Neway Tsegaye:
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ የማኔጅመንት ቦርድ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓም ባደረገው ስብሰባ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ለዶር በረከት ፋንታሁን አጸደቀ፡፡ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ የዶር በረከት ፋንታሁንን መረጃዎች ከገመገመ በኃላ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል፡፡
ፕሮፌሰር በረከት ፋንታሁን ይስማው በኮሌጁ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ፕረፌሰር ሲሆኑ በሙያቸው የህጻናት ሕክምና ስፔሻሊስት ናቸው፡፡ በሕጻናት ኢንዶክራይኖሎጂ ሕክምና ደግሞ የሰብ ስፔሻሊስት ስልጠና አላቸው፡፡ በሕክምና ትምህርት፣ በምርምር እና በጤና ሥርዓት ማጠናከር ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክተዋል፡፡ በአዲስ አበባ የተወለዱት ፕሮፌሰር በረከት በአሁኑ ወቅት በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡
የመጀመሪያ የሕክምና ትምህርታቸውን በጎንደር የሕክምና ሳይንስ ኮሌጅ ያጠናቀቁ ሲሆን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በሕጻናት ሕክምና የስፔሻሊቲ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡ በኬንያ በገርትሩድ የሕፃናት ሆስፒታል በሕፃናት ኢንዶክራይኖሎጂ ሰብስፔሻሊቲ ስልጠና ተከታትለዋል፡፡። እንዲሁም የዓለም አቀፉ የጤና አገልግሎት ጥራት ማህበር (ISQua) ፌሎው በመሆን ሰርተዋል፡፡
በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ የተመላላሽ ሕሙማን ክፍል ዳይሬክተር እና የሕጻናት ትምህርት ክፍል ሃላፊ ሆነው አገልግለዋል፡፡ በተጨማሪም የኤሌክትሮኒክ የሕክምና መረጃ ሥርዓት (EMR) ትግበራን በመምራት እና የሕፃናት የስኳር በሽታ መርሀግብርን በመላ አገሪቱ በማስፋፋት ሰርተዋል ።
ፕሮፌሰር በረከት በሕፃናት ኢንዶክራይኖሎጂ እና በሕፃናት የስኳር በሽታ ላይ ያተኮሩ በርካታ ጥናቶችን በአገር ውስጥና በዓለም አቀፍ መጽሔቶች አሳትመዋል፡፡ የምርምር ሥራቸውም የክሊኒካል ልምምድን እና የሕዝብ ጤና ውጤቶችን በማሻሻል አስተዋፅኦ አድርጓል። በተጨማሪም እንደ ታዋቂ ሴት ክሊኒካል ተመራማሪ እና በኢትዮጵያ ሕክምና ዘርፍ አርአያ በመሆናቸው በርካታ ሽልማቶችን ተቀብለዋል፡፡
ከአካዳሚክና ከክሊኒካል ሥራዎቻቸው ባሻገር፣ ፕሮፌሰር በረከት ለማህበረሰብ አገልግሎትና ለወጣት ባለሙያዎች ማብቃት ልዩ ቁርጠኝነት አላቸው። በተጨማሪም የሕፃናት ሕክምና ክፍል ውስጥ ተጋላጭ ሕፃናትንና ቤተሰቦቻቸውን የሚደግፍ የበጎ አድራጎት መስርተዋል፡፡ በተለያዩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ቦርድ አባል ሆና እያገለገሉ የሚገኙ ሲሆን ፣ በሕክምና በማህበረሰብ ጤና አገልግሎት ሥራዎችም በንቃት ይሳተፋሉ፡፡ እንዲሁም በሕክምና ዘርፍ የሴቶችን አመራር በመደገፍ ይታወቃሉ፡፡
የኢትዮጵያ የሕፃናት ሕክምና ማህበር ንቁ አባልና የቀድሞ የአስፈጻሚ ኮሚቴ አባል በመሆን ለሙያዊ እድገት አስተዋፅኦ እያበረከቱ ይገኛሉ፡፡
ፐሮፌሰር በረከት ፋንታሁን እንደ ሐኪም፣ መምህር ፣ ተመራማሪ፣ አማካሪ እና ሰብዓዊ አገልጋይ ያላቸው ሁለንተናዊ አስተዋፅኦ ወደ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ከፍ እንዲሉ የሚያስችላቸው በቂ መሠረት ነው፡፡ ይህም ለላቀ ሙያዊ ብቃት እና ለሕዝብ አገልግሎት የተሰጠ ረጅም ዘመናዊ አስተዋፅአቸውን ያንፀባርቃል።
The Managing Board of Saint Paul’s Hospital Millennium Medical College (SPHMMC), at its regular meeting held today, June 16, 2026, approved the promotion of Dr. Bereket Fantahun Yismaw to the rank of Full Professor.
After carefully reviewing her academic, clinical, research, and service achievements, the Board endorsed her promotion in recognition of her outstanding contributions to medical education, patient care, research, and institutional leadership.
With this promotion, Dr. Bereket becomes the first woman in the history of SPHMMC to attain the rank of Full Professor.
Professor Bereket Fantahun Yismaw is a distinguished pediatric endocrinologist, academician, and healthcare leader whose career exemplifies a deep commitment to advancing child health, medical education, and health system strengthening in Ethiopia. Born in Addis Ababa, she currently serves as a Consultant pediatrician at Saint Paul’s Millennium Medical College (SPHMMC), where she has earned recognition for excellence in clinical care, academic leadership, and transformative service.
Her academic journey spans leading institutions, including Gondar College of Medical Sciences and Addis Ababa University, with subspecialty training in pediatric endocrinology from Gertrude’s Children’s Hospital in Kenya. As a Fellow of the International Society for Quality in Health Care (ISQUA), she actively promotes quality improvement and innovation in healthcare delivery.
At SPHMMC, Professor Bereket has held key leadership roles, including Outpatient Department Director and Department Chair, where she has led major institutional advancements such as the implementation of electronic medical records and the expansion of childhood diabetes programs nationwide. Her influence extends beyond the institution, contributing to national health policy, clinical standards, and quality improvement initiatives across Ethiopia.
A prolific researcher, Professor Bereket has published extensively in national and international journals, with a focus on pediatric endocrinology and childhood diabetes. Her work has significantly contributed to improving clinical practice and public health outcomes. She has received multiple prestigious awards recognizing her as a leading female clinical researcher and a role model in Ethiopian medicine.