Enzi primary, secondary and preparatory school
前往频道在 Telegram
We will strive to have well educated, broad-minded, patriotic, curios, visionary and self motivated human resource.
显示更多688
订阅者
+124 小时
-27 天
+230 天
帖子存档
#የተከበራችሁ ዉድ የኢንዚ 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ:-
🌽የ2019 ዓ/ም የተማሪዎች ምዝገባና ወርሃዊ ክፍያ ዋጋ ዝርዝር ከዚህ በታች እንደሚከተለው ተቀምጧል🌽
🌽ማስታወሻ 🌽
👉ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ መመዝገቢያ 500 ብር
👉ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል ወርሃዊ ክፍያ 1500 ብር
👉ከ7ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ወርሃዊ ክፍያ 1600 ብር
👉ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ወርሃዊ ክፍያ 1800 ብር
መሆኑን እና ማንኛውም ተመዝጋቢም ሆነ አስመዝጋቢ ሲመጣ የምዝገባ እና የመስከረም ወርሃዊ ክፍያ በቅድሚያ መክፈል እንዳለበት እና እስከ ሀምሌ 25/2018 ዓ/ም ድረስ ያለ ቅጣት መመዝገብም ሆነ ማስመዝገብ የሚቻል መሆኑን በድጋሚ እናሳዉቃለን።
👉መረጃው ከት/ቤቱ!!
👉ለበለጠ መረጃ ከስር ባሉት ስልኮች ላይ ደውለው ይጠይቁ!!
☎️ +251 92 082 7464
☎️ +251 91 331 3391
☎️ +251 91 103 2158
#ይድረስ ለነባር ተማሪ ወላጆች በሙሉ:-
#የ2019 ዓ.ም ምዝገባ ከሀምሌ 1 እስከ 10 ሲካሄድ የነበረ ቢሆንም አንዳንድ ወላጆች መረጃ ያልደረሳቸው መሆኑን በስልክ እና በአካል እየመጡ ባነጋገሩን መሰረት የነበረባቸውን የስራ መደራረብና ችግር በመገንዘብ እስከ የነባር እና አዳድስ ተመዝጋቢ ተማሪዎችን እስከ #ሀምሌ 25/2018 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን እያሳወቅን በተጠቀሱት የጊዜ ገደብ ውስጥ ልጆን እንዲያስመዘግቡ እያሳሰብን ከዛ ውጭ ቀኑን አሳልፈው የሚመጡ ተመዝጋቢ ተማሪዎችን በቀሪ ውስን የቅበላ ቦታዎቻችን ላይ #የተመዝጋቢ ተማሪዎችን #ቁጥር በማየት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ብቻ በቅጣት የምናስተናግድ መሆናችንን በድጋሚ እናሳውቃለን።
👉ኢንዚ 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት!!
#እንኳን ደስ አላችሁ!!
#ለአሶሳ አጠ/ከ/ሁ/ደረጃ ት/ቤት እና
#ለኢንዚ 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራን እና ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን!!
#ተማሪ ሀይሌ አዳነ በ2013 ዓ/ም በኢንዚ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የ8ኛ ክፍል ትምህርቱን በመለያ ቁጥር/ኮድ 10463 የ1ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ የ8ኛ ክፍል ፈተና በመውሰድ 95.21 % በአማካይ ውጤቱም 100 ፐርሰንታይል በማግኘት እና ከክልሉ ጠቅላላ ተፈታኞችም አንደኛ በመውጣት ወደ 9ኛ ክፍል የተዛወረው ጀግናችን ተማሪ ሀይሌ አዳነ የ2ኛ ደረጃ ትምህርቱን በአሶሳ አጠ/ከ/ሁ/ደረጃ ት/ቤት ላይ ሲከታተል ቆይቶ የ12ኛ ክፍል ኢንትራንስ ከወሰዱት ተማሪዎች ዘንድ የተሻለ ውጤት በማምጣት ለመምህራኖቹና ለቤተሰቦቹ ኩራት ሆኖ መዝለቁ ይታወቃል።
#ዛሬም በተመሳሳይ መልኩ ተማሪ ሀይሌ አዳነ ላስተማሩት መምህራንና ውድ ቤተሰቦቹ እና ድፍን ለኢትዮጵያ ህዝብ ኩራት በመሆን የተሻለ እድል ለማግኘት የሄደበትን ርቀት በብቃት አጠናቆ የድል ችቦ በማብራቱ እንኳን ደስ አላችሁ በማለት መልእክቱን አጋርተናል።
#ኢንዚ 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት!!
የ4 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላር የትምህርት ዕድል አሸናፊው ተማሪ ኃይሌ አዳነ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ4 ነጥብ 1 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የነፃ ትምህርት ዕድል ተወዳድሮ በማሸነፍ 11 የአሜሪካ ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች መግባት መቻሉን ያረጋገጠው ተማሪ ኃይሌ አዳነ ትውልድ እና እድገቱ በአሶሳ ከተማ ነው።
የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአሶሳ ከተማ የተከታተለው ተማሪ ኃይሌ፤ ያገኘው ዕድል በዓለም ላይ ለመግባት እጅግ በጣም ከባድ ውድድር የሚጠይቁ እና የዓለምን ታሪክ የቀየሩ ሰዎችን ያፈሩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ናቸው።
ተማሪ ኃይሌ ነፃ የትምህርት ዕድል ካሸነፈባቸው ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ማሳቹሴትስ ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ፣ ፕሪንስተን ዩኒቨርሲቲ እና ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ፔንስልቬንያ ይገኙበታል።
ከቅዳሜ ማለዳ ፋና 90 ጋር ቆይታ ያደረገው ተማሪ ኃይሌ በራሱ ተነሳሽነት የተለያዩ የኦንላይን አማራጮችን በመጠቀም ዌብዴቨሎፕመንት ይማር እንደነበር ተናግሯል።
የክረምት ወቅትን አዳዲስ ክህሎቶችን ለመማር ባለው ጉጉት በአዲስኮደር የኮዲንግ ስልጠና በሀገር ውስጥ፤ ቲኤኤስኤስ እና ዋይዋይኤኤስ የተሰኙ ፕሮግራሞችን ደግሞ በአሜሪካ እና ዚምባቡዌ ተከታትሏል።
የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሰመር ካምፕ ስልጠናም በዘርፉ ልምድ ያላቸው መምህራን ከመሰረታዊ ጽንሰ ሀሳብ ጀምሮ እስከ የተለያዩ ደረጃዎችን በማለፍ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂዎችን በግልጽ እና በተግባር ቀስሟል።
ኃይሌ እና ጓደኞቹ ያገኙትን ዕውቀት በመጠቀም የአየር ንብረት ድርቅን የመጪዎቹን 6 ወራት አስቀድሞ በ95 በመቶ ትክክለኛነት ደረጃ መተንበይ የሚችል የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሞዴል አበልጽገዋል።
የዌብዴቨሎፕመንት ክህሎቱን ከየአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ጋር በማዋሃድ (ethioexam.et) የተሰኘ ተማሪዎች ለሀገር አቀፍ ፈተና እንዲዘጋጁ የሚረዳ የትምህርት መተግበሪያ ያበለጸገ ሲሆን፤ መተግበሪያው ከ20 ሺህ በላይ ተማሪዎችን እያገለገለ ይገኛል፡፡
የ19 ዓመቱ የኃይሌ ታሪክ በሀገራችን ለሚገኙ ተማሪዎች በትጋት ከሰሩ በዓለም አቀፍ ደረጃ መወዳደርና ማሸነፍ እንደሚችሉ ማረጋገጫ ነው።
ለኮምፒውተር እና ለቴክኖሎጂ ከፍተኛ ፍቅር ያለው ኃይሌ የመጨረሻ ምርጫውን በዓለም ላይ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ቁጥር አንድ በሆነው ማሳቹሴትስ ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ በማድረግ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ ትምህርቱን ይጀምራል።
በመጪው ሐምሌ ወር ወደ አሜሪካ በመጓዝ መላው ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ይወክላል።
በሄኖክ ለሜ
ምንጭ #Fana Broadcasting Corporate#
📢 ለተከበራችሁ የኢንዚ ትምህርት ቤት 12ኛ ክፍል ተማሪዎችና ወላጆች
ለ2019 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን መልቀቂያ የሚሰጠው እስከ ሐምሌ 25 ብቻ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን።
ከዚህ ቀን በኋላ መጥተው ለሚጠይቁ ወላጆች መልቀቂያው ወዲያውኑ የማይሰጥ ሲሆን፣ ለሌላ ቀን ቀጠሮ እንደሚሰጥ እንገልጻለን።
ስለዚህ ያለምንም እንግልትና መጉላላት ከወዲሁ በመገኘት መልቀቂያችሁን በተወሰነው ጊዜ እንድትወስዱ በትህትና እንጠይቃለን።
#ማሳሰቢያ:-የመመረቂያ ጋወን እስከ ሀምሌ 15/2018 ዓ/ም ድረስ እንድትመልሱ ት/ቤቱ ያሳስባል።🙏
👌የኢንዚ ትምህርት ቤት!!
👉ማስታወቂያ:-
#ለኢንዚ 1ኛ መካከለኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ:-
#እንደሚታወቀው የ2019 ዓ/ም የነባርና አዳዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ከሀምሌ 1/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ሀምሌ 10/2019 ዓ/ም ድረስ ያለ ቅጣት የምንመዘግብ መሆኑን በተማሪ ወላጆች ቀን በተገለጸላችሁና በማስታወቂያ በገለጽነው መሰረት የተማሪዎች ምዝገባ ነገ ሀምሌ 10/2018 ዓ/ም እስከ 10:30 ድረስ የምናስተናግድ መሆኑን እያሳወቅን #ከነገ በኋላ የሚመጡ ተመዝጋቢዎችን እስከ ሀምሌ 15/2018 ዓ/ም ድረስ በቅጣት የምናስተናግድ መሆኑን ጭምር እናሳውቃለን።
#ማሳሰቢያ:-ማንኛውም ተመዝጋቢ ሲመጣ የመመዝገቢያ እና የመስከረም ወርሃዊ ክፍያ ማጠናቀቅ እንዳለበት በድጋሚ እናሳስባለን!!
#ለኢንዚ 1ኛ መካከለኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት!!
