ar
Feedback
Esdros S.C

Esdros S.C

الذهاب إلى القناة على Telegram

እንኳን ወደ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ/ማህበር የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ፡፡ This is Esdros S.C's official Telegram channel. For more updates please visit www.Esdros.com

إظهار المزيد
3 171
المشتركون
+424 ساعات
+147 أيام
-130 أيام
أرشيف المشاركات
የ2018ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት ጀመረ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደረጃ የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶ
የ2018ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት ጀመረ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን  የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና  በአዲስ አበባ ከተማ  አስተዳደር ደረጃ የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በመፈተን ላይ ይገኛሉ፡፡ በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የትምህርት ዘርፍ እንዳስታወቀው ከሰኔ 8 እስከ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ለ3 ተከታታይ ቀናት  በሚሰጠው የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ 11 ቅርንጫፍ የአቡነ ጎርጎሪዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች 1,600 ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ባህርዳር፣ ወልዲያ እና ድሬደዋ) ፈተናውን እየተፈተኑ እንደሚገኙ አስታውቋል፡፡ በ5 የትምህርት ዓይነት የሚሰጠውን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ለፈተናው ዝግጅት የማጠናከሪያ ትምህርት፣ የተለያዩ የመለማመጃ ፈተናዎችን እንዲሁም ሁለንተናዊ የስነልቦና ዝግጅት ሥልጠናዎችን ሲወስዱ መቆየታቸው ታውቋል፡፡ የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸውን ተማሪዎች(በአዲስ አበባ፣ባህርዳር፣ በወልዲያ እና በድሬደዋ)  1,335 ተማሪዎች   98.2% ማለፋቸው ይታወሳል፡፡ ለበለጠመረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

photo content

photo content

ክቡራን ባለአክሲዮኖች፡፡ ስለ ኩባንያዎ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ  አስተያየት ጥቆማና መረጃ ለመስጠት ይህንን የቴሌግራም ቦት ይክፈቱ  ፡፡ ☞ @esdros_shareholders_service_bot በመቀጠልም /Start  ብለው ያስገቡ፡፡ ☞ባስመዘገቡን_ስልክ_ቁጥር_የቴሌግራም_አካውንት_መሆን_ይኖርበታል፡፡ ☞ አድራሻዬን አጋራ የሚለውን በሚነኩ ጊዜ ማረጋገጫ ይደርስዎታል፡፡ ስለ ጊዜዎ እናመሰግናለን፡፡ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ

ክቡራን ባለአክሲዮኖች፡፡ ስለ ኩባንያዎ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ  አስተያየት ጥቆማና መረጃ ለመስጠት ይህንን የቴሌግራም ቦት ይክፈቱ  ፡፡ ☞ @esdros_shareholders_service_bot በመቀጠልም /Start  ብለው ያስገቡ፡፡ ☞ባስመዘገቡን_ስልክ_ቁጥር_የቴሌግራም_አካውንት_መሆን_ይኖርበታል፡፡ ☞ አድራሻዬን አጋራ የሚለውን በሚነኩ ጊዜ ማረጋገጫ ይደርስዎታል፡፡ ስለ ጊዜዎ እናመሰግናለን፡፡ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ

በዚሁ መርሐ ግብርም የ2ኛው መንፈቀ ዓመት የተቋሙን ዋና ዋና ስኬቶችን እና ቁልፍ ተግባራትን የሚያሣዩ ፎቶ የግራፎች አውደርዕይ በወላጆች የተጎበኘበት፣ ተማሪዎች ፈጠራ ሥራዎች የሥዕል፣ ቅርጻ ቅርጽ
+4
በዚሁ መርሐ ግብርም የ2ኛው መንፈቀ ዓመት የተቋሙን ዋና ዋና ስኬቶችን እና ቁልፍ ተግባራትን የሚያሣዩ ፎቶ የግራፎች አውደርዕይ በወላጆች የተጎበኘበት፣ ተማሪዎች ፈጠራ ሥራዎች የሥዕል፣ ቅርጻ ቅርጽ እና የ“ICT” ለወላጆች ቀርበዋል፡፡ በየክፍሉ የልጆችን ባሕሪ ለመለየት ከወላጆች ጋር ስኬታማ የሆነ ውይይቶችን ያደረጉበት፣ ወላጆች በተቋሙ አገልግሎት ላይ ያላቸውን አስተያየቶች የሰጡበት እና የወላጆች የአገልግሎት እርካታ የዳሰሳ ጥናት መጠይቆች ተዘጋጅተው በወላጆች እንዲሞሉ የተደረገበት ከመርሐ ግበሩ መካከል ይገኙበታል፡፡ ይኸው የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች እሴትን መሠረት በማድረግ የተካሄደው መርሐ ግብር ሁለንተናዊ ግንኙነትን ከማሳደጉም በላይ የመማር ማስተማር ሥራውንም በቅርበት በመከወን ድርሻው ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል፡፡ የወላጆችና የመምህራን የገጽ ለገጽ ውይይት (ወላጅና መምህራን) መርሐ ግብር በየመንፈቀ ዓመቱ አጋማሽ ላይ የሚደረግ በመሆኑ የተማሪዎችን የ2ኛውን መንፈቀ ዓመት ውጤታቸውን ለማሳደግ የሚረዳ ያለመ እንደነበር ታውቋል፡፡ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ በ2004 ዓ.ም ዘመኑን በዋጁ 12 መሥራች አባላት ሥራ የጀመረ እና በአሁኑ ወቅት በ29 የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች 25,632 ተማሪዎችን ከቅድመ አንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል በማስተማር ለ1,979 ሠራተኞችም የሥራ ዕድል መፍጠር የቻለ ኩባንያ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

የ2018 ዓ.ም የትመህርት ዘመን የመጨረሻው የገጽ ለገጽ ውይይት ተካሄደ ************ በአቡነ ጎርጎርዮስ 29ኙም ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ2ኛ መንፈቀ ዓመት
+7
የ2018 ዓ.ም የትመህርት ዘመን የመጨረሻው የገጽ ለገጽ ውይይት  ተካሄደ ************ በአቡነ ጎርጎርዮስ 29ኙም ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ2ኛ መንፈቀ ዓመት  የገጽ ለገጽ ውይይት (ወላጅና መምህራን ) የትምህርት ባለሙያዎች፣ መምህራን እና ወላጆች በተገኙበት ተካሄደ፡፡ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው በዚሁ በአቡነ ጎርጎርዮስ 29ኙም ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች  መምህራን እና ወላጆች የገጽ ለገጽ ውይይት ከወላጆች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ  ወላጆች ከክፍል ተወካይ መምህራን ጋራ በልጆቻቸው የትምህርት ውጤትና ሥነ ምግባር ዙሪያም የገጽ ለገጽ ውይይት አድርገዋል፡፡

በተመሳሳይም በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 እና 8 የሥነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን አዘጋጅነት በተካሄደው የሥነ ምግባር የጥያቄና መልስ ውድድር የ5ኛ ክፍሉ ተማሪ ቴዎድሮስ እኩልነት የተጠየቀውን
በተመሳሳይም በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 እና 8 የሥነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን አዘጋጅነት በተካሄደው የሥነ ምግባር የጥያቄና መልስ ውድድር የ5ኛ ክፍሉ ተማሪ ቴዎድሮስ እኩልነት የተጠየቀውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ በመመለስ 1ኛ ደረጃን በማግኝት ልዩ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች አዋሬ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍል 100% ተማሪዎችን በማሳለፍ እና በወረዳ፣ በክፍለ ከተማ እና በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ በበርካታ ውድድሮች አሸናፊ በመሆን በርካታ ሽልማቶች አንደተበረከቱለት ይታወሳል፡፡ በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

የአቡነ ጎርጎርዮስ አዋሬ 1ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ በሁለት ውድደሮች አሸነፈ ************ በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 እና ወረዳ 8 ብሔረ ኢትዮጵያ ጉድኝት በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍል የ
የአቡነ ጎርጎርዮስ አዋሬ 1ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ በሁለት ውድደሮች አሸነፈ ************ በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 እና ወረዳ 8  ብሔረ ኢትዮጵያ ጉድኝት  በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍል የቀለም ትምህርት የጥያቄና መልስ ውድድር  እና በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 እና 8 የሥነ ምግባር እና ጸረ ሙስና  ኮሚሽን  አዘጋጅነት የሥነ ምግባር የጥያቄና መልስ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  አዋሬ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ  ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት  አሸናፊ ሆነ፡፡ ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም በብሔረ ኢትዮጵያ  1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተካሄደው የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የቀለም ትምህርት የጥያቄና መልስ ውድድር በ6ኛ ክፍል ተማሪ አፎሚያ ኃይሉ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን ስታሸንፍ፤ በ8ኛ ክፍል ተማሪ ፍቅር ምንውየለት የተጠየቀችውን ሁሉንም ጥያቄ በመመለስ 1ኛ ደረጃን በማግኘት አሸናፊ  ስትሆን ልዩ ሽልማት እና ሰርተፍኬት  ተበርክቶላቸዋል፡፡

የአቡነ ጎርጎርዮስ ባሕርዳር 2ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ በባሕርዳር ከተማ አሸናፊ ሆነ ************ በአማራ ክልላዊ መንግሥት ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ባዘጋጀው የትምህርት ቤቶች የሳይንስና ፈጠራ ክበ
+1
የአቡነ ጎርጎርዮስ ባሕርዳር  2ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ በባሕርዳር ከተማ  አሸናፊ  ሆነ ************ በአማራ ክልላዊ መንግሥት ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ባዘጋጀው የትምህርት ቤቶች የሳይንስና ፈጠራ ክበባት ሥልጠና እና ውድድር ላይ በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  ባሕዳር  2ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት  በክልል  ደረጃ 3ኛ በመሆን  አሸናፊ ሆነ፡፡ ግንቦት 1 እና 2 ቀን 2018 ዓ.ም በባሕርዳር ኢኖቬሽን ሴንተር  በተካሄደው ውድድር  በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  ባሕርዳር  2ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት በ11ኛ ክፍል ተማሪው ተማሪ  ሱራፌል ወርቁ  አማካኝነት ነው 3ኛ ደረጃን ያገኘው፡፡ በውድድሩ ተማሪ ሱራፌል ወርቁ ‘’Smart Attendance Management System’’ በመሥራት በውድድሩ ከተሳተፉ 20 የመንግሥት እና የግል  2ኛ ደረጃ ትምህርት  ቤቶች መካከል 3ኛ ደረጃን በመያዝ አሸናፊ የሆነው፡፡ በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  ባሕርዳር  2ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ትምህርት  በአማራ ክልላዊ መንግሥት ትምህርት ቢሮ በየዓመቱ በሚዘጋጅ የሳይንስ እና የፈጠራ ውድድር ከፍተኛ ውጤት በማምጣት አሸናፊ እንደነበር ይታወቃል፡፡ በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com  በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

photo content

የአቡነ ጎርጎርዮስ መሪ 2ኛ ደረጃ በአዲስ አበባ ከተማ አሸናፊ ሆነ ************ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አዘጋጅነት በተካሄደ የሳይንስ፣ የሒሳብ፤ የሥዕልና የአይቲ ውድድ
የአቡነ ጎርጎርዮስ መሪ 2ኛ ደረጃ  በአዲስ አበባ ከተማ  አሸናፊ  ሆነ ************ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ  አዘጋጅነት  በተካሄደ የሳይንስ፣ የሒሳብ፤ የሥዕልና የአይቲ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  መሪ 2ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት  ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማን በመወከል  በከተማ ደረጃ  አሸናፊ ሆነ፡፡ በሒሳብ  2ኛ ደረጃን በመያዝ   መምህር ዳንኤል ጫኔ የብር ሜዳሊያና ሰርተፍኬት ተሸላሚ  ሲሆኑ በሥዕል  ሥራ  በመምህር ዮሐንስ ሞገስ  3ኛ ደረጃን በመያዝ  የነሐስ ሜዳሊያ እና ሰርተፍኬት  በማግኘት ውድድሩን አጠናቀዋል ። መሪ 2ኛ ደረጃ  ቅርንጫፍ ት/ቤት በለሚ ኩራ  ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት  በተካሄደ የሳይንስ፣ የሒሳብ፤ የሥዕልና የአይቲ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች  መሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት  በክፍለ ከተማው ከሚገኙ  35 የመንግሥትና የግል 2ኛ ደረጃ  ትምህርት ቤቶች መካከል  1ኛ በመሆን አሸናፊ  መሆኑ ይታወሳል፡፡   በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com  በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

ye ana photo lakilegn

በመምህራን በሳይንስ የኬሚስትሪ የፈጠራ ሥራ መምህርት እመቤት ሞገስ የወርቅ ሜዳሊያ፣ በሥዕል የፈጠራ ሥራ መምህር ዮሐንስ ሞገስ የወርቅ ሜዳሊያ፣ በፊዚክስ እና በባዮሎጂ የፈጠራ ውድድር 2 የወርቅ ሜ
+3
በመምህራን በሳይንስ የኬሚስትሪ የፈጠራ ሥራ መምህርት እመቤት ሞገስ የወርቅ ሜዳሊያ፣ በሥዕል የፈጠራ ሥራ መምህር ዮሐንስ ሞገስ የወርቅ ሜዳሊያ፣ በፊዚክስ እና በባዮሎጂ የፈጠራ ውድድር 2 የወርቅ ሜዳሊያ መምህር ዳንኤል ጫኔ ተሸላሚ ሲሆኑ በተማሪዎች የፈጠራ ውድድር ተማሪ በእምነት ዘውዴ በሒሳብ እና ተማሪ ብሩክ ንጉሥ በሥዕል ውድድር የብር ሜዳሊያ በማግኘት በክፍለ ከተማ ደረጃ የአሸናፊዎች አሸናፊ ሆነዋል፡፡ በገላን ጉራ ትምህርት ቤት ግቢ በተካሄደው የመዝጊያ ስነ-ሥርዓት ላይ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ቤቶች የአሸናፋዎች አሸናፊ ውድድር ያሸነፉት የመሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዋንጫ ሽልማቱን ከለሚ ኩራ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት ኃላፊ ከወ/ሮ ሌሊስቱ ተስፋዬ እጅ ተረክበዋል። በቀጣይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ደረጃ በሚካሄደው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ የመንግሥትና የግል ትምህርት ተቋማት የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች መሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማን በመወከል እንደሚወዳደር ይጠበቃል፡፡ በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የአቡነ ጎርጎርዮስ መሪ 2ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ት/ቤት 1ኛ ሆነ ************ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት በተካሄደ የሳይንስ፣ የሒሳብ፤ የሥዕልና የአ
+1
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የአቡነ ጎርጎርዮስ መሪ 2ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ት/ቤት 1ኛ ሆነ ************ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት በተካሄደ የሳይንስ፣ የሒሳብ፤ የሥዕልና የአይቲ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች መሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በክፍለ ከተማው ከሚገኙ 35 የመንግሥትና የግል 2ኛ ትምህርት ቤቶች መካከል 1ኛ በመሆን አሸናፊ ሆነ፡፡ በዚሁ ውድድር በመምህራን የፈጠራ ሥራ ውድድር 4 መምህራን የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ሲሆኑ 2 ተማሪዎች የብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡

በመምህራን በሳይንስ የኬሚስትሪ የፈጠራ ሥራ መምህርት እመቤት ሞገስ የወርቅ ሜዳሊያ፣ በሥዕል የፈጠራ ሥራ መምህር ዮሐንስ ሞገስ የወርቅ ሜዳሊያ፣ በፊዚክስ እና በባዮሎጂ የፈጠራ ውድድር 2 የወርቅ ሜ
+3
በመምህራን በሳይንስ የኬሚስትሪ የፈጠራ ሥራ መምህርት እመቤት ሞገስ የወርቅ ሜዳሊያ፣ በሥዕል የፈጠራ ሥራ መምህር ዮሐንስ ሞገስ የወርቅ ሜዳሊያ፣ በፊዚክስ እና በባዮሎጂ የፈጠራ ውድድር 2 የወርቅ ሜዳሊያ መምህር ዳንኤል ጫኔ ተሸላሚ ሲሆኑ በተማሪዎች የፈጠራ ውድድር ተማሪ በእምነት ዘውዴ በሒሳብ እና ተማሪ ብሩክ ንጉሥ በሥዕል ውድድር የብር ሜዳሊያ በማግኘት በክፍለ ከተማ ደረጃ የአሸናፊዎች አሸናፊ ሆነዋል፡፡ በገላን ጉራ ትምህርት ቤት ግቢ በተካሄደው የመዝጊያ ስነ-ሥርዓት ላይ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ቤቶች የአሸናፋዎች አሸናፊ ውድድር ያሸነፉት የመሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዋንጫ ሽልማቱን ከለሚ ኩራ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት ኃላፊ ከወ/ሮ ሌሊስቱ ተስፋዬ እጅ ተረክበዋል። በቀጣይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ደረጃ በሚካሄደው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ የመንግሥትና የግል ትምህርት ተቋማት የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች መሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማን በመወከል እንደሚወዳደር ይጠበቃል፡፡ በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የአቡነ ጎርጎርዮስ መሪ 2ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ት/ቤት 1ኛ ሆነ ************ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት በተካሄደ የሳይንስ፣ የሒሳብ፤ የሥዕልና የአ
+3
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የአቡነ ጎርጎርዮስ መሪ 2ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ት/ቤት 1ኛ ሆነ ************ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት በተካሄደ የሳይንስ፣ የሒሳብ፤ የሥዕልና የአይቲ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች መሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በክፍለ ከተማው ከሚገኙ 35 የመንግሥትና የግል 2ኛ ትምህርት ቤቶች መካከል 1ኛ በመሆን አሸናፊ ሆነ፡፡ በዚሁ ውድድር በመምህራን የፈጠራ ሥራ ውድድር 4 መምህራን የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ሲሆኑ 2 ተማሪዎች የብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡

ቃሊቲ 2ኛ ደረጃ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ አሸናፊ ሆነ ************ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት በተካሄደ የሳይንስ እና የፈጠራ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት
+3
ቃሊቲ 2ኛ ደረጃ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ አሸናፊ ሆነ ************ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት በተካሄደ የሳይንስ እና የፈጠራ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ቃሊቲ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በክፍለ ከተማው ከሚገኙ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል አሸናፊ ሆነ፡፡ በዚሁ ውድድር ተማሪ ፍቅር በሱፍቃድ በባዮሎጅ የፈጠራ ሥራ 1ኛ ደረጃን በመያዝ የዋንጫ ተሸላሚ ሲሆን ተማሪ ቢኒያም ታደሰ በኬሚስትሪ የፈጠራ ሥራ 2ኛ ደረጃን አግኝቷል፡፡ በሥዕልና ቅርጻ ቅርጽ የፈጠራ ውድድር ተማሪ ገሊላ ዳኛቸው 3ኛ በመውጣት የሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆናለች፡፡ በደራርቱ ቱሉ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ በተካሄደው 19 የመንግሥት እና የግል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በተካሄደው የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ያሸነፉት የቃሊቲ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሽልማቱን ከአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከበደ ድሪባ ተረክበዋል። ተማሪ ፍቅር በሱፍቃድ እና ተማሪ ቢኒያም ታደሰ በቀጣይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አዘጋጅነት ለሚካሄደው የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማን በመወከል እንደሚወዳደሩ ይጠበቃል፡፡ በስልክ ቁጥር 0111575954/0930-36-37-79/0973-60-00-10 በመደወል ወይም/እና የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገጽ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

H

photo content