ru
Feedback
Esdros S.C

Esdros S.C

Открыть в Telegram

እንኳን ወደ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ/ማህበር የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ፡፡ This is Esdros S.C's official Telegram channel. For more updates please visit www.Esdros.com

Больше
3 493
Подписчики
+3824 часа
+1697 дней
+28430 день
Архив постов
የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶቻችን በተካሄደው የመዝጊያ መርሐ ግብር ላይ በትምህርት ዘመኑ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የዋንጫ፣ የሰርተፍኬት እና የተለያዩ ሽልማቶች በክብር እንግድ
+7
የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶቻችን በተካሄደው የመዝጊያ መርሐ ግብር ላይ በትምህርት ዘመኑ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የዋንጫ፣  የሰርተፍኬት እና የተለያዩ ሽልማቶች በክብር እንግድነት በተገኙ እንግዶች እና በርእሳነ መምህራን ተበርክቶላቸዋል፡፡ በ2018 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራው ላይ ከፍተኛ አበርክቶ ላደረጉ መምህራን፣ የአስተዳዳር ሰራተኞች፣ ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞችም ጭምር ልዩ ልዩ የማበረታቻ ሽልማት ተሸልመዋል፡፡ በመዝጊያ ሥነ ሥርዓቱ ማጠቃለያም ተማሪዎች የውጤት መግለጫ ካርዳቸውን ከየክፍል ተጠሪ መምህራን እጅ ተቀብለው የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል፡፡   የአቡነ ጎርጎርዮስ  ትምህርት ቤቶች በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በ29 ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች 25,623 ተማሪዎችን ሲያስተምር እንደነበር ይታወሳል፡፡   ለበለጠመረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

እሑድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው የትምህርት ዘመን የመዝጊያ መርሐ ግብር የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የኪነ ጥበብ ዝግጅቶችን፣ የበገና ድርደራ፣ መነባንብ እና የግጥም ሥራ
+2
እሑድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው የትምህርት ዘመን የመዝጊያ መርሐ ግብር የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የኪነ ጥበብ ዝግጅቶችን፣ የበገና ድርደራ፣ መነባንብ እና የግጥም ሥራዎችን በማቅረብ የመዝጊያ መርሐ ግብሩ ላይ አቅርበዋል፡፡

የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመዝጊያ መርሐ ግብር ተካሄደ ************* ************** ************ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን
+3
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን                                                       የመዝጊያ መርሐ ግብር ተካሄደ   ************* ************** ************ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች መዝጊያ መርሐ ግብር የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንደስትሪ አ.ማ የማኔጅመንት አባላት፣ የተማሪ ወላጆች፣ የትምህርት ቤቶቹ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተካሄደ፡፡ በመርሐ ግብሩ መክፈቻ ላይ ርእሳነ መምህራን በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተከናወኑ ተግባራትንና በቀጣይ ሊሠሩ የታቀዱ ዐበይት ተግባራትን የቀረቡበት፤ የወላጅ ኮሚቴዎች በቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ያከናወኗቸውን ተግባራት ሪፖርትና የቀረበበት እና የዋና መሥሪያ ቤት ተወካዮች አጠቃላይ ሁኔታዎች ላይ መልእክትና ምስጋና   የቀረበበት ዝግጅት አካሂደዋል፡፡፡

የአቡነ ጎርጎርዮስ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እየወሰዱ ይገኛሉ *********** ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተናውን 563,50
የአቡነ ጎርጎርዮስ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል  መልቀቂያ ፈተና  እየወሰዱ ይገኛሉ *********** ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም  የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተናውን 563,501 ተማሪዎች  በ607 የፈተና መስጫ ማዕከላት በበይነ መረብ (online)   እየተሰጠ  በሚገኘው ሀገር አቀፍ ፈተና 526 የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  ተማሪዎች  ይፈተናሉ፡፡ ቁጥራቸው 269 ወንድ እና 257 ሴት በድምሩ 526 የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማኅበራዊ ሳይንስ  ተማሪዎች በበይነ መረብ (online) እየተሰጠ የሚገኘውን  የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በአዲስ አበባ እና ባሕርዳር የሚገኙ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  ተማሪዎች ፈተናውን እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡ በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ትምህርት ዘርፍ እንዳስታወቀው በ5 ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ሲማሩ የነበሩ ቁጥራቸው 526  የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችም ፈተናቸውን በስኬት እና በውጤት እንዲያጠናቅቁ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን፤ በዚህም ከሥነ ልቦና ስልጠናዎች ጀምሮ በርካታ ፈተናዎችን በበይነ መረብ (online) እንዲወስዱ በማድረግ በርካታ ልምምድና ተግባራዊ ሥራዎች  መሠራቱን አስታውቋል፡፡ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ሀገር አቀፍ ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች የሪሚዲያል ውጤት ያመጡትን ጨምሮ 99.7% ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግባት የሚያስችላቸውን ውጤት ካስመዘገቡ ጥቂት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ እንደ ነበር ይታወሳል፡፡ ለበለጠመረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://es

የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና ያስፈተናቸውን ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ ባሕ
+6
የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና ያስፈተናቸውን ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ በወልድያ እና በድሬደዋ)   ተማሪዎች   100% ማለፋቸው ይታወሳል፡፡ ለበለጠመረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ ቤቶች በ8ኛ ክፍል 100% አሳለፈ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና በአዲስ አበባ ከተማ እና በ
+7
አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ ቤቶች በ8ኛ ክፍል 100% አሳለፈ    በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና  በአዲስ አበባ ከተማ  እና በድሬደዋ ከተማ  አስተዳደር ደረጃ  ይፋ በሆነ ውጤት መሠረት የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች 100% ተማሪዎችን ማሳለፋቸው ታወቀ።   ከሰኔ 11 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለ2 ተከታታይ ቀናት  በተሰጠው የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  1,226 ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ ወልድያ እና ድሬደዋ) ፈተናውን  የወሰዱ ሲሆን እስካሁን ውጤቱ ይፋ በተደረገባቸው በአዲስ አበባ እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደሮች ሁሉም ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ማለፋቸው ነው ይፋ የሆነው፡፡

አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ ቤቶች በ8ኛ ክፍል 100% አሳለፈ    በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና  በአዲስ አበባ ከተማ  እና በድሬደዋ ከተማ  አስተዳደር ደረጃ  ይፋ በሆነ ውጤት መሠረት የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች 100% ተማሪዎችን ማሳለፋቸው ታወቀ።   ከሰኔ 11 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለ2 ተከታታይ ቀናት  በተሰጠው የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  1,226 ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ ወልድያ እና ድሬደዋ) ፈተናውን  የወሰዱ ሲሆን እስካሁን ውጤቱ ይፋ በተደረገባቸው በአዲስ አበባ እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደሮች ሁሉም ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ማለፋቸው ነው ይፋ የሆነው፡፡

በ11 የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ቁጥራቸው 912 ወንድ እና 974 ሴት በድምሩ 1886 ተማሪዎች ለምረቃ ያዘጋጁትን መዝሙራት፣ ስነግጥም፣ ድራማ፣ ቲያ
+7
በ11 የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ቁጥራቸው 912 ወንድ እና 974 ሴት በድምሩ 1886 ተማሪዎች ለምረቃ ያዘጋጁትን መዝሙራት፣ ስነግጥም፣ ድራማ፣ ቲያትር እና ውረብ ጭምር በማጥናት  ታዳሚውን ያስደመመ ዝግጅታቸውን አቅርበዋል፡፡ ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

photo content
+9

የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅድመ አንደኛ ተማሪዎች በታላቅ ድምቀት ተመረቁ ************* ************** ************ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤቶች
+1
የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅድመ አንደኛ ተማሪዎች በታላቅ ድምቀት  ተመረቁ ************* ************** ************ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤቶች በአዲስ አበባ፣ በባሕርዳር፣ በድሬደዋ እና ወልድያ  ሰኔ 20 እና 21 በታላቅ ድምቀት  አስመረቀ:: የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ትምህርታቸውን ለ3 ተከታታይ ዓመታት ሲከታተሉ የነበሩ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ወላጆች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የሥራ ኃላፊዎች እና በውድ መምህራን ታጅበው በታላቅ ሥነ ሥርዓት የምርቃት መርሐ ግብር  አካሂዳዋል፡፡

photo content
+9

አስደሳች ዜና ለወላጆች ኩባንያችን ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ · በመሀል አዲስ አበባ በ22 አካባቢ ሌክስ ፕላዛ ህንጻ አጠገብ ጥራቱን ጠብቆ እየተገነባ ያለውን ሪል እስቴት
+1
አስደሳች ዜና ለወላጆች  ኩባንያችን  ኤስድሮስ  ኮንስትራክሽን ንግድ  እና ኢንዱስትሪ አ.ማ    · በመሀል አዲስ አበባ  በ22  አካባቢ ሌክስ ፕላዛ  ህንጻ አጠገብ   ጥራቱን ጠብቆ  እየተገነባ ያለውን ሪል እስቴት ቤት በመሸጥ ላይ ነው፡፡  ቤቶቹ በአብዛኛው የተሸጡ  ሲሆን  የተወሰኑ የቀሩ ቤቶችን በመግዛት ወይም ሌላ ሰው እንዲገዛ በማድረግ የመልካም እድል ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡ 1. ባለ 2 መኝታ ቤት  የገዛ ወይም ሌላ ሰው እንዲገዛ  ያደረግ ወላጅ  በ2019 የትምህርት ዘመን  በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት አንድ ልጅ በነጻ የማስተማር እድል ያገኛል፣ 2. ባለ3 መኝታ ቤት  የገዛ ወይም ሌላ ሰው እንዲገዛ  ያደረግ በ2019 የትምህርት ዘመን  ሁለት ልጆችን  በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት በነጻ የማስተማር እድል ያገኛል፣ 3. ሌላ ሰው እንዲገዛ አድርገው   የገዛው ሰው የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆን ከፈቀዱለት የገዛው ሰው በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት  አዲስ ልጅ ለማስመዝገብ  ቅድሚያ እንዲያገኝ እና በ2019 የትምህርት ዘመን ለባለ 2 መኝታ 1 ልጅ  እንዲሁ ለባለ 3 መኝታ 2 ልጆችን በነጻ የማስተማር እድል ያገኛል፡፡                         የቀሩን ቤቶች   ጥቂት ስለሆኑ  የእድሉ ተጠቃሚ ለመሆን   ይፍጠኑ !         ለተጨማሪ መረጃ         ስ.ቁ  0930363779  /0903020377

አስደሳች ዜና ለወላጆች ኩባንያችን ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ · በመሀል አዲስ አበባ በ22 አካባቢ ሌክስ ፕላዛ ህንጻ አጠገብ ጥራቱን ጠብቆ እየተገነባ ያለውን ሪል እስቴት
+1
አስደሳች ዜና ለወላጆች  ኩባንያችን  ኤስድሮስ  ኮንስትራክሽን ንግድ  እና ኢንዱስትሪ አ.ማ    · በመሀል አዲስ አበባ  በ22  አካባቢ ሌክስ ፕላዛ  ህንጻ አጠገብ   ጥራቱን ጠብቆ  እየተገነባ ያለውን ሪል እስቴት ቤት በመሸጥ ላይ ነው፡፡  ቤቶቹ በአብዛኛው የተሸጡ  ሲሆን  የተወሰኑ የቀሩ ቤቶችን በመግዛት ወይም ሌላ ሰው እንዲገዛ በማድረግ የመልካም እድል ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡ 1. ባለ 2 መኝታ ቤት  የገዛ ወይም ሌላ ሰው እንዲገዛ  ያደረግ ወላጅ  በ2019 የትምህርት ዘመን  በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት አንድ ልጅ በነጻ የማስተማር እድል ያገኛል፣ 2. ባለ3 መኝታ ቤት  የገዛ ወይም ሌላ ሰው እንዲገዛ  ያደረግ በ2019 የትምህርት ዘመን  ሁለት ልጆችን  በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት በነጻ የማስተማር እድል ያገኛል፣ 3. ሌላ ሰው እንዲገዛ አድርገው   የገዛው ሰው የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆን ከፈቀዱለት የገዛው ሰው በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት  አዲስ ልጅ ለማስመዝገብ  ቅድሚያ እንዲያገኝ እና በ2019 የትምህርት ዘመን ለባለ 2 መኝታ 1 ልጅ  እንዲሁ ለባለ 3 መኝታ 2 ልጆችን በነጻ የማስተማር እድል ያገኛል፡፡                         የቀሩን ቤቶች   ጥቂት ስለሆኑ  የእድሉ ተጠቃሚ ለመሆን   ይፍጠኑ !         ለተጨማሪ መረጃ         ስ.ቁ  0930363779  /0903020377

የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ሰኔ 20 እና 21 በድምቀት ይመረቃሉ ************* ************** ************ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤ
የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ሰኔ 20 እና 21  በድምቀት ይመረቃሉ ************* ************** ************   የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎችን ሰኔ 20 እና 21 በታላቅ ድምቀት ያስመርቃል:: በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የትምህርት ዘርፍ እንዳስታወቀው የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ከጀማሪ የትምህርት ደረጃ ጀምሮ ትምህርታቸውን ለ3 ተከታታይ ዓመታት ሲከታተሉ የነበሩ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ወላጆች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፣ የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የሥራ ኀላፊዎች እና ለዚህ ክብር እንዲደርሱ እንደ ወላጅ ተንከባክበው ባስተማሯቸው መምህራን ታጅበው በታላቅ ሥነ ሥርዓት የምርቃት መርሐ ግብር የፊታችን ቅዳሜና እሑድ ይካሄዳል፡፡ በዚሁ የ2018 ዓ.ም የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ምረቃ  በ 11 የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ቁጥራቸው 912 ወንድ እና 974 ሴት በድምሩ 1886  ተማሪዎች በክብር ይመረቃሉ፡፡ በዚሁ የምረቃ መርሐ ግብርም ተመራቂ ተማሪዎች ለምረቃ በዓላቸው የተለያዩ ዝግጅቶችን እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል፡፡ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች በአዲስ አበባ፣ በባሕርዳር፣ በድሬደዋ እና ወልዲያ በሚገኙ ቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤቶች የሚያስመርቃቸው ተማሪዎች በ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን  ወደ መደበኛ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንደሚሸጋገሩ ይጠበቃል፡፡   ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወ

የአቡነ ጎርጎሪዮስ ተማሪዎች ለመቄዶኒያ 2.125ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረጉ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በመቄዶንያ ገቢ ማሰባሰቢያ አካውንት ቁጥር 7979 በተጨማሪ ከመምህራን እና ከወ
የአቡነ ጎርጎሪዮስ ተማሪዎች  ለመቄዶኒያ 2.125ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረጉ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በመቄዶንያ ገቢ ማሰባሰቢያ አካውንት ቁጥር 7979 በተጨማሪ ከመምህራን እና ከወላጆች   ያሰባሰቡትን 2.125 ሚሊዮን ብር ድጋፍ    ለመቄዶንያ የዐረጋውያን እና አእምሮ ሕሙማን በጎ አድራጎት ድርጅት ገቢ በማሰባሰብ ድጋፍ አደረጉ፡፡ መቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር ምንም ጧሪና ደጋፊ የሌላቸውን በተለይም ደግሞ እራሳቸውን ችለው መንቀሳቀስ፣ መመገብ እና መጸዳዳት የማይችሉ የአልጋ ቁራኛ የሆኑና የሰው ድጋፍ የሚያፈልጋቸው  ከ9 ሺህ በላይ የሚሆኑ ዐረጋዊያን እና የአእምሮ ሕሙማንን ከወደቁበት ጎዳና ላይ በማንሳት አዲስ አበባን ጨምሮ በ56 ቅርንጫፎች የበጎ አድራጎት ሥራውን እያከናወነ ይገኛል፡፡ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  ተማሪዎች በተለያየ ጊዜ በርካታ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን እየሠሩ እንደሚገኝ የሚታወቅ ሲሆን መቄዶንያ በቅርቡ ባዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር ላይ በመገኘት ከመቄዶንያ አካውንት 7979  በተጨማሪ   ከተማሪዎች፣ መምህራን እና ወላጆች ያሰባሰቡትን 2.125( ሁለት ሚሊዮን አንድ መቶ ሃያ አምስት ሺህ ብር ለመቄዶንያ የዐረጋውያን እና አእምሮ ሕሙማን በጎ አድራጎት ድርጅት  ገቢ አድርገዋል፡፡ የአቡነ ጎርጎርዮስ ተምህርት ቤቶች ተማሪዎች በጎ አድራጎት ክበብ ከወላጆች ፣ ከመምህራን እና  ተማሪዎች አልባሳት፣ የምግብ ጥሬ እቃዎች እና የገንዘብ ድጋፍ  በመቄዶንያ፣ በሙዳይ እና ስለ እናት በጎ አድራጎት ማእከል በመገኘት  በልደት እና በትንሣኤ በዓላት ላይ ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ እየሠሩ እንደሚገኝ ከቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮ

ኤስድሮስ ለጀማሪ እኅት ወንድም እና ለዝውውር ማመልከቻ በበይነመረብ መሆኑን አስታወቀ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ለ2019 ዓ.ም የትመህርት ዘ
ኤስድሮስ ለጀማሪ እኅት ወንድም እና ለዝውውር  ማመልከቻ በበይነመረብ መሆኑን  አስታወቀ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ለ2019 ዓ.ም የትመህርት ዘመን ጀማሪ እኅት ወንድም እና ዝውውር ማመልከቻ ጊዜ እስከ ሰኔ15 ቀን 2018 ዓ.ም  በበይነመረብ ብቻ እንደሚያከናውን ነው ያስታወቀው፡፡ በዚህም ወላጆች  እስከ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ባለው ጊዜ ለእኅት ወንድም አመልካቾች (Sibling applicants) https://esdros.com/a/admission-request/ ሊንክ በመጠቀም እንድታመለክቱ የተገለጸ ሲሆን ከቅርንጫፍ ቅርንጫፍ ዝውውር አመልካቾች (Transfer requesting)    https://esdros.com/a/transfer-request እስከ ሰኔ 15 /10/2018 ዓ.ም ብቻ ማመልከት እንደምትችሉ  ያስታወቀ ሲሆን በቀጣይ በምዝገባ ወቅት በሚኖር ቦታዎች ላይ ምዝገባ የሚያካሄድ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ በ29 የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  ለ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአዳዲስ  እና ነባር ተማሪዎች ምዝገባ በቀጣይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የክልል ትምህርት ቢሮዎች በሚያወጡት መርሐግብር መሰረት ምዝገባ ለማከናወን ቅድመ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን  ያስታወቀው፡፡ ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

የ8ኛ ክፍል ፈተና መሰጠት ጀመረ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደረጃ የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫ
የ8ኛ ክፍል  ፈተና መሰጠት ጀመረ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን  የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና  በአዲስ አበባ ከተማ  አስተዳደር ደረጃ የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በመፈተን ላይ ይገኛሉ፡፡ በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የትምህርት ዘርፍ እንዳስታወቀው ሰኔ 11 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለ2 ተከታታይ ቀናት  በሚሰጠው የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች 1,226 ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ ወልዲያ እና ድሬደዋ) ፈተናውን እየተፈተኑ እንደሚገኙ አስታውቋል፡፡ በ6 የትምህርት ዓይነት የሚሰጠውን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ለፈተናው ዝግጅት የማጠናከሪያ ትምህርት፣ የተለያዩ የመለማመጃ ፈተናዎችን እንዲሁም ሁለንተናዊ የስነልቦና ዝግጅት “Exam success mind set and skillset”  ሥልጠናዎችን ሲወስዱ መቆየታቸው ታውቋል፡፡ የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና  ያስፈተናቸውን ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ በወልዲያ እና በድሬደዋ)  1,056 ተማሪዎች   100% ማለፋቸው ይታወሳል፡፡ ለበለጠመረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

የ2018ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት ጀመረ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደረጃ የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶ
የ2018ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት ጀመረ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን  የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና  በአዲስ አበባ ከተማ  አስተዳደር ደረጃ የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በመፈተን ላይ ይገኛሉ፡፡ በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የትምህርት ዘርፍ እንዳስታወቀው ከሰኔ 8 እስከ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ለ3 ተከታታይ ቀናት  በሚሰጠው የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ 11 ቅርንጫፍ የአቡነ ጎርጎሪዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች 1,600 ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ባህርዳር፣ ወልዲያ እና ድሬደዋ) ፈተናውን እየተፈተኑ እንደሚገኙ አስታውቋል፡፡ በ5 የትምህርት ዓይነት የሚሰጠውን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ለፈተናው ዝግጅት የማጠናከሪያ ትምህርት፣ የተለያዩ የመለማመጃ ፈተናዎችን እንዲሁም ሁለንተናዊ የስነልቦና ዝግጅት ሥልጠናዎችን ሲወስዱ መቆየታቸው ታውቋል፡፡ የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸውን ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ባህርዳር፣ በወልዲያ እና በድሬደዋ)  1,335 ተማሪዎች   98.2% ማለፋቸው ይታወሳል፡፡ ለበለጠመረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

photo content

photo content