General Wingate Polytechnic college-Official channel
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን። የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام General Wingate Polytechnic college-Official channel
کانال General Wingate Polytechnic college-Official channel (@wingetpolytechniccollege) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 12 257 مشترک است و جایگاه 16 405 را در دسته آموزش و رتبه 2 746 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 12 257 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 03 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -72 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -7 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 33.20% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.91% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 4 071 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 951 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 14 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን።
የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 04 ژوئیه | 0 | |||
| 03 ژوئیه | 0 | |||
| 02 ژوئیه | 0 | |||
| 01 ژوئیه | +1 |
| 2 | አስደሳች እድል ለ Cisco (ሲስኮ)ኔትዎርኪንግ/ICT ስልጠና ፈላጊዎች፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለውን(የአሜሪካ Cisco ት/ቤት )የሲስኮ ኔትወርኪንግ ስልጠና ለመስጠት ሙሉ ፍቃድ ያለው እናም የሲስኮ ኔትዎርኪንግ ማሰልጠኛ ማዕከል የሆነው አንጋፋው ኮሌጃችን ጄነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ በዘርፉ ብቃታቸውን ባረጋገጡ እና (Certified)ሰርቲፋይድ በሆኑ አሰልጣኞች አማካኝነት በገበያው እጅግ ተፈላጊ የሆኑ ስልጠናዎችን ለመስጠት ምዝገባ መጀመሩን በደስታ ይገልፃል።
የሚሰጡ ኮርሶች፡-
IT Essentials
CCNA
ልዩ ዕድሎች!
ለማንኛውም ኮርስ ሲመዘገቡ የሚከተሉትን ኮርሶች በነፃ ያገኛሉ::
F Introduction to Cybersecurity
F Introduction to Modern AI
F Python Essentials
F Digital Awareness
ማሳሰቢያ፡-
o ለሁሉም ኮርሶች ሰርተፊኬት ይሰጣል።
መመዝገቢያ ቦታ፡-
o አስተዳደር ህንፃ፣ 2ኛ ፎቅ፣ ቢሮ ቁጥር 208
ለበለጠ መረጃ፡- 0911717635 | 0911196315 | 0944767038 ይደውሉልን። | 2 444 |
| 3 | ሰኞ:- ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም
የCOC ምዘና ውጤትን ለማሻሻል የዊንጌት ክላስተር ኮሌጆችና የትምህርትና ስልጠና ቁጥጥር ባለስልጣኑ በቅንጅት ሊሰሩ ተስማሙ፡፡
የጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ጨምሮ በዊንጌት ክላስተር ስር የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እና የትምህርትና ስልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የብሔራዊ የሙያ ብቃት ምዘና (COC) ውጤትን ለማሻሻል የሚያስችል የጋራ የውይይት መድረክ አካሄዱ።
መድረኩ የ2017 ዓ.ም. የተመራቂ ሰልጣኞችን የብሔራዊ ምዘና አፈጻጸም ሪፖርት ለመገምገምና የ2018 ዓ.ም. የምዘና ሂደትን በተሻለ ውጤት ለማስፈጸም ያለመ ነው።
በዚሁ የውይይት መድረክ ላይ በዊንጌት ክላስተር ስር የሚገኙት የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ የደጃዝማች ገረሱ ዱኪ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እና የኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዋና ዲኖችና እና የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲኖች ተሳትፈዋል። በተጨማሪም ከአዲስ ከተማ፣ ከኮልፌ፣ ከአራዳ፣ ከጉለሌ እና ከልደታ ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ የትምህርትና ስልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የስራ ኃላፊዎች በጋራ መክረዋል።
በዕለቱ የውይይት ሰነዱን ያቀረቡት የሰልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ቢሮ የስልጠና ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አየለ ብርሃኑ ሲሆኑ በሰነዳቸውም የሰልጣኞችን የመብቃት ምጣኔ እና የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በዝርዝር አቅርበዋል።
ብሔራዊ ምዘና የሰልጣኞችን የሙያ ብቃት የሚያረጋግጥ ወሳኝ ሂደት መሆኑ በመድረኩ ላይ የተገለጸ ሲሆን በቀጣይ ሂደቱ የሚሳተፉ ሁሉም አካላት በቅንጅት፣ በኃላፊነትና በተጠያቂነት በመስራት የ2018 ዓ.ም. የምዘና ውጤትን ከፍ ማድረግ እንደሚገባቸው አቅጣጫ ተቀምጧል።
መድረኩ ሲጠናቀቅም ሁሉም ተሳታፊ አካላት በጋራ በመስራት ክፍተቶችን ለመሙላት የ2018 ዓ.ም | 3 562 |
| 4 | የጨረታ ማስታወቂያ
ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በግቢው ውስጥ የሚገኙና ያገለገሉ የግንባታ ቁሳቁሶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
የሚሸጡ ቁሳቁሶች ዝርዝር
1. ተነቃይ የጣራ ቆርቆሮ
2. ያገለገለ ቦሮንዳዮ ቆርቆሮ
3. ያገለገለ ሽክላ
4. ያገለገለ የብረት በር
5. ያገለገለ የእንጨት በር
ለጨረታ ተሳታፊዎች የሚሰጡ
መመሪያዎች
የቦታ ጉብኝት፦ ተጫራቾች ከመወዳደራቸው በፊት ቁሳቁሶቹ ያሉበትን ሁኔታ በአካል በመገኘት መመልከት ይጠበቅባቸዋል።
የጨረታ ሰነድ መውሰጃ፦ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከኮሌጁ የንብረት አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ከ12/10/2018 ዓ.ም እስከ 18/10/2018 ዓ.ም ድረስ መውሰድ ይችላሉ።
ጨረታው የሚከፈትበት ቀን፦ ጨረታው በዚሁ ዕለት ማለትም በ18/10/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በ4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
የጨረታ ማስከበሪያ፦ አሸናፊ የሆነ አካል በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ክፍያውን ፈጽሞ ንብረቱን ማንሳት አለበት።
እያንዳንዱ ተጫራች ለጨረታ ማስከበሪያ (CPO) 1,100 ብር (አንድ ሺህ አንድ መቶ ብር) በጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስም ማቅረብ ይኖርበታል።
ተጨማሪ መረጃ፦ ለጨረታው ተወዳዳሪ ያልሆኑ ወይም ያልተሟላ ሰነድ ያቀረቡ ተጫራቾች ከጨረታው ውጪ ይሆናሉ። ኮሌጁ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፦ ዊንጌት አደባባይ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን አጠገብ
ስልክ ቁጥር፦ 011 2 73 96 35
ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ | 5 305 |
| 5 | ማክሰኞ:- ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ‹‹ስማርት ሲቲ›› ማሰልጠኛ ሆኖ ተመረጠ!!
ኮሌጁ በአውሮፓ ህብረት የኢራስመስ (Erasmus+) የገንዘብ ድጋፍ የሚደገፍና ዘመናዊ የከተማ ልማትን (Smart City) የሚያግዝ ታላቅ ፕሮጀክት መተግበር መጀመሩን አስታወቀ።
ኮሌጁ 10 ከሚሆኑ ሀገራዊ ተቋማትና ዓለም አቀፍ አጋር አካላት ጋር በመቀናጀት ለዘመናዊ ከተማ ልማት የሚሆን የሰው ኃይል በብቃት ለማፍራት የሚያስችል ስምምነት አድርጓል።
ይህ ፕሮጀክት በጋራ ጥረት ላይ የተመሰረተ ሲሆን አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉን ዕድገትና ተግዳሮት የሚፈቱ ጥናትና ምርምር በመስራት፣ ፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ለዘርፉ አሰልጣኞች አሰልጣኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት፣ አምቦ ዩኒቨርሲቲ የገበያውን ፍላጎትና የአለም አቀፍ ደረጃን ያገናዘበ የካሪኩለም ቀረፃ ሃላፊነቱን በመወጣት፣ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የስልጠናው ጥራትና ውጤታማነት በሳይንሳዊ መንገድ መመራቱን በመቆጣጠር የሚሳተፉ ሲሆን ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቀረፀው ካሪኩለም መሰረት ስልጠናውን በተግባር በመስጠት የፕሮጀክቱ ዋና አካል ይሆኗል።
ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት በአጫጭር ስልጠናዎች የሚጀምር ቢሆንም በቀጣይ ወደ ደረጃ የስልጠና መርሃ-ግብር ለማሳደግ ስትራቴጂያዊ እቅድ ተይዟል።
ይህ እርምጃ አዲስ አበባ የጀመረችውን ‹‹ስማርት ሲቲ›› ጉዞ የሚያስቀጥል፣ በቴክኖሎጂ የዳበረ እና ለስራ ገበያው ዝግጁ የሆነ የሰው ኃይል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ድርሻ ይኖረዋል።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ይህንን ዓለም አቀፍ ዕድል ማግኘቱ ተቋሙ በዘርፉ ያለውን ተወዳዳሪነት የሚያሳይ ነው።
በተጨማሪም የአሰልጣኞች እውቀትና ክህሎት በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍ ለማድረግ የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት፣ ዘመናዊ የስልጠና መሳሪያዎችንና ቴክኖሎጂዎችን ግብዓት በማሟላት እና የሚሰጠው ስልጠና የተግባርና የምርምር ውጤት በመሆኑ ለሰልጣኞች በቀጥታ የገበያ ትስስር ለመፍጠር ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ ለኮሌጁ እንደ ትልቅ ዕድል ተቆጥሯል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት›› | 4 199 |
| 6 | بدون متن... | 4 615 |
| 7 | አርብ:- ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
53ኛው የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀን በልዩ ልዩ ሁነት ተከበረ!!
53ኛው የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ቀን ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከነገው ዛፍ ፕሮጀክትና ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በልዩ ልዩ መርሐግብሮች ተከብሯል።
በዛሬው ዕለት ከኮሌጁ ግቢ በመነሳት መዳረሻውን ጉለሌ እጽዋት ማዕከል ያደረገ የ5 ኪሎ ሜትር ማራኪ የእግር ጉዞ የተካሄደ ሲሆን ይህ ጉዞ የአካባቢ ጥበቃን መልዕክት በስፋት ከማስተላለፍ ባለፈ የተሳታፊዎችን የአካል ጤንነት ለመጠበቅ እና ለማነቃቃት ትልቅ ፋይዳ ነበረው።
ከእግር ጉዞው ጎን ለጎን የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራም የተከናወነ ሲሆን በመርሐግብሩ ላይ ስለ ጉዞው ዓላማና የቀጣይ ስራ እንቅስቃሴ በዝግጅቱ አስተባባሪዎችና በባለሙያዎች ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ በማብራሪያውም የዚህ እንቅስቃሴ ዋና ዓላማ "ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን የተተከሉትን በአግባቡ በመንከባከብ ዛፍ ሆነው ማየት፣ የአካባቢን የተፈጥሮ ሚዛን መጠበቅ እና ከዕፅዋት የሚገኙትን ልዩ ልዩ ገጸ-በረከቶች በአግባቡ መጠቀም ነው" ሲሉ አስገንዝበዋል።
በቀጣይም ኮሌጁ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ትብብር በማጠናከር ተመሳሳይ የአካባቢ ጥበቃ የእግር ጉዞዎች እንደሚኖሩ፣ የችግኝ ተከላ መርሐግብሮች በስፋት እንደሚካሄዱ እና በተለይም ችግኞችን ከተተከሉ በኋላ የቅርብ ክትትልና እንክብካቤ የማድረጉ ስራ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል አቅጣጫ ተቀምጧል።
በተመሳሳይ ዜና በዓሉን ምክኒያት በማድረግ በትናንትናው ዕለት የአካባቢ ጥበቃን ፅንሰ ሀሳብ እና ወቅታዊ ጉዳዮችን መነሻ ያደረገ የፓናል ውይይት ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በኮሌጁ ተካሂዷል።
«የነገው ዛፍ» በአካባቢ ጥበቃ፣ በተፈጥሮ ሚዛን መጠበቅ እና በአረንጓዴ ልማት ላይ ትኩረት አድርጎ የሚንቀሳቀስ ተራማጅ የአካባቢ ጥበቃ ፕሮጀክት ሲሆን «ዛሬ የምንተክለው ችግኝ፣ የነገው ትልቅ ዛፍና የትውልድ ዋስትና ነው» የሚለውን መርህ በመያዝ፣ ትኩረቱን በችግኝ ተከላ ላይ ብቻ ሳይሆን በድህረ-ተከላ እንክብካቤ ላይ ያደረገ ፕሮጀክት ነው።
ድርጅቱ የያዘውን በጎ ራዕይ ከጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር ተቀናጅቶ በመስራት ዓላማውን ለማሳካት ስምምነት ተፈራርሞ እየሰራ ይገኛል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት›› | 6 951 |
| 8 | بدون متن... | 5 144 |
| 9 | بدون متن... | 5 235 |
| 10 | 🚨 አዲስ ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ! 🚨
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመምህራንና ሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበር ብቁ ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
📌 የስራ መደቡ መጠሪያ:- የሂሳብ ባለሙያ
👥 ብዛት:- 1 (አንድ)
🎓 የትምህርት ደረጃ:- በአካውንቲንግ ደረጃ 4 እና ከዚያ በላይ
💼 የስራ ልምድ:- እስከ 2 ዓመት የስራ ልምድ
💻 ልዩ ክህሎት:- መሰረታዊ የኮምፒውተር እውቀት፣ በኤክሴል (Excel) እና ፒችትሪ (Peachtree) የተግባር ልምድ ያለው/ያላት
💰 ደመወዝ:- በስምምነት
📅 የማመልከቻ ጊዜ:- ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ማመልከት ይችላሉ።
📍 የመመዝገቢያ ቦታ:- ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ ውስጥበሚገኘው የህብረት ሥራ ማህበሩ ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ መመዝገብ ይችላሉ።
📞 ለበለጠ መረጃ: 0946 61 24 47 ወይም 0965 65 69 81 | 6 415 |
| 11 | 📣 የወደፊት ስኬትዎን በክህሎት ያረጋግጡ!
አዋጭና በገበያው ላይ እጅግ ተፈላጊ የሆኑ የአጫጭር ጊዜ ስልጠናዎች ጥሪ
የወቅቱን የገበያ ፍላጎት ያገናዘበ፣ በተግባር የተደገፈ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ስራ የሚያስገባ አስተማማኝ ክህሎት ማግኘት ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ እኛ ጋር መፍትሄው አለ!
ኮሌጃችን በኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዘርፍ (ራስዎን እና ተቋምዎን የሚቀይሩባቸውን እጅግ አዋጭ የስልጠና መስኮች ይዞላችሁ ቀርቧል።
1. ለዘመናዊ የመሰረተ-ልማት እና የሀይል አማራጮች
የሕንፃ ላይ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታና ሶላር ሲስተም (Building Electrical Installation & Solar System)
2. ለኢንደስትሪና ለከፍተኛ ማሽነሪዎች
የኢንደስትሪያል ሞተር ኮንትሮል እና ጀነሬተር ዝርጋታና ጥገና
ኢንደስትሪያል አውቶሜሽን (Industrial Automation) - ኒውማቲክስ ሲስተምን ጨምሮ
የሞተር ዋይንዲንግ (Motor Winding)
3. ለቴክኖሎጂ፣ ለደህንነት እና ለቤት ውስጥ እቃዎች
CCTV ካሜራ ዝርጋታና ኮንፊግሬሽን (CCTV Installation & Configuration
ሳተላይት ዲሽ ዝርጋታ፣ LED TV እና ሬሲቨር ጥገና
የቤት ውስጥ እቃዎች ጥገና (Home Appliances Maintenance)
📌 እኛን ሲመርጡ?
በተግባር (Practical) ላይ ያተኮረ ስልጠና
ምቹ የስልጠና ክፍለ-ጊዜዎች
ብቁ እና ልምድ ያላቸው አሰልጣኞች
ስልጠናውን በጥራት ላጠናቀቁ የምስክር ወረቀት
🎯 ማሳሰቢያ: የስልጠናው ቦታ ውስን ስለሆነ ፈጥነው በመመዝገብ የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ!
📞 ለበለጠ መረጃና ምዝገባ
አድራሻ: - ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ስልክ ቁጥር: 0913143307 ወይም 0911105037
"ክህሎት ያነገበ ትውልድ — ለቀጣይ ብሩህ ተስፋ!" | 7 045 |
| 12 | بدون متن... | 5 960 |
| 13 | بدون متن... | 6 391 |
| 14 | بدون متن... | 4 200 |
| 15 | بدون متن... | 0 |
| 16 | بدون متن... | 0 |
| 17 | بدون متن... | 0 |
| 18 | بدون متن... | 0 |
| 19 | የ16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አውደ-ርዕይ በደመቀ ሁኔታ ተጠናቀቀ።
🇪🇹አዲስ አበባ | ሚያዝያ 28/2018 ዓ.ም🇪🇹
ላለፉት ቀናት በአራዳ ፓርክ "የቴክኖሎጂ ልህቀት ለአገር ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየው 16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አውደ-ርዕይና የፈጠራ ስራዎች ውድድር ዛሬ በደመቀ ስነ-ስርዓት ተጠናቋል።
በማጠቃለያው ፕሮግራም ላይ ንግግር ያደረጉት አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ፤ የቴክኖሎጂ ታሪክ የኢኮኖሚ ልማት ታሪክ መሆኑን በጥልቀት በመተንተን፣ ባለፉት ቀናት የቀረቡት የፈጠራ ስራዎች የሀገሪቱን የልማት ተስፋና ተጨባጭ እንቅስቃሴ የሚያመላክቱ ናቸው ብለዋል። መንግስት የክህሎት መር የሥራ ስምሪትን እንደ ዋነኛ ፖሊሲ በመከተሉ፣ ወጣቶች ያላቸውን እምቅ አቅም በተግባር እንዲያሳዩና በ21ኛው ክፍለ ዘመን ራሳቸውን በእውቀት፣ በክህሎትና በስነ-ምግባር በማነጽ ለሀገራቸው ብልጽግና እንዲተጉ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተዋል። አክለውም፣ ወጣቶች የሥራን ክብር በመረዳትና ዲጂታል ክህሎታቸውን በማሳደግ የሀገር ግንባታ አካል እንዲሆኑና የጀመሩትን የፈጠራ ስራ ወደ ቢዝነስ በመቀየር ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ አደራ ብለዋል።
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ በበኩላቸው፣ የዘንድሮው አውደ-ርዕይ ቴክኖሎጂዎችን ለዕይታ ብቻ ከማቅረብ ባለፈ በቀጥታ ወደ ፋብሪኬሽን ኢንጂነሪንግ በማሸጋገር ለተጠቃሚው ተደራሽ እንዲሆኑ የሚያስችል አዲስ ስትራቴጂ የተተገበረበት መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የውጭ ምንዛሬን የሚያድኑ ተኪ ምርቶችን ማምረት እንደሚችሉ በተግባር ያረጋገጡበት መድረክ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዕለቱ በቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ በዲጂታል አይሲቲ ቴክኖሎጂዎች ፈጠራ፣ በፋሽን ዲዛይን ፤ በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር ከፍተኛ ውጤት እንዲሁም በ ስፖርት ዉድድር አሸናፊ በመሆን በደረጃ ለወጡት የእውቅና እና የሽልማት ስነ-ስርዓት ተካሂዷል። የተጀመረው የቴክኖሎጂ ሽግግርና የምርት መተካት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ የዝግጅቱ ፍጻሜ ሆኗል።
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/@bols20116?_t=ZM-8y9L28EOubG&_r=1
👉Facebook
https://www.facebook.com/addisababatvetbureau
👉Telegram
https://t.me/AABOLS
👉YouTube
https://youtube.com/@bureauoflaborandskill?si=t9ZklwKzGx9rRyXf
👉website
https://aabols.gov.et
👉ለቅሬታ፣ አስተያየትና ጥቆማ
https://complain.aabols.gov.et
👉ለነፃ የስልክ ጥሪ
6524 | 0 |
| 20 |
ሰኞ:- ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም
16ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዓውደ-ርዕይ በአራዳ ፓርክ ተከፈተ!!
“የቴክኖሎጂ ልህቀት ለሀገር ብልጽግና!” በሚል መሪ ቃል ለተከታታይ ሦስት ቀናት የሚቆየው 16ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዓውደ-ርዕይ ዛሬ በአራዳ ፓርክ በድምቀት ተከፍቷል።
ይህ ዓመታዊ ዓውደ-ርዕይ የብልፅግና ተምሳሌት የሆነችው አዲስ አበባ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያላትን ተወዳዳሪነት በተግባር የምታሳይበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል። በዕለቱም የሚሰሩ እጆችና የሚፈጥሩ አዕምሮዎች ለሀገር ግንባታ ያላቸው መሠረታዊ ሚና ጎልቶ ታይቷል።
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂን በመቅዳትና መልሶ በመጠቀም የዓለምን ፈጣን እድገት መቀላቀል መቻሏን የገለጹት የከተማው ከፍተኛ አመራሮች፣ በተለይም የውጭ ምንዛሪ እጥረትን የሚቀንሱ ተኪ ምርቶችን በማምረት ረገድ ትላልቅ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን አብራርተዋል።
በከተማዋ ፈጣን እድገት ውስጥ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን፣ በቀጣይም ተቋማቱ ውጤታቸውን እንዲያሰፉ ጥሪ ቀርቧል።
በተለይም የተለወጠ የሥራ ባህል መተግበር፣ የፈጠራ ስራዎችን ማጠናከር፣ የሀገሪቱን የልማት ፍላጎት የሚመጥኑ ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት ላይ ትኩረት እንዲደረግ አሳስበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለቴክኒክና ሙያ ዘርፉ የሚያደርገውን ያልተቋረጠ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በድጋሚ አረጋግጧል።
በመጨረሻም ይህን ደማቅ ዓውደ-ርዕይ በቅንጅት ላዘጋጁ የሥራ እና ክህሎት ቢሮ አመራሮች፣ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ አሰልጣኞች፣ ሠራተኞችና ሰልጣኞች ላበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ ምስጋና ቀርቦላቸዋል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት" | 0 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
