ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Открыть в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Больше2 936
Подписчики
+1424 часа
+3877 дней
+38530 дней
Архив постов
ሐምሌ30/11/2018 ዓ.ም 24ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል=================================
የአማራ ህዝብን እንደ ህዝብ ለማጥፋት ቆርጦ የተነሳው አብይ አህመድ ቅጥረኛ ሰራዊት እና ምስለኔዎች ዛሬም ታሪክ ይቅር የማይለውን አስነዋሪ ተግባር በአማራ ክልል በምስራቅ ጎጃም ዞን ጎዛምን ወረዳ በምትገኘው ገደማላ ቀበሌ በገደማላ አንደኛ ደረጃ ት/ት ቤት፣ በገደማላ ጤና ኬላ እና በእንስሳት ህክምና በሚሰጥበት ተቋም ላይ የበቀል በትርሩን አሳርፋል።
በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምዕ/ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 24 ክ/ጦር የቦቅላ አባይ ሻለቃ ስር የምትገኘው ገደማላ ቀበሌ በገደማላ 1ኛ ደረጃ ት/ት ቤት፣በጤና ኬላ ፣በማህበራት፣በጤና ባለሙያዎች ቤት፣በምህራን ቤት አና የእንስሳት ህክምና ተቋማትን ከሁለት ሳምንት በላይ ካንፕ አድሮጎ የቆየውና በየቤተክርስትያኑ በመዞር መስከረም ወር ላይ ትምህርት ላስጀምር ነው እያለ የድስኩር ፓለቲካውን ሲነዛ የነበረው የወረደውና የቀበሌዎ ካቢኔ/አመራር/ አንኳንስ በመስከረም ትምህርት ሊጀምር ይቅርና ትምህርትቤቱን አና የትምህርት ቤቱን ንብረት አስር መስከረሞችን ጠብቆ ዳግም እንዳይነሳ ጤና ኬላውን ሙልጭ አድርጎ ዘር ፎ እና የኢትዮ ቴለኮም ታዎር የሶላር ሲስተሙን በመቁረጥ ከስራ ውጭ አድርጎ ሙሉ በሙሉ አውድሞ የጤና ጎዙን ጠቅልሎ ሌላ ለጥፍት ያቀደውን ት/ት ቤት ጤና ኬላ እና የህዝብ መገልገያ ተቋማትን ፍለጋ በከባድ መሳሪያ ታግዞ ጮቄውን ክፍል ወረራ ቢፈፅምም በክንደ ነበልባሎቹ ፋኖዎች እየተገረፈ ይገኛል።
እኛም እንለላለን የተከበርከው ታላቁ የአማራ ህዝብ ሆይ አረመኔውና ጉጅሌው የአብይ አህመድ ጦር የአማራን ህዝብ ከምድረ ገፅ ለማጥፋት ቆርጦ መነሳቱን ከዚህ በላይ ማሳያ የለምና ከዚህ ከታወጀብን የዘር መጥፋት አደጋ ብቸኛው መዳኛ መንገድ ከፈጣሪ ቀጥሎ ክንድህ ነውና መሳሪያህን ወልውለህ ክንድህን አፈርጥመህ ከጀግናው ፋኖ ጋር ትቀላቀሉ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!!!
አዲስ ትውልድ አዲስ ተስፋ አዲስ አስተሳሰብ!!!!
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት
የወረኢሉ ህዝብ እንባ እና የከንቲባው ዘረፋ ለልማት የተመደበው በጀት ለጥቂቶች ኪስ መሙያ ሆነ!
የህዝቡ ህመም እና የሀብቱ ምዝበራ እየተካሄደ ያለው የወረኢሉ ከተማ ነዋሪዎች የመልካም አስተዳደር እጦት፣ የንጹህ ውሃ፣ የመንገድ እና የልማት ጥያቄዎቻቸው እንዲመለሱላቸው በአይን እያለቀሱ ባሉበት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት፤ ለህዝቡ እንባ ማበሻ ሊውል የታሰበው የህዝብና የመንግስት ሀብት በከንቲባውና በስራ ባልደረቦቻቸው አማካኝነት ያለአንዳች ርህራሄ ሲዘረፍ ውሏል።
የከተማው አስተዳደር ይፋ ያደረገው የ2018 ዓ.ም የበጀት ክንውን እንደሚያሳየው፣ የህዝቡን ህይወት ሊቀይሩ የሚችሉ ስራዎች ሙሉ በሙሉ ችላ በማለት ለህዝብ ልማት የተዘጋው በር ለከተማዋ የካፒታል ፕሮጀክቶች እና ለልማት ስራዎች ከተመደበው 89.8 ሚሊዮን ብር ውስጥ ለህዝብ ጥቅም ላይ የዋለው 13.7% (12.3 ሚሊዮን ብር) ብቻ ነው! የተቀረው የህዝቡ ተስፋና የልማት በጀት በጨለማ ውስጥ እንዲቀር ተደርጓል።
የስልጠና እና አበል ሽፋንዐለስራ ማስኬጃ ከተመደበው 32.1 ሚሊዮን ብር ውስጥ 26.2 ሚሊዮን ብሩ (81.78%) "ለስልጠና እና ለአበል" በሚል ሽፋን በጥቂት አመራሮች ተመዝብሮ ተበልቷል። በዚህም ከንቲባው ጽህፈት ቤት የዘረፋው ማዕከል ከተመዘበረው 26.2 ሚሊዮን ብር ውስጥ 14 ሚሊዮን ብሩ በቀጥታ በከንቲባ አቶ አቡሽ ይመር አሊ እና በአስተባባሪ አመራሮቻቸው አማካኝነት የተወሰደ መሆኑ ይፋ ሆኗል።
እውነቱን የተናገሩት የቁራጭ እንጀራ ስጋት ውስጥ ወድቀዋል! ይህ ሁሉ ግፍ አልበቃ ብሎ... የህዝቡ ሀብት መጠፋቱን አይተው ማለፍ ያልቻሉትና እውነታውን በህዝብ ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ይፋ ያደረጉት የበጀት አስተዳደሩ አቶ ዘውዱ ፀጋው፣ በአሁኑ ሰዓት በከንቲባውና በአስተባባሪ ኮሚቴው ከፍተኛ ማስፈራሪያና ጫና እየደረሰባቸው ይገኛል።
ለህዝብ አጋልጠህ ሰጥተኸናል፤ ይህንን መረጃ ካላጠፋህ ትታሰራለህ!" በሚል የቀረበላቸው ማስፈራሪያ፣ የፍትህ እና የእውነት ድምጽ ለማፈን የተሄደበትን አስከፊ መንገድ ያሳያል። የወረኢሉ ህዝብ የሚበላው አጥቶ፣ ልማት ናፍቆት እያለቀሰ በብልፅግና ሆድ አደሮች የብአዴን ካድሬ አመራሮች የህዝብን ሀብት እንዲህ ሲበዘብዙ ዝም ሊባል አይገባም! የሚመለከተው አካል በአስቸኳይ ጣልቃ በመግባት ይህንን ምዝበራ እንዲያስቆም እና ለህዝቡ እንባ ምላሽ እንዲሰጥ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ሲሉ የወርኢሉ ነዋሪዎች ገለፁ!
ታሪክን የሚቀይር አብዮት፦ የአማራ ፋኖ የማይበገረው ጉዞ!
በዓለማችን ታሪክ ላይ አዲስ ምዕራፍ እየተጻፈ ነው! የአማራ ፋኖ የሞት ፍርሃትን ድል አድርጎ፣ ለጽናትና ለፍትሕ ራሱን አሳልፎ የሰጠ የክፍለ-ዘመናችን አስደናቂ ትውልድ!
የዝምታው መስበር እና የታሪክ ጥሪ ፍትሕ በተደፈረበትና የሕልውና ስጋት በተደቀነበት ምድር፣ ይህ ትውልድ የሕዝቡን ጋሻ ለመሆን ነፍጥ አነሳ። የገዥው አካል የሐሰት ትረካዎችና ውጫዊ ሽፋን እንደ እንቧይ ካብ ሲፈርስ፣ ፋኖ ግን የነፃነትና የታላቅ ዓላማ ምልክት ሆኖ በአምባገነንነት ላይ የፅናት ግንብ አቆመ!
ከጦር መሣሪያ በላይ የሆነ ኃይል የፋኖ የበላይነት ከጦር መሣሪያ ብዛት የሚመነጭ አይደለም፤ ይልቁንም የማይናወጥ እውነት፣ የታሪክ ልዕልና እና የጽኑ ሞራል ውጤት ነው! በጦር ሜዳው ብቻ ሳይሆን በሐሳብና በጽናት የበላይነት ዓለምን የሚያስደምም የነፃነት አርማ ሆኗል።
የነገዋ ዓለም አቀፍ የሰላም ተስፋ ይህ አዲስ ትውልድ የታሪክ መዛባቶችን በማቅናት፣ ፍትሕና እውነት የሚነግሱባትን ብሩህ ነገ ለመገንባት የተነሳ ባለ-አሻራ ነው።
ፋኖነት በአንድ እይታ፦
• ትላንት፦ የጀግንነትና የታሪክ መነሻ!
• ዛሬ፦ የሕልውናና የነፃነት ጋሻ!
• ነገ፦ የቀጠናው የሰላምና የፍትሕ ዋስትና! #Dave #Amhara
በማጀቴ ቀጠና የቀበሌዎች አስተዳደራዊ መዋቅር ማሻሻያ ማካሄዱ ተገለፀ!!
ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ የይፋትና ጥሙጋ አውራጃ የማጀቴ ቀጠና የትግል እንቅስቃሴን ይበልጥ ለማጠናከር እና የህዝቡን የደጀንነት ሚና ለማሳደግ ያለመ ሰፊ ህዝባዊ መድረክ በቀን 29/11/2018 ዓ.ም ተካሄደ።
ከዕዙ አመራሮች በተጨማሪ ከኮር እና ከክፍለ ጦር አመራሮች ጋር በመቀናጀት በተለያዩ ቀበሌዎች በመገኘት ከህዝቡ ጋር ጥልቅ ውይይት ተደርጎ መዋቅራዊ ማሻሻያ ማድረጋቸውን ኮሩ ገለፀ። ውይይቱ በሦስት ቀበሌዎች በገተም ጎጆ ውሃ፣ በካብና ሳር አምባ ደጉቼ እንዲሁም በሰለሎ ሚራሚር ቀበሌዎች ተካሒዷል።
በውይይቱ የመዋቅር ማሻሻያ ማድረግ ያስፈለገበትን ወታደራዊ እና ህዝባዊ ምክንያት በተመለከተ ከአመራሮች ሰፊ ማብራሪያ የተሠጠ ሲሆን፣ ከህዝቡ ለተነሱ ጥያቄዎች ግልጽ ምላሽ ተሠጥቷል።
በመድረኩ የተገኙ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ወቅታዊውን የትጥቅ ትግል ደረጃ፣ የኃይል ቁመና እና የቀጣይ ግቦችን በተመለከተ ማብራሪያ በመስጠት፤ ህዝቡ ለተቀናጀው የነጻነት እና የህልውና ትግል ደጀንነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥልና ለቀጣይ ወታደራዊ ስምሪቶች የነቃ ዝግጁነት እንዲኖረው ጥሪ አቅርበዋል።
የአካባቢው ነዋሪዎችም በበኩላቸው የትግሉ ባለቤት እና ዋና ደጀን መሆናቸውን በመግለጽ፤ ከልማት፣ ከመልካም አስተዳደር እና ከመሰረታዊ አቅርቦቶች ጋር ተያይዘው ለቀረቡ ጥያቄዎች ከአመራሩ አጥጋቢ ምላሽ ማግኘታቸውን አረጋግጠው፡ አዲስ የተሾሙት አመራሮችም ሕዝባቸውን በኃላፊነት፣ በታማኝነት፣ በቅንነት ለማገልገል ቃለ መሀላ በመፈፀም ውይይቱ ተጠናቋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነዉ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ወገኖቼ ሆይ! ተመልከቱ! ጠላት ከአራቱም አቅጣጫ በቁጥር ብዛት ሊያስፈራራን፣ በሃይሉ ሊያንበረክከንና ታሪካችንን ሊያጠፋ ተነሥቷል። ነገር ግን የእኛን መሠረት፣ የእኛን ደምና የውስጥ ማንነት አያውቅም።
እኛ ውጊያን ፍለጋ አንሄድም፤ የሰውን መሬትና ክብር አንመኝም። ነገር ግን መብታችንና ማንነታችን ሲነካ፣ ድንበራችን ሲደፈር አንሸሽም። እኛ አማራዎች ነን፤ ጦርነት ለእኛ ሰርጋችን ነው!
ለሀገር፣ ለክብርና ለማንነት የሚከፈል መስዋዕትነት ለእኛ የልቅሶና የሐዘን ምክንያት አይደለም፤ ይልቁንም በወኔ የምንቀበለው፣ በሺህ እልልታና ፉከራ የምናደመቀው የጀግንነት ድግሳችን ነው።
አባቶቻችን በየዘመናቱ የመጡትን የወረራ ማዕበሎች እንዴት እንዳከሸፉት፣ የታሪክ ማህደራት ምስክሮች ናቸው። በየትኛውም አቅጣጫዎች የመጡብንን ታሪካዊ ጠላቶች በጥበብ የመመከት ጀግንነት ከአባቶቻችን የወረስነው ተፈጥራዊ ፀጋችን ነው።
ይህ ጥበብ በደማችን ውስጥ ያለ፣ ከእናታችን ጡት ወተት ጋር የጠጣነው፣ ከተራሮቻችን ጽናትና ግርማ የወሰድነው ድንቅ ስጦታችን ነው። ጠላት በብዛትና በሜካናይዝድ መሳሪያ ሲመጣ፣ እኛ በመስዋዕትነት፣ በበሰለ የጦር ጥበብ፣ በማይወላወል አንድነትና በጽኑ ወኔ እንመልሰዋለን! ይህች ምድር የነፃነት እንጂ የባርነት አፈር አላበቀለችም!
የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር1ኛ ዙር ኮማንዶ ተመራቂዎች #Dave #Amhara
ታሪክ ጠንቅቆ የሚያውቀን፣ ፈጣሪ በጥበቡ ውብ አድርጎ የፈጠረን ነን! በአማራነታችን ውብ ሆነው ከተፈጠሩት የዓለማችን ሕዝቦች መካከል የፊት መስመሩን ድርሻ የምንወስድ ነን።
የአሳምነው፣ የበላይ፣ የቴዎድሮስ... ደግሞም የሚኒልክ ጀግንነት ማንነታችንን ከተፈጥሮ ጋር አብሮ ያስተሳሰረን ነን፤ ኃያላን አገራት በውበታችንና በጀግንነታችን የሚመኩብን አማራውያን ነን!
ለሚወዱን ራሳችንን አሳልፈን የምንሰጥ የጀግና ልጅ ጀግኖች ነን። ከጎንደር ከጎጃም፣ ከወሎ፣ ከሸዋ እና ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በፍቅርና ተሳስረን የምንኖር፣ ተፈጥሮ በጸጋዋ አሸብርቃ የፈጠረችን ነን። #Dave #Amhara
#ለሆዳአደር_ባንዳ_ምህረት_የለንም‼️
አመራር እንዲመታ ተልኮ የተሰጠው ሰው በላው አልሳካለት ሲል አንድ ፋኖ መቶ ጠላት ሊቀላቀል ያለ ባንዳ በቁጥጥር ስር ዋለ!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር 99ኛ ክ/ጦር የኢንጅነር ሻለቃ በዋድ ቀጠና የፋኖ አመራር እንዲመታ ተልኮ የተሰጠው #ባዩ ሞሴ የተባለ ግለሰብ የተሰጠው ተልኮ አልሳካለት ሲል አንድን #የፋኖ_አባል_በመግደል እና የአንድ የፋኖ አባል መሳርያ በመዋስ ወደ #ጠላት_ሊቀላቀል እንቅስቃሴ ላይ እያለ #በኢንጅነር_ክበር_ተመስገን_ሻለቃ አባላት ብርቱ እርብርብ በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል።
የሆድ አደር እና ባንዳ ምህረት የለንም ።
በከንቱ የአማራን ደም የሚያፈሱ ሁሉ ደማቸው ይፈሳል።
©#99ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት መምርያ!
29/11/2018 ዓ.ም
+2
የ75ኛ ክ/ጦር የ1ኛ ሻለቃ ም/አዛዥ ፻ አለቃ ምተኩ ተደመሰሰ"‼️
ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም
====================
የ206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር የማይበገሩት የደባይ ጮቄ ሻለቃ ፻ አለቃ ምትኩ የተባለውን የሻለቃ አዛዥ ጨምሮ በርካታ የጠላትን አስክሬንን በማደራረብ ጀብድ ሰርተዋል።
በአምስት አቅጣጫ በመንቀሳቀስ በደባይ ጠላት ግን ወረዳ ወረራ የፈፀመው የአረመኔው ሰራዊት በማይበገሩት የደባይ ጮቄ ሻለቃ በተቀናጀ መልኩ በወሰዱበት ጥቃት ፻ አለቃ ምትኩ የተባለውን የሻለቃ ም/አዛዥ ጨምሮ በርካታ ሰራዊቱ በጀረምስ ግንባር ተደምስሷል።
የጠላትን የማጥቃት ዕቅድ በመረዳት ጠላትን ወደ ስበት ማዕከል በማስገባት ከፍተኛ ጥቃት የከፈቱት የ206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ደባይ ጮቄ ሻለቃ እና የቦቅላ አባይ ሻለቃ ደግሞ ጠላትን ከበባ ውስጥ በማስገባት በሌላ አቅጣጫ ሙትና ቁስለኛ እያደረጉት ይገኛል። ትንቅንቁ በበርካታ አካባቢዎች የቀጠለ ሲሆን ጠላት የተከበበውን ሰራዊት ለማውጣት መድፍ፣ ዙ-23 ፣ ሞርተር ተጠቅሟል ከበባ ውስጥ ያለው ጠላት መውጣት አልቻለም።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ!
©የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት!
29/11/2018 ዓ.ም
የአፋብን|ቴዎድሮስ እዝ‼
"በአማራ ህዝብ ማህበረሰባዊ ታሪክ፥ በኢትዮጲያ ዘመናዊ የፖለቲካ ታሪክ፥ በአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ እጅግ ወሳኝ የታሪክ ምእራፍ ላይ እንገኛለን። በዚህ ምእራፍ መቀመጥም፥ መተኛትም መሳሳትም ዳግሞ እድልና ይግባኝ የሌላቸው መጥፊያዎች ናቸው። ስለዚህ ለወርቃማው አላማችን ሌት ተቀን እንሰራለን፥ በስሌት እንጓዛለን። እናሸንፋለን!"
አርበኛ ዘመነ ካሴ
አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር በሸበል በረንታ ወረዳ የዕድውሃ ከተማ በሰርጎ ገብ ጥቃት ባንዳ ላይ እርምጃ ወሰደ!!
64ኛ ክ/ጦር ሀምሌ 29/3018 ዓ.ም
~~~~~~
ባንዳ ቅጣው ሃብታሙ በሸበል በረንታ የዕድውሃ ከተማ ኖሪ ሲሆን በየዕድውሃ ከተማ የአገዛዙ ብልፅግና ገዳይ ቡድን በአዘጋጃቸው የተለያዩ መድርኮችና በምክክር ኮምሽነር መድረክ የአማራ ፋኖን ስም በማጥፋት ለአገዛዙ ሽፋን በመስጠት የሚታወቅ ቀንደኛ ባንዳ ነው።
በየዕድውሃ ከተማ ክላሽ እንኮፕ፣ እስታር ሽውጡን በመያዝ በፋኖ ሀይሎች ከፍተኛ ንቀትና የሐሰት ስም ማጥፋት ዘመቻ በማካሄድ የሚታወቀው ወደል ባንዳ ከአማራን ህዝብ ገዳዩች ጋር በማበር በሀብቱ፣ በጉልበቱና የፋኖን እንቅስቃሴ በመመረጅ ለብልፅግና አገዛዝ መረጃ በማገዝ ከፍተኛ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል።
ባንዳ ቅጠው ሀብታሙ በሸበል በረንታ የዕድውሃ ከተማ በተለያዩ መንገድ የተያዙ ግለሰቦች ፋኖ ናቸው ከተማ ላይ መሰቀል አለባቸው፣ የፋኖ ቤተሰብ መረሸን አለበት በማለት በተለያዩ የአገዛዙ መድርኮች እርህራሄ በሌለው አንደበቱ ሲናገር ቆይቷል። በመጨረሻም ይህ ወደል ባንዳ በ64ኛ ክ/ጦር ከፍተኛ ክትትል አማካኝነት ሀምሌ 29/2018 ዓ.ም በየዕድውሃ ከተማ በጠራራ ፀሀይ እርምጃ ተወስዶበታል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ ተስፋ፣ አዲስ አስተሳሰብ!!
ሀምሌ 29/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክፍለ ጦር ሕዝብ ግንኙነት
+1
ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም
ሰሞኑን ከእየ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች ተወጣጥቶ ስምሪት የተሰጠው የአገዛዙ ቅልብ ሀይል በመጀሪያ ስምሪቱ የጥይት ሰለባ ሆነ !
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ (5ኛ) ኮር አካል በሆነው የግዙፋ ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ቀጠና ላይ ሰሞኑን ከእየ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች ተወጣጥቶ ሰልጥኖ ስምሪት ተሰጥቶት ወገራ ወረዳ ሰንበትየ እና ጉንትር አቦ ቀበሌዎች በሌሊት የገባው የአገዛዙ ወንበር አስጠባቂ ሀይል ያልጠበቀው ገጥሞት የጎንደሬዎችን ክንድ ሲቀምስ ውሏል።
የጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር አሀድ በሆኑት የቴዎድሮስ ብርጌድ ነጋሪት ሻለቃ እና የአጥናፋ ብርጌድ እያየይ አስምሮ ሻለቃ አባላት ፊት ለፊት ተጋድሎ እንዲሁም በይታየው ብርጌድ አባላት ግራና ቀኝ ክንፍ ድጋፍ ሰጭነት ጠላትን መፈናፈኛ ነስተውት ውለዋል። ዛሬ ነሀሴ 29/2018 ዓ/ም ከንጋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ ስምንት ሰዓት በተደረገው ከፍተኛ አውደ ውጊያ ከጠዳ ዩኒቨርስቲ የሰለጠነው የአገዛዙ ጥምር ባንዳ ብትንትኑ ወጥቶ የድረሱልን ጥሪ አሰምቶ ከዳባት፣ ከገደብየ እና ከአምባጊዎርጊስ ከተሞች መከላከያ ተብየው በዙ _23 እና በዲሽቃ ታጅቦ ድጋፍ በመስጠት ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ወደ ገደብየ ከተማ ፈርጥጦ ተመልሷል።
በአውደ ውጊያው ከ11 በላይ ባንዳ ላይመለስ እስከ ወዲያኛው ሲሸኝ ከ8 በላይ የሚሆነው ደግሞ ከከባድ እስከ ቀላል ቁስለኛ አስተናግዷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
#_11የሚሊሻ_አባላቶች_ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው ፋኖን ተቀላቅለዋል።
►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
..........ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም
የአገዛዙ ብልፅግና ስረዓት አስፈፃሚ የነበሩ 11 የሚሊሻ አባላት 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር የተቀላቀሉት፦
1ኛ.እያለ እንደ......ሚሊሻ
2ኛ.እያያ ከባዱ.......ሚሊሻ
3ኛ.ካሳ አብየ.........ሚሊሻ
4ኛ.በለጠ አብየ......ሚሊሻ
5ኛ.ጋሎ አብየ.......ሚሊሻ
6ኛ.ልንገረው አዳሙ......ሚሊሻ
7ኛ.ተሜ አስራደ........ሚሊሻ
8ኛ.ሰማው አባተ.........ሚሊሻ
9ኛ.ወንዲፍራው አለሙ........ሚሊሻ
10ኛ.እየያያ ትልቁ......ሚሊሻ
11ኛ.ጌትየ ቸኮል.........ሚሊሻ አባላት ሲሆኑ ከደብረ ወርቅ ከተማ በመውጣት ሀምሌ 29/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ተቀላቅለዋል።
በክፍለጦር አመራሮችም ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን አሁንም ቢሆን ለአንድ አረመኔ ርህራሄ ለሌለው ስርአት መተኪያ የሌለው ህይወታቹህን አትገብሩ ኑ ወደ ትክክለኛ ማንነታቹህ ተመለሱ በክብር እንቀበላቹሀለን።
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የዘመነ ካሴዎች ትግልና የባጫ ደበሌ ኑዛዜ...
አራት ኪሎማ ከኛ ወዲህ ማ አለ?
ዳንኪረኛው ባጫ ደበሌ፣ በሶ በጥባጩ አትንኩት ምን እያለ ነው?
ኮንትሮባንዲስቱ አምባሳደርና ምርኮኛው ጄኔራል ለBBC አማርኛ ስርጭት እንዲህ ሲል ተናገረ "ዘመነ ካሴ አራት ኪሎ ና ቢባልም አይመጣም፤ብቃትም የለውም።" አስቀድመን ፍሬ-ነገሩን የሚንዱ ሀቆችን እናነሳለን። በዋናነት ግን የባጫን ፕሮፖጋንዳ እንድምታ እንናገራለን።
ባጫ የዘመነ ካሴ ባውቄን ወደ አራት ኪሎ መምጣት አይችልም ፉከራ ያደረገው የአርበኛ ዘመነ ካሴን ግላዊ ብቃት በማሳነስ ዓይነት ነው። እውነታው ግን ከባጫ ፉከራ የተለዬ ነው። አርበኛው በማስተርስ ዲግሪ የዋንጫ ተሸላሚ ነው። ይህ ዲግሪ በችሮታ የተሰጠ ወይም በትዕዛዝ የታደለው አይደለም፤ በተመሰከረ ብቃቱ ያገኘው ነው። እንዲህ ያለ የተረጋገጠ ዲግሪ ያለው ሰው በባጫ የዳንኪራ ክለብ ውስጥ የለም።
አርበኛው ለአስርት ዓመታት የዘለቀ የትግል ልምድ አለው። በዚህ ልምዱ በተግባር የተፈተነ የመምራት፣ የማስተባበር፣ የማደራጀትና የማብቃት ችሎታውን አሳይቷል። ይህ የጸሐፊው ማወደሻ ቃል አይደለም። ታሪክ በደማቅ ብዕሩ እየከተበው ያለ የተኖረ ጀግንነት ነው። ማንም ሊክድው የማይሞክር፣ ሊያስተባብለው ሆነ ሊያሳንሰው የማይቻለው ግዙፍ የታግሎ ማታገል ታሪክ ያለው ነው። በባጫ የዳንሰኞች ክለብ እንዲህ ያለ የለም። ሀቀኛ የኦሮሞን ወጣቶች ትግል የሚጠልፍ አጭበርባሪ እንጅ ታግሎ የሚያታግል አለቃ ኖሮት አያውቅም አትንኩት።
አርበኛው ከእነዚህ ሁሉ የሚበልጥ ሌላኛው ብቃቱ በማያቋርጥ ንባብና ማሰላሰል ውስጥ የሚኖር ብርቱ ማንነት ያለው መሆኑ ነው። የአባቶቹን ድርሳን፣ የምሁራኑን ጥናቶችና ሌሎች የታሪክ መዛግብትን ብቻ ሳይሆን ተፈጥሮንና ሁኔታን በንስር ዓይኖቹ ይመረምራል። የአፍሪካ ቀንድን መልክዓ ፖለቲካ(GeoPolitics) አንብቦት ብቻ ሳይሆን ኖሮት ያውቀዋል። የአትንኩት አለቃ ግን ዓባይን በአዋሽ ለመተካት ከመዳከር በቀር መልክዓ-ፖለቲካውን አይረዳውም። ባጫ ደበሌ እንዲህ ያለውን የፖለቲካና ኢኮኖሚ ሙዚቃ ሊደንስበት ቀርቶ አይሰማውም።
አርበኛው ደንበኛ የአማራ ብሄርተኛ ነው። የታወቀና የማያሻማ ውግንና፣ ዓላማና ግብ አለው። የሚኖርለት ዓላማ የሚሰዋለት እውነት አለው። የአማራ ብሔርተኝነትና ኢትዮጵያዊነትን፣ የሌሎችን ብሔሮች ጥያቄዎችና የአማራን ህዝብ ጥያቄዎች እንደ ዋሸራ ቅኔ በሰምና ወርቅ ያዋድደዋል። ኢትዮጵያውያንን ሁሉ በእኩልነት፣ በነጻነትና በአንድነት የሚመሩበትን የህግ፣ የኢኮኖሚክስ፣ የሰላምና ጸጥታ፣ የዲፕሎማሲ እውቀቶች ብቻ ሳይሆን የጠራ የሞራል ልዕልናንም ታጥቋል። ኮንትሮባንዲስቱ ባጫ የኖረበት ክለብ ውስጥ እንዲህ ያሉ ሰዎች የሉም።
ዳንኪረኛው ባጫ ከኮንትሮባንድ ንግዱ ፋታ በመውሰድ ፋኖዎች ብቃት የላቸውም በሚል አዝማች የተከሰተው ለምንድን ነው? የሚለው ጥያቄ ዋናው ቁምነገሩ የታጨቀበት ነው።
ባጫ የአማራን ወጣት፣ አዲሱን ትውልድ አያውቀውም። የአማራ ሴቶች እንደ ፋንቱ ተስፋዬ ያሉ ይመስሉታል። እልፍ ጣይቱ ብጡሎች እንዳሉት አልተረዳም። የአማራ ሴቶች እንደ ዝናሽ ያሉ ኤልዛቤሎች ይመስሉታል። በእውቀት፣ በምግባርና በሞራል የተገነቡ የፍትህና የእውነት ቀንዲሎች መሆናቸውን አያስተውልም። ባጫ የአማራ ሰው እንደ ተመስገን ጥሩነህ ወይም እንደ ይርጋ ሲሳይ ሰነፍና ተቅበዝባዥ ይመስለዋል። የአማራ ወጣት ከእኩልነትና ከነጻነት በቀረ ሌላ ለምንም የማይበገር የአባቶቹ ልጆች መሆኑን ልብ አላለም።
ትልቁ ቁምነገር ደግሞ ዘመነ ካሴ ባውቄ ብቻውን አለመሆኑ ነው። ምርኮኛው ባጫ አርበኛውን በስም ጠቅሶ ውሸቱን በማሰራጨቱ አርበኛውን በስም ጠቀስን እንጂ ከአርበኛው ውጭ፣ የገዘፈ ሞራል፣ ብቃትና ህልም ያላቸው ብዙ የአማራ ልጆች አሉ። የነጻነት ስሜቱንና የሞራል ልዕልናውን ተጋርተው የተመሙ ሚሊዮን ዘመነ ካሴዎች አሉ። በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የአማራ ጭንቅላቶች በዘመነ ዙሪያ መኖራቸውን ያውቅ ዘንድ የባጫ ማሰቢያ አይቻለውም።
ትግሉ ለዘመነ ወይም ለአንድ ነጠላ ጉዳይ ወይም እንደ ባጫና አብይ አህመድ አሊ ለጥቂት ጎረምሶች ብልግና የሚደረግ አይደለም። ባጫ እንዳለው ለገንዘብ ፍላጎት የሚደረግም አይደለም። የአማራ ትግል የህልውና ትግል ነው። ለዚህ የህልውና ትግል ደግሞ ምንም ቅድመ ሁኔታ ሳይቀመጥበት ሁሉም አማራ እየተዋደቀበት ያለ ነው።
ከዚህ ሁሉ የሚበልጠው ግን ባጫ ደበሌ በዚህ ጊዜ የፋኖ መሪዎችን በስም እየጠቀሰ "አራት ኪሎ መምጣት አይችሉም" ማለት የተገደደበት ምክንያት ምንድን ነው? የሚለው ነው። ለስሙ ያህል ባጫ ዲፕሎማት ነው፣ ባጫ ጄኔራል ነው፤ ለወጉ ያህል አትንኩት የብልጽግና ከፍተኛ አመራር ነው። ይህን ሁሉ ማዕረግ የደረደረው ባጫ ተራ የስም ማጥፋት ዘመቻ ላይ ተሰማርቶ መገኘቱ ለምንድን ነው?
መልሱ አጭርና ግልጽ ነው። አለቃው አብይ አህመድ አሊ በፕሮፖጋንዳ ልሳኖቹ እየዞረ በአማርኛ የተናገረውን በኦሮሞኛ እየሻረ፣ በአፋን ኦሮሞ የተናገረውን በትግርኛ እየካደ የህዝብ ትግል የጠለፈበትን አጨብርባሪነቱን በአዲስ የሙዚቃ ስልት፣ የምክክር ኮሚሽን በሚባል አታሞ አጅቦ መዝፈን ለጀመረው ድግስ ባጫ መውረግረግ መጀመሩ ነው።
በዘመነ ካሴዎች የሚመራው የአዲሱ ትውልድ ሀቀኛ ትውልድ በችሮታ፣ በጥሪና በማጭበርበር ሳይሆን በሀቅ፣ በእኩልነትና በአንድነት መርሆች እየተመራ አራት ኪሎ ይገባል። ይህ እንዲሆን የባጫ ምስክርነት፣ የአብይ አህመድ ፍቃድ አያስፈልገውም።
ባጫ ጮሆ ሊደብቀው የፈለገው አንድ ጉዳይ አለ። በአራት ኪሎ ምኒልክ ቤተ-መንግስት የሚጠቅም ሰው አለመኖሩንና መሪ አልባ ነን የሚለውን ስምምነት ለማስተባበል ጥሯል። ዛሬ ላይ ቤተ-መንግስቱ ከሞራልም፣ ከእውቀትና ከቅንነትም አርባ ክንድ የራቁ ማፍያዎች፣ ሌቦች፣ ጨፍጫፊዎችና ኮንትሮባንዲስቶች የተሰባሰቡበት እንጅ የህዝብ መሪዎች የሉበትም። ትግላችን ለህዝብ ሰላምና ደህንነት፣ እድገትና መሻሻል፣ እኩልነትና ነጻነት፣ ዴሞክራሲና ብሩህ ተስፋ የሚተጉ መሪዎችን በአራት ኪሎ ቤተ-መንግስት ከመሰየም የሚያስቀረው አንዳች ኃይል የለም።
ሼር ይደረግና ይድረሰው ለባጫ!!
የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ አርበኛ ጋዜጠኛ ወግድረስ ጤናው ዘውድ
