅ ስንል በጥብቅ እናሳስባለን አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒሊልክ ዕዝ 101ኛ ኮር ሚድያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዉን አድርሷል።   መዳረሻውን ድልና ነፃነት ያደረገው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! ©አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ! ነሃሴ 1/2018 ዓ.ም 01/12/2018 ዓ.ም

ጀግናው የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በብልፅግናው አየር ወለድ ሰራዊት ላይ ባካሄደው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ድል መቀዳጀቱን አስታወቀ! ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር፣ እራሱን "101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር" ብሎ በሚጠራው የአገዛዙ ሰራዊት ላይ ትላንት ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ባደረገው የተቀናጀ ወታደራዊ ኦፕሬሽን አኩሪ ድል መጎናፀፉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ። የአገዛዙ ኃይል መነሻውን ከመርሐቤቴ አውራጃ ሬማ ከተማ በማድረግ፣ የህዝብ አለኝታ የሆነውን የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ሰራዊት ለማጥቃት ወደ መጅት እና ቢራባ ቀበሌዎች እንቅስቃሴ አድርጎ ለማጥቃት ቢሞክርም የክፍለ ጦሩ የጦር ጠበብቶች በወታደራዊ ስልት የጠላትን ኃይል ወዳዘጋጁለት የውጊያ ቀጠና በስቦ መምታት ስልት፡ በወታደራዊ የበላይነት የሬማ ዙሪያ አካባቢዎችን በወቅቱ በቁጥጥር ስር በማስገባት ጠላት ወደ ኋላ እንዳይመለስ መንገድ በመዝጋት በተከናወነው በዚህ የተሳካ ኦፕሬሽን፣ የአገዛዙ ኃይል ከፍተኛ ወታደራዊና ቁሳዊ ኪሳራ አስተናግዷል። በዜሮ መስዋዕትነት በተጠናቀቀው በዚህ ልዩ ኦፕሬሽን የተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች፦ ➠ የተደመሰሰ የጠላት ኃይል፡ 09 ➠ የቆሰለ የጠላት ኃይል፡ ከ14 በላይ እንዳቀደው ያልተሳካለት ጠላት ከፋኖ በደረሰበት ሽንፈት የተበሳጨው ወደ መጣበት ሲመለስ እንደለመደው ንፁሀንን የበቀል እርምጃ፡ የብስጭት ማብረጃ እያለ ንፁሀን ወገኖች ከፍተኛ ድብደባ የተፈፀመባቸው ሲሆን የመጅት ቀበሌ የ8 ዓመት ታዳጊ ህፃን ቶፋው ጋሻው የተባለች እንስት በጥይት ተመታ መቁሰሏን የአይን እማኞች ተናግረዋል። ሽንፈቱን የተከናነበው ጠላት የቆሰሉት አባላቱን ለሕክምና በሬማ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና በሬማ ከተማ ጤና ጣቢያ የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና እየተደረገላቸው ሲሆን፣ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው አባላቱን ዛሬ ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም ከንጋቱ 12:30 ላይ ወደ መርሐቤቴ ዓለም ከተማ እናት ሆስፒታል መዛወራቸውን የኮሩ መረጃዎች አረጋግጠዋል። "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

መማረክን ከመሪዎቹ የተማረ ሰራዊት ! እርግጥ በ leadership አስተምህሮት የአንድ መሪ ጥሩ መለኪያዋች ውስጥ ተተኪ መሪ ማውጣት እንደሆነ መፅሐፍት ያስረዳሉ ። ብርሐኑ ጁላም ይሁን በጫ ደበሌ ተተኪ መሪ እያወጡ ይመስላል ። አስተማሪም የሚያስተምረው ተማሪ የተሻለ እንዲሆን ነው ። የብርሐኑ ጁላ ልጆቹም በዚህ እረገድ የተሻለ የመማረክ ሪከርድ እያሳዩ ነው ። ስለዚህ በፋኖ መነፅር እና በወጣንለት ዓላማ አንፃር ብርሐኑ ጁላ ጥሩ መሪ ነው ማለት ይቻላል ¡ እንዴት መከላከያ እንደሆነ ? ማንን እንደሚወጋ ? ምን ዓላማ እንደሚያሳካ ? ማንን ለማስደሰት እንደሚዋጋ ? ተጨባጭ ምክንያት ሳይኖረው ፣ ሳያውቅ እና ሳይረዳ መዳከር ላይ ይገኛል ። የህልውና አደጋ ገጥሞት በአዲሱ አቢዮተኛ ትውልድ ተወክሎ የሚዋደቅን ህዝብ እንዴት ማሸነፍ ይችላል ? መቸም ከባጫ በሶ መበጥበጥና ለጭፈራ ካልሆነ በስተቀር ይሄን ያብራራልናል ብለን አናስብም ታፍሶ የመጣ የአብይ ወንበር ጠባቂ ሀይል ቢማረክ ነገ የጦር አዛዥ የመሆን እድል እንዳለው ብርሐኑ ጁላን ምሳሌ አድርጎ የመጣ ስመ መከላከያ ፋኖ እንደተጠጋው እጅ ይሰጣል እንጅ ለድል የሚያበቃ ስነ-ልቦና ከሲሳይ አጌናም ይሁን ከባጫ ደበሌ መዋስ ስለማይችል ከፋኖ አውደ ውጊያ በኋላ መማረካቻው የተለመደ ሰበር ዜና ከመሆን ውጭ ሌላ አማራጭ የለውም ። ከሁሉም በላይ ግን አስር አለቃ ብርሐኑ ጁላ ከዚህ በፊት በመማረኩ ህይወቱን አትርፎ አሁን የሀገሪቱ ጦር አዛዥ መሆኑን የተረዳ ሰራዊት መሰዋዕት ሁኖ ያውም የአብይን አገዛዝ ለማስቀጠል ይታገላል ማለት "ገሣ ከመብረቅ ይከላከላል" እንደማለት ነው ። ይሄ አቢዮተኛ ትውልድ እንደሚነሳ በመተማመን የክልሉ ርዕሰ መዲና ባህር- ዳር ከተማ ላይ ተኩስ ከፍቶ አቢዮቱን ያስነሳን ምትሐተኛ መሪን ማለትም አርበኛ ዘመነ ካሴን ከፊቱ አድርጎ የወጣ ትውልድ እንዴት የሴት ልጅ ጡት በሚቆርጥ ሞራል የለሽ የካድሬ ዘበኛ ፋኖን ማሸነፍ ይችላል ? እንዴት ግብር እየከፈለ ደሞዝ የሚቆርጥለትን ማህበረሰብ የሚወጋ አመክንዮ የለሽ ሰራዊት በነፃ ለነፃነት የሚዋጋ ሰራዊትን ማሸነፍ ይችላል ? ይሄ ትውልድ እኮ ከአማራነቱ በተጨማሪ በስልጠና ያገኘው ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ የአስተዳደር ብቃት አለው ። ብልፅግና ዛሬ ላይ ወደ ሰሜን ክተት መክት ማርከህ ታጠቅ ብሎ የሚዘምተው ሳይሆን ዛሬ ላይ ለ3 ዓመት ሙሉ የብልፅግናን ክፍለ ጦር ተቋቁሞ እየማረከ ያለ የአማራ ሰራዊት በራሱ ላይ መዝመቱን እረስተውት ነው ? ለማንኛውም ' ውሐ ሲበላ እያሣሣቀ ' የሚለውን አባባል ፋኖ ሲያጠቃ እያስለቀሰ በሚለው አውዳዊ ፍች ቀይራችሁ ተጠቀሙበት ። ከዚህ በፊት በትርፍ ጊዚያችን እየታገልነ ከዚህ ያደረስናችሁ አሁን ላይ በሙሉ ጊዚያችን እየመጣንባችሁ ስለሆነ ቻሉት ። አሁን እኛ ፋኖዎች ብቻችን አይደለንም ከብዙ አጋሮች ጋር ብዙ መሣሪያ ታጥቀን እየመጣን ነው ። ቻሉት ልመርጥላችሁ ነው ያለን ማን ነበር ? ብርሐኑ ጁላ ወይስ ባጫ ደበሌ ? ለማንኛውም ቻሉት እኛም አንመርጥላችሁም ። ሰይፍ ከማንሳቱ በፊት በሰልፍም በደብዳቤም ሲጠይቅ መተዛዘቢያ ከማድረጋችሁ በላይ ልጆቹን ስታስሩ እና ስትገሉበት የነበረው የአማራ ህዝብ ዛሬ ፊት ለፊት ገጥሟችኋል ቻሉት ። ምን ምን እንደሚልም ቅመሱት ። በሁለት ሳምንት እናጠፋዋለን ብላችሁ ሁለት አመት ሞላችሁ ። ሶስት ጥቁር ክላሽ ነው ተሸክመው ሚወዛወዙ ብላችሁ ሹተር በሹተር አደረጋችሁን ። ፅንፈኛ ስትሉን ማርከን በዓለም ፊት ለቀይ መስቀል አስረከብን ከናንተ የተሻልነ ሐላፊነት የሚሰማን ታጋዮች እንደሆነ ዓለም አወቀን ተደመመብን ፋኖ መንግስት መሆን እንደሚችል ትዝብታቸውንም ወሰዱ ። አንድ ሐቅ ግን አለ በቁማችሁ እንደተገተራችሁ የአማራ ህዝብ አንድ የጋራ ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ርዕይ እንዲኖረው የሚያደረገውን ጉዞ አጠናቀን ትመለከቱ ዘንድ ግድ ነው ። ፋኖ የትግሉ የስበት ማዕከል ሁኖ ሌሎቹን ኢትዮጵያዊ ፀረ- ብልፅግና ኃይሎች ከምስራቅ አፍሪካ የትብብር ኃይሎች ጋር አብሮ በመሆን እነ ባጫ በጫት አፋቸው የሚያወሩለትን ቤተ መንግስት ለትክክለኛ አገር ወዳዱ ኃይል ለቀው መፈርጠጣቸው ግድ ነው ። አርበኛ ግሩም ምሳሌ በአፋብን የጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ

የንስር ሻለቃ የትግል ዝግጁነቱን ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ ልዩ የተሀድሶና የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና መድረክ ተካሔደ!!            ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ተወርዋሪው የንስር ሻለቃ፣ ህዝባዊ ትግሉን በተሻለ ስትራቴጂያዊ ዝግጁነትና ወታደራዊ ዲስፕሊን ለማጠናከር ያለመ ልዩ የተሀድሶና የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና ማሳደጊያ መድረክ በታላቅ ድምቀት አካሂደዋል።  በዓላማ ፅናትና በወታደራዊ ስትራቴጂ ዝግጁነት የታነፀው ይህ መድረክ የአማራ ህዝብ እያካሄደ ባለው ፍትሃዊ የህልውና ተጋድሎ ውስጥ የኃይል ሚዛኑን ሙሉ በሙሉ ወደ ድል ለመቀየር ያለሙ ቁልፍ ውሳኔዎች የተበሰሩበት ሆኖ አልፏል።  በመድረኩ ላይ የአፋብን ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ፣ የአፋብን መካናይዝድ ጦር መምሪያ ሃላፊ አርበኛ አብረሃም ኩራባቸውን ጨምሮ የዕዙ ከፍተኛ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች፣ የንስር ሻለቃ መሪዎች እንዲሁም በክብር እንግድነት የተገኙት የአፄ አምደፂዎን ኮር አመራሮች ተሳትፈዋል።           የመድረኩ ዋና ዋና ዓላማዎች ~ የአመራርና የሻለቃውን ወታደራዊ ብቃት ማሳደግ፡ ~የተሀድሶ መድረኩ የወታደራዊ ስልቶች ማሻሻያዎች ~ የግዳጅ አፈፃፀም ግምገማዎችንና የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን በጥልቀት በመገምገም የትግል ዝግጁነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ተማሻገር ~ርዕዮተ-ዓለማዊና ፖለቲካዊ አንድነትን ማጠናከር ~የትግሉን ፖለቲካዊ ግቦች ማስረፅ የሠራዊቱንና የአመራሩን የእርስ በእርስ ውህደትና የዓላማ አንድነት የበለጠ ለማጠናከር  ~የጋራ ትብብርና አድነትን ማጠናከር እንደ ስማቸው ሁሉ በከፍታ ላይ በመብረር የጠላትን እንቅስቃሴ ከሩቅ የሚቃኙትና የመመታት አቅማቸው ከፍተኛ የሆነው የንስር ሻለቃ አባላት በዚህ የፖለቲካና የውጊያ ተሀድሶ ይበልጥ ታድሰውና ተዘጋጅተው ለተጨማሪ ግዳጅ መቅረባቸው ተገልጿል።  ይህ የተሀድሶ መድረክ አመራርና አባላት የህዝባቸውን ነፃነት፣ ክብርና ህልውና ለማረጋገጥ የሚያደርጉትን ተጋድሎ እስከ አሸናፊነት ለመምራት ያላቸውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ሆኗል።  " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ርዕስ፡ የአማራ ድክመትና መሽሞንሞን ባለፉት 50 ዓመታት፣ በአማራ ሕዝብ ላይ በስውርና በግልጽ ማንነቱን፣ ታሪኩን፣ ሀብቱንና መሬቱን የሚወነጅል፣ የሚዘርፍና የሚያሳድድ የማይረሳ ግፍ ተፈጽሟል። ይህ አጭር ጽሑፍ ወቅታዊውን እውነታ እንድንገነዘብና የወደፊት አቅጣጫችንን እንድንጠቁም ለማስቻል የተዘጋጀ ማብራሪያ ነው። በጥናትና በመረጃም ሊደገፍ የሚችል ሀቅ ነው። የ1966ቱ አብዮት "መሬት ላራሹ" በሚሉና በተለያዩ አራማጅ መፈክሮች በመነሳቱ፣ የንጉሡ ሥርዓት በደምና በግድያ ታሪክ እንዲደመደም አድርጓል። የለውጡን ሂደት መርምሮ ማስተካከል ይቻል የነበረ ቢሆንም፣ አገሪቱ ግን የእንቁ ወርቅ የሆኑትን የአማራ ልጆቿን በማያቋርጥና አላስፈላጊ ግድያ አጥታለች። "የፊውዳል ሥርዓት ናፋቂ" በሚል አገር በቀል ባልሆነ ፍልስፍና (ርዕዮተ-ዓለም) እምነታችን ተደፍጥጦ፣ የአማራ ወግና ባህል ሲወድም ቆይቷል። አማራን የጥላቻ መነሻና መድረሻ አድርጎ የመስበኩ ተግባር እንደ ሥርዓት እምነት ተወስዶ፣ ሕዝቡን ሲቀጠቅጥና ጡት ሲነቅል ኖሯል። እንዲያውም ይህ ስብከት በየጊዜው እያሻቀበና እየከረረ ስር ሰዶ፣ ዛሬ ለደረስንበት የ"እሳት ዘመን" ዋነኛ ምክንያት ሆኗል። ይሁን እንጂ፣ "እስከ ዛሬ ድረስ ይህ ሁሉ ሲሆን ዝምታው ለምን ሰፈነ? ጠያቂውስ እንዴት ጠፋ?" የሚለው ጥያቄ ሁላችንንም ሊያሳስበን ይገባል። የደርግ ሥርዓት ከወደቀ በኋላም፣ በድጋሚ በተሻሻለውና በረቀቀው ሕገ-መንግሥት ውስጥ የፈጠራ ትረካዎች (አፈ-ታሪኮች) ደምቀውና ጠንክረው እንዲሰፍሩ ተደርጓል። በዚህም ሳቢያ በአማራ ሕዝባችን ላይ መዋቅራዊ ዝርፊያ፣ ግድያና መፈናቀል እንደ ናዳ ወርዶበታል። ለ27 ዓመታት በሕወሃት/ኢሕአዴግ መሪነት የተዘራው የጥላቻ መርዝ አብቦ፣ ዛሬ የመኖርና አለመኖር የህልውና እጣ ፈንታ ውስጥ ጥሎናል። ከሐረርጌ እስከ አርሲ፣ ከወለጋ እስከ ናዝሬት (አዳማ) እንዲሁም እስከ አዲስ አበባ ድረስ የሸዋ ታሪካዊ መሬቶች ላይ የሚኖረውን አማራ "መጤ" በማለት የማፈናቀል፣ ከአስተዳደር መዋቅር የማስወገድና "ነፍጠኛ" በሚል ስም የማጥፋት ዘመቻ በግድያ ታጅቦ ተከናውኗል። "ብሔር ብሔረሰቦች" በሚል የሽፋን ስም በአማራው ላይ የከረረ በደል ሲያሸክሙት ቆይተዋል። ይህንን ሁሉ ግፍ የጠጣው የአማራ ማኅበረሰብ ግን አሁን "በቃኝ!" በማለት ማንነቱንና ታሪኩን በወርቅ ቀለም ለመጻፍ ቆርጦ ተነስቷል። የፋኖ መነሳት ታሪኩን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማብሰርና ልክ እንደ አባቶቹ ጣሊያንን እንደመከቱት ሁሉ፣ ዛሬም ወደ ሚኒሊክ ቤተ-መንግሥት (አራት ኪሎ) ለመጓዝ የጀመረውን ጉዞ ያሳያል። የቀድሞውን ሥርዓት የተካውና ስልጣን ላይ ያለው የብልጽግና (ኦህዴድ/ኦፒዲኦ መራሹ) ሥርዓት ደግሞ ይህንኑ መዋቅር በማሻሻል፣ ዓለም አይቶት የማያውቅ ዘግናኝ የወንጀል ድርጊቶችን ፈጽሟል። ይህ ለታሪክና ለትውልድ በሰነድና በመረጃ የሚቀርብ ይሆናል። የብልጽግና መሪዎችና ደጋፊዎቻቸው ከተጠያቂነት አያመልጡም። የተሰውት ንጹሐን የአማራ ሕዝቦችና የፋኖ ጀግኖች አጽም፣ እስከ እለተ ሞታችን ድረስ ፍትሕን እንድንጠይቅ ግድ ይለናል።ታዲያ በዚህ ሁሉ ሂደት ውስጥ ሁል ጊዜ የሚያስደነግጠኝና እረፍት የሚነሳኝ ነገር ቢኖር፡ "ይህ ሁሉ ግፍ ሲፈጸም ‘ወገን’ የምንለው    አማራዎች '  ለምን ዝምታን መረጡ?" የሚለው ጥያቄ ነው  ምንጩ #ጆ #ዘአሜሪካ ነው

ርዕስ፡ የአማራ ድክመትና መሽሞንሞን ባለፉት 50 ዓመታት፣ በአማራ ሕዝብ ላይ በስውርና በግልጽ ማንነቱን፣ ታሪኩን፣ ሀብቱንና መሬቱን የሚወነጅል፣ የሚዘርፍና የሚያሳድድ የማይረሳ ግፍ ተፈጽሟል። ይህ አጭር ጽሑፍ ወቅታዊውን እውነታ እንድንገነዘብና የወደፊት አቅጣጫችንን እንድንጠቁም ለማስቻል የተዘጋጀ ማብራሪያ ነው። በጥናትና በመረጃም ሊደገፍ የሚችል ሀቅ ነው። የ1966ቱ አብዮት "መሬት ላራሹ" በሚሉና በተለያዩ አራማጅ መፈክሮች በመነሳቱ፣ የንጉሡ ሥርዓት በደምና በግድያ ታሪክ እንዲደመደም አድርጓል። የለውጡን ሂደት መርምሮ ማስተካከል ይቻል የነበረ ቢሆንም፣ አገሪቱ ግን የእንቁ ወርቅ የሆኑትን የአማራ ልጆቿን በማያቋርጥና አላስፈላጊ ግድያ አጥታለች። "የፊውዳል ሥርዓት ናፋቂ" በሚል አገር በቀል ባልሆነ ፍልስፍና (ርዕዮተ-ዓለም) እምነታችን ተደፍጥጦ፣ የአማራ ወግና ባህል ሲወድም ቆይቷል። አማራን የጥላቻ መነሻና መድረሻ አድርጎ የመስበኩ ተግባር እንደ ሥርዓት እምነት ተወስዶ፣ ሕዝቡን ሲቀጠቅጥና ጡት ሲነቅል ኖሯል። እንዲያውም ይህ ስብከት በየጊዜው እያሻቀበና እየከረረ ስር ሰዶ፣ ዛሬ ለደረስንበት የ"እሳት ዘመን" ዋነኛ ምክንያት ሆኗል። ይሁን እንጂ፣ "እስከ ዛሬ ድረስ ይህ ሁሉ ሲሆን ዝምታው ለምን ሰፈነ? ጠያቂውስ እንዴት ጠፋ?" የሚለው ጥያቄ ሁላችንንም ሊያሳስበን ይገባል። የደርግ ሥርዓት ከወደቀ በኋላም፣ በድጋሚ በተሻሻለውና በረቀቀው ሕገ-መንግሥት ውስጥ የፈጠራ ትረካዎች (አፈ-ታሪኮች) ደምቀውና ጠንክረው እንዲሰፍሩ ተደርጓል። በዚህም ሳቢያ በአማራ ሕዝባችን ላይ መዋቅራዊ ዝርፊያ፣ ግድያና መፈናቀል እንደ ናዳ ወርዶበታል። ለ27 ዓመታት በሕወሃት/ኢሕአዴግ መሪነት የተዘራው የጥላቻ መርዝ አብቦ፣ ዛሬ የመኖርና አለመኖር የህልውና እጣ ፈንታ ውስጥ ጥሎናል። ከሐረርጌ እስከ አርሲ፣ ከወለጋ እስከ ናዝሬት (አዳማ) እንዲሁም እስከ አዲስ አበባ ድረስ የሸዋ ታሪካዊ መሬቶች ላይ የሚኖረውን አማራ "መጤ" በማለት የማፈናቀል፣ ከአስተዳደር መዋቅር የማስወገድና "ነፍጠኛ" በሚል ስም የማጥፋት ዘመቻ በግድያ ታጅቦ ተከናውኗል። "ብሔር ብሔረሰቦች" በሚል የሽፋን ስም በአማራው ላይ የከረረ በደል ሲያሸክሙት ቆይተዋል። ይህንን ሁሉ ግፍ የጠጣው የአማራ ማኅበረሰብ ግን አሁን "በቃኝ!" በማለት ማንነቱንና ታሪኩን በወርቅ ቀለም ለመጻፍ ቆርጦ ተነስቷል። የፋኖ መነሳት ታሪኩን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማብሰርና ልክ እንደ አባቶቹ ጣሊያንን እንደመከቱት ሁሉ፣ ዛሬም ወደ ሚኒሊክ ቤተ-መንግሥት (አራት ኪሎ) ለመጓዝ የጀመረውን ጉዞ ያሳያል። የቀድሞውን ሥርዓት የተካውና ስልጣን ላይ ያለው የብልጽግና (ኦህዴድ/ኦፒዲኦ መራሹ) ሥርዓት ደግሞ ይህንኑ መዋቅር በማሻሻል፣ ዓለም አይቶት የማያውቅ ዘግናኝ የወንጀል ድርጊቶችን ፈጽሟል። ይህ ለታሪክና ለትውልድ በሰነድና በመረጃ የሚቀርብ ይሆናል። የብልጽግና መሪዎችና ደጋፊዎቻቸው ከተጠያቂነት አያመልጡም። የተሰውት ንጹሐን የአማራ ሕዝቦችና የፋኖ ጀግኖች አጽም፣ እስከ እለተ ሞታችን ድረስ ፍትሕን እንድንጠይቅ ግድ ይለናል።ታዲያ በዚህ ሁሉ ሂደት ውስጥ ሁል ጊዜ የሚያስደነግጠኝና እረፍት የሚነሳኝ ነገር ቢኖር፡ "ይህ ሁሉ ግፍ ሲፈጸም ‘ወገን’ የምንለው አማራዎች ' ለምን ዝምታን መረጡ?" የሚለው ጥያቄ ነው ምንጩ #ጆ #ዘአሜሪካ ነው

የሕልውና ተጋድሎ እና የታሪካዊው አባትነት ​አንድ ሕዝብ የመኖር መብቱ አደጋ ላይ ሲወድቅ፣ በገዛ ቀዬው እንደ ባእድ ሲቆጠር እና ሰብአዊ ክበሩ ሲገፈፍ ዝምታ ከበደሉ ይበልጣል። ባለፉት ዓመታት በአማራ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ማንነትን መሠረት ያደረገ ግፍ፣ መፈናቀል እና ስቃይ የትውልድን ሕሊና የሚፈታተን ከባድ የታሪክ እጥፋት ሆኗል። የንጹሃን እንባ፣ የእናቶች አለቀስ እና የሕፃናት ተስፋ መቁረጥ የትኛውንም ድንበር ተሻግሮ የሁሉንም ሰው የሕሊና ደወል ያናውጣል። ​በኢትዮጵያ የታሪክ ድማቅ ገጽ ላይ አቡነ ጲጥሮስ ለሕዝባቸው ፍትሕ እና ለሀገራቸው ክብር ሲሉ በፋሺስት ግፍ ፊት ሳይበገሩ እውነትን መስክረው አልፈዋል። ዛሬም ሕዝብ በመከራ ማዕበል ውስጥ በሚያልፍበት በዚህ ፈታኝ ወቅት፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የዚያን ታላቅ ሰማዕትነት በመከተል የሕዝባቸው ጋሻና መከታ ሊሆኑ ይገባል። ​"አባቶች ከቻላችሁ እንደ አቡነ ጲጥሮስ ሁሉ ይህ አረመኔያዊ ሰርዓት ዘር ቀለም ሙስሊም ክርስቲያን አልፎም ወንድ ሴት ሳይል አማራ ከምድር ገፅ ሊያጠፋ የተነሳ ነው ከቻላችሁ እንደ አቡነ ጲጥሮስ ሁኑ ከአማራ ፋኖ ጋር ሁኑ ​እውነተኛ አባትነት እና የታሪክ ባለደራሽነት የሚለካው ሕዝብ መከራ ውስጥ ሲወድቅ አብሮ በመቆም፣ የደከመውን በማበርታት እና ፍትሕን በመሻት ነው። የመከራው ሌሊት አልፎ የፍትሕ እና የሰላም ንጋት እንዲበራ የሁሉም የሕሊና ባለቤት ከበደለኞች ይልቅ ከተበደለው ሕዝብ ጎን መቆም ወቅቱ የሚጠይቀው የማይታለፍ ታሪካዊ ኃላፊነት ነው። አባቴ ፈጣሪ ይባርክዎ ፈጣሪ ክብር ያድልልኝ ውድ ልጅዎ #Dave #Amhara

ከህልዉና ትግሉ ጎን ለጎን ህዝባዊ መድረኮች ተጠናክረዉ ቀጥለዋል! በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ አግሪት -አስፋ ፀበላት ክላስተር የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ መድረክ አካሔደ። በንቅናቄ መድረኩ ከማህበረሰቡ ጋር ሰፊ ዉይይት የተደረገ ሲሆን ሕዝቡም በመቄትና አካባቢው ካሉ የፋኖ ኃይሎች ጋር የተጀመረው ትስስር እና አንድነት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አውንታዊና ጠንካራ ምክር-ሃሳቦችን የሰጠ ሲሆን ፋኖ የአማራ ሕዝብ ስርዓት ወለድ በሆነ መንገድ የገጠመውን ሁለተናዊ የሕልውና አደጋ ለመቀልበስ የሚያደርገውን ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል በሙሉ ልብ ሁለተናዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን በመድረኩ ቃል ገብቷል። ማህበረሰቡ በትግሉ ተደራሺነትና ቅቡልነት ዙሪያ እንዲሁም በድርጅታዊ ዕድገትና የዲፕሎማሲ ስራዎች ዙሪያ ጠንካራ ሃሳቦችን ሰንዝሯል።  ሰራዊቱ ፍፁም ለትግሉ የታመነ ፣ በጥሩ ሰነ-ምግባር የታነፀ ፣ ለጓዱና ማህበረሰቡ ክበር ያለው እንዲሆን ድርጅቱ አበክሮ መሰራት እንዳለበት ማህበረሰቡ ያሳሰበ ሲሆን በድርጅታዊ ዕደገትና ዓለም አቀፍ ተቀባይነትን ድርጅቱ በእጅጉ ማሳደግ አለበትም ብሏል። ሌላው ፋኖ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች የትምህርት ፣ የጤና ፣ የግብርና እና ሌሎች አገልግሎቶች በአግባቡ እንዲፈፀሙ ፋኖ እያደረገ ያለውን አዎንታዊ ድጋፍ አድንቀው በህዝብ ሀብት የተገነቡ ተቋማትን ማህበረሰቡም ይሁን ፋኖ መጠበቅ እንዳለበት በመድረኩ ማህበረሰቡ ገልጿል። በመድረኩ  የአማራ ፋኖ ብራሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የአደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አሰፋ መሰለ፣ የዕዙ ዕቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አራጋው ያለው እና የዕዙ ም/ሕዝብ አስተዳደር ኃላፊ አርበኛ ጋሻው ሙሉጌታ እና የመቄት ወረዳ ጊዜያዊ ሕዝብ አስተዳር አመራሮች የ303ኛ እንዲሁም  81ኛ ክፍለ ጦር እመራሮችና የ16ኛ(106) ኮር 22ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች  የተገኙ ሲሆን ለንቅናቄ መድረኩ የሚመጥን በሁሉም ዘርፍ ማብራሪያ ተስጥቷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን  መምሪያ!! ቀን 29/11/2018 ዓ.ም