fa
Feedback
FastMereja.com

FastMereja.com

رفتن به کانال در Telegram

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام FastMereja.com

کانال FastMereja.com (@fastmereja) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 48 142 مشترک است و جایگاه 3 625 را در دسته آموزش و رتبه 683 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 48 142 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 26 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -620 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -24 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 13.37% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.97% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 6 435 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 3 835 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 22 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 27 اوت, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

48 142
مشترکین
-2424 ساعت
-1817 روز
-62030 روز
آرشیو پست ها
የ8 ሰዓት የእንቅልፍ ህግ ጊዜው አልፎበታል ተባለ፡ አንድ ሰው በእርግጥ ምን ያህል ሰዓት መተኛት አለበት? ​#FastMereja I ለዘመናት ሰዎች በቀን ውስጥ ስምንት ሰዓት መተኛት አለባቸው የሚለው እምነት የተሳሳተና ጊዜው ያለፈበት መሆኑን አዳዲስ የህክምና እና የሳይንስ ጥናቶች ይፋ አደረጉ። ​በቅርቡ በ”ብሬን ሜዲሲን” ሳይንሳዊ መጽሔት ላይ የወጡ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት፣ እያንዳንዱ ሰው እንደ እድሜው፣ እንደ ፆታው እና እንደ አካላዊ ሁኔታው የሚያስፈልገው የእንቅልፍ መጠን ይለያያል። የሰርይ ዩኒቨርሲቲ የፋክስ እና የእንቅልፍ ተመራማሪዎች እንዳረጋገጡት፣ የ8 ሰዓት የእንቅልፍ ህግ አመጣጥ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ “8 ሰዓት ለስራ፣ 8 ሰዓት ለመዝናናት፣ 8 ሰዓት ለእንቅልፍ” በሚል ከተቀረጸ ማህበራዊ ፍልስፍና እንጂ ፍጹም ሳይንሳዊ መሰረት ያለው አይደለም። ​ተመራማሪዎች የኤሌክትሪክ መብራት እና የቴክኖሎጂ ውጤቶች በሌሉባቸው ጥንታዊ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ ባደረጉት ጥናት፣ ሰዎች በቀን ከ5.7 እስከ 7.1 ሰዓታት (በአማካይ 6.4 ሰዓት) ብቻ ተኝተው ሙሉ ጤንነታቸውን ጠብቀው መኖር እንደሚችሉ አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በዘመናዊው አለም ሰፊ የሰውነት እና የአእምሮ ምርመራ ያደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ ለሰው ልጅ አካላዊ ጤንነት እና ለአካል ክፍሎች እድሜ ማደስ አነስተኛ እና ተስማሚ የሚባለው የእንቅልፍ መጠን ከ6.4 እስከ 7.8 ሰዓታት መካከል ነው። ​የአሜሪካ የብሔራዊ የእንቅልፍ ፋውንዴሽን መረጃ እንደሚያመላክተው፣ እድሜያቸው ከ26 እስከ 64 ባሉ አዋቂዎች ዘንድ ከ7 እስከ 9 ሰዓት መተኛት የተለመደ ቢሆንም፣ ለአንዳንዶች ግን ከ6 እስከ 10 ሰዓት ባለው ውስጥ መተኛት ተፈጥሮአዊ ሊሆን ይችላል። ከተፈለገው መጠን በላይ አብዝቶ መተኛትም ሆነ አነስተኛ እንቅልፍ ማግኘት ለልብ ህመም፣ ለስትሮክ እና ለክብደት መጨመር እንደሚያጋልጥ በጥናቱ ተመልክቷል።

የሚስ ወርልድ ውድድር ለአሸናፊነት የሚያበቁ መስፈርቶች ​#FastMereja I የአለም አቀፉ የቁንጅና ውድድር (Miss World) አሸናፊዎችን የሚለይበትንና ተወዳዳሪዎች የሚመዘኑባቸው ከውጭ አካላዊ ውበት ይልቅ ለተወዳዳሪዎች የበጎ አድራጎት ስራዎች፣ የንግግር ችሎታ፣ አካላዊ ብቃትና ልዩ ክህሎቶች ከፍተኛ ነጥብ የሚሰጥበት ነው። ተወዳዳሪዎች ወደ መጨረሻው የዘውድ ምዕራፍ ለማለፍ “Fast Track” በተሰኙ መስፈርቶች አልፈው በዳኞች ይገመገማሉ። ​ዓለም አቀፉ የሚስ ወርልድ ድርጅት ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት፣ ተወዳዳሪዎችን ለተፈለገው ዘውድ የሚያበቁትና ዳኞች ነጥብ የሚሰጡባቸው ዋና ዋና የምዘና መስፈርቶች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፦ 📌 ​Beauty with a Purpose ይህ መስፈርት የውድድሩ ዋናና ትልቁ ማዕከል እንደሆነ ተገልጻል። ተወዳዳሪዎች በሀገራቸው ውስጥ የሚመሩትን ወይም የፈጠሩትን የበጎ አድራጎትና የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክት ለዳኞች ያቀርባሉ። የማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያደርጉት ጥረትና ያመጡት ለውጥ ከፍተኛውን ነጥብ ያስገኛል። ​📌 Head-to-Head Challenge የተወዳዳሪዎችን በህዝብ ፊት የመናገር ብቃት፣ የማህበራዊ ግንኙነት ችሎታ፣ አጠቃላይ እውቀትና የአስተሳሰብ የበሰለነት ደረጃ የሚመዘንበት ምዕራፍ ነው። 📌 ​የክህሎትና ፈጠራ ውድድር (Talent Round) ተወዳዳሪዎች እንደ ዘፈን፣ ውዝዋዜ፣ ሙዚቃ መሣሪያ መጫወት ወይም ሌሎች ልዩ ልዩ የኪነ-ጥበብ ፈጠራዎቻቸውን በመድረክ ላይ በማቅረብ ችሎታቸውን ያሳያሉ። 📌 ​የፋሽንና ሞዴሊንግ ብቃት (Top Model) ተወዳዳሪዎች ያላቸውን የመድረክ ላይ መተማመን፣ የፋሽን አቀራረብ፣ የአካሄድ ስልትና የልብስ አሰራርን የማስተዋወቅ ብቃት በዳኞች የሚገመገምበት መስፈርት ነው። 📌 ​የስፖርትና አካል ብቃት (Sports Challenge) ተወዳዳሪዎች ያላቸውን አካላዊ ጥንካሬ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴና የአካል ብቃት የሚያሳዩበት ልዩ የውድድር ክፍል ነው። 📌 ​የማህበራዊ ሚዲያና መልቲሚዲያ (Multimedia) ተወዳዳሪዎች በዲጂታል አማራጮች ከህዝብ ጋር ያላቸውን ቁርኝት፣ የሚያዘጋጁትን የመረጃ ይዘትና የሚያገኙትን የህዝብ ድጋፍ መጠን ለመለካት የሚያገለግል መስፈርት እንደሆነ ተመልክቷል። ይህ መስፈርት አሁን ህዝቡ ድምጽ እየሰጠበት ያለው ውስጥ ይካተታል።

ሀገር እና ትውልድን ለሚገነቡ የማህበራዊ ሚዲያ ባለሙያዎች የ15 ሚሊዮን ብር የወርቅ ሜዳሊያ ሽልማት ተዘጋጀ #FastMereja I ሀገርን፣ ህዝብን እና መልካም እሴቶችን በማስቀደድ በቲክቶክ፣ ፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቴሌግራም በጎ ተፅዕኖ ለፈጠሩ 36 የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በአጠቃላይ 15 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የ280 ግራም ወርቅ ሜዳሊያ እና ልዩ ልዩ ሽልማቶች የሚሰጥበት የዕውቅና መርሃ ግብር መዘጋጀቱ ተገለጸ። ይኸው ግዙፍ የዕውቅና እና የሽልማት መርሃ ግብር ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ በሚያውሉ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና ህብረተሰብን የሚጠቅሙ አዳዲስ ሀሳቦች ባሏቸው ባለሙያዎች ላይ ያተኮረ ነው። መርሃ ግብሩ በሁለት ዋና ዋና ዘርፎች ተከፍሎ ሽልማቶቹን የሚያበረክት ሲሆን፣ ከመጀመሪያው ዘርፍ ከአመቱ ሙሉ የየወሩ አሸናፊዎች መካከል ለሚመረጡ ሶስት ተሸላሚዎች በአጠቃላይ 180 ግራም የወርቅ ሜዳሊያ ተዘጋጅቷል። በዚህም መሰረት አንደኛ ለወጣው ባለሙያ የ100 ግራም፣ ለሁለተኛው የ50 ግራም እንዲሁም ለሶስተኛው የ30 ግራም የወርቅ ሜዳሊያ የሚሰጥ ይሆናል። በሁለተኛው ዘርፍ ደግሞ “ሀገር ተስፋ የምታደርጋቸው” በሚል መሪ ቃል በስራ ፈጠራ፣ በፋሽን ዲዛይን፣ በቱሪዝም፣ በካፒቴንነት፣ በትምህርት እና በተለያዩ ሙያዎች ተሰማርተው ህብረተሰቡ ዘንድ ብዙም ሳይታወቁ ለሀገር እና ለትውልድ የሚጠቅም ስራ ለሰሩ ሙህራን እና ባለሙያዎች የ100 ግራም ወርቅ ሜዳሊያ ሽልማት ተመድቧል። በዚህ ዘርፍ አንደኛ ለሚወጣው የ50 ግራም፣ ለሁለተኛው የ30 ግራም እና ለሶስተኛው የ20 ግራም የወርቅ ሜዳሊያ የሚበረከት ሲሆን፣ ከ4ኛ እስከ 20ኛ ደረጃ ለሚይዙ ተወዳዳሪዎችም ልዩ ልዩ የዕውቅና እና የስጦታ መርሃ ግብሮች ተዘጋጅተዋል። በተጨማሪም ይኸው መርሃ ግብር የዘመኑን የዲጂታል መድረኮች ተጠቅመው ለሀገር ውለታ የዋሉ ከ10 በላይ የሀገር ባለውለታዎች የምስጋና ስነ-ስርዓት የሚያቀርብ ሲሆን፣ አጠቃላይ የሽልማት ዝግጅቱ የፈጠራ ሰዎችን ማበረታታት እና የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን ለሀገር ግንባታ ማዋልን አለማ ያደረገ መሆኑ ተጠቅሷል።

የክብር ዶክተር አርቲስት ማህሙድ አህመድ “ለታሪክ” የተሰኘ የመጨረሻ አልበሙን ሊለቅ ነው ​#FastMereja I ለስድስት አስርት ዓመታት በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ የማይተካ አስተዋጽኦ ያበረከተው የክብር ዶክተር አርቲስት ማህሙድ አህመድ “ለታሪክ” የተሰኘውን 26ኛ እና የመጨረሻ አልበሙን ለአድማጮች ሊያደርስ መሆኑን ዛሬ በሸራተን አዲስ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አበሰረ። ​ይህ አልበም የቀደሙትን የኢትዮጵያ ሙዚቃ ቅርሶች፣ ለዛና ወግ ሳይለቁ ለአዲሱ ትውልድ ለማስረከብ ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፣ የአርቲስቱን ልዩ የመድረክና የድምፅ ስልት መሠረት ያደረገ እንደሆነ ተገልጿል። በስራው ላይ ዘመናዊ የሙዚቃ መሳሪያዎች እና ባህላዊ የቅኝት ድምፆች በተዋጣለት መልኩ የተዋሃዱበት ሲሆን፣ የፍቅር፣ የሀገር፣ የህይወት ፍልስፍና እና ማህበራዊ እሴቶችን የሚያንፀባርቁ አዳዲስና በትዝታ የተቃኙ ስራዎች ተካተውበታል። ​በአልበሙ ዝግጅት ላይ አንጋፋ እና ወጣት የዜማና ግጥም ደራሲያን እንዲሁም የሙዚቃ አቀናባሪዎች በጋራ የተሳተፉ ሲሆን፣ አርቲስቱ ይህ አልበም የኪነ-ጥበብ ህይወቱ የመጨረሻ ስራ መሆኑን በመግለፅ አዲሱ የሙዚቃ ትውልድ የሀገርን ባህል፣ ቅኝት እና ማንነት ሳይለቅ ዘመናዊነትን እንዲቀላቅል ጥሪ አቅርቧል። ​አልበሙን በዓለም አቀፍ ደረጃ የማሰራጨቱንና የማስተዋወቁን ስራ ይሳቃል ኢንተርቴይመንት ከሌሎች የሙዚቃ ኩባንያዎች ጋር በመተባበር የሚያከናውነው ሲሆን፣ በSpotify, Apple Music እና YouTube ጨምሮ በሁሉም ዲጂታል መድረኮች ለህዝብ ይደርሳል። በእንቁጣጣሽ ዋዜማ አንድ ነጠላ ዜማ የሚለቀቅ ሲሆን ሙሉ አልበሙ ደግሞ በመስከረም አጋማሽ ለአድማጮች ክፍት ይደረጋል።

ድምጻዊት ተዓምር ግዛው “በፍቅር” የተሰኘ የመጀመሪያ የሙዚቃ አልበሟን ለአድማጮች ልታቀርብ ነው #FastMereja I ከአጋሮ ከተማ “ጥበብ ብርሃን” የኪነት ቡድን በመነሳት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ የራሷን አሻራ እያሳረፈች የምትገኘው ድምጻዊት ተዓምር ግዛው፣ ለአራት ዓመታት ስትሰራበት የቆየችውን “በፍቅር” የተሰኘ የመጀመሪያ አልበሟን ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ለአድማጮች በይፋ እንደምታበቃ አስታወቀች። አልበሙ በድምጻዊቷ ይፋዊ የዩቲዩብ (YouTube) ቻናል እና በተለያዩ የሙዚቃ ማደመጫ መተግበሪያዎች ላይ የሚለቀቅ ይሆናል። ይህ 16 የሙዚቃ ሥራዎችን ያቀፈው አልበም የጓይላ (ትግርኛ) እና የፎሌ (ኦሮምኛ) ስልተ-ምቶችን ጨምሮ በኦሮምኛ እና በትግርኛ ቋንቋዎች የተሰሩ ህብረ ብሄራዊ ይዘት ያላቸውን ስራዎች አካቷል። ለአንዱ ሙዚቃ የተሰራው የቪዲዮ ክሊፕ ዝግጅትም ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁ ተገልጿል። በአልበሙ ዝግጅት ላይ በዜማ ደራሲነት አበበ ብርሃኔ፣ እሱባለው ይታየው፣ ምሕረታብ ደስታ፣ አቤል ሙሉጌታ፣ ቢንያምር አሕመድ እና ዳን አድማሱ የተሳተፉ ሲሆን፤ በግጥም ደግሞ ወንድወሰን ይሁብ፣ ዳን አድማሱ እና ጎይትኦም ሃይለማርያም ድርሻቸውን አበርክተዋል። የሙዚቃ ቅንብሩ በሚካኤል ሃይሉ (ሚኪ ጃኖ)፣ ታምሩ አማረ እና ብሩክ አፈወርቅ የተሰራ ሲሆን፣ የ16ቱ ሙዚቃዎች ማስተሪንግ (Mastering) በኪሩቤል ተስፋዬ ተከናውኗል። ስራውን አስመልክቶ አስተያየቱን የሰጠው የሙዚቃ አቀናባሪው ሚካኤል ሃይሉ (ሚኪ ጃኖ) “ያንጻሉ፣ ያዝናናሉ፣ ያክማሉ ብለን የሰራናቸውን ሙዚቃዎች ለአድማጮች አበርክተናል፤ አስተማሪና አስደሳች ጊዜ አሳልፈን ለዚህ በመብቃታችን አድማጮች ልባዊ አስተያየታቸውን እንዲለግሱ እጠይቃለሁ” ብሏል። ድምጻዊት ተዓምር ግዛው በበኩሏ ቀኑ በሕይወቷ እጅግ የምትጓጓለት መሆኑን ገልጻ፣ ፈተናዎችን አሳልፈው ለዚህ ላበቋት ባለሙያዎች ምስጋና አቅርባለች። በተጨማሪም ከ”ዮጵ” የተሰጥዖ ውድድር ጀምሮ ላላለያትና ድጋፍ ላደረገላት ድምጻዊ ጸሐይ ዮሐንስ አክብሮቷን በመግለጽ፣ ሁሉም አዳዲስ ባለሙያዎችን የማበረታታት ባህል ሊኖረው እንደሚገባ አሳስባለች። ድምጻዊ ጸሐይ ዮሐንስ አልበሙን በጉጉት እንደሚጠብቀው እና ተዓምር ድንቅ ስራ መስራቷን እንደምትቀጥል እምነቱን የገለጸ ሲሆን፣ የድምጻዊቷ ማኔጀር አቶ ሄኖክ ግዛው በበኩላቸው በአልበሙ ላይ ከፍተኛ ድካምና ጊዜ መዋዕለ ንዋይ ፈሶበት ጥራቱን የጠበቀ ስራ መዘጋጀቱን አረጋግጠዋል። #ኪነ_ጥበብ

ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ ለአዲስ ዓመት ልዩ ቅናሽ ማዘጋጀቱን አስታወቀ። #Fastmereja I ቀደም ሲል “ያሥሚን ጀማል ኮንስትራክሽን” በሚል ስያሜ ይታወቅ የነበረው ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ፣ አዲሱን የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ ለደንበኞቹ እስከ 30 በመቶ የሚደርስ ልዩ የበዓል ቅናሽ ማዘጋጀቱን ገለጸ። የኮምፓስ ፕሮፐርቲስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ኑረዲን መሐመድ እንደገለፁት፣ በቦሌ አትላስ እና በካዛንቺስ የሚገነቧቸውን አዳዲስ ፕሮጀክቶች ለሽያጭ ማቅረቡን ገለፀዋል። አቶ ኑረዲን አክለዉም በቦሌ አትላስ ሳይት የሶሪንግ (የመደገፊያ) ሥራ መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፣ በካዛንቺስ ደግሞ 5 የቤዝመንት ደረጃዎች ተጠናቀው ህንፃው ግራውንድ ፍሎር ላይ መድረሱ በሰጡት መግለጫ አስረድተዋል። ለሽያጭ የቀረቡት የመኖሪያ አፓርትመንቶች እና የንግድ ሱቆች ሲሆኑ፣ የመኖሪያ ቤቶቹ ስፋት ከ55 ካሬ ሜትር studio እስከ 165 ካሬ ሜትር የሦስት መኝታ ክፍል እንደሚሸፍኑ የተገለፀ ሲሆን የካሬ ሜትር መነሻ ዋጋም ከብር 80,500 የሚጀምር ሲሆን፣ የቀረበው እስከ 30 በመቶ የሚደርስ ቅናሽ እስከ መስከረም 30 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ ብቻ እንደሚቆይ ተገልጿል። ድርጅቱ ደንበኞቹን ከዋጋ ንረት ለመጠበቅ የ”ዋጋ ዋስትና” (Price Protection) አሰራር መዘርጋቱን የገለጸ ሲሆን፣ በዚህም መሠረት በግንባታ ወቅት የገበያ የምንዛሬ ጭማሪም ሆነ የዕቃዎች ዋጋ መወደድ ቢከሰት ደንበኞች በተዋዋሉበት የኢትዮጵያ ብር መጠን ብቻ ክፍያቸውን አጠናቀው በጊዜው ቤታቸውን እንደሚረከቡ አስታውቋል። በተጨማሪም ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ የማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በአንድ የበጎ አድራጎት ተቋም እና በሦስት ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ሴት ተማሪዎች የንፅህና መጠበቂያ (ሞደስ) ድጋፍ እንደሚያደርግ የገለጸ ሲሆን፣ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት በሀገሪቱ የሪል ስቴት ዘርፍ ከግንባር ቀደም 5 ተቋማት ተርታ ለመሰለፍ ራዕይ ሰንቆ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል።

ታሪክ ሰሪው የሀድያ ዞን ተማሪ ሮቤል ጌታቸው በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሀገሪቱን 2ኛ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል ​#FastMereja I በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ በሀድያ ዞን ግቤ ወረዳ የተገኘው የሊች ጎጎ ትምህርት ቤት ተማሪ ሮቤል ጌታቸው ገብሬ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ከቀረቡበት 600 ጥያቄዎች ውስጥ 590 ያህሉን በትክክል በመመለስ አስደናቂ የስኬት ታሪክ አስመዝግቧል። ​ይህ የተመዘገበው የላቀ ውጤት በዘመኑ የፈተና ታሪክ ውስጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሁለተኛው ከፍተኛ ውጤት ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፣ የተማሪውን ጠንካራ የጥናት ባህልና በትምህርቱ ላይ የነበረውን ከፍተኛ ትጋት የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል። የተማሪ ሮቤል ጌታቸው ስኬት ለተማረበት ሊች ጎጎ ትምህርት ቤት፣ ለዞኑ እንዲሁም ለመላው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትልቅ ኩራትና ለቀጣይ ተፈታኞችም አርአያ የሚሆን አዎንታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩ ተጠቅሷል።

ኢትዮጵያ የ2028 የአፍሪካ ዋንጫን (AFCON) ለማስተናገድ ይፋዊ የጨረታ ሰነድ አቀረበች ​#FastMereja I የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (EFF) የ2028 የአፍሪካ ዋንጫን (AFCON) ለማስተናገድ የሚያስችለውን ይፋዊ የማመልከቻ ሰነድ ለአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) ማስረከቡን አስታወቀ። ​የኢፌዴሪ መንግሥት ሙሉ ድጋፍ የተሰጠው ይህ የጨረታ ሰነድ የካፍን መስፈርቶች ሙሉ በሙሉ ያሟላና ሀገሪቱ ውድድሩን ለማስተናገድ ያላትን ዝግጁነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ፌዴሬሽን ገልጿል።

ኤርትራዊቷ ሞዴል ስኒት ሀብተአብ በ2 ሰዓት ውስጥ 100ሺ ድምጽ አገኘች ​#FastMereja I በዓለም አቀፉ Miss World ውድድር ኤርትራን ወክላ በመሳተፍ ላይ የምትገኘው ሞዴል ስኒት ሀብተአብ በህዝባዊ የኦንላይን ድምፅ አሰጣጥ በዓለም ደረጃ የመጀመሪያውን ደረጃ በመያዝ አዲስ ታሪክ አስመዘገበች። ​በቀረበው ወቅታዊ መረጃ መሰረት ሞዴል ስኒት ሀብተአብ በተደረገላት ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ በሁለት ሰዓታት ውስጥ ብቻ 100 ሺህ ተጨማሪ ድምፆችን በማከማቸት አጠቃላይ ያገኘችውን የድምፅ መጠን ከ700 ሺህ ወደ 800 ሺህ በላይ ማሳደግ ችላለች። ይህም በውድድሩ የህዝብ ድምፅ ምዕራፍ እየመራች ሲሆን የድምፅ አሰጣጡ ፍጥነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ እንደሚገኝ ታይቷል። በሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያዊቷ ሞዴል ሩት ድምጽ አሰጣጥ ምሽቱን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ቅስቀሳ እየተደረገላት ሲሆን በርካታ ድምጽ እያገኘች ትገኛለች።

የዓለማችን ፈጣኑ ሰው ዩሴን ቦልት ከ13 ዓመታት የፍቅር ቆይታ በኋላ ለካሲ ቤኔት የጋብቻ ጥያቄ አቀረበ ​#FastMereja I ስምንት የኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያዎች ባለቤቱ እና የዓለማችን ፈጣኑ ሰው ዩሴን ቦልት ለረጅም ጊዜ አብራው ለዘለቀችው የህይወት አጋሩ ካሲ ቤኔት የጋብቻ ጥያቄ አቀረበ። ​ጃማይካዊ የሩጫ አትሌት የጋብቻ ጥያቄውን ያቀረበው በኪንግስተን ጃማይካ በተዘጋጀው የልደት በዓል አከባበር ስነ-ስርዓት ላይ በወዳጅ ዘመዶቻቸው ፊት ተንበርክኮ የ5 ካራት አልማዝ የጋብቻ ቀለበት በማሰር እንደሆነ ተገልጿል። ​እንደተረጋገጠው ሁለቱ ጥንዶች እ.ኤ.አ. ከ2013 ጀምሮ ላለፉት 13 ዓመታት በፍቅር አብረው የዘለቁ ሲሆን፣ የ6 ዓመቷ ኦሊምፒያ ላይትኒንግ እና የ5 ዓመት መንትያ ወንዶች ልጆች ታንደር እና ሴንት ሊዮ የተባሉ ሶስት ልጆችን አፍርተዋል። ​በስነ-ስርዓቱ ወቅት የ34 ዓመቷ ሞዴል እና ነጋዴ ካሲ ቤኔት የቀረበላትን ጥያቄ በደስታ የተቀበለች ሲሆን፣ የተደረገላት ሰርፕራይዝ እና የጋብቻ ጥያቄ ፈፅሞ ያልጠበቀችው እንደነበር ቅርብ ወዳጆቻቸው በማህበራዊ ሚዲያ ገፃቸው አስፍረዋል።

የጉራጊኛ ሙዚቃን ጥራት ለማሳደግ ያለመው “ታውስማ” አልበም ሊመረቅ ነው! #Fastmereja:- በጉራጊኛ ሙዚቃ ዘርፍ የሚታወቀው ድምፃዊ ተፈራ ፍቃዱ “ታውስማ” የተሰኘውን ሁለተኛ የሙዚቃ አልበሙን ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ሊያስመርቅ መሆኑን በዛሬዉ እለት በተሰጠ መግለጫ አስታዉቋል። በሰባት የተለያዩ ስቱዲዮዎች የተዘጋጀው ይህ አልበም፣ የጉራጌ ብሄረሰብ ሙዚቃን ጥራት ባለው መልኩ ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በስራው ላይ እንደ ደምሴ ተካ፣ ደሳለኝ መርሻ፣ ፈለቀ ማሩ፣ አብራር ደሊል፣ ጎፈር፣ መስፍን ብርሃኑ እና ጋዜጠኛ ሙሉቀን ሀሰን ያሉ አንጋፋ ባለሙያዎች በግጥም እና ዜማ ተሳትፈዋል። እንዲሁም በአቀናባሪነት አሌክስ ይለፍ፣ መሀመድ ኑርሴን፣ ዘሪሁን ሳህለማርያም፣ ኤርሚያስ ዘውዱ፣ ከድርሁሴን፣ በሀይሉ ዘርአይ እና ህስቅያስ ዘውዱ የተሳተፉበት ሲሆን፣ ታዋቂ ድምፃውያንን ያጀቡ የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋቾች በቀጥታ (Live) ቅንብር ያጀቡት ሲሆን የአልበሙ አጠቃላይ ማኔጅመንት በአርቲስት ደሳለኝ መርሻ የተመራ መሆኑ ተገልጿል። የምርቃት ስነ-ስርዓቱ ነሐሴ 24 ቀን ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ መካኒሳ አቦ ቤተክርስቲያን ከፍ ብሎ በሚገኘው ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ እንደሚካሄድ ነዉ የተገለፀዉ። በአልበሙ የምርቃት መርሃ-ግብር ላይ ሀይሉ ፈረጃ፣ ደሳለኝ መርሻ፣ ረሻድ ከድር፣ ፈለቀ ማሩ እና ኮሜዲያን አዝመራው ሙሉሰውን ጨምሮ 11 አርቲስቶች ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ በመግለጫዉ ተገልጿል። አልበሙ በምርቃቱ ዕለት በድምፃዊው የዩቲዩብ ቻናል (Tefera.Fikadu) እና በዓለም አቀፍ የዲጂታል ፕላትፎርሞች ላይ ለህዝብ እንደሚደርስ ነዉ የተገለፀዉ። #ኪነ_ጥበብ

በአሜሪካ የፓርኪንግ ስራ ክፍያ በሰአት እስከ 22 ዶላር እንደሚያስገኝ ተገለጸ ​#FastMereja I በአሜሪካ የፓርኪንግ (የመኪና ማቆሚያ) አስተናጋጅነት እና ቁጥጥር ስራ የተሰማሩ ሰራተኞች በአማካይ በሰአት ከ15 እስከ 17 ዶላር ክፍያ እንደሚያገኙ የቅርብ ጊዜ የስራ ገበያ መረጃዎች አመላከቱ። ​በአሜሪካ የኢንዱስትሪ መረጃዎችና የቅጥር ኤጀንሲዎች ይፋ ባደረጉት ትንተና መሰረት፣ በዚሁ ዘርፍ የተሰማሩ ሰራተኞች እንደ የስራ ቦታቸው፣ ልምዳቸው እና እንደሚሰሩበት ግዛት ሁኔታ በሰአት ከ9.62 ዶላር ጀምሮ እስከ 22.84 ዶላር የሚደርስ ገቢ ያገኛሉ። ይህም በዓመት በአማካይ ከ30,000 እስከ 36,000 ዶላር የሚደርስ አጠቃላይ ገቢ እንደሚያስገኝ ተመልክቷል። ​በተለይም እንደ ካሊፎርኒያ፣ አላስካ እና ኮሎራዶ ባሉ ግዛቶች የፓርኪንግ ሰራተኞች ክፍያ ከተጠቀሰው አማካይ መጠን ከፍ ያለ ሲሆን፣ በሰአት እስከ 21 ዶላር የሚደርስ ክፍያ ይከፈላቸዋል። ከዚህ በተጨማሪም እንደ ቫሌት ፓርኪንግ ባሉ አሰራሮች ላይ የሚሰሩ ሰራተኞች ከተወሰነላቸው መሰረታዊ ደሞዝ በተጨማሪ ከአገልግሎት ተቀባዮች ከሚያገኙት ተጨማሪ ስጦታ (Tips) አጠቃላይ ገቢያቸውን ያሳድጋሉ። ​የስራው ተፈጥሮ የመኪና ማቆሚያ ስፍራዎችን መቆጣጠር፣ ትኬት መስጠት፣ ደንበኞችን ማስተናገድ እና መኪና ማቆምን ማመቻቸት ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ለስራው የሚጠየቀው መስፈርትም አነስተኛ መሆኑ ለብዙዎች የመጀመሪያ የስራ እድል እንዲሆን አድርጎታል።

3ኛው የአፍሪካ ስታር ዋይድ አዋርድ በመስከረም ወር ይካሄዳል! #Fastmereja:- “ክብር ለሚገባው ክብር እንስጥ፤ መመሰጋገን ባሕላችን እናድርግ” በሚል መሪ ቃል የሚከናወነው 3ኛው ዙር የአፍሪካ ስታርዋይድ አዋርድ የሽልማት ሥነ-ሥርዓት በመጪው መስከረም ወር እንደሚካሄድ አዘጋጁ ከለር ፉል ኢቨንት ኦርጋናይዘር በዛሬዉ እለት በአምባሳደር ሆቴል በሰጠዉ መግለጫ አስታዉቋል። በዝግጅቱ ላይ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) እና ከአፍሪካ ህብረት (Aሀ) የተወጣጡ ተወካዮች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የውጭ ሀገራት እንግዶች እንዲሁም ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እንደሚታደሙ ተጠቅሷል። የዘንድሮው ዝግጅት ከአምናው በበለጠ አድማሱን በማስፋት አህጉራዊ ተደራሽነት ያለው እንዲሆን መደረጉ ተገልፆ ለዚህም ይረዳ ዘንድ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ምሁራንና ባለሙያዎች በዳኝነትና በኮሚቴነት መካተታቸዉም ነዉ የተገለፀዉ። ሽልማቱ በተለያዩ 11 ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን የአመራር አባልና ኢንቨስትመንት ዘርፍ፣ የኮንስትራክሽንና ሪል እስቴት ዘርፍ፣አገልግሎት ሰጪ ተቋማትና ባንክ፣ አቪየሽንና ቱሪዝም፣ሴትና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች፣ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች እንደሆኑ ተገልጿል። የአዋርዱ ዋነኛ አላማ በዘርፉ የለፉና የደከሙ ግለሰቦችንና ተቋማትን ፈልፍሎ በማዉጣት የሃገር ባለዉለታ ስለመሆናቸዉና በትዉልዱ ዘንድ ሊመሰገኑ ሊዘከሩ እንደሚገባና ትዉልዱም ከመልካም ሥራቸዉና ከዘወትር ትጋታቸዉ ልምድ እንዲቀስም እድሉን ለማመቻቸት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። ይህ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የቱሪዝም እና የኢንቨስትመንት አቅም ለውጭ ሀገር አልሚዎች ለማስተዋወቅ ትልቅ እድል የሚፈጥር በመሆኑ፣ አሸናፊዎችን በትክክል ለመለየት ከሙያተኞች ግምገማ በተጨማሪ ህዝቡ በድረገፅ አማካኝነት በስልክ፣ በአሜይል፣ በቴሌግራም እና በዋትስአፕ ጥቆማዎችን መስጠቱን እንዲቀጥል አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል። የአፍሪካ ስታርዋይድ አዋርድ ለሕዝብ እና ለአገር በጎ ነገር ያበረከቱ ግለሰቦችና ስኬታማ የኢኮኖሚ ጃግኖች፣ በትጋት በቅንነት እና በሀገር ፍቅር መስራት ተምሳሌት የሆኑ አመራሮች፣ ዉስጥ በመሳተፍ በሙያቸዉ አንቱ ለተባሉ ግለሰቦችና ድርጅቶች ዕውቅና የሚያበረክት ነዉ።

በናይጄሪያ የዲኤንኤ ምርመራ ካደረጉ አራት ወንዶች መካከል አንዱ የልጁ ባዮሎጂካዊ አባት አለመሆኑ ተረጋገጠ ​#FastMereja I በናይጄሪያ በግል ተቋም የዲኤንኤ (DNA) የምርመራ አገልግሎት ከሚሰጡት ዋነኛው የሆነው “ስማርት ዲኤንኤ” ይፋ ባደረገው የ2025/2026 አዲስ ሪፖርት መሠረት፣ የአባትነት ማረጋገጫ ከተደረገላቸው ወንዶች መካከል 23.6 በመቶ የሚሆኑት የልጆቹ እውነተኛ ባዮሎጂካዊ አባት እንዳልሆኑ ተረጋገጠ። ይህም አሃዝ ባለፈው ዓመት ከተመዘገበው 24 በመቶ እና በ2023 ከነበረው 26.1 በመቶ ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ቅናሽ ያሳየ ነው። ​ሆኖም ዋና መሥሪያ ቤቱን በሌጎስ ያደረገው ይህ ተቋም፣ ይህ ውጤት በጠቅላላው የናይጄሪያ ሕዝብ ውስጥ ከሚገኙ አራት ሕፃናት አንዱ የሌላ አባት ልጅ ነው ማለት እንዳልሆነ በጽኑ አስጠንቅቋል። ተቋሙ እንዳብራራው ምርመራውን ለማድረግ ወደ ተቋሙ የሚመጡት ሰዎች አስቀድመው ጥርጣሬ ያደረባቸው በመሆናቸው መላውን የናይጄሪያ ሕዝብ በዘፈቀደ የሚወክሉ አይደሉም። ​ከተደረጉት የዲኤንኤ ምርመራዎች መካከል አብዛኞቹ ማለትም 87 በመቶ የሚሆኑት በፍርድ ቤት ትእዛዝ ወይም ለስደት (ኢሚግሬሽን) ጉዳይ ሳይሆን ሰዎች ለግል የአእምሮ እፎይታና ጥርጣሬን ለማጥፋት ያደረጉት እንደሆነ ተገልጻል። በተጨማሪም የዲኤንኤ ምርመራ ጥያቄዎችን ከሚያቀርቡት መካከል 79 በመቶ ያህሉ ወንዶች ሲሆኑ፣ ምርመራውን ካደረጉት ወንዶች መካከል ደግሞ ወደ ግማሽ የሚጠጉት ዕድሜያቸው 41 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆኑ ናቸው። ​የዲኤንኤ ምርመራ ፍላጎት በሌሎች የናይጄሪያ ግዛቶችም እየጨመረ የመጣ ቢሆንም፣ ከተመዘገቡት የዲኤንኤ ምርመራዎች ውስጥ አብዛኛው ማለትም ሶስት አራተኛው (75%) የተካሄደው የሀገሪቱ ትልቁ የንግድ ማዕከል በሆነችው ሌጎስ ከተማ ውስጥ ነው።

በ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ ጃላል ግርማ #FastMereja I በ2018 ዓ.ም በተሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የኦሮሚያ ልማት ማህበር (ኦልማ) ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው ጃላል ግርማ ኩሳ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ በሀገር አቀፍ ደረጃ 1ኛ መሆኑ ታውቋል። ተማሪ ጃላል ግርማ ኩሳ በፈተናው 591.6 ከፍተኛ ነጥብ ያስመዘገበ ሲሆን፣ ይህ ስኬት በሀገር አቀፍ ደረጃ ካሉ ተፈታኞች ሁሉ በላቀ ውጤት አንደኛ ደረጃን እንዲይዝ አስችሎታል።

9ኛው ዓመታዊ የጳጉሜ ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው! #Fastmereja:- «ጳጉሜ፤ የአፍሪካ ወርቃማ ወር» በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው 9ኛው ዓመታዊ የ«ጳጉሜ አብ ፌስቲቫል» ከጳጉሜ 1 እስከ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ለማካሄድ ዝግጅት መጠናቀቁን አዘጋጆቹ በዛሬው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ። በጳጉሜ አብ ፌስቲቫል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አዘጋጅነት፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ይህ ፌስቲቫል፤ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ባህላዊ እሴቶች፣ የኪነ-ጥበብ ሀብቶችና የኢንቨስትመንት አማራጮች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ጎብኚዎች ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በዝግጅቱ ላይ የአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የዲፕሎማቲክ ኮሚኒቲ አባላት፣ የ12ቱ ክልሎችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የባህል ቡድኖች እንዲሁም ልዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚታደሙ በመግለጫዉ ተገልጿል። በተጨማሪም ፌስቲቫሉ የኢትዮጵያን ልዩ የ13ኛ ወር ገጽታ ለዓለም ለማስተዋወቅና ጳጉሜ በUNESCO ደረጃ እንድትመዘገብ የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ አዘጋጆቹ አብራርተዋል። ፌስቲቫሉ በአምስቱ ቀናት በተለያዩ ጭብጦች ተከፋፍለው የሚካሄዱ ሲሆን፣ ዋና ዋና መርሃ-ግብሮቹም፡- ጳጉሜ 1 (ለሰላምና ለፍቅር): የፖሊስ ማርሽና የፈረስ ጉግስ ትርኢት፣ የከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎች ንግግር እና ስለ ሰላምና እርቅ የሚያተኩርየፓናል ውይይት፣ ጳጉሜ 2 (ለባህልና ለአፍሪካ አንድነት): የሁሉም ክልሎች ተወካዮች የሚሳተፉበት ባህላዊ የፋሽን ሾው እና የባህላዊ ምግቦችና መጠጦች ቅምሻ፣ ጳጉሜ 3 (ጳጉሜ ለልጆች): «ታላቁ ሩጫ በዝናብ»፣ የህፃናት ባህላዊ ጨዋታዎችና የመዝናኛ ፕሮግራሞች፣ ጳጉሜ 4 (እንነግድ በጳጉሜ): የአፍሪካውያንን የጋራ ገበያ የሚያጎለብት የንግድ ትስስር (B2B) እና የንግድ ፓናል ውይይት፣ ጳጉሜ 5 (የተፈጥሮ ውበታችን ለቱሪዝም መስህብ): የጳጉሜ ቆንጆ ውድድር፣ የቱሪዝም ውይይት እና የስፖንሰሮች የእውቅና ፕሮግራም ይከናወናሉ። የፌስቲቫሉ መደበኛ የመግቢያ ዋጋ 500 ብር ሲሆን፣ በመጨረሻው ቀን ለሚካሄደው ታላቅ የሙዚቃ ድግስ የመግቢያ ክፍያው 1,500 ብር መሆኑ ተጠቅሷል።

በሴሬብራል ፓልሲ ለተጎዱ ህፃናት ድምፅ የሚሆን ታላቅ የህዝብ እግር ጉዞ ተዘጋጀ! #Fastmereja:-በኢትዮጵያ በሴሬብራል ፓልሲ (CP) ምክንያት ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸውን ህፃናት እና ወላጆቻቸውን በመደገፍ ላይ የሚገኘው «እዝነት አካል ጉዳተኛ ህፃናትና ወላጆች መርጃ ድርጅት» ለ3ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም የሴሬብራል ፓልሲ ቀን አስመልክቶ ታላቅ ሀገር አቀፍ ንቅናቄ እና የህዝብ እግር ጉዞ ማዘጋጀቱን አስታወቀ። ድርጅቱ በዛሬው ዕለት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመለከተው፣ «ለሲፒ ጉዳተኛ የነገ ተስፋ እጓዛለሁ» በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ታላቅ የእግር ጉዞ በመጪው ጥቅምት 8 ቀን 2019 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ ከፒያሳ አድዋ ዐዐ እስከ ኩባ ፓርክ እንደሚካሄድ ተገልጿል። የድርጅቱ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ዘቢባ አህመድ በመግለጫቸው እንደተናገሩት፣ በሴሬብራል ፓልሲ ምክንያት ተደራራቢ ጉዳት የደረሰባቸው ህፃናት ያለ ሰውና መሳሪያ ድጋፍ መቆም፣ መቀመጥና መራመድ የማይችሉ እንዲሁም ስሜታቸውን ከማልቀስ ውጭ መግለጽ የማይችሉ መሆናቸዉን ገልፀዋል። ወ/ሮ ዘቢባ አክለዉም በርካታ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰቦችም በድህነት ምክንያት ህፃናቱን ከፀሐይና ከሰው እይታ ሰውረው በቤት ውስጥ ለማቆየት መገደዳቸውን ገልጸዋል። በዕለቱ የሪባን መቁረጥ ሥነ-ሥርዓት፣ የማርሽ ባንድ፣ የማስኮት (Mascot) ትርኢት፣ የሰርከስ እና የጋራ አካል ብቃት እንቅስቃሴዎች ከልዩ ልዩ የመድረክ ፕሮግራሞች ጋር እንደሚቀርቡም ነዉ የተገለፀዉ። በመድረኩ ላይ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ ባለሀብቶች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ተማሪዎች እና አጋር ድርጅቶች የሚገኙ ሲሆን፣ ድርጅቱ ለዝግጅቱ ያዘጋጃቸውን ልዩ ቲሸርቶች በመግዛት መላው ህብረተሰብ የህፃናቱ ድምፅ እንዲሆን ጥሪ ቀርቧል። ለዝግጅቱ የተዘጋጁ ቲሸርቶች የሚገኙበት ቦታ በቅርቡ በድርጅቱ ሚዲያዎቹ ማለትም በፈስቡክ፣ በቲክቶክ፣ ቴለግራም፣ ኢንስተግራም እንዲሁም በወብሳይቱ እንደሚያሳውቅ የተገለፀ ሲሆን፣ ፍላጎት ያላቸው ወገኖች በ 0907404111 ወይም 0906200020 በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል። ድርጅቱ ከተመሰረተበት ከየካቲት 17 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ላለፉት አምስት ዓመታት በቤት ለቤት ድጋፍ እና በማዕከል ደረጃ የትራንስፖርት፣ የምግብ፣ የመኝታ፣ የንፅህና እና የፊዚዮቴራፒ አገልግሎቶችን ሲሰጥ የቆየ ቢሆንም፣ በዘርፉ ያለው ግንዛቤና ተደራሽነት አሁንም አነስተኛ በመሆኑ ይህንን ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ማዘጋጀት ማስፈልጉ ተጠቅሷል።

በትግራይ በ35 ሚልዮን ብር በጀት የተገነባ የሶላር የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ ​#FastMereja I በትግራይ ክልል ሰሜን ምዕራብ ዞን ፅምብላ ወረዳ ዓዲ ገብሩ ከተማ እና አካባቢዋ ከ13 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር የሚቀርፍ፣ በ35 ሚልዮን ብር በጀት በሶላር ኤነርጂ የሚሰራ የውሃ ፕሮጀክት ተገንብቶ ለምረቃ የበቃ ሲሆን ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። ​ይህ በዓዲ ገብሩ ከተማ እና በህንፀት ጣቢያ የሚገኙ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርገው የውሃ ፕሮጀክት በሉትራን ዓለም ለኸ ፌደሬሽን (LWF)፣ 3R እና ወርልድ ቪዥን በተሰኙ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ከትግራይ ክልል ውሃ እና ኤነርጂ ቢሮ ጋር በመተባበር የተገነባ ነው። ፕሮጀክቱ በሰከንድ 9 ሊትር ውሃ የማምረት አቅም ያለው በመሆኑ በቆሸሸ ውሃ ምክንያት ለተለያዩ ውሃ ወለድ በሽታዎች ሲጋለጡ እና ንጹህ ውሃ ፍለጋ ረጅም ኪሎ ሜትሮችን ሲጓዙ ለነበሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ዘላቂ መፍትሔ ይዞ መጥቷል።

ኢትዮጵያዊው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ የግማሽ ማራቶን የዓለም ሪኮርድን በአስደናቂ ሁኔታ ሰበረ #FastMereja I ኢትዮጵያዊው የረጅም ርቀት ሯጭ ዮሚፍ ቀጄልቻ በቡኤኖስ አሬስ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር 56 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ በመግባት አዲስ የዓለም ሪኮርድ አስመዝግቧል። በአርጀንቲና ዋና ከተማ ቡኤኖስ አሬስ ዛሬ ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ዮሚፍ፣ ከዚህ ቀደም በኡጋንዳዊው አትሌት ጃኮብ ኪፕሊሞ ተይዞ የነበረውን የ57 ደቂቃ ከ20 ሰከንድ ሪኮርድ በ29 ሰከንዶች ማሻሻል ችሏል። በዚህም ውጤት ዮሚፍ በታሪክ የመጀመሪያው የግማሽ ማራቶን ርቀትን ከ57 ደቂቃ በታች በመግባት ያጠናቀቀ አትሌት በመሆን አዲስ ታሪክ ፅፏል። ይህ አስደናቂ የስፖርት ስኬት ዮሚፍ ቀጄልቻ በዘመናዊው የረጅም ርቀት ሩጫ ላይ እያሳየ ያለውን የበላይነት ያረጋገጠበት ሌላው ክስተት ነው። አትሌቱ ባለፈው ሚያዝያ ወር በለንደን ማራቶን ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋዊ የውድድር መስመር ማራቶንን በ1 ሰዓት ከ59 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ ከሁለት ሰዓት በታች በይፋ ከሮጡ ጥቂት አትሌቶች አንዱ መሆኑ ይታወሳል።

ግሎባል ጀነራል ኮንስትራክሽን በ2018 ጥሩ አፈጻጸም ያሳዩ ሰራተኞችን አመሰገነ ​#FastMereja I ግሎባል ጀነራል ኮንስትራክሽን ዛሬ ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በሐዋሳ ሐይሌ ሪዞርት ባካሄደው መድረክ የ2018 የበጀት ዓመት የሥራ እንቅስቃሴውን ከድርጅቱ ሰራተኞች ጋር በመሆን ገምግሟል። ​በግምገማ መድረኩ ላይ በ2017 በጀት ዓመት ግንባታቸው ተጀምረው ተጠናቀው የተረከቡ፣ እንዲሁም በ2018 በጀት ዓመት ተጀምረው በጥሩ አፈጻጸም ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች የደረሱበት ደረጃ እና የቀጣይ የሥራ ዕቅዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። ​በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ከድር ሐሰን፤ የድርጅቱ ትልቁ መሣሪያና የሥኬቱ መሠረት ሠራተኞቹ መሆናቸውን በመግለጽ፣ እያንዳንዱ ሠራተኛ ላበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል። አክለውም በበጀት ዓመቱ የላቀ የሥራ አፈጻጸም ላሳዩ የድርጅቱ ሰራተኞች እውቅና ሽልማት ሰጥቷል። ​ ግሎባል ጀነራል ኮንስትራክሽን፤ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ፣ በኦሮሚያ ክልል ከተሞች እንዲሁም በፌዴራል ተቋማት የተለያዩ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶችን በመገንባትና በማስረከብ ላይ ይገኛል።