ቆንጆ ሙስሊም ሴት❤️❤️❤️📖
رفتن به کانال در Telegram
أَفَحَسِبْتُمْ أَنَّمَا خَلَقْنَاكُمْ عَبَثًا وَأَنَّكُمْ إِلَيْنَا لَا تُرْجَعُونَ «የፈጠርናችሁ ለከንቱ መኾኑን እናንተም ወደኛ የማትመለሱ መኾናችሁን ጠረጠራችሁን» 👋እንኳን ወደ ቤታችሁ ተቀላቀላችሁ እያልን👋 ይህ ቻናል በአላህ ፍቃድ ከቁርአን ከሀዲስ ከኡለሞች የተውጣጡ የተለያዩ ሀሳቦችን ምንተዋወስበት ይሆናል።
نمایش بیشتر2 932
مشترکین
-324 ساعت
-207 روز
-4530 روز
آرشیو پست ها
2 933
ከመጥፎ ሠዎች ጋር ጣፋጭ ነገርን ከምትበላ ከደጋግ ሠዎች ጋር ድንጋይ ብትሸከም ላንተ የተሻለነው!
📒ኢብኑል ቀዩም ረሂመሁላህ
2 933
"አማኝ (ሙዕሚን) ለወንድሙ እንደ መስታወት ነው፤ በእሱ ላይ ስህተት ካየ... ያስተካክለው (ይቀረፈለት)"
🌍ነብዩ ሙሐመድ ﷺ✅
2 933
ትዳር ሲዘገይብሽ ለምን ብለሽ ውስጥሽ አይረበሽ አላህ ሁሌም ምክንያት አለው።እኛ እንቸኩላለን እንጂ አላህ ዘግይቶ አያውቅም!!!
2 933
ታላቁ መካሪ ኢብኑ አል ጀውዚይ رحمه الله
በቁርአን እራሱን ማከም ያልቻለ በሽተኛ ሆኖ ከመኖር መቼም አይወገድም ይላሉ።
2 933
4ቱን የዒዳ ዓይነቶች ከቁርአንና ሐዲስ ደሊል ጋር፦
1. ዒዳ የእርጉዝ ሴት — عِدّة الحامل
ደሊል፦
﴿وَأُولَاتُ الْأَحْمَالِ أَجَلُهُنَّ أَنْ يَضَعْنَ حَمْلَهُنَّ﴾
(الطلاق: 4)
ትርጉም፦ “እርጉዝ የሆኑት ሴቶች የዒዳቸው ጊዜ ጭነታቸውን (ልጃቸውን) እስኪወልዱ ድረስ ነው።”
2. ባሏ የሞተባት — عِدّة المتوفى عنها زوجها
ደሊል፦
﴿وَالَّذِينَ يُتَوَفَّوْنَ مِنكُمْ وَيَذَرُونَ أَزْوَاجًا يَتَرَبَّصْنَ بِأَنْفُسِهِنَّ أَرْبَعَةَ أَشْهُرٍ وَعَشْرًا﴾
(البقرة: 234)
ትርጉም፦ “ከእናንተ መካከል የሚሞቱና ሚስቶችን የሚተዉ ሰዎች ሚስቶቻቸው ለ4 ወርና 10 ቀን ይጠብቃሉ።”
3. የወር አበባ የምታይ የተፈታች — عِدّة المطلقة ذات الحيض
ደሊል፦
﴿وَالْمُطَلَّقَاتُ يَتَرَبَّصْنَ بِأَنْفُسِهِنَّ ثَلَاثَةَ قُرُوءٍ﴾
(البقرة: 228)
ትርጉም፦ “የተፈቱ ሴቶች ሦስት ቁሩእ ጊዜያት ራሳቸውን ይጠብቃሉ።”
ማስታወሻ፦ قروء ላይ ዑለማዎች ልዩነት አላቸው፤ በሻፊዒይ መዝሀብ እና በአብዛኛው ዑለማ መሠረት እዚህ ላይ የተፈለገው የወር አበባ ጊዜ ነው።
4. የወር አበባ የማታይ — عِدّة من لا تحيض
ይህም የወር አበባ የማታይ ሴት ለምሳሌ በልጅነት ወይም በማረጥ ምክንያት ከሆነ፦
ደሊል፦
﴿وَاللَّائِي يَئِسْنَ مِنَ الْمَحِيضِ مِن نِّسَائِكُمْ إِنِ ارْتَبْتُمْ فَعِدَّتُهُنَّ ثَلَاثَةُ أَشْهُرٍ وَاللَّائِي لَمْ يَحِضْنَ﴾
(الطلاق: 4)
ትርጉም፦ “ከሴቶቻችሁ መካከል ወር አበባን በመመልከት ተስፋ የቆረጡት፣ ብትጠራጠሩ ዒዳቸው 3 ወራት ነው፤ እንዲሁም ወር አበባ ያላዩትም።”
ስለዚህ በአጭሩ፦
🤰 እርጉዝ → እስክትወልድ
🕊️ ባሏ የሞተባት → 4 ወርና 10 ቀን
🩸 የወር አበባ የምታይ → 3 ቁሩእ
🌙 የወር አበባ የማታይ → 3 ወራት
©
2 933
የመግሪብ አዛን ይደርሳል ብለህ እርግጠኛ ሆነህ በትእግስት #እንደምትፆመው ከችግር በኋላም ደስታ ይመጣልና ታግሰህ #በአላህ ላይ ጥርጣሬህን #እያሳመርክ ጠብቅ።
©
2 933
የጠዋትና የማታ ዚክር የለም፤ዱዓና ኢስቲግፋር ተረስቷል፤ቂያሙ-ለይልና ሰደቃህ ጠፍቷል...ከዚያም መጥተህ «ጨነቀኝ፣ ከፋኝ፣ ደበረኝ» ትላለህ! ያለ ዚክርና ያለ ዱዓ የኖረ ቀልብ... እንዴትስ አይደብረው?! እንዴትስ አይከፋው?!
2 933
እውነት እላችኋለሁ፣ ደካማ ሴት አልወድም።
ሪዝቄ እና ህይወቴን የሚመራው ባሌ ነው ብላ የምታስብ፣ እርሱ ቢተዋት ህይወቷ የሚያበቃ የሚመስላት ሴት ባሏን ፈጣሪዋ አድርጋለች። ባሏ ላይ ጥፋትና ሐራሙን እያየች «ትዳሬ ይፈርሳል» በሚል ፍርሃት የምታልፍ፣ መድረሻ አጣለሁ ብላ ግፍን፣ ድብደባንና ስድብን በፍቅር ስም የምትሸከም ሴት ነጻነቷን አጥታለች።
የዚህ ዓይነቷ ሴት የአላህ ሳይሆን የሰው ባሪያ ናት። ሰዎች የሪዝቅ ምክንያት እንጂ ሰጪው አላህ መሆኑን የረሳች ናት።
t.me/Sle_qelbachn1
t.me/Sle_qelbachn1
