Esdros S.C
رفتن به کانال در Telegram
እንኳን ወደ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ/ማህበር የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ፡፡ This is Esdros S.C's official Telegram channel. For more updates please visit www.Esdros.com
نمایش بیشتر4 131
مشترکین
+724 ساعت
+437 روز
+87130 روز
آرشیو پست ها
4 131
ልክ የዛሬ 36 ዓመት ሐምሌ 22 ቀን 1982 ዓ.ም በዛሬዋ ዕለት ያኔ የገዳሙ መጋቢ የነበሩት አባ ተጠምቀ በጭንቀት ተውጠዋል። ከአቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ እግር ሥር ወድቀው "ግድ የልዎትም አባ የዛሬው ጉዞ ይቆይዎ። እኔ ጥሩ ሕልም አላየሁም። እባክዎ እግርዎን ከዚህ ቤት አያንሡ፤ እንደው እባክዎ" እያሉ ይለምኗቸዋል። አቡነ ጎርጎርዮስ ግን ወደ መቂ ጊዮርጊስ ለአገልግሎት ለመሄድ ቆርጠው ተነሥተው ነበርና ሳልሄድ አላድርም ብለው እምቢ አሉ። በእርግጥ በዚያች የጉዞ ቀን ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ቀድመው ሳይረዱት ቀርተው አይመስልም። ምክንያቱም "ዛሬ ጥሩ ሕልም አላየሁምና አይሂዱ" ላሏቸው አባ ተጠምቀ " እኔስ ብሆን አንዳች ምልክት ያላየሁ ይመስልሃል። ዛሬ ጠዋት ሱሬን ስታጠቅ ሰባት ጊዜ መልሶ ሲፈታብኝ ነበር" ሲሉ መልሰውላቸዋል። ይሁን እንጂ በመቂ የሚገኝ እጅግ ሕመም የጸናበት አንድ የሚያውቁት ክርስቲያን ስለ ነበር ከራሳቸው ሕይወት ይልቅ ለዚያ ሰው ነፍስ ዋጋ ሰጥተው "አረ ሳላቆርበው እንዳይሞትብኝ" እያሉ አባ ጎርጎርዮስ ወደ መኪናው ፈጥነው ወጡ። ነገር ግን ከዚያ መኪና በሕይወት አልወረዱም። ብፁዕነታቸው ከማረፋቸው ከአንድ ሳምንት በፊት በአላጌ ሕፃናት አምባ የልጆች ማሳደጊያ ተገኝተው በዚያ ቦታ ለሚሠራ ቤተ ክርስቲያን መሠረት ካኖሩ በኋላ "ሰው የሚፈልገውን ከሠራ የሚጠብቀው ሞቱን ነው" ብለው ተናግረው ነበር።
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ከአዲስ አበባ ሕዝብ ጭኖ ከመጣ ተሽከርካሪ ጋር እርሳቸው ያሉበት መኪና ተጋጭቶ ሐምሌ 22 ቀን 1982 ዓ.ም ወደ መቂ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ለአገልግሎት ሲጓዙ በድንገተኛ የመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም ድካም በተወለዱ በሃምሳ ዓመታቸው ማረፋቸው ይታወሳል፡፡
ለበለጠመረጃ፡-
በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል
4 131
ልክ የዛሬ 36 ዓመት ሐምሌ 22 ቀን 1982 ዓ.ም በዛሬዋ ዕለት ያኔ የገዳሙ መጋቢ የነበሩት አባ ተጠምቀ በጭንቀት ተውጠዋል። ከአቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ እግር ሥር ወድቀው "ግድ የልዎትም አባ የዛሬው ጉዞ ይቆይዎ። እኔ ጥሩ ሕልም አላየሁም። እባክዎ እግርዎን ከዚህ ቤት አያንሡ፤ እንደው እባክዎ" እያሉ ይለምኗቸዋል። አቡነ ጎርጎርዮስ ግን ወደ መቂ ጊዮርጊስ ለአገልግሎት ለመሄድ ቆርጠው ተነሥተው ነበርና ሳልሄድ አላድርም ብለው እምቢ አሉ። በእርግጥ በዚያች የጉዞ ቀን ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ቀድመው ሳይረዱት ቀርተው አይመስልም። ምክንያቱም "ዛሬ ጥሩ ሕልም አላየሁምና አይሂዱ" ላሏቸው አባ ተጠምቀ " እኔስ ብሆን አንዳች ምልክት ያላየሁ ይመስልሃል። ዛሬ ጠዋት ሱሬን ስታጠቅ ሰባት ጊዜ መልሶ ሲፈታብኝ ነበር" ሲሉ መልሰውላቸዋል። ይሁን እንጂ በመቂ የሚገኝ እጅግ ሕመም የጸናበት አንድ የሚያውቁት ክርስቲያን ስለ ነበር ከራሳቸው ሕይወት ይልቅ ለዚያ ሰው ነፍስ ዋጋ ሰጥተው "አረ ሳላቆርበው እንዳይሞትብኝ" እያሉ አባ ጎርጎርዮስ ወደ መኪናው ፈጥነው ወጡ። ነገር ግን ከዚያ መኪና በሕይወት አልወረዱም። ብፁዕነታቸው ከማረፋቸው ከአንድ ሳምንት በፊት በአላጌ ሕፃናት አምባ የልጆች ማሳደጊያ ተገኝተው በዚያ ቦታ ለሚሠራ ቤተ ክርስቲያን መሠረት ካኖሩ በኋላ "ሰው የሚፈልገውን ከሠራ የሚጠብቀው ሞቱን ነው" ብለው ተናግረው ነበር።
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ከአዲስ አበባ ሕዝብ ጭኖ ከመጣ ተሽከርካሪ ጋር እርሳቸው ያሉበት መኪና ተጋጭቶ ሐምሌ 22 ቀን 1982 ዓ.ም ወደ መቂ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ለአገልግሎት ሲጓዙ በድንገተኛ የመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም ድካም በተወለዱ በሃምሳ ዓመታቸው ማረፋቸው ይታወሳል፡፡
ለበለጠመረጃ፡-
በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-1
4 131
ልክ የዛሬ 36 ዓመት ሐምሌ 22 ቀን 1982 ዓ.ም በዛሬዋ ዕለት ያኔ የገዳሙ መጋቢ የነበሩት አባ ተጠምቀ በጭንቀት ተውጠዋል። ከአቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ እግር ሥር ወድቀው "ግድ የልዎትም አባ የዛሬው ጉዞ ይቆይዎ። እኔ ጥሩ ሕልም አላየሁም። እባክዎ እግርዎን ከዚህ ቤት አያንሡ፤ እንደው እባክዎ" እያሉ ይለምኗቸዋል። አቡነ ጎርጎርዮስ ግን ወደ መቂ ጊዮርጊስ ለአገልግሎት ለመሄድ ቆርጠው ተነሥተው ነበርና ሳልሄድ አላድርም ብለው እምቢ አሉ። በእርግጥ በዚያች የጉዞ ቀን ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ቀድመው ሳይረዱት ቀርተው አይመስልም። ምክንያቱም "ዛሬ ጥሩ ሕልም አላየሁምና አይሂዱ" ላሏቸው አባ ተጠምቀ " እኔስ ብሆን አንዳች ምልክት ያላየሁ ይመስልሃል። ዛሬ ጠዋት ሱሬን ስታጠቅ ሰባት ጊዜ መልሶ ሲፈታብኝ ነበር" ሲሉ መልሰውላቸዋል። ይሁን እንጂ በመቂ የሚገኝ እጅግ ሕመም የጸናበት አንድ የሚያውቁት ክርስቲያን ስለ ነበር ከራሳቸው ሕይወት ይልቅ ለዚያ ሰው ነፍስ ዋጋ ሰጥተው "አረ ሳላቆርበው እንዳይሞትብኝ" እያሉ አባ ጎርጎርዮስ ወደ መኪናው ፈጥነው ወጡ። ነገር ግን ከዚያ መኪና በሕይወት አልወረዱም። ብፁዕነታቸው ከማረፋቸው ከአንድ ሳምንት በፊት በአላጌ ሕፃናት አምባ የልጆች ማሳደጊያ ተገኝተው በዚያ ቦታ ለሚሠራ ቤተ ክርስቲያን መሠረት ካኖሩ በኋላ "ሰው የሚፈልገውን ከሠራ የሚጠብቀው ሞቱን ነው" ብለው ተናግረው ነበር። ይህም ንግግራቸው ዘመን ተሻጋሪ ንግገራቻበረከታቸው ይደርብን!!!
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ከአዲስ አበባ ሕዝብ ጭኖ ከመጣ ተሽከርካሪ ጋር እርሳቸው ያሉበት መኪና ተጋጭቶ ሐምሌ 22 ቀን 1982 ዓ.ም ወደ መቂ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ለአገልግሎት ሲጓዙ በድንገተኛ የመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም ድካም በተወለዱ በሃምሳ ዓመታቸው ማረፋቸው ይታወሳል፡፡
ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ን
4 131
+2
በተያያዘም በአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች፣የቀድሞ የአቡነ ጎርጎርዮስ ጎርጎሪዮስ ተማሪዎች ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ የረፍታቸውን መታሰቢያ የጧፍ ማብራት እና የተለያዩ መርሐግብራት የብፁዕነታቸውን አስተምህሮ፣ሥራዎቻቸውና ለሀገርና ለቤተክርስቲያን ያበረከቷቸውን ዘመን ተሸጋሪ አሻራዎችን በመዘከር እና በተለያዩ መርሐ ግብሮች ዘክረው ውለዋል፡፡
4 131
+3
በመርሐግብሩም የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ካፋሯቸው የመጀመሪያዎቹ ከ1980-1982 ድረስ በክረምት ኮርስ ተከታትለው ከተማሩት 12 ደቀመዛሙርት መካከል አንዱ የሆኑት ሊቀ ትጉሐን ቀሲስ ዶ/ር ሙልጌታ ስዪም ከብጹነታቸው በአካል ከሰሙት፣አንዲሁም ስለ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ህይወትና ሰራዎች ዙሪያ ያደረጉትን ጥልቅ ጥናት በመርሐግብሩ አቅርበዋል፡፡
በቀረበው ጥናትም የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ በ10 ዓመታት የሊቀጳጳስነት ህይወታቸው(1971-1982) በርካታ ስራዎችን ከዝዋይ ሐመረ ብር ሐንቅዱስ ገብርኤል ገዳም እስከ ዓለም አቀፍ የሀይማኖት ጉባኤ ያበረከቱት፣ከ6 በላይ ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ቋንቋን አቀላጥፈው መናገራቸው፣በዓለም አቀፍ ጉባያትም ጥልቅ ጥናት በማቅረብ ይታወቁ እነደነበር ፣ከ17 በላይ ሊቃነ ጳጳሳትን ከማፍራት በላይም በአጭር የአገልግሎት ዘመናቸው በርካታ አበርክቶቸውን እና ህይወታቸውን የሚያሳይ ጥልቅ ጥናት የቀረበበትም ነበር፡፡
4 131
+1
በመርሐግብሩም የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ካፋሯቸው የመጀመሪያዎቹ ከ1980-1982 ድረስ በክረምት ኮርስ ተከታትለው ከተማሩት 12 ደቀመዛሙርት መካከል አንዱ የሆኑት ሊቀ ትጉሐን ቀሲስ ዶ/ር ሙልጌታ ስዪም ከብጹነታቸው በአካል ከሰሙት፣አንዲሁም ስለ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ህይወትና ሰራዎች ዙሪያ ያደረጉትን ጥልቅ ጥናት በመርሐግብሩ አቅርበዋል፡፡
በቀረበው ጥናትም የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ በ10 ዓመታት የሊቀጳጳስነት ህይወታቸው(1971-1982) በርካታ ስራዎችን ከዝዋይ ሐመረ ብር ሐንቅዱስ ገብርኤል ገዳም እስከ ዓለም አቀፍ የሀይማኖት ጉባኤ ያበረከቱት፣ከ6 በላይ ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ቋንቋን አቀላጥፈው መናገራቸው፣በዓለም አቀፍ ጉባያትም ጥልቅ ጥናት በማቅረብ ይታወቁ እነደነበር ፣ከ17 በላይ ሊቃነ ጳጳሳትን ከማፍራት በላይም በአጭር የአገልግሎት ዘመናቸው በርካታ አበርክቶቸውን እና ህይወታቸውን የሚያሳይ ጥልቅ ጥናት የቀረበበትም ነበር፡፡
4 131
+3
36ኛ ዓመት የብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ፪ የዕረፍታቸው መታሰቢያ ተካሄደ
ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም የሸዋ ሊቀ ጳጳስ የነበሩት የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ 36ኛ ዓመት መታሰቢያ መርሐግብር ተካሄደ፡፡ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት ሰራተኞች 36ኛውን የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የዕረፍታቸውን መታሰቢያ ዘክረዋል፡፡
በመርሐግብሩም የብፁዕነታቸውን ህይወት፣ዕምነት፣ስራዎችና ዝናት የሚያወሳ ዝማሜ እንዲሁም የብፁዕነታቸውን አስተምህሮ፣ሥራዎቻቸውና ለሀገርና ለቤተክርስቲያን ያበረከቷቸውን ዘመን ተሸጋሪ አሻራዎችን የሚያሳይ ጥናት የቀረበበት ደማቅ የዝክር መርሐግብር ተካሄዷል፡፡
4 131
ማስታወቂያ ለወሰን ኮተቤ 02 አካባቢ ወላጆች
ትምህርት ቤታችን አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤቾች ለ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ወሰን ኮተቤ 02 አካባቢ አዲስ ለከፈተው ቅድመ አንደኛ (ከነርሰሪ እስከ ዩኬጂ ምዝገባ መጀመሩን በታላቅ ደስታ ይገልጻል፡፡
የተማሪዎች ምዝገባም በመሪ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ቅድሚያ ተመዝጋቢዎችን ተቀብሎ ለማስተማር እየመዘገበ ይገኛል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡-
- 0111575954
- 0930363779
- 0973600010
በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይችላሉ።
4 131
ማስታወቂያ
አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት ተጨማሪ ቅርንጫፍ ሊከፍት ነው
ለ2019ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከላምበረት ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ወደ ኮተቤ 02 መግቢያ 300 ሜትር ገባ ብሎ አጸደ ህጻናት ቅርንጫፍ ለመክፈት በዝግጅት ላይ ይገኛል። ስለሆነም በአቅራቢያው የምትገኙ ነዋሪዎች የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ስንል በደስታ እንገልጻለን።
ለበለጠ መረጃ ከታች ባሉት ስልክ ቁጥሮች
- 0111575954
- 0930363779
- 0973600010
ደውለው ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይችላሉ።
4 131
በአዲስ አበባ አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ ቤቶች በ6ኛ ክፍል 99.6% አሳለፈ
የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደረጃ ይፋ በሆነ ውጤት መሠረት የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች 99.6% ተማሪዎችን አሳለፈ።
ከሰኔ 8 እስከ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ለ3 ተከታታይ ቀናት በተሰጠው የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ ወልድያ እና ድሬዳዋ) ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን እስካሁን ውጤቱ ይፋ በተደረገው በአዲስ አበባ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ማለፋቸው ነው ይፋ የሆነው፡፡
በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የትምህርት ዘርፍ እንዳስታወቀው የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ 11 ቅርንጫፍ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች 1,600 ተማሪዎች (በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ ወልድያ እና ድሬዳዋ) ፈተናውን መውሰዳቸው ታውቋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 97.48% የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 50% እና ከዚያ በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መዘዋወራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ይፋ ያደረገው መረጃ ያሳያል፡፡
ለበለጠመረጃ፡-
በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::
4 131
+7
የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶቻችን በተካሄደው የመዝጊያ መርሐ ግብር ላይ በትምህርት ዘመኑ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የዋንጫ፣ የሰርተፍኬት እና የተለያዩ ሽልማቶች በክብር እንግድነት በተገኙ እንግዶች እና በርእሳነ መምህራን ተበርክቶላቸዋል፡፡
በ2018 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራው ላይ ከፍተኛ አበርክቶ ላደረጉ መምህራን፣ የአስተዳዳር ሰራተኞች፣ ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞችም ጭምር ልዩ ልዩ የማበረታቻ ሽልማት ተሸልመዋል፡፡
በመዝጊያ ሥነ ሥርዓቱ ማጠቃለያም ተማሪዎች የውጤት መግለጫ ካርዳቸውን ከየክፍል ተጠሪ መምህራን እጅ ተቀብለው የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል፡፡
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በ29 ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች 25,623 ተማሪዎችን ሲያስተምር እንደነበር ይታወሳል፡፡
ለበለጠመረጃ፡-
በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::
4 131
+2
እሑድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው የትምህርት ዘመን የመዝጊያ መርሐ ግብር የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የኪነ ጥበብ ዝግጅቶችን፣ የበገና ድርደራ፣ መነባንብ እና የግጥም ሥራዎችን በማቅረብ የመዝጊያ መርሐ ግብሩ ላይ አቅርበዋል፡፡
4 131
+3
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመዝጊያ መርሐ ግብር ተካሄደ
************* ************** ************
የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች መዝጊያ መርሐ ግብር የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንደስትሪ አ.ማ የማኔጅመንት አባላት፣ የተማሪ ወላጆች፣ የትምህርት ቤቶቹ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተካሄደ፡፡
በመርሐ ግብሩ መክፈቻ ላይ ርእሳነ መምህራን በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተከናወኑ ተግባራትንና በቀጣይ ሊሠሩ የታቀዱ ዐበይት ተግባራትን የቀረቡበት፤ የወላጅ ኮሚቴዎች በቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ያከናወኗቸውን ተግባራት ሪፖርትና የቀረበበት እና የዋና መሥሪያ ቤት ተወካዮች አጠቃላይ ሁኔታዎች ላይ መልእክትና ምስጋና የቀረበበት ዝግጅት አካሂደዋል፡፡፡
4 131
የአቡነ ጎርጎርዮስ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እየወሰዱ ይገኛሉ
***********
ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተናውን 563,501 ተማሪዎች በ607 የፈተና መስጫ ማዕከላት በበይነ መረብ (online) እየተሰጠ በሚገኘው ሀገር አቀፍ ፈተና 526 የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ይፈተናሉ፡፡
ቁጥራቸው 269 ወንድ እና 257 ሴት በድምሩ 526 የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በበይነ መረብ (online) እየተሰጠ የሚገኘውን የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በአዲስ አበባ እና ባሕርዳር የሚገኙ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ፈተናውን እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡
በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ትምህርት ዘርፍ እንዳስታወቀው በ5 ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ሲማሩ የነበሩ ቁጥራቸው 526 የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችም ፈተናቸውን በስኬት እና በውጤት እንዲያጠናቅቁ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን፤ በዚህም ከሥነ ልቦና ስልጠናዎች ጀምሮ በርካታ ፈተናዎችን በበይነ መረብ (online) እንዲወስዱ በማድረግ በርካታ ልምምድና ተግባራዊ ሥራዎች መሠራቱን አስታውቋል፡፡
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ሀገር አቀፍ ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች የሪሚዲያል ውጤት ያመጡትን ጨምሮ 99.7% ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግባት የሚያስችላቸውን ውጤት ካስመዘገቡ ጥቂት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ እንደ ነበር ይታወሳል፡፡
ለበለጠመረጃ፡-
በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://es
4 131
+6
የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና ያስፈተናቸውን ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ በወልድያ እና በድሬደዋ) ተማሪዎች 100% ማለፋቸው ይታወሳል፡፡
ለበለጠመረጃ፡-
በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::
4 131
+7
አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ ቤቶች በ8ኛ ክፍል 100% አሳለፈ
በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና በአዲስ አበባ ከተማ እና በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ደረጃ ይፋ በሆነ ውጤት መሠረት የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች 100% ተማሪዎችን ማሳለፋቸው ታወቀ።
ከሰኔ 11 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለ2 ተከታታይ ቀናት በተሰጠው የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች 1,226 ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ ወልድያ እና ድሬደዋ) ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን እስካሁን ውጤቱ ይፋ በተደረገባቸው በአዲስ አበባ እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደሮች ሁሉም ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ማለፋቸው ነው ይፋ የሆነው፡፡
4 131
አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ ቤቶች በ8ኛ ክፍል 100% አሳለፈ
በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና በአዲስ አበባ ከተማ እና በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ደረጃ ይፋ በሆነ ውጤት መሠረት የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች 100% ተማሪዎችን ማሳለፋቸው ታወቀ።
ከሰኔ 11 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለ2 ተከታታይ ቀናት በተሰጠው የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች 1,226 ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ ወልድያ እና ድሬደዋ) ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን እስካሁን ውጤቱ ይፋ በተደረገባቸው በአዲስ አበባ እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደሮች ሁሉም ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ማለፋቸው ነው ይፋ የሆነው፡፡
4 131
+7
በ11 የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ቁጥራቸው 912 ወንድ እና 974 ሴት በድምሩ 1886 ተማሪዎች ለምረቃ ያዘጋጁትን መዝሙራት፣ ስነግጥም፣ ድራማ፣ ቲያትር እና ውረብ ጭምር በማጥናት ታዳሚውን ያስደመመ ዝግጅታቸውን አቅርበዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡-
በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::
4 131
+1
የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅድመ አንደኛ ተማሪዎች በታላቅ ድምቀት ተመረቁ
************* ************** ************
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤቶች በአዲስ አበባ፣ በባሕርዳር፣ በድሬደዋ እና ወልድያ ሰኔ 20 እና 21 በታላቅ ድምቀት አስመረቀ::
የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ትምህርታቸውን ለ3 ተከታታይ ዓመታት ሲከታተሉ የነበሩ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ወላጆች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የሥራ ኃላፊዎች እና በውድ መምህራን ታጅበው በታላቅ ሥነ ሥርዓት የምርቃት መርሐ ግብር አካሂዳዋል፡፡
