Enzi primary, secondary and preparatory school
Открыть в Telegram
We will strive to have well educated, broad-minded, patriotic, curios, visionary and self motivated human resource.
Больше688
Подписчики
-124 часа
+37 дней
+1630 день
Архив постов
#ሰላም እንዴት ናችሁ ውድ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች:-
#ከስር የምትመለከቱት ተማሪ መሀመድ አብዱልቃድርን ያያችሁ በአስቸኳይ ወደ ፈተና ጣቢያ እንድትልኩልን በማለት የመልካም ትብብራችሁን እንፈልጋለን!!
+7
#ሀምሌ 1/2018 ዓ/ም!
#የኢንዚ 2ኛ ደረጃ እና ገመሀሮ ት/ቤት #የ3ኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ፈተናቸውን ጀመሩ!!
#መልካም ውጤት!!
Repost from Enzi primary, secondary and preparatory school
#ማስታወቂያ:-
👉ለኢንዚ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ:-
👉የ3ኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ 12ኛ ክፍል ተፈታኞች በገመሀሮ ክላስተር ት/ቤት ላይ ከጧቱ 1:00 ጀምሮ እንድገኙ በማለት የት/ቤቱ አስተባባሪዎችና ት/ቤቱ ርዕሰ መምህር በድጋሚ የጥሪ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
#ማሳሰቢያ:- በፈተና ወቅት የማይፈቀዱ ማንኛውንም አይነት ክልከላዎች ባለመፈጸም እንድተባበሩ በማለት እናሳውቃለን!!
#ማስታወቂያ:-
👉ለኢንዚ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ:-
👉የ3ኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ 12ኛ ክፍል ተፈታኞች በገመሀሮ ክላስተር ት/ቤት ላይ ከጧቱ 1:00 ጀምሮ እንድገኙ በማለት የት/ቤቱ አስተባባሪዎችና ት/ቤቱ ርዕሰ መምህር በድጋሚ የጥሪ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
#ማሳሰቢያ:- በፈተና ወቅት የማይፈቀዱ ማንኛውንም አይነት ክልከላዎች ባለመፈጸም እንድተባበሩ በማለት እናሳውቃለን!!
+6
#በግልጽ የሚታየው የትምህርት #ካላንደር ይፋ ሆነ‼️
##የ2019 ዓ/ም የትምህርት ካላንደር ይፋ የሆነ ሲሆን #ከነሀሴ 26_ ጳጉሜ 5/2018ዓ/ም #የተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወንበት መሆኑና #ከመስከረም 5/1/2019 ዓ.ም ትምህርት የሚጀመርበት ቀን ነው።
#ማሳሰቢያ:- ይህንን መረጃ በድጋሚ የማጋራችሁ #የሐጀመሪያው ስካን ያደረጉት ስለማይነበብ መሆኑን ብቻ እንድትገነዘቡት ጭምር ነው።
#ኢንዚ 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት!!
#ማስታወቂያ:-
#ለኢንዚ 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የተማሪ ወላጆችና ተማሪዎች በሙሉ:-
#የኢንዚ 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት #የ2018 ዓ.ም የተማሪ ወላጆች ቀን #ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግ #የፊታችን እሁድ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም #ከጧቱ 2፡30 ጀምሮ እስከ 5:00 ሰዓት ድረስ አመታዊ የት/ቤት መዝጊያ በዓል ላይ ውድ ተማሪዎችና ወላጆች እንዲገኙልን በማለት ጥሪያችንን እናሳዉቃለን።
#ኢንዚ 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤቱ!!
Repost from Benishangul Gumuz Education Bureau
+9
ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ቀን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በኦን ላይን እየተሰጠ ነው
------ ---------- -----
(ሰኔ 26/2018 ፤ አሶሳ) ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ቀን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በኦን ላይን እየተሰጠ ነው።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) ፤ የቢሮው ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ መሀመድ ኡስማን ፣ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ሃላፊ ወ/ሮ ጎጃም አያናና የቢሮ ዳሬክተሮች በገመ ሃሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማዕከል በኦን-ላይን እየተሰጠ ያለውን ፈተና ተመልክተዋል።
ፈተናው ደህንነቱን በጠበቀና ሰላማዊ ሆኖ እየተሰጠ መሆኑንም የስራ ሃላፊዎች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በክልል በ16 የመፈተኛ ጣቢያዎቾ ፈተናውን በበይነ-መረብ ይሰጣል እየተሰጠ ይገኛል። 5,017 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በበይን መረብ ፈተናውን ይወስዳል ፤ በጥቅሉ 7,705 ተማሪዎች ፈተናውን የሚወስዱ ሲሆን 4,336 የተፈጥሮ ሳይንስ 3369 የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ መሆናቸው ታውቋል። የዘገባው የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው።
#አስቸኳይ መረጃ ለሁሉም!!
#እባክዎ ለሁሉም ተማሪዎችና ቤተሰብ እንድደርስ #ሸር በማድረግ ይተባባሩ!!
+9
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የ12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና መስጠት ተጀምሯል
****
(አሶሳ፤ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የ12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና መስጠት ተጀምሯል።
ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም በ6 ዙሮች የሚሰጠው ፈተና ዛሬ በተፈጥሮ ሳይንስ የበይነ መረብ ፈተና ተጀምሯል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የቢሮው አመራሮች በአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ማዕከላት ተገኝተው የበይነ መረብ ፈተናውን ያስጀመሩ ሲሆን፣ የፈተና አሰጣጡንም ተመልክተዋል።
የቢሮ ኃላፊው ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ በክልሉ ዘንድሮ 7 ሺህ 705 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ይወስዳሉ።
በክልሉ ፈተናው በ16 ማዕከላት ይሰጣል ያሉት ኃላፊው፣ 14ቱ ማዕከላት የበይነ መረብ ፈተና እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
ከተፈታኞች ውስጥ 65 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች ፈተናውን በበይነ መረብ የሚወስዱ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ በወረቀት እንደሚፈተኑ ገልጸዋል።
ፈተናው በሰላም እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡም ዶ/ር ተመስገን ጥሪ አቅርበዋል።
በአሶሳ ዪኒቨርሲቲ የበየነ መረብ የፈተና አስተባባሪ ወንድም መኩሪያው (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ለፈተናው በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።
የመብራትና የኔትወርክ መቆራረጥ እንዳይከሰት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በተሰራው ቅድመ ዝግጅት ሶስት ዘመናዊ ጄነሬተሮች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
