ru
Feedback
ቆንጆ ሙስሊም ሴት❤️❤️❤️📖

ቆንጆ ሙስሊም ሴት❤️❤️❤️📖

Открыть в Telegram

أَفَحَسِبْتُمْ أَنَّمَا خَلَقْنَاكُمْ عَبَثًا وَأَنَّكُمْ إِلَيْنَا لَا تُرْجَعُونَ «የፈጠርናችሁ ለከንቱ መኾኑን እናንተም ወደኛ የማትመለሱ መኾናችሁን ጠረጠራችሁን» 👋እንኳን ወደ ቤታችሁ ተቀላቀላችሁ እያልን👋 ይህ ቻናል በአላህ ፍቃድ ከቁርአን ከሀዲስ ከኡለሞች የተውጣጡ የተለያዩ ሀሳቦችን ምንተዋወስበት ይሆናል።

Больше
3 015
Подписчики
+124 часа
-137 дней
-4930 день
Архив постов
قال رسول الله ﷺ : الدُّعاءَ لا يُردُّ بينَ الأذانِ والإقامةِ

سبحان الله الحمد لله الله اكبر

ሰዎች ያለ ጥፋትህ ስምህን ሲያጠፉና ሲያዋርዱህ፣ ትኩረትህ እነሱ ላይ አይሁን። ኢብኑል ቀይም እንዳሉት ያለ ምክንያት በሰዎች ዘንድ መጠላት የወንጀል አንዱ መዘዝ ሊሆን ይችላል። ​ስለዚህ ከሰው ጋር መካሰስህን አቁመህ «ከ አላህ ሐቅ ምን ያጎደልኩት ነገር አለ?»ብለህ ራስህን መርምር። ከአላህ ጋር ያለህን መስተጋብር ስታሳምር፣ የሰዎችም ሁኔታ በራሱ ጊዜ ይስተካከላል። منقول

አንዳንዶቹ የሆነ ሰው ስላንተ ባወራውና በገለፀበት እይታ እንጂ በራሳቸው እይታ አይመለከቱህም ..
አንዳንዶቹ የሆነ ሰው ስላንተ ባወራውና በገለፀበት እይታ እንጂ በራሳቸው እይታ አይመለከቱህም ..

«እዉቀት ማለት ቁርአን ሀዲስን በትክክል መገንዘብ እንጂ፤ አፈ ቀላጤነት አይደለም። ምን አልባት አንድ ሰዉ በአፈ ቀላጤነቱ፣ በአንደበተ ርቱነቱ ብቻ ባጢሉን እዉነት አድርጎ ሊያቀርበዉ ይችላል። የመረጃ ጉዳይ ብቻ አይደለም።» ( ሸይኽ ኢሊያስ አሕመድ)

﴿وَلَا تَيْأَسُوا مِن رَّوْحِ اللَّهِ ۖ إِنَّهُ لَا يَيْأَسُ مِن رَّوْحِ اللَّهِ إِلَّا الْقَوْمُ الْكَافِرُونَ﴾ [ يوسف: 87] 🎧 القارئ عبد الباسط عبد الصمد

سبحان الله الحمد لله الله اكبر

قال رسول الله ﷺ : إن أخوف ما أخاف عليكم الشرك الأصغر : (الرياء) يقول الله يوم القيامة إذا جزى الناس بأعمالهم : اذهبوا إلى الذ
قال رسول الله ﷺ : إن أخوف ما أخاف عليكم الشرك الأصغر : (الرياء) يقول الله يوم القيامة إذا جزى الناس بأعمالهم : اذهبوا إلى الذين كنتم تراؤون في الدنيا فانظروا هل تجدون عندهم جزاء ؟؟

መጨረሻችንን ካለማወቃችን በላይ የሚያስፈራ ነገር ያለ አይመስለኝም ! በምን ሁኔታ ላይ ሆነን ይሆን የምንሞተው ? አሏህ ወዶን ? ወይንስ ከእሱ ርቀን ? አናውቅም ። ዐለይከ ረበና ቢሁስኒል ኺታሚ 🤲

اللهم صل وسلم على نبينا محمد ❤️‍🩹🍃

ይነበብ❗️

በነገራችን ላይ...ይህ የገጠመህ ሁኔታ በብዙ ወጣቶች ላይ በተለይም ደግሞ በሶሻል ሚዲያ ረዘም ላለ ጊዜ አውርተው ወደ አካል ግንኙነት በሚሸጋገሩበት ወቅት የሚከሰት የተለመደ ፈተና ነው። ምክኒያቱም
በነገራችን ላይ...ይህ የገጠመህ ሁኔታ በብዙ ወጣቶች ላይ በተለይም ደግሞ በሶሻል ሚዲያ ረዘም ላለ ጊዜ አውርተው ወደ አካል ግንኙነት በሚሸጋገሩበት ወቅት የሚከሰት የተለመደ ፈተና ነው። ምክኒያቱም በሶሻል ሚዲያ ለረጅም ጊዜ ስናወራ፣ ሳናውቀው በአዕምሯችን ውስጥ ፍጹም የሆነን ሰው እንስላለን። በአካል ስንገናኝ ግን የምናየው እውነታ ከአዕምሮአችን ምናባዊ ምስል ጋር ሊጋጭ ይችላል። 📕ለዚህም ነው ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ለአንድ ሊያገባ ለፈለገ ሶሃባ እንዲህ ብለውታል፦❝ሂድና እያት፤ በመካከላችሁ ፍቅርና ስምምነት እንዲሰርጽ ያደርጋልና።❞ (ቲርሚዚ) 🌷ኢስላም ከመጋባት በፊት ጥንዶች በተፈቀደው ሸሪዓዊ መንገድ እንዲተያዩ የፈቀደበት ዋናው ምክንያት በመካከላችሁ መሳሳብ,መኖሩን ለማረጋገጥ ነው። በአካል ከተያያችሁ በኋላ ስሜትህ ሙሉ በሙሉ ከቀነሰ እና ምንም ዓይነት የመሳብ ስሜት ካላገኘህ፣ ይህንን ስሜት ችላ ብሎ ወደ ትዳር መግባት ከባድ ሊሆን ይችላል። 🚫«እንዳይከፋት ብዬ ነው የማወራት» የሚለው ስሜትህ ካለህ መልካምነትህ ቢሆንም፣ በትዳር ህይወት ውስጥ ግን ይህ አካሄድ አዋጭ ላይሆን ይችላል።አያዋጣም'ም። ✅ለእሷም በደል ነው።እሷም ሙሉ ፍቅር የሚሰጣት፣ በአካልም በስሜትም የሚወዳት ባል የማግኘት መብት አላት። አንተ ስሜትህ ሳይኖር «እንዳይከፋት» ብለህ ብታገባት፣ ነገ በትዳር ውስጥ ተገቢውን ፍቅርና እንክብካቤ ሳትሰጣት ስትቀር የሚደርስባት ህመም አሁን ከምትከፋው እጅግ የላቀ ይሆናል።ትዳር ደሞ የእርካታና የሰላም ምንጭ መሆን አለበት። ስሜትህ ሳይኖርበት ወደ ትዳር ከገባህ ትዳሩ ሸክም ሊሆንብህ ይችላል። ✅እንደኔ የምመክርህ ነገር ቢኖር...ራስህን ጠይቅ። ማለቴ... ፍቅርህ የቀነሰበት ትክክለኛ ምክንያት ምንድን ነው? ከአካላዊ ገጽታዋ ጋር የተያያዘ ነው? ወይስ በአካል ስትገናኙ ካየኸው ባህሪዋ ወይም አነጋገሯ? ምክንያቱን በግልጽ ለይተህ ለማወቅ ሞክር። ❤️በአካል ካየሃት በኋላ ሙሉ በሙሉ ልብህ ካልፈቀዳትና የወደፊት የትዳር አጋሬ ናት ብለህ ለመቀበል ካልቻልህ፣ነገሩን እያሳበብክ ጊዜ ከመግደልና የእሷንም ስሜት ይበልጥ ከመጉዳትህ በፊት በግልጽ መነጋገር ይበጃል። 🌸እና ደሞ ሁሌ ምክር ለሚጠይቁኝ ሰዎች እንደምለው ኢስቲኻራህ ስገድ። ዋናውና ትልቁ መፍትሄ በአላህ ውሳኔ መተማመን ነው። ሁለት ረከዓ ሰግደህ የኢስቲኻራህን ዱዓዕ አድርግ። ይህንንም አድርገህ...ለመለያየት ከወሰንክ፣ በሰበብ አስባብ ከመራቅ ይልቅ በጨዋነትና በለሰለሰ ቋንቋ«ስለ ሁሉም ነገር አመሰግናለሁ፣ ነገር ግን በውስጤ ወደ ትዳር ለመግባት ዝግጁ እንዳልሆንኩ ተሰምቶኛል/አልተሳካልኝም...» በሚል የእሷን ማንነትና ክብር በማይነካ መልኩ ነገሩን በሰላም ማቆም ትችላለህ። 🎙️ባጭሩ፦ በትዳር ውስጥ ፍቅር መኖሩ ወሳኝ ነው። አሁን የሌለህን ስሜት በኋላ ይመጣል ብሎ በግምት ወደ ትዳር መግባት አደጋ አለው። ስለዚህ በጉዳዩ ላይ በጥልቀት አስብበት፣ ኢስቲኻራህ ስገድ፣ ከዚያም ልብህ የወሰነውን በግልጽነትና በአደብ ተግብረው። አላህ ያንተንም የእሷንም ህይወት የተስተካከለና የተባረከ ያድርግላችሁ። t.me/Sle_qelbachn1 t.me/Sle_qelbachn1

🔖ኢብኑ ሶላሕ አላህ ይዘንላቸዉና እንዲህ ይላሉ፦ “የጠዋት እና የማታ ዚክሮችንከሶላቶች በኋላ የሚባሉ ዚክሮችን እና የመኝታ ዚክሮችን ተጠባብቆ የሚል ሰው =  አላህን በብዛት ከሚያወሱት ሰዎች ይመደባል።” ~ አል አዝካር ሊነወዊይ (57)    

➡️ሂፍዝ ላይ ላሉ እህትና ወንድሞች ከልብ የሆነ ወንድማዊ ምክር በእርግጥም አንዳንዴ ያለን ፈጣንነትና የግንዛቤያችን ዘግ ማለት ሊያስተክዘን ይችላል በሌላም ጊዜ የሂፍዝ አቅማችን ደካማነትም እንዲሁ..! አረ እንደውም ሂፍዝ ካቅማችን በላይ ሆኖ በተደጋጋሚም ወድቀን ተነስተንም ይሆናል ! ግን አደራ ቀልባችን እንዲቆጣጠረው አትችሉም በሚል ሊያመሳስልብንና አናንተ ለምንም አትሆኑም ደካማ ናቹ በሚል ሊያሳምነን ለሸይጧን ትንሽም ቢሆን ቀዳዳ እንዳንከፍትለት ይህ ከሆነ ግን የጀመርነውን የመልካም ጉዞን እንተወዋለን መንገዱንም ተራና ጥቅም የለሽ አድርገን እናስበዋለን..! አዎ የሂፍዝ አካሄዳችን አርዝመንና ቆየንበት ብለንም አናስብ ለመጨረስም አንቻኮል ምክንያቱም እውቀት ከእኛ ኢኽላስ ትግስት እውነተኛነትና በአላህ ላይ መመካትን የሚፈልግ እንጂ ጥቅል በሆነ መልኩ በአንዴ ሚገኝ ነገር አይደለማ!. ስለዚህ አላህ እንደሚያሳካልን እርግጠኛ ሆነን እንለምነው እንዲያግዘንም እንለማመጠው እሱ ዘንድም እንዋደቅ ለእርሱ ባሉት ውብ ስሞቹም እኛው ምንጠቀምበትና ሌሎችን ምንጠቅምበት እውቀትም እንዲሰጠን እንጠይቀው።! ውጤታማ ማለት አላህ ውጤታማ ያደረገው ብቻ ነውና وباالله التوفيق አቡ ዚክራ✍

ثبت عن النبي ﷺ أنه كان يصوم يوم عاشوراء ويرغب الناس في صيامه. لأنه يوم نجا الله فيه موسى وقومه وأهلك فيه فرعون وقومه فيستحب ل
ثبت عن النبي ﷺ أنه كان يصوم يوم عاشوراء ويرغب الناس في صيامه. لأنه يوم نجا الله فيه موسى وقومه وأهلك فيه فرعون وقومه فيستحب لكل مسلم ومسلمة صيام هذا اليوم شكرًا لله عز وجل. وهو اليوم العاشر من محرم ويستحب أن يصوم قبله يومًا أو بعده يومًا مخالفة لليهود في ذلك. 🌹💚

⚡️#ነገን_ረቡዕ_ከመጾም_አንዘንጋ ​ረሱል ({ﷺ}) እንዲህ ብለዋል “የሚቀጥለው ዓመት ከደረስኩ በአላህ ፈቃድ የአሹራን ቀን ፆም ዘጠነኛውንም ጨምሬ እፆማለሁ::” ​📚ሙስሊም ዘግበውታል: 1134

የአሹራ ቀን ፆም! ➖ረሱል ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ ﴿صيامُ يومِ عاشوراءَ، إنِّي أحتَسِبُ على اللَّهِ أن يُكَفِّرَ السَّنةَ الَّتي قبلَهُ﴾ ➖“የአሹራ ቀን ፆም ያለፈውን አመት ኃጢአት እንደሚያብስ ከአላህ እጠብቃለሁ።” ሙስሊም ዘግበውታል: 1162 በሌላ ሀዲስ ➖ረሱል ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ ﴿فَإِذَا كَانَ الْعَامُ الْمُقْبِلُ - إِنْ شَاءَ اللَّهُ - صُمْنَا الْيَوْمَ التَّاسِعَ﴾ የሚቀጥለው ዓመት ከደረስኩ በአላህ ፍቃድ የአሹራን ቀን ፆም ዘጠነኛውን ጨምሬ እፆማለሁ።” ሙስሊም ዘግበውታል: 1134 የዘንድሮ (1448 ዓ.ሂ) ዓሹራ ጾም የፊታችን ሀሙስ ሰኔ 18/2018 ነው የሚውለው። ቀኑን መፆሙ የ አንድ ዓመት ያለፈ ወንጀልን ያስምራል። ከፊት 9ነኛውን ቀን ወይም ከኋላ 11ኛውን ቀን መጾም ተወዳጅ ነው።    እና በዱአቹ  እንዳትረሱኝ  አደራ አላህ ደርሰው ከሚፆሙት ያድርገን🤲አሚን

﴿ وَإِذَا سَأَلَكَ عِبَادِي عَنِّي فَإِنِّي قَرِيبٌ ۖ أُجِيبُ دَعْوَةَ الدَّاعِ إِذَا دَعَانِ ۖ فَلْيَسْتَجِيبُوا لِي وَلْيُؤْمِنُوا بِي لَعَلَّهُمْ يَرْشُدُونَ﴾ [ البقرة: 186] 🎧 القارئ محمد صديق المنشاوي