fa
Feedback
ቆንጆ ሙስሊም ሴት❤️❤️❤️📖

ቆንጆ ሙስሊም ሴት❤️❤️❤️📖

رفتن به کانال در Telegram

أَفَحَسِبْتُمْ أَنَّمَا خَلَقْنَاكُمْ عَبَثًا وَأَنَّكُمْ إِلَيْنَا لَا تُرْجَعُونَ «የፈጠርናችሁ ለከንቱ መኾኑን እናንተም ወደኛ የማትመለሱ መኾናችሁን ጠረጠራችሁን» 👋እንኳን ወደ ቤታችሁ ተቀላቀላችሁ እያልን👋 ይህ ቻናል በአላህ ፍቃድ ከቁርአን ከሀዲስ ከኡለሞች የተውጣጡ የተለያዩ ሀሳቦችን ምንተዋወስበት ይሆናል።

نمایش بیشتر
2 932
مشترکین
-324 ساعت
-207 روز
-4530 روز
آرشیو پست ها
ከመጥፎ ሠዎች ጋር ጣፋጭ ነገርን ከምትበላ ከደጋግ ሠዎች ጋር ድንጋይ ብትሸከም ላንተ የተሻለነው! 📒ኢብኑል ቀዩም ረሂመሁላህ

"አማኝ (ሙዕሚን) ለወንድሙ እንደ መስታወት ነው፤ በእሱ ላይ ስህተት ካየ... ያስተካክለው (ይቀረፈለት)" 🌍ነብዩ ሙሐመድ ﷺ✅

ለእኛ ብለው ዝቅ እንዳሉት አላህ በጀነት ከፍ ያርጋቸው እናቶች።

[ ምሽቱ ሲመጣ ደስ ይለኛል ከሰዎች እይታ ስለሚያሳርፈኝ ] ® ሱፊያነ ሰውሪ ረሂመሁላህ

ትዳር ሲዘገይብሽ ለምን ብለሽ ውስጥሽ አይረበሽ አላህ ሁሌም ምክንያት አለው።እኛ እንቸኩላለን እንጂ አላህ ዘግይቶ አያውቅም!!!

ታላቁ መካሪ ኢብኑ አል ጀውዚይ رحمه الله በቁርአን እራሱን ማከም ያልቻለ በሽተኛ ሆኖ ከመኖር መቼም አይወገድም ይላሉ።

سبحان الله الحمد لله الله اكبر

የአንድ ሰው ከእስልምናው ማማር የማይመለከተውን ነገር መተዉ ነው። ረሱል ሶለላሁ ዓይሂ ወሰለም

4ቱን የዒዳ ዓይነቶች ከቁርአንና ሐዲስ ደሊል ጋር፦ 1. ዒዳ የእርጉዝ ሴት — عِدّة الحامل ደሊል፦ ﴿وَأُولَاتُ الْأَحْمَالِ أَجَلُهُنَّ أَنْ يَضَعْنَ حَمْلَهُنَّ﴾ (الطلاق: 4) ትርጉም፦ “እርጉዝ የሆኑት ሴቶች የዒዳቸው ጊዜ ጭነታቸውን (ልጃቸውን) እስኪወልዱ ድረስ ነው።” 2. ባሏ የሞተባት — عِدّة المتوفى عنها زوجها ደሊል፦ ﴿وَالَّذِينَ يُتَوَفَّوْنَ مِنكُمْ وَيَذَرُونَ أَزْوَاجًا يَتَرَبَّصْنَ بِأَنْفُسِهِنَّ أَرْبَعَةَ أَشْهُرٍ وَعَشْرًا﴾ (البقرة: 234) ትርጉም፦ “ከእናንተ መካከል የሚሞቱና ሚስቶችን የሚተዉ ሰዎች ሚስቶቻቸው ለ4 ወርና 10 ቀን ይጠብቃሉ።” 3. የወር አበባ የምታይ የተፈታች — عِدّة المطلقة ذات الحيض ደሊል፦ ﴿وَالْمُطَلَّقَاتُ يَتَرَبَّصْنَ بِأَنْفُسِهِنَّ ثَلَاثَةَ قُرُوءٍ﴾ (البقرة: 228) ትርጉም፦ “የተፈቱ ሴቶች ሦስት ቁሩእ ጊዜያት ራሳቸውን ይጠብቃሉ።” ማስታወሻ፦ قروء ላይ ዑለማዎች ልዩነት አላቸው፤ በሻፊዒይ መዝሀብ እና በአብዛኛው ዑለማ መሠረት እዚህ ላይ የተፈለገው የወር አበባ ጊዜ ነው። 4. የወር አበባ የማታይ — عِدّة من لا تحيض ይህም የወር አበባ የማታይ ሴት ለምሳሌ በልጅነት ወይም በማረጥ ምክንያት ከሆነ፦ ደሊል፦ ﴿وَاللَّائِي يَئِسْنَ مِنَ الْمَحِيضِ مِن نِّسَائِكُمْ إِنِ ارْتَبْتُمْ فَعِدَّتُهُنَّ ثَلَاثَةُ أَشْهُرٍ وَاللَّائِي لَمْ يَحِضْنَ﴾ (الطلاق: 4) ትርጉም፦ “ከሴቶቻችሁ መካከል ወር አበባን በመመልከት ተስፋ የቆረጡት፣ ብትጠራጠሩ ዒዳቸው 3 ወራት ነው፤ እንዲሁም ወር አበባ ያላዩትም።” ስለዚህ በአጭሩ፦ 🤰 እርጉዝ → እስክትወልድ 🕊️ ባሏ የሞተባት → 4 ወርና 10 ቀን 🩸 የወር አበባ የምታይ → 3 ቁሩእ 🌙 የወር አበባ የማታይ → 3 ወራት ©

የመግሪብ አዛን ይደርሳል ብለህ እርግጠኛ ሆነህ በትእግስት #እንደምትፆመው ከችግር በኋላም ደስታ ይመጣልና ታግሰህ #በአላህ ላይ ጥርጣሬህን #እያሳመርክ ጠብቅ። ©

سبحان الله الحمد لله الله اكبر

وَلَا تُلْقُوا بِأَيْدِيكُمْ إِلَى التَّهْلُكَةِ “በእጃችሁ ራሳችሁን ወደ ጥፋት አትጣሉ።”

«በድብቅ የሌሊት ሶላት ይሰገዳል እንጅ በድብቅ ሚስት አይገባም ፣ በድብቅ ይሰደቃልጅ በድብቅ ልጅ አይወለድም»

የጠዋትና የማታ ዚክር የለም፤ዱዓና ኢስቲግፋር ተረስቷል፤ቂያሙ-ለይልና ሰደቃህ ጠፍቷል...​ከዚያም መጥተህ «ጨነቀኝ፣ ከፋኝ፣ ደበረኝ» ትላለህ! ​ያለ ዚክርና ያለ ዱዓ የኖረ ቀልብ... እንዴትስ አይደብረው?! እንዴትስ አይከፋው?!

سبحان الله الحمد لله الله اكبر

እውነት እላችኋለሁ፣ ደካማ ሴት አልወድም። ሪዝቄ እና ህይወቴን የሚመራው ባሌ ነው ብላ የምታስብ፣ እርሱ ቢተዋት ህይወቷ የሚያበቃ የሚመስላት ሴት ባሏን ፈጣሪዋ አድርጋለች። ባሏ ላይ ጥፋትና ሐራሙን እያየች «ትዳሬ ይፈርሳል» በሚል ፍርሃት የምታልፍ፣ መድረሻ አጣለሁ ብላ ግፍን፣ ድብደባንና ስድብን በፍቅር ስም የምትሸከም ሴት ነጻነቷን አጥታለች። የዚህ ዓይነቷ ሴት የአላህ ሳይሆን የሰው ባሪያ ናት። ሰዎች የሪዝቅ ምክንያት እንጂ ሰጪው አላህ መሆኑን የረሳች ናት። t.me/Sle_qelbachn1 t.me/Sle_qelbachn1