ru
Feedback
ኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር(አቡ ዓማር)

ኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር(አቡ ዓማር)

Открыть в Telegram

የአላህ  መልዕክተኛ (ﷺ)  እንዲህ  ብለዋል፦ (ከሰዎች መካከል የመልካም በር ከፋች የሆኑና የመጥፎ በር ዘጊዎች የሆኑ አሉ ፤ እንዲሁም ከሰዎች መካከል የሸር  በር ከፋች የሆኑና የመልካም በር ዘጊ የሆኑ አሉ። አላህ የመልካም በር መክፈቻ ቁልፍ በእጁ ላደረገለት ‘ጡባ’ አለለት ፤  አላህ  የመጥፎ  በር መክፈቻ  ቁልፍ  በእጁ  ላደረገለት  ‘ወይል’ አለለት።) [ኢብኑ ማጃህ (237) ዘግበውታል። 

Больше
7 704
Подписчики
-124 часа
-157 дней
-3830 день
Архив постов
እምነትህን ስትቀይር ዜግነትህና ታሪክህ ይሻራልን? ================ 🌿የአምስቱ ጓደኛሞች ውይይት (የኢትዮጵያዊነት ማሳያ) በአንድ ትምህርት ቤት አብረው ተምረው ካደጉ አምስት የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ጓደኛሞች መካከል አራቱ በጊዜ ሂደት እምነታቸውን ይቀይራሉ። አንደኛው ሙስሊም፣ ሁለተኛው ካቶሊክ፣ ሦስተኛው ፕሮቴስታንት፣ አራተኛው ደግሞ የይሖዋ ምስክር እምነት ተከታይ ሲሆኑ፤ አምስተኛው ግን በኦርቶዶክስ እምነቱ ይጸናል። ከዓመታት በኋላ በአካል ተገናኝተው ስለ አገርና ስለ እኩልነት ሲወያዩ፣ እምነቱን ያልቀየረው ጓደኛቸው በንዴትና በቁጣ ተሞልቶ እንዲህ ይላቸዋል፦ "እናንተ መጤዎች! ከእኛ ከነባሩ ህዝብ ጋር አገርን በእኩልነት እንጋራ ለማለት ደረሳችሁ? ኦርቶዶክስ አገር ያቆመች፣ ፊደል ቀርጻ ያስተማረች፣ እናንተ ተሰዳችሁ ስትመጡ የተቀበለች ነች።" በዚህ ጊዜ ጓደኛሞቹ የሰጡት ምላሽ የፖለቲካዊ ማንነትን ስህተት ፍንትው አድርጎ ያሳያል፦   ✅ የካቶሊክ እምነት ተከታዩ ምላሽ፦ "እምነትን መቀየር መጤ የሚያደርግ ከሆነ፣ ኦርቶዶክስን የኢትዮጵያዊነት ብቸኛ መለኪያ እያደረግከው ነው። ኦርቶዶክስ አገር ስትገነባ እኛም በወቅቱ ኦርቶዶክስ ስለነበርን ያንን ታሪክ አብረን የሰራነው እኛ ነን።" ✅ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዩ ምላሽ፦ "ከዓመታት በፊት እምነቴን ከመቀየሬ በፊት ኦርቶዶክስ ለሀገር ባበረከተችው አስተዋፅኦ ሁሉ ውስጥ እኔና አባቶቼ አለንበት። እምነቴን ስለቀየርኩ ብቻ የትናንት የታሪክ ድርሻዬና አሻራዬ ሊሻር አይችልም!" ✅ የሙስሊም እምነት ተከታዩ ምላሽ፦ "አማኝን መጤ አድርጎ የሚፈርጀው ይህ አስተሳሰብ እያለ ያለው፦ 'አማራ ክርስቲያን ከሆነ ነባር ነው፣ አማራ ሙስሊም ከሆነ ግን መጤ ነው፤ ትግራዋይ ክርስቲያን ከሆነ ነባር ነው፣ ትግራዋይ ሙስሊም ከሆነ ግን መጤ ነው፤ ኦሮሞ ክርስቲያን ከሆነ ነባር ነው፣ ኦሮሞ ሙስሊም ከሆነ ግን መጤ ነው' እያለ መሆኑን አስተውላችኋልን? ይህ ከድንቁርና በቀር ምን ይባላል?" ✅ የይሖዋ ምስክር እምነት ተከታዩ ምላሽ፦ "ሃይማኖትን መቀየር የውስጥ ማንነትን መገለጫ የሆነውን 'ዲ ኤን ኤ' (DNA)  ወይም የዘር ግንዱን አይቀይረውም። የተቀየረው እምነት እንጂ የአገሬው ተወላጅነቱ አይደለም።" ✒️ ከዚህ ውይይት በስተጀርባ ያሉትን መሠረታዊ የታሪክና የህግ እውነታዎች በአራት ዋና ዋና ነጥቦች እንገምግማቸው፦ ሀ) ዜግነት በሕግና በደም፣ ሃይማኖት በነፃነት! ዜግነትና ሀገራዊ መብት የሚገኘው በደም (ከወላጆች) እና በሕግ እንጂ በሃይማኖት ምዝገባ አይደለም። አንድ ሰው እምነቱን ስለቀየረ ብቻ፣ የቀደሙ አባቶቹ ከጥንት ጀምሮ የገነቡትን አገር ባለቤትነት አያጣም። ሃይማኖት የምርጫ ጉዳይ እንጂ የሀገር ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ አይደለም። ለ) ታሪክን በሃይማኖት ብቻ የመመዘን ስህተት የኢትዮጵያ ታሪክ የሃይማኖት ታሪክ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ፣ የግብርና፣ የቋንቋ፣ የኪነ-ህንጻ፣ የሉዓላዊነት፣ የንግድና የባህል ታሪክ ድምር ነው። በእነዚህ ሁሉ ታሪኮች ውስጥ የተሳተፉት ደግሞ ከሁሉም እምነት የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን እንጂ የአንድ ሃይማኖት ተከታዮች ብቻ አይደሉም። ሐ) 99% የ"መጤነት" እውነታ! ከውጭ አገር የመነጨን እምነት መከተል ሰውን "መጤ" የሚያደርግ ከሆነ፣ 99% የሚሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጤ ነው! ምክንያቱም ኦርቶዶክስ፣ እስልምና፣ ፕሮቴስታንት፣ ካቶሊክ፣ ሁሉም መነሻቸው ከመካከለኛው ምስራቅና ከውጭ አገራት የመጡ እምነቶች ናቸው። መ) "እንግዶቹ እንኳን ደህና መጡ!" በእርግጥም መጤ የምንላቸው ከሌላ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ መጥተው እምነቱን ያስተማሩንን የውጭ አገር ሰባኪያን ነው። ለምሳሌ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ትልቅ ስፍራ የተሰጣቸውና ታቦት የተሰየመላቸው ታላላቅ አባቶች ሁሉም ከውጭ የመጡ ስደተኞች ነበሩ [6]፦ 1️⃣  አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል)፦ የመጡት ከሮም [6] 2️⃣ አቡነ ጴንጤሌዎን፦ የመጡት ከሮም [6] 3️⃣  አቡነ ገሪማ (ይስሐቅ)፦ የመጡት ከሮም [6] 4️⃣  አቡነ የማታ፦ የመጡት ከሶርያ [6] 5️⃣  አቡነ አፍጼ፦ የመጡት ከቱርክ (አናቶሊያ) [6] 6️⃣  አባ ሰላማ (ከሳቴ ብርሃን)፦ የመጡት ከሶርያ 7️⃣ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፦ የመጡት ከግብፅ እኛ ኢትዮጵያውያን እነዚህን የእምነት መምህራን (የክርስትናም ሆነ የእስልምና) በስደትና በእንግድነት ሲመጡ መቀበላችን እንግዳ ተቀባይና ደግ ህዝቦች መሆናችንን ያሳያል። መጤዎቹ መምህራን እንኳንም መጡ፤ እኛም እነርሱን በእንግድነት በመቀበላችን እንኮራለን! ⬅️ ኢትዮጵያዊነት የጋራ ቤታችን እንጂ የአንድ ወገን ወይም የአንድ እምነት ውርስ አይደለም። እምነትን መቀየር ታሪክን፣ አሻራን እና ዜግነትን አያሳጣም። ስለዚህ፣ ይህንን አገርን የሚከፋፍል የ"ነባርና መጤ" የድንቁርና ትረካ ወደ ጎን ትተን፣ አገራችንን በሕግ የበላይነት፣ በዜጎች እኩልነትና በጋራ እሴቶቻችን ላይ በፅኑ መሰረት እንገንባት! ✍አሕመዲን ጀበል https://t.me/ibnukedir

🌿🌿🌿🍃ጥቆማ🍃🌿🌿🌿 ማነው መጤው? ሙስሊሙ መብቱን በጠየቀ፣ ጭቆናን በተቃወመ፣ እምነቱን ባስተማረ ቁጥር "እናንተ ሙስሊሞች ወደ ኢትዮጵያ ስትገቡ አክብረን በተቀበልን እንዴት ውለታችን ይረሳል?" እያሉ በቅጥፈት ለሚመፃደቁ አካላት "እንዴ! እኛ እኮ ኢትዮጵያውያን እንጂ መጤዎች አይደለንም" እያሉ በከንቱ መድከም አያስፈልግም ብዬ በፅኑ አምናለሁ። ሰዎቹ እንዲህ አይነት አመክንዮ የሚገባቸው አይደሉም። ድንጋይ ላይ ውሃ ማፍሰስ ነው። መፍትሔው ማጥቃት እንጂ መከላከል አይመስለኝም። በራሱ ቋንቋ አናግረው። በዚህ ድንቁ ^ ርና ላይ በሰፊው የሚታወቁት በዋናነት የአንድ እምነት ተከታዮች ናቸው። እነሱ ናቸው "የእስላም አገሩ መካ፣ የአሞራ አገሩ ዋርካ" የሚል ምሳሌያዊ አነጋገር ፈጥረው ድንቁርናቸውን ከትውልድ ትውልድ የሚያሻግሩት። እንዴት አድርገው እንደሚጠርቧቸው እንጃ በዚህ ዘመን እንኳ አልተቀየሩም። የለውጥ ተስፋ የሚታይባቸውም አይደሉም። አስቂኙ ነገር ደግሞ ራሳቸውን የአይ^ሁድ ዘር አድርገው መኮፈሳቸው ነው። ሃገሪቱን ለሰባት መቶ ዓመታት በላይ የቦጠቦጠው ራሱን "ሰለሞናዊ መንግስት" ብሎ የሚጠራው መዥገር ስርአትኮ ባህር ተሻግሮ የሰሎሞን ዘር ነኝ የሚል ነው። መጤ ነኝ ማለት አይደል ይሄ? አፄ ምኒልክ "ዳግማዊ" ምኒልክ የተባለው ጥንት ከንጉስ ሰለሞን የተገኘ "ቀዳማዊ" ምኒልክ ነበር ብለው ስለሚያምኑ ነው። "የናዝሬቱ እየሱስ፣ የዮርዳኖስ ወንዝ፣ ቃና ዘገሊላ፣ ቤተልሄም፣ እየሩሳሌም፣ ... " እያለ እምነቱን ከባህር ማዶ ጋር የሚያይዝ አካል እንዴት ሙስሊሞችን መጤ ሊያደርግ ይዳፈራል?! የሙስሊሙን ኢትዮጵያዊነት መቀበል የከበዳቸው ጭንቅላቶች "ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት" የሚል ያረጀ ያፈጀ ተረት ዛሬም ይተርታሉ። ለመሆኑ እነሱ ዘንድ ኢትዮጵያ ማለት የቷ ናት? ለመሆኑ ኢትዮጵያ ሲሉ አፋርን፣ ሶማሊን፣ ሀረርን፣ ስልጤን፣ ከፊል ጉራጌን፣ ሰፊውን ኦሮሚያን፣ ሀላባን፣ አብዛኛው ወሎን፣ አብዛኛውን በኒሻንጉልን፣ ድሬዳዋን፣ አርጎባን፣ ... ይጨምራል ወይ? እስኪ እነዚህን አካባቢዎች ቆርጠው ያውጡና የደሴቷን ካርታ ይመልከቱ። ካርታው ላይ የሚታየው ቀዩ ክፍል ነው የሚቀራቸው። ከዚያ የቀራችሁን የክርስቲያን ደሴት ተመልከቷት! የምትዘምሩላት ኢትዮጵያ ይቺ ናት? ለማንኛውም "በቀዳማዊ ምኒልክ በኩል የሰለሞን ዘር ነን"፣ "ነገደ ይሁዳ ነን"፣ "የይሁዳ አንበሳ ነን" የሚለውን የአባቶቻችሁን ተረት የምታምኑበት ከሆነ መጤዎች እንደሆናችሁ በራሳችሁ ላይ መስክራችኋል። እኛ ሙስሊሞች ዐረቦች ነን አላልንም። ኢትዮጵያውያን ነን። እናንተ "የሁ^ዶች ነን" ካላችሁ እኛ ነን የተቀበልናችሁ። "አይ" ካላችሁ "አይ^ሁድ ነን" የሚለውን የአባቶቻችሁን ተረት ውሸት እንደሆነ አስረግጣችሁ ወርውራችሁ ጣሉ። ከዚያ በኋላ ራሳችሁን የኢትዮጵያዊነት አከፋፋይና ድርጎ ሰፋሪ አድርጋችሁ ማየታችሁን አቁሙ። የነውረኝነታችሁ ዳፋ ለደካሞች ይተርፋልና ጥፍራችሁን ሰብስቡ። በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት የከረፋ ሃሳብ ስታንፀባርቁ ታንኩም ባንኩም በእጃችሁ በነበረበት የቀደመው ዘመን ያደረሳችሁትን ማሰብም ይሰቀጥጣል። ✍IbnuMunewor https://t.me/ibnukedir

🌿አዲስ ደርስ 📚ኪፋየቱል ሙተዓቢድ..... 🎙ክፍል፡20 💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🕌 በኢማሙ ነወዊይ የሂፍዝ ማዕከል የተሰጠ። https://t.me/ibnukedir

🌿አዲስ ደርስ 📚ረውደቱል አንዋር 🎙ቁጥር፡77 💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🕌 ቃሊቲ ነስር መስጂድ የተደረገ @ibnukedir

📚የቁርአን ተፍሲር ቁ፡254 📖ሱረቱ-ሩም          🎙ክፍል፡1 💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🕌  አቃቂ ቢላል መስጂድ የተሰጠ @ibnukedir

📤📤📤📤📤📤📤 🌿የጁምዓ ኹጥባ ቁ፡116 🔖በረካን መፈለግ⁉️     💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🔻ሊደመጥ የሚገባ ወቅታዊ ኹጥባ! 💫የአጅሩ ተካፋይ እንድንሆን ሼር! 🕌  ቃሊቲ ነስር መስጂድ የተደረገ @ibnukedir

🌿🌿🌿🍃ጥቆማ🍃🌿🌿🌿 የሺርክና የቢድዐ ጉዳዮች በብዙ አስተማሪዎች የማይደፈሩ ርእሶች ናቸው። ከዚህም የባሰው ግን የዘረኝነት ርእስ ነው። እንደ ሃገር በአራቱም ማእዘናት በዘረኝነት ብንታመስም ስለ ጉዳዩ ደፍሮ የሚያስተምረው ግን ከጥቂትም ያነሰ ነው። ዘረኝነት የእልፎችን ህይወት ቀጥፏል። ሌሎች እልፎችን አፈናቅሏል። በውል የማይታወቁ ንብረቶችን አውድሟል። እምነታዊ ትስስራችንን በእጅጉ ሸርሽሯል። በዘረኝነት በዚህ ልክ ብንግጎዳም ሸይኹም ምሁሩም ፀጥ ብሏል። ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ሁለት ነው። 1ኛ፦ እነሱ ራሳቸው የችግሩ ሰለባዎች መሆናቸው ነው። እንኳን ስለ ጉዳዩ ሊያነሱ በሌሎች ጠንከር ያለ ትምህርት ቢስሰጥ የማይጥማቸው ናቸው። ይሄ በተግባር የታየ አሳፋሪም፣ አሳዛኝም ሐቅ ነው። 2ኛው፦ ምክንያት ደግሞ መንጋውን መፍራት ነው። በዘረኝነት ልክፍት የተበከለው መንጋ ርህራሄ የለውም። ስም ከማጉደፍ፣ በስድብ ከማጥረግረግ በላይ ህይወት ሊነጥቅ ይችላል። መስማት የሚሻው የሚያስፈልገውን ሳይሆን የሚፈልገውን ነው። የፖለቲካውም ይሁን የእምነት ቅኝቱ ይሄው ነው። ከዚህ ለወጣበት ምላሱም እጁም ጨካኝ ነው። በዚህ ስጋት የተነሳ መሬት ላይ በሚያዩት መሪር እውነታ ልባቸው ቢደማም ለችግሩ የሚመጥን ጥንካሬ ያለው ትምህርት ለመስጠት የማይደፍሩት ብዙ ናቸው። ግን እስከ መቼ በዚህ ሁኔታ መዝለቅ ይቻላል? ችግሩን ከመሰረቱ ካልተጋፈጥነው መጨረሻው ለሁሉም በጣም አስፈሪ ነው። አላህ ልብ ይስጠን። ✍IbnuMunewor https://t.me/ibnukedir

📤📤📤📤📤📤📤 🌿የጁምዓ ኹጥባ ቁ፡115 🔖የጀነት ፀጋና ገፅታ ⁉️     💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🔻ሊደመጥ የሚገባ ወቅታዊ ኹጥባ! 💫የአጅሩ ተካፋይ እንድንሆን ሼር! 🕌  ቃሊቲ ነስር መስጂድ የተደረገ @ibnukedir

🌿አዲስ ደርስ 📚ኪፋየቱል ሙተዓቢድ..... 🎙ክፍል፡19 💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🕌 በኢማሙ ነወዊይ የሂፍዝ ማዕከል የተሰጠ። https://t.me/ibnukedir

🌿አዲስ ደርስ 📚ረውደቱል አንዋር 🎙ቁጥር፡76 💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🕌 ቃሊቲ ነስር መስጂድ የተደረገ @ibnukedir

📚የቁርአን ተፍሲር ቁ፡253 📖ሱረቱ-ሉቅማን          🎙ክፍል፡3 💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🕌  አቃቂ ቢላል መስጂድ የተሰጠ @ibnukedir

🌿🌿🌿🍃ጥቆማ 🍃🌿🌿🌿 ልቤ ሆይ!! ልቤ ሆይ ልብ አድርግ - ለመልካሙ ትጋ - ከክፋት ተገታ ምላሴ ሆይ እረፍ - ጦስህ ያስፈራኛል - በጧትም በማታ እጄ ሆይ ተመከር - "እጄን በ’ጄ" እንዳልል - በሚያስጨንቅ ቦታ እግሬ እግር አታብዛ - ታዋርደኛለህ - በጭንቁ ቀን ለታ አዋጅ ሰምቻለሁ - እጅግ የሚያስፈራ - ከሰማዩ ጌታ። (يَوْمَ تَشْهَدُ عَلَيْهِمْ أَلْسِنَتُهُمْ وَأَيْدِيهِمْ وَأَرْجُلُهُمْ بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ) "በእነሱ ላይ ምላሶቻቸው፣ እጆቻቸውና እግሮቻቸውም ይሰሩት በነበሩት ነገር በሚመሰክሩባቸው ቀን (ከባድ ቅጣት አላቸው)፡፡"  [አንኑር: 24] ✍IbnuMunewor https://t.me/ibnukedir

📤📤📤📤📤📤📤 🌿የጁምዓ ኹጥባ ቁ፡113 🔖ለመልካም ነገር ቁልፍ ሁን⁉️     💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🔻ሊደመጥ የሚገባ ወቅታዊ ኹጥባ! 💫የአጅሩ ተካፋይ እንድንሆን ሼር! 🕌  ቃሊቲ ነስር መስጂድ የተደረገ @ibnukedir

🌿አዲስ ደርስ 📚ኪፋየቱል ሙተዓቢድ..... 🎙ክፍል፡18 💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🕌 በኢማሙ ነወዊይ የሂፍዝ ማዕከል የተሰጠ። https://t.me/ibnukedir

🌿አዲስ ደርስ 📚አል-መባዲኡ ናፊዓ.... 🎙ክፍል፡18 💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🔻ለጀማሪ ቀላልና ጣፋጭ ኪታብ ! 🌿የመጨረሻ ክፍል 🕌 በኢማሙ ነወዊይ የሂፍዝ ማዕከል የተሰጠ። https://t.me/ibnukedir

🌿አዲስ ደርስ 📚ረውደቱል አንዋር 🎙ቁጥር፡75 💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🕌 ቃሊቲ ነስር መስጂድ የተደረገ @ibnukedir

📚የቁርአን ተፍሲር ቁ፡252 📖ሱረቱ-ሉቅማን          🎙ክፍል፡2 💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🕌  አቃቂ ቢላል መስጂድ የተሰጠ @ibnukedir

https://vt.tiktok.com/ZSCpuMHco/ 🔖መታለል ቁ፡2 💺 ኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🔺በቲክቶክ ይከታተሉን፤ ለሌሎችም ያጋሩ። 📥📥📥📥📥📥📥📥📥📥

📤📤📤📤📤📤📤 🌿የጁምዓ ኹጥባ ቁ፡113 🔖የእረፍት ግዜን መጠቀም⁉️     💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🔻ሊደመጥ የሚገባ ወቅታዊ ኹጥባ! 💫የአጅሩ ተካፋይ እንድንሆን ሼር! 🕌  ቃሊቲ ነስር መስጂድ የተደረገ @ibnukedir

🌿አዲስ ደርስ 📚ኪፋየቱል ሙተዓቢድ..... 🎙ክፍል፡17 💺በኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር 🕌 በኢማሙ ነወዊይ የሂፍዝ ማዕከል የተሰጠ። https://t.me/ibnukedir