ሰላም ካቶሊክ ቴሌቪዥን - PAX Catholic TV
Открыть в Telegram
ሰላም ካቶሊክ ቲቪ Pax Catholic TV መረጃዎችን በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉን ✅ YT – https://youtube.com/pax_ctv ✅ Fb – https://facebook.com/ethiocatholic.addis ✅ X – https://x.com/CatholicTVEthi2 ✅ Ig– https://instagram.com/pax_ctv Contact - 0978 15 8461
Больше2 254
Подписчики
Нет данных24 часа
+27 дней
+830 день
Архив постов
+9
ዓመታዊው የቅዱስ ዮሴፍ ክብረ በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ተከበረ።
በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በአዲስ አበባ አገረስብከት በቅዱስ ዮሴፍ ቁምሥና ዓመታዊው የቅዱስ ዮሴፍ ክብረ በዓል ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ተከበረ።
+9
በቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፊ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ ወደ ኢትዮጵያ ገቡ።
ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም. በቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል (ዳይካስትሪ) ኃላፊ የሆኑት ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ፣ ክቡር አባ ድሚትሮ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ዋና ጸሃፊ፣ ክቡር አባ ጃሮዝላቭ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ተወካይ ወደ ኢትዮጵያ ጉብኝት ለማድረግ ገብተዋል።
ብፁዕነታቸው ወደኢትዮጵያ ሲገቡ በአዲስ አበባ አለም አቀፍ ኤርፖርት እና በቫቲካን ኤምባሲ በብፁዓን ጳጳሳት፣ ካህናት፣ ገዳማውያን እና የምዕመናን ተወካዮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በመቀጠልም በልደተ ማርያም ካቶሊክ ካቴድራል በብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ ሊቀጳጳሳት ዘካቶሊካውያን እና በአዲስ አበባ ሀገረስብከት ካህናት አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን የጉብኝታቸውን ማስጀመሪያ የጸሎት መርሃግብር ተካሂዷል።
ጉብኝታቸውን በአዲስ አበባ ሀገረስብከት የሴቶች እድገት የሙያ ማሰልጠኛ እና በቅዱስ ዮሃንስ ጳውሎስ ዳግማዊ የሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ የጀመሩ ሲሆን ተማሪዎችንም በስልጠና ላይ ሰላምታቸውን አቅርበዋል።
ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ በኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በተቋሙ በመገኘትም ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞችን አግኝተዋል። ብፁዕነታቸው በጠቅላይ ጽ/ቤቱ ያለውን የሥራ ሂደት እና ዘርፈ ብዙ የአገልግሎት ዘርፎች ገለጻ ተደርጎላቸው አጠር ያለ ጉብኝት አድርገዋል።
ሲ/ር በርናዴት ወልደማርያም በተወለዱ በ92 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፤
ነፍሳቸው በክርስቶስ ሰላም ትረፍ።
✨ የሳምንታዊ የቀጥታ የቅዱስ ቁርባን ስግደት ፕሮግራማችን 🙏
ኑ በፀሎት፣ በአምልኮ እና በበረከት ጊዜ ከእኛ ጋር ይሁኑ!
🔴 LIVE እዚህ ይቀላቀሉ👇
https://www.youtube.com/live/o-qwJba-HEw?si=GHvqZ9mW8m_WPodb
💫 ለሌሎችም ያጋሩ!
የወንጌልን አገልግሎት ስላገዛችሁ እግዚአብሔር ይስጥልን።
አሁንም የበረከቱ ተካፋይ ለመሆን ለምትፈጉ
ECC - ACS Social Communication
ንግድ ባንክ፡ 1000395912589
ንብ ባንክ፡ 700001695912589
ቴሌ ብር፡ 0995599036
+9
በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በአዲስ አበባ አገረስብከት የክርስቲያኖች ረዳት ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
